EBC Corporate

EBC Corporate EBC is a Pan Africanist Media station providing reliable and trustworthy news and programs.

እሑድ ቤት የእያንዳንዳችን መልክ ነው፡- አቶ ጌትነት ታደሰ************"እሑድ ቤት የእያንዳንዳችን ኢትዮጵያውያን መልክ ነው፤ እሑድ ቤት ሀገር ነው፤ እሑድ ቤት ቤተሰብ ነው፤ እሑድ ቤ...
21/06/2025

እሑድ ቤት የእያንዳንዳችን መልክ ነው፡- አቶ ጌትነት ታደሰ
************

"እሑድ ቤት የእያንዳንዳችን ኢትዮጵያውያን መልክ ነው፤ እሑድ ቤት ሀገር ነው፤ እሑድ ቤት ቤተሰብ ነው፤ እሑድ ቤት ትዝታችንን የምናይበት የትዝታችን መልክ ነው" ሲሉ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ ገልጸዋል፡፡

እሑድ ቤት ውስጥ ያለው የተለያየ ዕድሜ፣ አመለካከት እንዲሁም ማንነት ያለው ቤተሰብ ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ በዚህ ውስጥ በዓይነታቸው ለየት ያሉ ፕሮግራሞች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚዲያው ልዩ ትኩረት በመስጠታቸው ኢቢሲ ትልቅ የሚዲያ ኮምፕሌክስ እንዲኖረው እንዳስቻሉ አቶ ጌትነት አንስተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚዲያ ኮምፕሌክሱን የመረቁ ዕለትም ኢቢሲ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩን ጠቅሰው፣ ቀሪው ሥራ ይዘት ላይ መሆን እንዳለበት መመሪያ መስጠታቸውን አስታውሰዋል፡፡

በዚህም መነሻነት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን "ወደ ይዘት" የሚል እንቅስቃሴ ከጀመረ አንድ ዓመት እንዳለፈው ዋና ሥራ አስፈጸሚው ገልጸዋል፡፡

በሂደቱም በርካታ የይዘት ማሻሻያ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተዋል፡፡ በዚህም የተወሰኑት አየር ላይ መዋላቸውን እና እሑድ ቤትም በስፋት ታስቦባቸው ከተሠሩት ይዘቶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በለሚ ታደሰ

#ሙሉዓለምታደሠ #ሚካኤልታምሬ #እሑድቤት #ጌትነትታደሰ

ኢቢሲ ለሌሎች ተቋማት አርዓያ መሆን የሚችል ተቋም ነው፡- የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች*********************የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የኮሙኒኬሽን ...
16/06/2025

ኢቢሲ ለሌሎች ተቋማት አርዓያ መሆን የሚችል ተቋም ነው፡- የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች
*********************

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የኮሙኒኬሽን ባለሙዎች፣ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የሁሉም ወረዳዎች ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሚዲያ ኮምፕሌክስን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸው የኢቢሲን ሙዚየም፣ ሰው ሰራሽ ሐይቅ፣ ስቱዲዮዎችን እና ምድረ ግቢውን ተመልክተዋል።

የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ምርምር ኃይሌ በኢቢሲ የተሰሩ ስራዎችን ለመጎብኘት እንዲሁም ከተቋሙ ልምድ ለመቅሰም ወደ ተቋሙ መምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡

ኃላፊዋ የሁሉም ኢትጵያውያን የሆነውን አንጋፋ ተቋም በጉብኝታችን ከጠበቅነው በላይ ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል፡፡

ኢቢሲ ከጊቢው ጀምሮ ለሰራተኛ ምቹ የሆነ የስራ አካባቢን በመፍጠር ለሌሎች ተቋማት አርዓያ መሆን የሚችል ስራ መስራቱን አያይዘው ተናግረዋል፡፡

በክፍለ ከተማው የወረዳ 07 ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደገሙ ደንደር በበኩላቸው፤ በሚዲያው ዘርፍ የሚገኙ ኃላፊዎችም ሆኑ ባለሙያዎች የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስን መጎብኘት እንዳለባቸው ነው ያመላከቱት፡፡

ኢቢሲ አንጋፋ ተቋም እንደመሆኑ ለሌሎች ተቋማት ልምዱን እና እውቀቱን ስልጠና በመስጠት ማጋራት እንደሚገባውም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በንፍታሌም እንግዳወርቅ

እሑድ ቤት - ሊጀመር ነው ይጠብቁን
16/06/2025

እሑድ ቤት - ሊጀመር ነው ይጠብቁን

15/06/2025

እሑድ ቤት - ከሰሞኑ ይጠብቁን

#ከሰሞኑ

ኢቢሲ ትውልድ ከማነፅ አኳያ የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው፡- የደጃዝማች ወንድይራድ ተማሪዎች***********የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ትውልድ ከማነፅ አኳያ የራሱን አስተዋፅኦ...
13/06/2025

ኢቢሲ ትውልድ ከማነፅ አኳያ የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው፡- የደጃዝማች ወንድይራድ ተማሪዎች
***********

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ትውልድ ከማነፅ አኳያ የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ የሚገኝ ተቋም ነው ሲሉ የደጃዝማች ወንድይራድ ተማሪዎች ተናግረዋል።

የደጃዝማች ወንድይራድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የኢቢሲ ሚዲያ ኮምሌክስን በዛሬው ዕለት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

ተማሪዎቹ በጉብኝታቸው የኢቢሲን ሙዚየም፣ ሰው ሰራሽ ሐይቅ፣ ስቱዲዮዎችን እና ምድረ ግቢውን ተመልክተዋል።

ተማሪዎቹ በዚህ ወቅት ኢቢሲን የመጎብኘት ዕድል በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ተቋሙ የትውልድ ቤት መሆኑን መረዳታቸውንም ተናግረዋል።

ኢቢሲ የእነርሱም ቤት ጭምር እንደሆነ ተማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል።

በሀብተሚካኤል ክፍሉ

ኢቢሲ እየፈጠረው ያለው ተቋማዊ አደረጃጀት የሚዲያውን ቀዳሚነት የሚመጥን ነው - አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ*********************** የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እየፈ...
13/06/2025

ኢቢሲ እየፈጠረው ያለው ተቋማዊ አደረጃጀት የሚዲያውን ቀዳሚነት የሚመጥን ነው - አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ
***********************

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እየፈጠረ ያለው ተቋማዊ አደረጃጀት የተቋሙን ቀዳሚነት የሚመጥን መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ተናገሩ።

በሚኒስትር ዴኤታው የተመራ የሱፐርቪዥን ቡድን የኢቢሲን ተቋማዊ ሁኔታ፣ ዕቅድ ዝግጅት፣ አጀንዳ ቀረጻ እና የዲጂታል ሚዲያው (ዶት ስትሪም) ያለበትን ደረጃ ተመልክቷል።

ከምልከታው በኋላ አስተያየታቸውን የሰጡት አቶ ተስፋሁን፣ ኢቢሲ ምቹ የሥራ ቦታን በመፍጠር እንዲሁም የሰው ሀብት አስተዳደሩን ለይዘት ግብአት በሚሆን መልኩ በማብቃት ረገድ አመርቂ ሥራ ሠርቷል ብለዋል።

ተቋሙ ያለውን አቅም ተጠቅሞ ይዘቶችን ለማሻሻል እየሠራ ያለውን ሥራም አድንቀዋል።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ነቅሰው የሚያወጡ፣ አሰባሳቢ ትርክትን የሚፈጥሩ እና የሕፃናትን የነገ ተስፋነት የሚያጎሉ ጉዳዮች ላይ ጠንክሮ መሥራት አለበት ብለዋል።

በተለይም ሕፃናት ከሚዘነጉ የኅብረተሰብ ክፍሎች መካከል እንደሆኑ የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ሀገርን ለማስቀጠል ሕፃናት ላይ መሥራት እንደሚገባ እና ኢቢሲ በዚህ ረገድ እያደረገው ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ኢቢሲ በዲጂታል ሚዲያው በኩል እየሠራቸው ያሉት ሥራዎችም ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው ያሉት አቶ ተስፋሁን፣ ይህ ደግሞ ቀዳሚነቱን ይዞ ከዓለም ጋር እንዲጓዝ የሚያደርገው መሆኑን ጠቅሰዋል።

ተቋሙ የመንግሥት ኢኒሼቲቭ የሆኑትን እንደ የሌማት ትሩፋት ያሉ ተግባራትንም እየከወነ ያለበት መንገድም ውጤታማ እንደሆነ ነው ሚኒስትር ዴኤታው የገለጹት።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኢቢሲ የጀመራቸው የይዘት ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፣ ተቋሙ ብሔራዊ ጣቢያነቱን የሚመጥን ሥራ እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው፣ በዚህም ከጅማሮው አበረታች ግብረ-መልስ እያገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢቢሲ የመንግሥትን አቅጣጫዎች ተከትሎ እየሠራ መሆኑን ያወሱት አቶ ጌትነት፣ ከመንግሥት አስፈፃሚ አካላት፣ ከሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን አካላት እንዲሁም ከውስጥ የሚመነጩ የአተያይ ችግሮች በሥራው ሂደት ተግዳሮቶች እንደሆነበት ጠቅሰዋል።

ከመንግሥት አስፈፃሚዎች አካባቢ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና ተጠያቂነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ መረጃ የመስጠት ዳተኝነት እንደሚስተዋል ጠቅሰው፣ ይህ የመንግሥትን ትክክለኛ አቅጣጫ የሚያስት አካሄድ መቀረፍ አለበት ብለዋል።

ኢቢሲ እነዚህን ተግዳሮቶች ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ እየሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኩል ያለው ተቋሙን የመረዳት እሳቤ ወደ መንግሥት አስፈፃሚ አካላትም መውረድ እንዳለበት፣ ለዚህ ደግሞ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

ኢቢሲ የኢትዮጵያን ታሪክ የሰነደ ተቋም እንደመሆኑ መጠን ሰነዶቹ (archive) ሳይበላሹ ለትውልድ በሚተላለፉበት መልኩ ዲጂታላይዝ እያደረገ መሆኑንም አቶ ጌትነት ጠቅሰዋል።

ይህ ሥራ ከፍተኛ አቅም ስለሚጠይቅ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ጠይቀዋል።

በለሚ ታደሰ

የሚዲያ አቅም ለመገንባት በምናደርገው ጥረት ሀገራዊና ማህበራዊ እሴታችን ከፍ እንዲል የካበተ ልምድ ባለቤት የሆነውን የኢቢሲን ሙያዊ ድጋፍ እንፈልጋለን፡-  ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ******...
11/06/2025

የሚዲያ አቅም ለመገንባት በምናደርገው ጥረት ሀገራዊና ማህበራዊ እሴታችን ከፍ እንዲል የካበተ ልምድ ባለቤት የሆነውን የኢቢሲን ሙያዊ ድጋፍ እንፈልጋለን፡- ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ
***************

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ጋር በጋራ በሚሰሯቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

ሁለቱ ተቋማት በተለይ በሥነ-ምግባር እሴት እና በሥነ-ምግባር የታነፀ ዜጋ ግንባታ ላይ የየራሳቸውን ስራ እየሰሩ ያሉ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ይህንንም ተግባር በጋራ አጠናክረው ለመስራትና ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት መግባባት ላይ ተደርሷል።

ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በውይይቱ ላይ ኢቢሲ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በፍትሃዊነት ለማገልገል እየሰራ ለመሆኑ አድናቆታቸውን የገለፁ ሲሆን፤ በሃገራዊ ጉዳዮች ላይም የሚሰሩ ተግባራትን እንደሚደግፉ እና በጋራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ የሚዲያ አቅም ለመገንባት በሚያደርገው ጥረት ሀገራዊና ማህበራዊ እሴቱ ከፍ እንዲል የካበተ ልምድ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሙያዊ ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ጠይቀዋል።

ኢቢሲ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እያከናወናቸው ያሉ የሀገርና ትውልድ ግንባታ ተግባራትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

ኢቢሲ የሃገር ምልክት ነው፤ በሚሰራቸው ሃገራዊ ተልዕኮዎች እና ተግባራትም ደስተኞች ነን ብለዋል ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ።

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰ፥ ኢቢሲ ሁሉም ቤተ-እምነቶች በእኩልነት የሚጠቀሙበት መሆንኑ በመግለፅ፤ ተቋማቱ ኢትዮጵያዊነትን ለማፅናት እና በሥነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመገንባት እያደረጉት ያለውን ጥረት ማገዝ እንዳለበት ያምናል ብለዋል።

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር በቀጣይነት የሚሰራቸው ስራዎችም የጋራ ሀገር በማፅናት እና ትውልድ በመገንባት ላይ ያተኮሩ እንደሚሆኑም ገልፀዋል።

የሁለቱ ተቋማት አመራሮች በዕውቀት ሽግግር፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም ማህበራዊ ሃላፊነትን ከመወጣት አኳያ በትብብር መሥራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተው ከጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል።

በላሉ ኢታላ

"የቅዳሜ መልክ"  የዜና ሾው ተጀምሯል **********መልከ ብዙው የቅዳሜ መልክ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል። "የቅዳሜ መልክ"  የዜና ሾው ቅዳሜ የቤተሰብ ቀን፤ የገበያ ቀን፤ የመዝናኛ ...
07/06/2025

"የቅዳሜ መልክ" የዜና ሾው ተጀምሯል
**********

መልከ ብዙው የቅዳሜ መልክ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል።

"የቅዳሜ መልክ" የዜና ሾው ቅዳሜ የቤተሰብ ቀን፤ የገበያ ቀን፤ የመዝናኛ ቀን፤ የጉብኝት ቀን ፤ የጥበብ ቀን፤ የስፖርት ቀን ነው።

በኢቲቪ ዜና ቻናል እየተላለፈ ከሚገኘው የቀጥታ ስርጭት በተጨማሪ በኢቢሲ ዶትስትሪም የማህበራዊ ትስስር አማራጮች በፌስቡክ፣ በዩቲዩብ እና በቲክቶክ ገፆቻችን "የቅዳሜ መልክ" የዜና ሾው የቀጥታ ስርጭትን ማግኘት ይችላሉ።

ባመችዎት አማራጭ ለመከታተል እንዲያመችዎ ከታች በመልእክት ማስቀመጫው ስፍራ ላይ ሊንኮቹን አስቀምጠናል።

#ለኢትዮጵያልዕልና #የቅዳሜመልክ

የቅዳሜ መልክ ቅዳሜ መልኩ ብዙ ነው፡፡ ቅዳሜ የቤተሰብ ቀን፤ የገበያ ቀን፤ የመዝናኛ ቀን፤  የጉብኝት ቀን ፤ የጥበብ ቀን፤ የስፖርት ቀን  ነው፡፡ የቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ነገ ይጀምራል፡፡...
06/06/2025

የቅዳሜ መልክ
ቅዳሜ መልኩ ብዙ ነው፡፡ ቅዳሜ የቤተሰብ ቀን፤ የገበያ ቀን፤ የመዝናኛ ቀን፤ የጉብኝት ቀን ፤ የጥበብ ቀን፤ የስፖርት ቀን ነው፡፡
የቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ነገ ይጀምራል፡፡
ኢቢሲ ይህን የዘርፈ ብዙ መገለጫ ቀን የሆነውን ቅዳሜን “የቅዳሜ መልክ “ ብሎ አዲስ የዜና ሾው ይዞ ቀርቧል፡፡
በቅዳሜ መልክ ለቤተሰብ የሚመጥኑ ዝግጅቶች ፤ አስገራሚና አስደናቂ የገበያ ገጠመኞች ፤ አስደናቂ እና አነጋጋሪ የሆኑ ጥበባዊ ስራዎች ፤ ሊታዩ ሊጎበኙ የሚገባቸው ስፍራዎች የሚዳሰሱበት ፤ ሰፊ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በርካታ የሀገር ውስጥና አለምአቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች ከታዋቂ ባለሙያዎችና ተንታኞች ጋር መረጃ እየሰጠ ፤ እያዝናና እውቀትን እያስጨበጠ ወደ ርስዎ ለማድረስ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
ግንቦት 30 / 2017 የሚጀምረው የቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ዘወትር ቅዳሜ ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 5 ሰዓት ወደ ተመልካቾች ይቀርባል፡፡
በቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ተመልካቾች እየተሳተፉ ይሸለማሉ፤ ባህላዊ ክዋኔዎች፤ ወጎች፣ ትውፊቶች፤ የተፈጥሮ ገጽታዎች ይጎበኛሉ፤ አዝናኝና አስተማሪ የጥበብ ስራዎች ይቀርባሉ፤ አሁናዊ ትኩስና አነጋጋሪ ስፖርታዊ ክስቶች ከታዋቂ የስፖርት ተንታኞች ጋር ይቀርባል ይተነተንማል፡፡
ሁሌም ለኢትዮጵያ ልዕልና የሚተጋው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን “ወደ ይዘት” በሚል እያካሄደ ያለውን የይዘትና የአቀራረብ ሪፎርም በቅርቡም ሌሎች አዳዲስ የዜና ሾዎችና ወቅታዊ ፕሮግራሞች፤ የመዝናኛና የስፖርት ጉዳዮችን በተለያዩ ሚዲየሞቹ በአዳዲስ ይዘትና አቀራረብ ወደ ተመልካቾች ለማድረስ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን፡፡
የቅዳሜ መልክ
ነገ ቅዳሜ ግንቦት 30 ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 5 ሰዓት በኢቲቪ ዜና ይጠብቁን!!
ኢቢሲ
ለኢትዮጵያ ልዕልና
#ለኢትዮጵያልዕልና

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa
1000

Telephone

+251115172539

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC Corporate posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EBC Corporate:

Share