Ali Eshetu - AE

Ali Eshetu - AE ምንም ያህል ብትጠማ፣ መቼም ቢሆን ውሃ ልትለምናቸው የማይገቡ አንዳንድ ሰዎች አሉ።

14/07/2026
✅ታላቁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት አብርሃም ሊንከን በአንድ ወቅት ስለ ራሱ ፊቱ ሻካራነትና አስቀያሚነት ሁሉም ከጀርባውም በፊቱም ይወራ ነበር። ታድያ እሱ እየቀለደ እንዲህ የሚል ታሪክ አወራ።.."...
14/07/2026

✅ታላቁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት አብርሃም ሊንከን በአንድ ወቅት ስለ ራሱ ፊቱ ሻካራነትና አስቀያሚነት ሁሉም ከጀርባውም በፊቱም ይወራ ነበር። ታድያ እሱ እየቀለደ እንዲህ የሚል ታሪክ አወራ።..
"አንድ ቀን ጫካ ውስጥ ብቻዬን ስጓዝ አንድ ፈረሰኛ አገኘሁ። ሰውየው ፈረሱን አቁሞ ወረደና ትልቅ ቢላዋ አውጥቶ ወደ እኔ ዘረጋው። ደንግጬ 'ምንድነው?' ስለው... 'ይህንን ቢላዋ ያዝ፤ ከአንተ የበለጠ አስቀያሚ ፊት ያለው ሰው ስታገኝ ስጠው ተብዬ ነበር። ካየሁህ ጀምሮ ግን ይህ ቢላዋ ያንተ መሆን እንዳለበት አምኛለሁ!' አለኝ።"..
✅ይኸን ሲያወራ እሱን ጨምሮ ሁሉም በሳቅ ፈነዱ፤ ከዚያ በኋላ በመልኩ ያሾፈ ሰው የለም። ..
በራሳችን ላይ መሳቅ የምንችለው የውስጥ በራስ መተማመን ሲኖረንና ማንነታችንን ሙሉ በሙሉ ስንቀበለው ብቻ ነው። የሰዎች አስተያየትና ትችት የማይበግረው ጠንካራ ማንነት የሚገነባው ከውስጥ ነው።

14/07/2026

#ተዋቸው

አይነ-ስውሩና ወርቅ                    **********✅ዐይነ ስውሩ  በእኩለ ሌሊት ማንም አያየኝም ብሎ ካሰበ በኋላ፣ የያዘውን ወርቅ በቤቱ በረንዳ አጠገብ መሬት ቆፍሮ ቀበረ። ...
14/07/2026

አይነ-ስውሩና ወርቅ
**********
✅ዐይነ ስውሩ በእኩለ ሌሊት ማንም አያየኝም ብሎ ካሰበ በኋላ፣ የያዘውን ወርቅ በቤቱ በረንዳ አጠገብ መሬት ቆፍሮ ቀበረ። ነገር ግን በሌሊት ድምፅ የሰማው ጎረቤቱ አይነ ስውሩ ወደ ቤት ሲገባ ጠብቆ ወርቁን ቆፍሮ ወሰደበት። ከጥቂት ቀናት በኋላ ዐይነ ስውሩ ወርቁን ሊፈትሽ ሲሄድ ቦታው ባዶ ሆኖ አገኘው። ማንም ሊወስደው እንደሚችል በጥልቀት አሰበና በመጨረሻም ጎረቤቱን ጠረጠረ። ..
✅ግን ከመጣላት ይልቅ በብልሃት ወርቁን ለማስመለስ አቀደ። ጎረቤቱን ጠርቶ "ወዳጄ ሆይ! ላማክርህ ፈልጌ ነበር። ከጥቂት ቀናት በፊት የቀበርኩት ወርቅ ነበረኝ። አሁን ደግሞ ተጨማሪ በጣም ብዙ ወርቅ አገኘሁ። እናም ይሄኛውንም ካለፈው ጋር አብሬው ልቅበረው ወይስ ሌላ ቦታ?" ብሎ ጠየቀው።...
✅ጎረቤቱ ተጨማሪው ወርቅ ስላጓጓው "ካለፈው ጋር በአንድ ላይ ብትቀብረው ይሻላል" አለው። ሰውዬው ሌላኛውን ወርቅ ጭምር ለመስረቅ በማሰብ፣ ዐይነ ስውሩ ሳይደርስበት በፊት የቀደመውን ወርቅ በፍጥነት ወስዶ ቦታው ላይ መለሰው።..
ዐይነ ስውሩም ወርቁ መመለሱን አረጋገጠ። በዚያኑ ሌሊት አንድ ትልቅ ባዶ ፌስታል ይዞ ወጣና ወርቁን ወስዶ ባዶውን ፌስታል ቀብሮ ወደ ቤቱ ተመለሰ።..
✅ጎረቤቱም እንደለመደው ሌሊት ወጥቶ በጉጉት ሲቆፍር ያገኘው ባዶ ፌስታል ብቻ ነበር! ..
ብልሃት ከጉልበት ይበልጣል።

የሶስተኛውን ስም በትክክል ለመለሰ ሽልማት ይኖረኛል፡፡
14/07/2026

የሶስተኛውን ስም በትክክል ለመለሰ ሽልማት ይኖረኛል፡፡

ከማትከበርበት ቦታ አትቆይ
14/07/2026

ከማትከበርበት ቦታ አትቆይ

**** በሬና ዝንብ *****✅ አንዲት ዝንብ ዝናብ ዘንቦባት በረዳትና በአንድ ትልቅ በሬ ቀንድ ላይ አርፋ ፀሐይ እየሞቀች ረዥም ሰዓት ቆየች። ብርዱ ከለቀቃት በኋላ  ወደ በሬው ጆሮ ጠጋ አ...
13/07/2026

**** በሬና ዝንብ *****
✅ አንዲት ዝንብ ዝናብ ዘንቦባት በረዳትና በአንድ ትልቅ በሬ ቀንድ ላይ አርፋ ፀሐይ እየሞቀች ረዥም ሰዓት ቆየች። ብርዱ ከለቀቃት በኋላ ወደ በሬው ጆሮ ጠጋ አለችና፡ "አዝናለሁ በሬ ሆይ... እንግዲህ መሄዴ ነው" አለችው።..
በሬውም ዘወር ብሎ፡ "ስታርፊ አልተሰማኝም፤ ስትነሺም የሚሰማኝ አይመስለኝም!" ብሎ መለሰ። . .
በሕይወታችን ውስጥ አንዳንዶች መኖራቸው የማይጠቅም፣ መሄዳቸው የማይጎዳ ሆነው ሳለ... ራሳቸውን እንደ ትልቅ ነገር የሚቆጥሩ (Main character syndrome ያለባቸው) አሉ።..
✅ክብደታችሁን የማያውቁ ሰዎችን "እሄዳለሁ" ማስፈራሪያ አትቁጠሩት። መሄዳቸው ክብደት ለቀነሰላችሁ ሰዎች በሬው የሰጠውን አይነት ምላሽ ስጡና እረፉ!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ali Eshetu - AE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share