
21/06/2025
እሑድ ቤት የእያንዳንዳችን መልክ ነው፡- አቶ ጌትነት ታደሰ
************
"እሑድ ቤት የእያንዳንዳችን ኢትዮጵያውያን መልክ ነው፤ እሑድ ቤት ሀገር ነው፤ እሑድ ቤት ቤተሰብ ነው፤ እሑድ ቤት ትዝታችንን የምናይበት የትዝታችን መልክ ነው" ሲሉ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ ገልጸዋል፡፡
እሑድ ቤት ውስጥ ያለው የተለያየ ዕድሜ፣ አመለካከት እንዲሁም ማንነት ያለው ቤተሰብ ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ በዚህ ውስጥ በዓይነታቸው ለየት ያሉ ፕሮግራሞች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚዲያው ልዩ ትኩረት በመስጠታቸው ኢቢሲ ትልቅ የሚዲያ ኮምፕሌክስ እንዲኖረው እንዳስቻሉ አቶ ጌትነት አንስተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚዲያ ኮምፕሌክሱን የመረቁ ዕለትም ኢቢሲ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩን ጠቅሰው፣ ቀሪው ሥራ ይዘት ላይ መሆን እንዳለበት መመሪያ መስጠታቸውን አስታውሰዋል፡፡
በዚህም መነሻነት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን "ወደ ይዘት" የሚል እንቅስቃሴ ከጀመረ አንድ ዓመት እንዳለፈው ዋና ሥራ አስፈጸሚው ገልጸዋል፡፡
በሂደቱም በርካታ የይዘት ማሻሻያ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተዋል፡፡ በዚህም የተወሰኑት አየር ላይ መዋላቸውን እና እሑድ ቤትም በስፋት ታስቦባቸው ከተሠሩት ይዘቶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ሙሉዓለምታደሠ #ሚካኤልታምሬ #እሑድቤት #ጌትነትታደሰ