Ethio-Daily

Ethio-Daily አዳድስ እና ወቅታዊ መረጃዎች።

01/12/2025

ከፍተኛ ግብር የሚጣልባቸው የመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ከ150,000 ብር ጀምሮ እንዲሆን ተጠየቀ

የሠራተኞች መነሻ የደመወዝ ወለል 8,384 ብር እንዲሆን ተጠየቀ

* መንግሥት መነሻ ወለል ከ1,200 እስከ 2,000 ብር በሚል ረቂቅ አዋጅ አቅርቧል

ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ገለጸ፡፡

የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሪፖርተር እንዳሉት፣ ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ተቀጣሪ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በሥራ ላይ ቆይቷል የተባለውን የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008ን ለማሻሻል ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ከተባሉ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ እስከ ሁለት ሺሕ ብር የሚከፈላቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደንግጓል፡፡

ኢሠማኮ እስከ 8,384 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ተቀጣሪዎች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በደብዳቤ እንደጠየቀ አስታውቋል፡፡ አቶ ካሳሁን በዓለም ባንክ መረጃ መሠረት ዕለታዊ ገቢው ከሦስት ዶላር በታች የሆነ ሰው ደሃ በመሆኑ፣ የመንግሥት የገቢ ግብር በዚህ ወለል ሥር ያሉ ተቀጣሪዎችን ታሳቢ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡

በማናቸውም ቀጣሪ ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች በወር ከ8,384 ብር እስከ 22,974 ብር ደመወዝ የሚያገኙ ሠራተኞች፣ አሥር በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው መንግሥትን መጠየቁን ኢሠማኮ ገልጿል፡፡

ከ22,975 እስከ 44,530 ብር ወርኃዊ ደመወዝ ተከፋዮች የ15 በመቶ፣ ከ44,531 እስከ 72,336 ብር የሚከፈላቸው ደግሞ 20 በመቶ፣ እንዲሁም ከ72,337 እስከ 107,449 ብር የ25 በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው ኢሠማኮ በደብዳቤው አሳስቧል፡፡

ከ107,450 እስከ 150,107 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ሠራተኞች 30 በመቶ ግብር፣ እንዲሁም 150,108 ብር እና ከዚያ በላይ የሚከፈላቸው ተቀጣሪ ሠራተኞች ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ለመንግሥት ባቀረበው ደብዳቤ ኢሠማኮ መጠየቁን ገልጿል፡፡

አሁን በሥራ ላይ ባለው የሠራተኞች የገቢ ግብር አዋጅ መሠረት እስከ 600 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ ሲሆኑ፣ ከ10,900 ብር ጀምሮ ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ከአንድ ሳምንት በፊት ለውይይት ይፋ ባደረገው የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ 1,200 ብር፣ 1,600 ብር እና 2,000 ብር ወርኃዊ ደመወዝተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ድንጋጌ መኖሩ ይታወሳል፡፡

የመንግሥት የገቢ ግብር ማሻሻያው ሠራተኞች ያለባቸውን ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ታሳቢ ያላደረገ እንደሆነ የተለያዩ የውይይት ተሳታፊዎች አስተያየት መስጠታቸው አይዘነጋም።

Ethio-Daily

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት...
19/10/2025

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል፡፡

07/10/2025

የዕለቱ ዜና | ጥቅምት 7, 2025
ሀገር ውስጥ
ፖለቲካ እና መንግስት
* ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር መንግስት የውጭ ጫናዎችን በብቃት መቋቋሙን ገለጹ። ፕሬዝዳንቱ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መንግስት በሚቀጥለው ዓመት ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው እንዲሆን በትጋት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
* የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ በድምቀት ተከበረ። "ኢሬቻ ለሀገር ማንሠራራት" በሚል መሪ ቃል በሀርሰዴ ሐይቅ የተከበረው በዓል ላይ አባ ገዳዎች፣ ሀዳ ሲንቄዎች እና ከመላው ኦሮሚያ የተውጣጡ እንግዶች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
* ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ 8.3 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በ2017 በጀት ዓመት የተገኘው ገቢ በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛው መሆኑን አስታውቀዋል። የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚም የተጠናከረ እድገት እያሳየ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ገምግሟል።
* በሶማሌ ክልል የዩሪያ ማዳበሪያ እና የነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ተጀመረ። በጎዴ ከተማ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት የሀገሪቱን የግብርና ምርታማነት ከፍ ለማድረግና የነዳጅ ፍላጎትን ለማሟላት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
ማህበራዊ
* በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የህክምና መሳሪያዎች ወደ ስራ ተመለሱ። በመቀሌ የሚገኘው የአይደር ኮምፕሬሄንሲቭ ሪፈራል ሆስፒታል በጦርነት ወቅት ከጥቅም ውጪ የነበሩ የህክምና መሳሪያዎችን በመጠገን ዳግም አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታውቋል።
* ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በምንጃር ለሞቱት ዜጎች ሀዘናቸውን ገለጹ። በምንጃር ወረዳ፣ አረርቲ ከተማ በሚገኝ ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰ አደጋ ከ30 በላይ ምዕመናን ህይወት ማለፉን ተከትሎ ፓትርያርኩ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸው፣ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜና
* እስራኤል በጋዛ ጦርነቱ እንደገና መቀስቀሱን አስታወቀች። ከሁለት ወራት የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ እስራኤል በጋዛ ላይ ዳግም ሙሉ ጦርነት ማወጇን ገልጻለች።
* የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ጉባኤ በተርክሜኒስታን ተጀመረ። ኢትዮጵያን ጨምሮ 32 የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የሚሳተፉበት 3ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኮንፈረንስ ተጀምሯል። የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሀገራቱ የሚያጋጥሟቸውን የልማትና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች በንግግራቸው አንስተዋል።
* የአሜሪካ ፍርድ ቤት በጾታቸው የተቀየሩ ዜጎች ጦሩን እንዳይቀላቀሉ የተጣለውን እገዳ ሻረ። ውሳኔው በሀገሪቱ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።
* በአፍሪካ ከፍተኛ የሙቀት መጠን እና የአየር ንብረት ቀውስ ስጋት መሆኑ ተገለጸ። እ.ኤ.አ. 2024 በአፍሪካ ታሪክ ከፍተኛ ሙቀት የተመዘገበበት ዓመት ሲሆን፣ በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች የተከሰቱ ድርቆችና ጎርፎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን አፈናቅለዋል።
* በቱርክ የፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ዋነኛ ተቀናቃኝ በቁጥጥር ስር ዋሉ። ይህ እስር በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ ተጨማሪ ውጥረት ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል።

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ።
27/09/2025

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ።

ቆሜ ልመርቅሽ ❗️==========ተቀበይኝ እማ ቆሜ ልመርቅሽ፣ ሕይወትን መርቀሽ ሰጥተሽኝ እኔማ።ይህ ቀረኝ የምለው የሚቆጨኝ በዓለም፣ኢትዮጵያ ዕድሜ ላንቺ ያላየሁት የለም።አንገትሽ ራስሽን ች...
09/09/2025

ቆሜ ልመርቅሽ ❗️
==========
ተቀበይኝ እማ ቆሜ ልመርቅሽ፣
ሕይወትን መርቀሽ ሰጥተሽኝ እኔማ።
ይህ ቀረኝ የምለው የሚቆጨኝ በዓለም፣
ኢትዮጵያ ዕድሜ ላንቺ ያላየሁት የለም።
አንገትሽ ራስሽን ችሎ ልየውና፣
ማግስቱን ይውሰደኝ አስር ሞት ይምጣና።
ትንቢትሽ ይፈፀም ከመሬት ጠብ አይበል፣
ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ገድልሽ ይንበልበል፤
ሰንደቅሽ ከፍ ይበል ይቁም ለዘላለም፣
ሰላም፣ ጥጋብ፣ ደስታ፣ ይታይብሽ ዓለም።
ሴራው ይክሸፍበት የመታብሽ አድማ፣
እጁን ሣር ያድርገው ጉልበቱን ቄጤማ፤
ካቀባበለብሽ ብረት ከደገነ
አምላክ ያግዝልሽ ላንቺ የወገነ፤
ፀሎትሽ ይሰማ አምላክ ይለመንሽ፣
ፈተናው አይለቅ የሚፈታተንሽ፤
አንገትሽ ራስሽን ችሎ ልየውና
ማግስቱን ይውሰደኝ አስር ሞት ይምጣና፤
በሰው ሀገር ምድር ለተበተኑት፣
ለልጆችሽ ሁኚ ዞሮ መግቢያ ቤት፤
በዓለም አደባባይ ከመንግሥታት ደጅ
ሞልቶሽ ተርፎሽ እንጂ ጎድሎብሽ አትሂጅ፤
ጎተራሽ አይጉደል አይድረቅ ሌማትሽ
ከክፉ ሰውሮ ያድንሽ እምነትሽ፤
ላንቺ የማይተኙ የማያንቀላፉ፣
ብን ይበሉ እንደጉም ከምድረ ገጽ ይጥፉ፤
ካረግንልሽ በላይ የምትሆኝልን፣
መጠሪያ እናታችን አንቺው ቆዪልን !!!

🇪🇹ቆሜ ልመርቅሽ #አርቲስት ጥላሁን ገሠሰ💪

እንኳን 1500 ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።
04/09/2025

እንኳን 1500 ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።

ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳውዲ ቴሌኮም የቢዝነስ አጋርነታቸውን ለማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉበሳውዲ ቴሌኮም የሴልስ ከርየር እና ሆልሴል ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ዚያድ ሃማድ...
30/08/2025

ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳውዲ ቴሌኮም የቢዝነስ አጋርነታቸውን ለማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ

በሳውዲ ቴሌኮም የሴልስ ከርየር እና ሆልሴል ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ዚያድ ሃማድ ኤ. አልሃሶን እና የከርየር ሴልስ ዳይሬክተር ሚስተር ባንደር ኤ. አልኮዳይር የተመራ ልዑክ ከኩባንያችን ማኔጅመንት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡

ውይይቱ በሁለቱ ኦፕሬተሮች መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ሲሆን፣ በተለይም ነባሩን የቢዝነስ ትብብር ለማሳደግ፣ አዳዲስ የዕድገት አማራጮችን ለመክፈት እና የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን ለማቅረብ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡

ዋና ስራ አስፈፃሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ “ለጋራ ተጠቃሚነት ብዙ ልንተባበርባቸው እና አዳዲስ የዕድገት እድሎችን ልንከፍት የምንችላቸው ዘርፎች ያሉ ሲሆን፤ የጋራ ዲጂታል ሽግግር የሚያሳድጉና ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ ልማትን የሚያፋጥኑ ናቸው” ብለዋል።

ውይይቶቱ የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ የሆልሴል ቢዝነስ እና የዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በተለይም የዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማሳደግ፣ የድንበር ተሻጋሪ የሀዋላ እና የክፍያ ሥነ ምህዳሮችን ለማጠናከር ያለመ ነው።

ልዑካኑ የኢትዮ ቴሌኮምን የላቀ የቢዝነስ አፈፃፀም ብቃት አስመልክቶ ያላቸውን አድናቆት የገለጹ ሲሆን፣ በተለይም ባለፉት ስድስት ዓመታት ኩባንያው ያስመዘገባቸው አስደናቂ ለውጦች እና ለተገኘው ስኬትም ከፍተኛ እውቅና ሰጥተዋል።

ሆልሴልንና ከርየርን ለማስፋፋት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን፣ በፊንቴክ፣ በዓለም አቀፍ ሀዋላ፣ የዲጂታል መፍትሄዎችና በርካታ የቢዝነስ ዘርፎች ላይ አዳዲስ በር የሚከፍት ይሆናል፡፡

Ethio-Daily

22/08/2025
ቻይና የመዳፍ ክፍያ ቴክኖሎጂን አስተዋወቀች!ኤቲኤም ካርድም ሆነ ስልክ አያስፈልግምቻይና ኤቲኤም ካርዶችም ሆነ ስልኮች ሳያስፈልጉ የእጅ መዳፍን ስካን በማድረግ ብቻ ክፍያዎችን መፈጸም የሚያስ...
11/08/2025

ቻይና የመዳፍ ክፍያ ቴክኖሎጂን አስተዋወቀች!
ኤቲኤም ካርድም ሆነ ስልክ አያስፈልግም
ቻይና ኤቲኤም ካርዶችም ሆነ ስልኮች ሳያስፈልጉ የእጅ መዳፍን ስካን በማድረግ ብቻ ክፍያዎችን መፈጸም የሚያስችል ቴክኖሎጂ ይፋ አድርጋለች፡፡
ይህም ማለት ማንኛውም መደብር ወይም ሱቅ ገብቶ ግብይት ለመፈጸም የሚያስፈልገው እጅ ብቻ ነው - የእጅ መዳፍ!
አዲሱ የክፍያ ቴክኖሎጂው፤ በቴንሴንትስ ዌይክሲን ፓልም ስካን እና አሊፔይ ባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂ የበለጸገ ሲሆን፤ ቴክኖሎጂው የመዳፍን ውጫዊ ቅርጾችና የደም ስሮችን በፍጹም ልከኝነት ያነባል ተብሏል።
ከዚህ ቀደም በWeChat Pay ወይም Alipay ይከናወን የነበረው የክፍያ ሥርዓት፣ አሁን በቀላሉ እጅን ስካነር ላይ በማድረግ ብቻ በቅጽበት መፈጸም ይቻላል - በአዲሱ የቻይና የክፍያ ሥርዓት፡፡
በሺዎች በሚቆጠሩ 7-ኢለቨን መደብሮች፣ የሜትሮ ጣቢያዎች፣ አየር ማረፊያዎችና ካምፓሶች ውስጥ የገባው አዲሱ ቴክኖሎጂ፤ በቅርቡ በዓለም ዙሪያ እንደሚሰራጭ ይጠበቃል፡፡
ቴክኖሎጂው ፈጣን፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ምቹ ነው ተብሏል፡፡ ነገር ግን የባዮሜትሪክ መረጃ አንዴ ከተጣሰ ሊቀየር ስለማይችል የግል ምስጢሮች ደህንነት ላይ ስጋቶች መፍጠሩ አልቀረም፡፡
Join Our Telegram channels
https://t.me/abyssinia_22
https://t.me/alldigital_24
https://t.me/EthioTechhub24
https://t.me/forall2021
https://t.me/digital_2022

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio-Daily posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Ethio Daily ኢትዮ- ወቅታዊ

አዳድስ እና ወቅታዊ መረጃዎች & አዝናኝ ቪዲዎችን እንዲሁም ፎቶዎችን የምታገኙበት ነው ፡፡ ለሌሎች በማጋራት ይተባበሩን

1.Facebook account=https://www.facebook.com/profile.php?id=100011264252109&ref=bookmarks

2.page=https://www.facebook.com/AEB2543/

3.Youtube channel= https://www.youtube.com/channel/UCYFtGLfiUT1STzTqzGBcOLQ?view_as=subscriber