Ethio-Daily

Ethio-Daily አዳድስ እና ወቅታዊ መረጃዎች።

የኢትዮጵያ ብር በሩሲያ የባንክ ምንዛሬ ውስጥ ተካተተ*******የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ሌሊት ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ የኢትዮጵያን ብር በምንዛሬ ዝርዝር ውስጥ አካቷል።ይህም ማለት ብርን ወደ...
11/07/2025

የኢትዮጵያ ብር በሩሲያ የባንክ ምንዛሬ ውስጥ ተካተተ
*******

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ሌሊት ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ የኢትዮጵያን ብር በምንዛሬ ዝርዝር ውስጥ አካቷል።

ይህም ማለት ብርን ወደ ሩብል እንዲሁም ሩብልን ደግሞ ወደ ብር መመንዘር የሚያስችል ዕድልን ይሰጣል።

በዚህም መሰረት ባንኩ ለ100 የኢትዮጵያ ብር 57.5872 ሩብል ወይም ለ1 ብር 0.575872 ሩብል የምንዛሬ ተመን አስቀምጧል።

ባንኩ ለኢትዮጵያ ብር ምንዛሬ ተመን የኮድ ቁጥር 230 የሰጠ ሲሆን በየዕለቱም የምንዛሬ ተመኑን የሚያሳውቅ ይሆናል።

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያን ብር ጨምሮ የ12 ሀገራት ገንዘቦች ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ጋር ያላቸውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ለማስቀመጥ ውሳኔ ላይ መድረሱን ከቀናት በፊት ማስታወቁ ይታወሳል።

Ethio-Daily

22/06/2025
አሜሪካ በ3 የኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ሰነዘረች******************አሜሪካ ፎርዶውን ጨምሮ ኢራን ውስጥ በሚገኙ 3 የኒውክሌር ተቋማት  ላይ ጥቃት ማድረሷን ፕሬዘዳንት ዶና...
22/06/2025

አሜሪካ በ3 የኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ሰነዘረች
******************
አሜሪካ ፎርዶውን ጨምሮ ኢራን ውስጥ በሚገኙ 3 የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ማድረሷን ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይሎች በፎርዶ፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃን በሚገኙ የኢራን የኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ “በጣም የተሳኩ” ጥቃቶችን ማድረጋቸውን እና አሁን ሁሉም የአሜሪካ አውሮፕላኖች ከኢራን የአየር ክልል ውጭ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

በጥቃቱ የዩኤስ ቢ-2 ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች ተሳትፈዋል ተብሏል፡፡

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ የማህበራዊ ትስሰር ገፃቸው ባስተለለፉት መልዕከት “የቴህራን የኒውክሌር መርሃግብር ዘውድ” የሆነው ፎርዶው ጠፍቷል ሲሉ ገልፀዋል።

ሮይተርስ እንደዘገበው ኢራን በፎርዶው የኒውክሌር ጣቢያ ጥቃት መድረሱን አረጋግጣለች።

ለካ ጦርነትም ትርፍ አለው!ኢራን እስካሁን ኢስራኢል ላይ ለተኮሰቻቸው መሳሪያዎች 900 ሚሊየን ዶላር አውጥታለች  ። **** Ethio-Daily ***ኢራን 5ኛ ትውልድ የተባለውን  የመጨረሻ ...
17/06/2025

ለካ ጦርነትም ትርፍ አለው!

ኢራን እስካሁን ኢስራኢል ላይ ለተኮሰቻቸው መሳሪያዎች 900 ሚሊየን ዶላር አውጥታለች ።

**** Ethio-Daily ***

ኢራን 5ኛ ትውልድ የተባለውን የመጨረሻ ቴክኖሎጂ የተገጠመለትን የአሜሪካ ድሮን ከመሬት አፍርጣዋለች። የዚሕን ድሮን ሚስጥሮች ሩሲያ በብርቱ ትፈልገው ነበርና ለኢራን 2 ቢሊየን ዳላር አቅርባለች።

➢ የመጨረሻው ቴክኖሎጂ ባለካሜራው የእስራኤል ሚሳኤል ብዙም ሳይጎዳ በኢራን በረሐዎች ወድቋል። ይሕንን ከድምፅ በ8እጥፍ የበለጠ ሚሳኤል ለመመርመር ሰሜን ኮርያ 500 ሚሊየን፣ ቻይና 2 ቢሊየን ዋጋ ለኢራን አቅርበዋል።

➢በአሪያን ሻሮን ስም የተሰየመውን አየር ላይ የሚቆም ተምዘግዛጊ ሔሊኮፕተርን ከኢራን ለመግዛት የደቡብ አፍሪካው ሐፓች አምራች 800 ሚሊየን አቅርቧል።

“የሙሴ ድልድይ” በቀይ ባህር ላይ ሊገነባ ነው።Ethio Daily ሳውዲ አረቢያ እና ግብፅ ሁለቱን ሀገራትና አህጉራት  ለማገናኘት በቀይ ባህር ላይ በአህጉሪቱ በርዝመቱ ቀዳሚ የሆነና 4 ቢሊ...
09/06/2025

“የሙሴ ድልድይ” በቀይ ባህር ላይ ሊገነባ ነው።

Ethio Daily

ሳውዲ አረቢያ እና ግብፅ ሁለቱን ሀገራትና አህጉራት ለማገናኘት በቀይ ባህር ላይ በአህጉሪቱ በርዝመቱ ቀዳሚ የሆነና 4 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ የሚፈጅ "የሙሴ ድልድይ” ለመገንባት ስምምነት ላይ በመድረስ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተዘግቧ ።

አፍሪካን እና እስያንን በቀይ ባህር ለማገናኘት ይችላል የተባለዉና ለግንባታዉ የ4 ቢሊየን ዶላር በጀት የተበጀተለት ይህ ድልድይ ራስ ሀሚድን በግብፅ ሲናይ ባሕረ ገብ መሬት ሻርም ኤል ሼክን ያገናኛል። ተብሏል ።

የግብፁ ህዝብ ግኑኝነት እንደገለፁት ከሆነ ለሳውዲው ንጉስ ክብር ሲባል "የንጉስ ሳልማን ቢን አብዱላዚዝ" እንዲባል ሃሳብ ቀርቦ የነበር ቢሆንም ከቀይ ባህር ሃይማኖታዊ ታሪክ በመነሳት ህዝቡ ባቀረበዉ ጥያቄ ስያሜው “የሙሴ ድልድይ” እንዲባል ተወስኗል ስያሜዉም #ሙሴ ቀይ ባህርን የከፈለበትን ታሪክ መሰረት ያደረገ ነዉ ብለዋል ።

Ethio-Daily

 የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2026 አሸናፊዎች ቅዳሜ ሚያዚያ 25/2017 ዓ/ም ይፋ ይደረጋሉ።ለዲቪ (Diversity Visa) 2026 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram...
01/05/2025



የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2026 አሸናፊዎች ቅዳሜ ሚያዚያ 25/2017 ዓ/ም ይፋ ይደረጋሉ።

ለዲቪ (Diversity Visa) 2026 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።

NB. የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation Number በማለት አስፈለጊ መረጃ በመሙላት በኢሜል አዲስ ቁጥር ማግኘት ይቻላል።

ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የሚደርስ የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ተዘጋጅቷል። ይህ ቁጥር ብቁ የሆኑ ሀገራትን ሁሉ የሚጠቃልል ሲሆን #ኢትዮጵያም አንዷ ናት።

የዲቪ ሎተሪ መውጫ መድረሱን ተከትሎ " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል ፣ ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው ምንደውለው / ይህን ኢሜል / ቴክስት የምንልከው " በማለት የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች ሊጠነቀቁ ይገባል።

አንድ አመልካች ዲቪ 2026 ደርሶት እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማወቅ የሚችልበት ብቸኛው መንገድ ከላይ የተጠቀሰው ድረገጽ ብቻ ነው።

አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ ጨምሮ) ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 55 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።

Ethio-Daily

ቻይና ከአሜሪካ ወደ አገሯ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ 84 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ አደረገች፡፡Ethio-Daily ከዚህ ቀደም ቻይና የ34 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ አድርጋ የነበር ሲሆን፤አሜሪካ ዛሬ ማለ...
09/04/2025

ቻይና ከአሜሪካ ወደ አገሯ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ 84 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ አደረገች፡፡

Ethio-Daily

ከዚህ ቀደም ቻይና የ34 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ አድርጋ የነበር ሲሆን፤አሜሪካ ዛሬ ማለዳ በቻይና ላይ 104 በመቶ ታሪፍ ጭማሪ ማድረጓን ተከትሎ ታሪፉን ከፍ አድርጋዋለች፡፡

ሁለቱ አገራት ወደ ንግድ ጦርነት እንዳይገቡ ስጋቶች የነበሩ ቢሆንም፤ ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገዉ የቻይና የ84 በመቶ ታሪፍ የንግድ ጦርነቱን አስጀማሪ ነዉ ተብሏል፡፡

ትራምፕም ሆነ አስተዳደራቸዉ የታሪፍ ጭማሪ የተደረገባቸዉ አገራት ዉሳኔዉን በጸጋ እንዲቀበሉ ማሳሰባቸዉ ይታወሳል፡፡

እንደ ቻይና እና ብራዚል ያሉ አገራት ጉዳዩን እንደማይቀበሉት በተደጋጋሚ ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡

አሜሪካ ታሪፍ ጭማሪ ማድረጓን ተከትሎ ቻይና ተመሳሳዩን እርምጃ የወሰደችበትን ውሳኔ እንድትቀለብስ እስከ ዛሬ ረቡዕ ድረስ ቀነ ገደብ አስቀምጠዉ ነበር፡፡

ቻይና በበኩሏ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ በሚል አሜሪካ ለጣለችባት የታሪፍ ጭማሪ የአጸፋ ምላሽ ሰጥታለች፡፡

ትራምፕ ከቻይና በተጨማሪ በ60 አገሮች ላይ ከፍተኛ ታሪፍ ዛሬ ተግባራዊ አድርገዋል፡፡

ትራምፕ ቤጂንግ ከዋሽንግተን ጋር ስምምነት ላይ እስክትደርስ ድረስ አሜሪካ በቻይና ላይ የጣለቻቸው ቀረጦች ተግባራዊ ሆነው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል፡፡

Celebrating my 6th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉
09/04/2025

Celebrating my 6th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉

05/04/2025

በዛሬው እለት ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ተጓዦች ታገቱ

- በተከፈተ የተኩስ እሩምታ የሞቱ መንገደኞችም እንዳሉም ታውቋል

ከባህር ዳር ከተማ ተነስተው በዛሬው እለት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ የነበሩ የአንድ አውቶቡስ ተሳፋሪ መንገደኞች በመንገዳቸው መሀል እንደታገቱ ታውቋል።

ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው እገታው የተፈፀመው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጎሀፂዮን ከተማ አቅራቢያ ነው። ታጣቂዎቹ የተኩስ እሩምታ አውቶቡሱ ላይ በመክፈታቸው የተገደሉ መንገደኞች እንዳለ የታወቀ ሲሆን የተረፉትን ይዘው ወደ ጫካ መግባታቸው ታውቋል።

"ከእገታው ያመለጡ የተወሰኑ ሰዎች አሉ፣ የፌደራል ፖሊስ ደርሶ ከታጣቂዎች ጋር እየተታኳሱ ነው" በማለት አንድ የአካባቢው ምንጭ ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

ድርጊቱ መፈፀሙን 'የሹፌሮች አንደበት' የተባለው ገፅ ያረጋገጠ ሲሆን "ከጎሀፂዮን እና ቱሉ ሚሊክ ማዕከል አንድ አውቶብስ ሙሉ ሰው ታፍነው መወሰዳቸውን እና በተተኮሰ ጥይት የተሳፋሪ ህይወት ማለፉ ተሰምቷል" ብሏል።

በተመሳሳይ ከሁለት ሳምንት በፊት በፍቼ እና ጎሀፂዮን ከተሞች መሀል 58 ዜጎች መታገታቸው ይታወሳል። እነዚህን መንገደኞች ለመልቀቅ መንግስት 'ኦነግ ሸኔ' ብሎ የሚጠራቸው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት ለአንድ ታጋች እስከ 1.5 ሚልዮን ብር እየጠየቁ እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።

መጋቢት 8 ቀን የተፈፀመው ይህ እገታ በመንግስት ሚድያዎችም ሆነ በባለስልጣናት ምንም ቃል ያልተተነፈሰበት መሆኑ እጅጉን እንዳሳዘናቸው የታጋች ቤተሰቦች ገልፀው አሁን ላይ የቻሉትን ለመሰብሰብ የየቤቱ እየዞሩ እየለመኑ እንዲሁም በሶሻል ሚድያ ለህዝብ የእርዳታ ጥሪ እያቀረቡ መሆኑን ጠቁመው ነበር።

በዚህ መስመር ከዚህ በተደጋጋሚ እገታዎች የሚፈፀሙ ሲሆን በአካባቢው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት በስፋት እንደሚንቀሳቀሱበት ይታወቃል።

መረጃው =መሰረት ሚዲያ

05/04/2025

ደሴ በ1885 ዓ.ም ተመሰረተች።

31/03/2025

የህሊና ፍርድ ስጡ

‼️‼️‼️‼️
22/03/2025

‼️‼️‼️‼️

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio-Daily posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Ethio Daily ኢትዮ- ወቅታዊ

አዳድስ እና ወቅታዊ መረጃዎች & አዝናኝ ቪዲዎችን እንዲሁም ፎቶዎችን የምታገኙበት ነው ፡፡ ለሌሎች በማጋራት ይተባበሩን

1.Facebook account=https://www.facebook.com/profile.php?id=100011264252109&ref=bookmarks

2.page=https://www.facebook.com/AEB2543/

3.Youtube channel= https://www.youtube.com/channel/UCYFtGLfiUT1STzTqzGBcOLQ?view_as=subscriber