EBC Corporate

EBC Corporate EBC is a Pan Africanist Media station providing reliable and trustworthy news and programs.

ኢቢሲ ገዥ ትርክቶችን በማስረጽና የኢትዮጵያን ገጽታ በመገንባት ረገድ የሚደነቅ ሥራ እየሠራ ነው፡- ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)**** የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን...
07/04/2026

ኢቢሲ ገዥ ትርክቶችን በማስረጽና የኢትዮጵያን ገጽታ በመገንባት ረገድ የሚደነቅ ሥራ እየሠራ ነው፡- ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
****
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ገዥ ትርክቶችን ለማስረጽና የኢትዮጵያን ከፍታ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ የሚደነቅ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር አብሮ መሥራት በሚቻልበት ሁኔታ በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

ኢቢሲ ገዥ ትርክቶችን ለማስረጽና የኢትዮጵያን ከፍታ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ የሚደነቅ ተግባር እያከናወነ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የሕዝቦች አንድነት ይበልጥ እንዲጠናከርና በልማት ኮሪደሮች የሕብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲያድግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበትም አመልክተዋል።

ክልሉ ያለውን እምቅ የልማት አቅምና የተፈጥሮ ጸጋ ለዓለም ለማስተዋወቅ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙክታር ሁሴን በበኩላቸው፤ ተቋሙ የጀመራቸውን የሀገር ግንባታ ሥራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልና የታርጫ ስቱዲዮን በግብዓት ለማሟላት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

የኮርፖሬሽኑ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘላለም እንዳሻው በበኩላቸው፤ የክልሉን የልማት አቅሞች ከማስተዋወቅ ባለፈ የሚዲያ ባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት በቅንጅት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።

የኢቢሲ ከፍተኛ አመራሮች ከክልሉ አመራር ጋር ያደረጉት ውይይት የክልሉን የሥራ እንቅስቃሴዎችና ተግባራት ለማስተዋወቅና ሕዝቡ ወቅታዊና እውነተኛ መረጃን እንዲያገኝ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል፡፡

በሰለሞን ባረና

ለመመዝገብ የቀሩት 3 ቀናት ብቻ ናቸው!!!!*********************ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ ሦስት ቀናት ብቻ ቀርተዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊ...
03/04/2026

ለመመዝገብ የቀሩት 3 ቀናት ብቻ ናቸው!!!!
*********************
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ ሦስት ቀናት ብቻ ቀርተዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ የመራጮች ምዝገባ እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
የምዝገባው ሂደት ሊጠናቀቅ 3 ቀናት ብቻ ስለቀሩት፣ እስካሁን የምርጫ ካርድ ያልወሰዳችሁ ዜጎች ቀሪዎቹን ቀናት እንድትጠቀሙ እናስታውሳለን።
ምርጫ ካርድ አለመውሰድ የራስዎን እና የቤተሰብዎን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ሌላ አካል እንዲወስን በራስዎ ፈቃድ ዕድሉን አሳልፎ መስጠት ነው።
በሀገርዎ የዴሞክራሲ ልምምድ ውስጥ ለመወሰን እና የዜግነት ግዴታዎን ለመወጣት የድምፅ መስጫ ካርድዎን ይያዙ።
ድምፅ መስጠት መብትዎ ብቻ ሳይሆን የዴሞክራሲ ተሳትፎዎ መገለጫ ነው።
በሚቀርብዎ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት ወይም በምርጫዬ መተግበሪያ በዲጂታል አማራጭ መመዝገብ ይችላሉ።
ምርጫዬ መተግበሪያን፦
ለአንድሮይድ (Play Store): https://play.google.com/store/apps/details..
ለአይፎን /iOS/ (App Store): https://apps.apple.com/us/app/mirchaye/id6756587049
በድረ-ገጽ https://mirchaye.portal.nebe.org.et/
ጊዜው ሳይረፍድ ዛሬውኑ ካርድዎን ይውሰዱ፤ በምርጫ ብቻ ለውጥ ያምጡ።

ለመመዝገብ የቀሩት 3 ቀናት ብቻ ናቸው!!!!
*********************

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ ሦስት ቀናት ብቻ ቀርተዋል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ የመራጮች ምዝገባ እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።

የምዝገባው ሂደት ሊጠናቀቅ 3 ቀናት ብቻ ስለቀሩት፣ እስካሁን የምርጫ ካርድ ያልወሰዳችሁ ዜጎች ቀሪዎቹን ቀናት እንድትጠቀሙ እናስታውሳለን።

ምርጫ ካርድ አለመውሰድ የራስዎን እና የቤተሰብዎን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ሌላ አካል እንዲወስን በራስዎ ፈቃድ ዕድሉን አሳልፎ መስጠት ነው።

በሀገርዎ የዴሞክራሲ ልምምድ ውስጥ ለመወሰን እና የዜግነት ግዴታዎን ለመወጣት የድምፅ መስጫ ካርድዎን ይያዙ።

ድምፅ መስጠት መብትዎ ብቻ ሳይሆን የዴሞክራሲ ተሳትፎዎ መገለጫ ነው።
በሚቀርብዎ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት ወይም በምርጫዬ መተግበሪያ በዲጂታል አማራጭ መመዝገብ ይችላሉ።

ምርጫዬ መተግበሪያን፦
ለአንድሮይድ (Play Store): https://play.google.com/store/apps/details..
ለአይፎን /iOS/ (App Store): https://apps.apple.com/us/app/mirchaye/id6756587049
በድረ-ገጽ https://mirchaye.portal.nebe.org.et/

ጊዜው ሳይረፍድ ዛሬውኑ ካርድዎን ይውሰዱ፤ በምርጫ ብቻ ለውጥ ያምጡ።

"ኢቢሲ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጎለብቱ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል" - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ********************የኢትዮጵያ ብሮድካስቲ...
11/03/2026

"ኢቢሲ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጎለብቱ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል" - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
********************

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠነክሩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ተናገሩ።

ኢቢሲ እና የጋምቤላ ክልል መንግሥት በተለያዩ ጉዳዮች በጋራ በመሥራት ላይ ያተኮረ ምክክር አድርገዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ፤ ለሀገር የሚተርፍ እምቅ የተፈጥሮ ሀብት የሚገኝበት ክልል በመሆኑ፣ ሀብቱን በአግባቡ ለማልማት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ሁሉም ኢትዮጵያውያን በጋራ በሚኖሩበት በጋምቤላ ክልል፣ በሰላም ግንባታ እና በተለያዩ የልማት ዘርፎች የክልሉ መንግሥት ከኢቢሲ ጋር በቅንጅት እንደሚሠራም ገልጸዋል።

ኢቢሲ ኅብረብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ የማኅበረሰቡን ባህላዊ እና ታሪካዊ እሴቶች ለማጎልበት የጀመራቸውን የለውጥ ሥራዎች ሊያጠናክር እንደሚገባውም ርዕሰ መስተዳድሯ ተናግረዋል።

የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የቴሌቪዥን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘላለም እንደሻው፣ ኢቢሲ የኢትዮጵያን ልዕልና ለማረጋገጥ እንደ ሀገር የተያዘውን ተልዕኮ ለማሳካት የበኩሉን ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ተቋሙ ዘመናዊ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከቴሌቪዥንና ከሬዲዮ በተጨማሪ በርካታ ተከታይ ባሏቸው በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጽ አማራጮች ፈጣን፣ ትክክለኛ እና ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃዎች ለሕዝብ ተደራሽ በማድረግ ላይ መሆኑንም አቶ ዘላለም አብራርተዋል።

የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የቋንቋዎች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙክታር ሁሴን በበኩላቸው፣ አንጋፋው ኢቢሲ በተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቋንቋዎች፣ በበርካታ ቻናሎቹ አማካኝነት ዜና እና ፕሮግራሞችን በማሰራጨት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የሀገራችን ሕዝቦች ያላቸውን አኩሪ ታሪክ፣ ቱባ ባህል እና ትውፊቶችንም የበለጠ በማስተዋወቅ እና በማስተሳሰር፣ ኢቢሲ ለዓመታት ያካበተውን ልምድ በመጠቀም በትኩረት እየሠራ ስለመሆኑም አቶ ሙክታር ተናግረዋል።

በሚፍታህ አብዱልቃድር

Ethiopian Broadcasting Corporation

ኢቢሲ እና የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ፈረሙ********የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እና የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በጋራ ለመስ...
20/01/2026

ኢቢሲ እና የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ፈረሙ
********

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እና የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የስምምነት ፊርማ ተፈራረሙ።

የስምምነት ፊርማውን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቢኒያም ኤሮና የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሃፍታይ ገብረ እግዚአብሔር ፈርመዋል።

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቢኒያም ኤሮ፤ የብልፅግና ተምሳሌት የሆነችውን አዲስ አበባ ከፍ የሚያደረጉ የማስተዋወቅና ገፅታን የሚገነቡ የዘገባ ስሥራዎች በጣቢያው የተለያዩ የመገናኛ አማራጮች እንደሚሰሩ በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል።

በዚህም በጋራ ለመስራት መፈራረማችን በሚዲያው በኩል ውጤታማ የሆነ ሥራ እንድንሰራ ያግዛል ሲሉ ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለጹት።

አቶ ሃፍታይ ገብረ እግዚአብሔር በበኩላቸው፤ ኢቢሲ የምንኮራበት ብሔራዊ ጣቢያችን በመሆኑ በመዲናዋ አዲስ አበባ የልማት ሥራዎችን ለማስተዋወቅ እና ገፅታን ለመገንባት ትልቅ አቅም የሚሆን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ብሔራዊ ጣቢያው በበርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ቋንቋዎች ዜና እና ፕሮግራሞችን የሚያስተላልፍ በመሆኑም፣ አምራና ተውባ እየተሰራች ያለችውን አዲስ አበባን ገፅታ ለመገንባት መልካም አጋጣሚ ይኖረዋል ብለዋል።

በይመር አደም

የኢቢሲ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዱራህማን ሩቤ  ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ*********የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ የነበሩት አቶ አብ...
23/12/2025

የኢቢሲ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዱራህማን ሩቤ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
*********

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ የነበሩት አቶ አብዱራህማን ሩቤ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል::

ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል::

የአቶ አብዱራህማን ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈፀማል::

አቶ አብዱራህማን ከሪፖርተርነት እስከ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነት በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት አገልግለዋል::

በተለይም በኦቢኤን እና በኢቢሲ ከሪፖርተርነት ጀምሮ በኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል::

ህይወታቸው እስከአለፈበት ቀን ድረስ ደግሞ የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ ነበር::

አቶ አብዱራህማን ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት ነበሩ::

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብዱራህማን ሩቤ ህልፈት የተሰማውን ሃዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጆቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል::

ኢቢሲ እና የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማሕበራት ምክር ቤት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ*****************የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና የኢት...
19/12/2025

ኢቢሲ እና የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማሕበራት ምክር ቤት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
*****************

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማሕበራት ምክር ቤት ጠንካራ የንግድ ማህበረሰብ ለመፍጠር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

የመግባቢያ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቢኒያም ኤሮ እና የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማሕበራት ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ ተፈራርመዋል።

የኢቢሲ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቢኒየም ኤሮ በስምምነቱ ወቅት መንግስት የግሉ ዘርፍ ከምንጊዜውም በላይ እንዲጠናከር የፖሊሲ ሪፎርም ማድረጉን ተከትሎ የንግድ ገበያው ለዓለም ክፍት ሆኗል ብለዋል።

ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ህግና ስርዓት ተከትለው፤ ፈጠራዎቻቸውን አጎልብተው፤ በዓለም ላይ ተፎካካሪ እንዲሆኑ ኢቢሲ በሁሉም የመገናኛ አማራጮች አስተማሪ መረጃ መስጠቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማሕበራት ምክር ቤት በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድና ኢንቨስትመንትን ማስተዋወቅ፤ ለንግድ ስራ አስቻይ ሁኔታ እንዲፈጠርማድረግ እንደሁም ነጋዴዎች የዓለም አቀፍ የገበያ ስርዓትን እንዲያውቁ ማድረግ ሀላፊነቱን ለመወጣት ጥረት እያደረገ መሆኑን ዋና ፀሃፊው ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ ጂዲፒ የግሉ ዘርፍ አሁን ያለው ድርሻ 15 በመቶ ብቻ ነው ያሉት ዶ/ር ቀነኒሳ በሚቀጥሉት10 ዓመታት ውስጥ የዘርፉን ድርሻ ከ50 በመቶ በላይ ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በስምምነቱመሰረት ሁለቱ ተቋማት በኢትዮጵያ ጠንከራና በዓለም ተወዳዳሪ የሆነ የግል ንግድ ተዋናዮችን ለመፍጠር ይሰራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በላሉ ኢታላ

#ኢትዮጵያ

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa
1000

Telephone

+251115172539

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC Corporate posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EBC Corporate:

Share