Ethiopian News ዜና ዘ ኢትዮጵያ

Ethiopian News ዜና ዘ ኢትዮጵያ ትኩስ ዜናዎች የሚቀርቡበት የመረጃ ድር

" በአንድ ቀን እናቴንና ነፍሰ ጡር ባለቤቴን ያሳጣኝ ባለሥልጣን እስር ቤት መሆኑን እንጂ መለቀቁን አላዉቅም ነበር " - ሚስትና እናቱን በአንዴ ያጣ ግለሰብ " ግለሰቡ ከእስር ቤት ወጥቷል፤...
24/03/2025

" በአንድ ቀን እናቴንና ነፍሰ ጡር ባለቤቴን ያሳጣኝ ባለሥልጣን እስር ቤት መሆኑን እንጂ መለቀቁን አላዉቅም ነበር " - ሚስትና እናቱን በአንዴ ያጣ ግለሰብ

" ግለሰቡ ከእስር ቤት ወጥቷል፤ ዉሳኔዉ ተገቢ ያልሆነና ከፍተኛ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት የታየበት ነዉ ! " - የሕግ ባለሙያዎች

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዲኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ሚጁ ታህሳስ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ስልጣንን ያለ አግባብ በመገልገል ያለመንጃ ፈቃድ የመንግስትን መኪና ለልምምድ በሚል ሲያሽከረክሩ በወረዳዉ አፉርሲ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሰርግ መርሃግብር ላይ የነበሩ ሰዎች ላይ አደጋ አድርሰዋል።

በዚህም አንዲት ነፍሰ ጡር ሴትን ጨምሮ 2 ሰዎች ሞተዋል ፤ በ28 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት በባለስልጣኑ ደርሷል።

ባለስልጣኑ የጌዲኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዉ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ብሏቸው የ13 ዓመት ፅኑ እስራትና 10 ሺህ ብር ቅጣት ብይን ከሰጠ በኋላ የቅጣት ዉሳኔዉን ወደ 3 ዓመት ከ7 ወር ማዉረዱንና በ2 ዓመት ገደብ እንዲፀና በማድረግ ከእስር እንዲፈቱ ማድረጉን የተጎጂ ቤተሰቦች እና የጌዲኦ ዞን ፍትሕ አካላት መናገራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ አስነብቧል።

በአንድ ቀን ወላጅ እናቱንና ነፍሰ ጡር ባለቤቱን ያጣዉ አቶ ኩራባቸዉ ኤደማ " ወላጅ እናቴን እና ነፍሰ ጡር ሚስቴን ማጣቴ ለእኔ መግለፅ ከምችለዉ በላይ መሪር ሀዘን ነዉ " ብለዋል።

" ደማቸዉ ሳይደርቅ ገና በሁለተኛ ወሩ ሕይወታቸው እንዲያልፍ ያደረገዉ ባለስልጣን ከእስር ቤት ተለቆ ወደ ቤቱ መግባቱን ሰዎች ሲነግሩኝ በጣም አዝኛለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።

" እኔ አሁን ወደ ፈጣሪ ከማልቀስ በስተቀር የምካሰስበት አቅምም ሆነ ባለስልጣን ዘመድ የለኝም " የሚሉት አቶ ኩራባቸዉ " ከባለቤቴና ወላጅ እናቴ ሞት በኋላ ያለሁበትን መከራ እጅጉን ከባድና ተንቀሳቅሼ መስራት ስላልቻልኩ ሶስት ልጆቻችንን፣ አዛውንት አባቴን መመገብ ከአቅሜ በላይ ሆኖብኛል " ብለዋል።

አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተሉ የነበሩ የመንግስት የስራ ኃላፊ የዞኑ መንግስት የበላይ አመራሮች ጣልቃ ገብነት አደጋው ከተከሰተበት ማግስት ጀምሮ ይስተዋል እንደነበር ተናግረዋል።

በወቅቱ ተጎጂዎች ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ ከማድረግ ይልቅ የሟቾችን መቃብር በሲሚንቶ በማሰራትና ባለሥልጣኑ እንዳይታሰር በማድረግ ስራ ተጠምደው ነበር ብለዋል።

" ባለስልጣኑ ከታሰሩ በኋላም ለተወሰኑ ጊዜያት እስር ቤት ሆነዉ ለወረዳዉ አመራሮች የስራ መመሪያ ይሰጡ እንደነበር፣ አልፎ አልፎም ካቢኔ ጠርተዉ ይሰበስቡ እንደነበርም " ገልፀዋል።

አንድ የዞኑ ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ " የዞኑ ባለስልጣናት ጣልቃ ገብነት ከጅምሩ ዋና አስተዳዳሪው አቶ ተስፋዬ ሚጁ በቁጥጥር ስር እንዳይዉል ከማድረግና ክስ እንዳይከፈትበት በማስጠንቀቅም ጭምር የቀጠለ ነበር " ይላሉ።

" በዞኑ ዐቃቤ ሕጎች ፅኑ አቋም ክስ ተመስርቶባቸው በጌዲኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል የወንጀል ድርጊቱን እንደፈፀሙ በማመናቸው ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ህግንና የተከሳሹን የግራና ቀኝ ክርክር ከሰማ በኋላ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ መነሻ ጥፋተኛ በማለት በእርከኑ መነሻ ቅጣት በ8 ዓመት ፅኑ እስራትና የ13 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ብይን ከሰጠ በኋላ ከሁለቱም ወገን የቅጣት አስተያየት እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ለዉሳኔ መጋቢት 5 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር " ሲሉ ገልፀዋል።

" ዐቃቤ ሕግ ያቀረባቸዉን የቅጣት ማክበጃዎች ያልተቀበለው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሹ ያቀረቡት ሰባት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን ተቀብሎ መጋቢት 05 ቀን 2017 ዓ/ም ከተጠቀሰ ስምንት (8 ) ዓመት ጽኑ እስራትና 13 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣትን ወደ 3 ዓመት ከ7 ወርና 2 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት በማዉረድ የቅጣት አወሳሰን መምሪያ 2/2006 በማይፈቅድ ሁኔታ ቅጣቱን ወደ ገደብ ያመጣበት አግባብ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበትና የዞን ባለስልጣናት ጣልቃ ገብነት በግልፅ የታየበት ነዉ " ብለዋል።

እንደ ባለሞያው አስተያየት " 1ኛ የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 543 (3) የእስራት ቅጣት ከ5-15 ዓመት ጽኑ እስራትና ከ10-15 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጫ የሚል፣ 2ኛ የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 559 (2) እና (3) የወንጀል ክስ ለጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተደራራቢ የወንጀል ድርጊት በመሆኑ ተደራራቢ ክስ ቀርቦበት የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩ በህግ አግባብ በማየትና ከጉዳዩ ገለልተኛ በመሆን መወሰን ሲገባው በፖለቲካ ጫና ዉሳኔዉን ወደ ገደብ ዝቅ አድርጓል " ሲሉ ተናግረዋል።

የዐቃቤ ሕግ ቡድኑ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ለመጠየቅ ቢወስንም በበላይ ኃላፊዎች በኩል አሁንም ጫናዎች መኖራቸዉንና ተጎጂዎች ትክክለኛዉን ፍትሕ እስኪያገኙ የበኩላቸውን እንደሚወጡም አስታዉቀዋል።

በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ወደ ጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሳሙኤል ፍቃዱ የእጅ ስልክ እንደደወለ ያስነበበው ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃዉን ለመስጠት የስራ ፈቃድ፣ ለመስሪያ ቤታቸው በአድራሻ የተፃፈ ደብዳቤ እና የሠራተኛው መታወቂያ ኮፒ ይዛቾሁ በአካል ካልመጣችሁ መረጃ አንሰጣችሁም መባሉን ጠቅሷል።

👇
የገደብ ቅጣት ከየትኛውም አይነት ወንጀል ራሳቸውን አቅበው፤ የትኛውም የወንጀል ድርጊት ላይ እንዳይገኙ የሚል ነው። የወንጀል ድርጊት ላይ ተሳትፈው ቢገኙ ግን የታገደው የቅጣት ውሳኔ ተፈፃሚ ይሆናል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ጊዜ ለአንድ ዓመት ሊራዘም እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጡየትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተቋቋመበት “ህግ ተሻሽሎ”፤ የስልጣን ጊዜው ለተጨማ...
20/03/2025

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ጊዜ ለአንድ ዓመት ሊራዘም እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጡ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተቋቋመበት “ህግ ተሻሽሎ”፤ የስልጣን ጊዜው ለተጨማሪ አንድ ዓመት ሊራዘም እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥቆማ ሰጡ። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ስራ ከተገመገመ በኋላ፤ “በግለሰቦች ደረጃ ለውጥ ሊካሄድ እንደሚችልም” አብይ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የትግራይ ጉዳይ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታን በተመለከተ፤ ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው። አብይ በዚሁ ምላሽቸው፤ የትግራይ ክልልን በአሁኑ ወቅት እየመራ የሚገኘው ጊዜያዊ አስተዳደር “የተሰጠው” የሁለት ዓመት ጊዜ ማለቁን አመልክተዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩን የስልጣን ጊዜ ለማራዘም፤ “የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚያከብር መንገድ” “የህግ ማሻሻያ” እንደሚያስፈልግም ለፓርላማ አባላቱ አስረድተዋል። በትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም የሚያስችል ደንብ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የጸደቀው መጋቢት 9፤ 2015 ነበር።

በትግራይ በአሁኑ ወቅት ያለው ሁኔታ “በቅርቡ” እንደሚገመገም የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ ከዚያ በኋላ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የተቋቋመበትን ህግ ወደማሻሻል እንደሚገባ አስረድተዋል።

“ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተገምግሞ፣ መጠነኛ ለውጥ ተደርጎ፤ የፕሪቶሪያን ስምምነት በሚያከብር መንገድ እስከሚቀጥለው ምርጫ ድረስ ስራውን እየሰራ፣ ህዝቡን ለምርጫ ማዘጋጀት እና ህዝቡን የስልጣን ባለቤት የማድረጉን ሂደት ማረጋገጥ ይጠበቅበታል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀጣይ ሂደቱን አካሄድ አመልክተዋል።
.......

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ

" እንደዚህ ዘመን... ሰው እንዳሻው የሚናገርበት፣ ሁሉ ጉዳይ ፖለቲካ የሆነበት ዘመን ያለ አይመስለኝም" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግሥታቸው “ለትችት በጣም ክፍት”...
20/03/2025

" እንደዚህ ዘመን... ሰው እንዳሻው የሚናገርበት፣ ሁሉ ጉዳይ ፖለቲካ የሆነበት ዘመን ያለ አይመስለኝም" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግሥታቸው “ለትችት በጣም ክፍት” እንደሆነ እና የአሁኑ ወቅት “ሰው እንዳሻው የሚናገርበት” ነው ብለው እንደሚያምኑ ለምክር ቤት አባላት ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዘለግ ያለ ደቂቃ ወስደው ለጠየቁት ጥያቄ ምላሽ ነው። የምክር ቤት አባሉ ደ/ር ደሳለኝ ጥያቄ ሲያቀርቡ በግጭቶች እና በመንግሥት ኃይሎች ስለተገደሉ ሰዎች የተለያዩ ተቋማት ሪፖርቶችን በመጥቀስ ዘርዝረዋል።

እንዲሁም በእስራ ላይ ስለሚገኙ የአማራ ተወላጅ “ጋዜጠኞች፣ ምሁራን እና ፖለቲከኞችን” አንስተዋል። ዶ/ር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ “ብልጽግና የሚታየው ጦርነት፣ የሚሰማውም የቄስ ሞገሴዎችን ከንቱ ውዳሴ፣ ከተናገረም ነጭ ፕሮፓጋንዳ ወይም ውሸት ነው” ሲሉ ወቅሰዋል።

ዶ/ር ደሳለኝ በገዢው ግልጽግና ፓርቲ የሚመራውን መንግሥት “የሙሉ ጊዜ ጦረኛ እና ግጭት ጠማቂ” እንዲሁም “ጠቅላይ አገዛዝ” ስርዓትን የሚከተል ነው በማለት ወንጅለዋል። ግጭቶችን የማስቆም “ተቀዳሚ ኃላፊነት” የመንግሥት መሆኑን ጠቅሰው ያሳሰቡት የምክር ቤት አባሉ፤ የፋኖ እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ኃይሎች ሰላማዊ ዕድሎችን “አሟጠው እንዲጠቀሙ” ጠይቀዋል።

ለዶ/ር ደሳለኝ ጥያቄ በቀጥታ ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ “ይህንን ‘ጦር ሰባቂ’ መንግሥት በዚህ ልክ ሲተቹት፤ ሕዝብ እንዳይወጣ እንዳይገባ፣ እንዳይማር፣ እንዳያርስ ያደረገውን ኃይል ለምን ባላየ ባልሰማ አለፉት?” ሲሉ መልሰው ትችት ሰንዝረዋል።
ዐቢይ፤ ብልጽግና ፓርቲ “የሚሰማው የቄስ ሞገሴዎችን ከንቱ ውዳሴ” ነው ለሚለው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፤ “እኛ ሰፈር ፊታውራሪ መሸሻ የሉም ፊት አውራሪ መሸሻ በሌሎበት ቄስ ሞገሴ ምን ይሰራል?” ሲሉ ጠይቀዋል።

“ባይሆን እኛ ጉዱ ካሳዎች ብንባል ያምራል እንጂ፤ በየት በኩል ነው እኛ ሰፈር ቄስ ሞገሴዎች ሚታዩት? ምክንያቱም እኛ ትናንትን ናፋቂዎች፣ ትናንትን ለማጽናት የምናሸረግድ ሰዎቸ ሳንሆን፤ ነገን ለልጆቻችን ለማጽናት መጋፈጥ የማይገባንን ጉዳይ የምንጋፈጥ ለውጥ ፈላጊዎች ነን” ሲሉም ተናግረዋል።

ዶ/ር ደሳለኝ የሰዎችን እስር በተመለከተ ላቀረቡት ትችት ዐቢይ በሰጡት ምላሽም በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁኔታ ከቀድሞው ጋር አነጻጽረው ተናግረዋል። “እርሶ እዚህ ፓርላማ አካባቢ ከመቅረብዎ በፊት እኔ የዚህ ፓርላማ አባል ነበርኩኝ። ቅድም እንዳደረጉት ግላጭ ስድብ ፓርላማ ውስጥ አይፈቀድም። ነበርንበት፤ እናውቀዋለን” ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ሰው በንግግሩ የሚታሰር ከሆነ ጦረኛ፣ ግጭት ጨማቂ፣ ጆሮ የሌለው ከሚል በላይ ሌላ ምን ስድብ አለ? እዚህ ፊት ለፊታችን ሆነው እየተሳደቡ እንኳ ካልታሰሩ ሰው በንግግሩ ብቻ አይታሰርም ማለት ነው” ብለዋል።

ዐቢይ መንግሥታቸው “ለትችት በጣም ክፍት” መሆኑን የገለጹት “ዩቲዩብ ላይ የተናገረ ሁሉ” ጋዜጠኛ ተብሎ መጠቀሱን ተቃውመዋል።
“በዚህ ፓርላማ፣ ከዚህ ፓርላማም ውጪ ያሉት ይታዘባሉ፤ እንደዚህ ዘመን ሰው ሁሉ ያሻውን የሚናገርበት፣ ሁሉ ጉዳይ ፖለቲካ የሆነበት ዘመን ያለ አይመስለኝም” ሲሉ ለምክር ቤት አባሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

" ጨርሶ ይዘጋል አይዘጋም የሚለውን የምናውቀው ነገር የለም ስራ አቁሙ ብቻ ነው የተባልነው የመጨረሻ ውሳኔ መቼ እንደሚታወቅ እርግጠኞች አይደለንም " - የVOA የኢትዮጵያ ዘጋቢ የአሜሪካ ድ...
17/03/2025

" ጨርሶ ይዘጋል አይዘጋም የሚለውን የምናውቀው ነገር የለም ስራ አቁሙ ብቻ ነው የተባልነው የመጨረሻ ውሳኔ መቼ እንደሚታወቅ እርግጠኞች አይደለንም " - የVOA የኢትዮጵያ ዘጋቢ

የአሜሪካ ድምጽ ራድዮ VOA የፕሬዝደንት ትራምፕ ውሳኔን ተከትሎ ስራ ማቆም ጀመሯል።

በዛሬው ዕለት (የካቲት 8 /2017 ዓ.ም) ቪኦኤ ቴሌቪዥን ስርጭቱን አቁሞ ውሏል። በአንዳንድ ሃገራት ደግሞ ሙዚቃ ብቻ እያስተላለፈ ይገኛል።

በመላው ዓለም ከ1,300 በላይ ሰራተኞች ያሉት የአሜሪካ ድምፅ በየዓመቱ የሚመደብለት የ267.5 ሚሊዮን ዶላር በጀት ተሰርዞ ሠራተኞቹ የግድ እረፍት ደብዳቤ ተሰጥቷቸዋል።

83 ዓመታትን ያስቆጠረው ቪኦኤ በዶናልድ ትራምፕ ውሳኔ ጣቢያው በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስርጭቱን አቋርጧል። ውሳኔውም በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ዘጋቢዎቹን አስደንግጧል።

በኢትዮጵያ በሶስት ቋንቋዎች በአማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ እና ትግርኛ ስርጭቱን ያከናውን የነበረው ቪኦኤ በኢትዮጵያ የሚገኙ ዘጋቢዎቹም ከቅዳሜ ጀምሮ ስራቸውን እንዲያቆሙ እንደተነገራቸው ስሜ አይጠቀስ ያሉ የተቋሙ ዘጋቢ መናገራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ አስነብቧል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ ፈለጉት የቪኦኤው ዘጋቢ " እኛ በሰራነው ነው ይከፈለን የነበረው ከቅዳሜ ጀምሮ እንድናቆም በኤዲተሮቻችን በኩል ተነግሮናል።

ቪኦኤ አዲስ አበባ ፣ ድሬደዋ ፣ደሴ ፣ባህር ዳር ፣መቀሌ እና ሃዋሳ ያሉ ዘጋቢዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 11 ዘጋቢዎች በኢትዮጵያ አሉት።

የአሜሪካን የፌደራል ተቋማት ላይ ያለውን ነገር በብዙ መልኩ ስለምንሰማው እና የተለያዩ ተቋማት ስራዎቻቸው እና ሰራተኞቻቸው ሲቀነሱ ስለምናይ ለውጥ እንደሚኖር ስንጠብቀው ነበር ነገር ግን በዚህ ደረጃ አልነበረም።

ከቪኦኤ ጋር በተያያዘ ብቻ ሳይሆን ቪኦኤ የሚገኝበት እናት ድርጅት ጋር በተገናኙ አገልግሎቶች ላይ አዲሱ አመራር የሚያነሱት ጥያቄ ስላለ የምንጠብቀው ነገር ነበር ነገር ግን በዚህ ደረጃ አልጠበቅንም አስደንግጦናል።

ጨርሶ ይዘጋል አይዘጋም የሚለውን የምናውቀው ነገር የለም ስራ አቁሙ ብቻ ነው የተባልነው የመጨረሻ ውሳኔ መቼ እንደሚታወቅ እርግጠኞች አይደለንም።

ኢትዮጵያ ውስጥ ከ 10-15 ዓመት የሰራን ሰራተኛን ጨምሮ ከተቀጠረ ወር እንኳን ያልሞላው ሰራተኛ ነበር።

ተስፋችን ሙሉ በሙሉ አይዘጋም የሚል ነው በጀት እና ሰራተኛ ይቀነስ ይሆናል የሚቀነስ ሰራተኛ ካለ የእነሱ አካል እንሆናለን አንሆንም የሚለውን አናውቅም።

እስካሁን ዩኤስኤይድን ጨምሮ ተመሳሳይ ነገር የገጠማቸው የአሜሪካን ተቋማት ሰራተኞቻቸውን እየቀነሱ ነው ያሉት በዛ መንገድ ያስቀጥሉት ይሆናል የሚል ተስፋ አለን።

በምንሰማው መረጃ ሙሉ በሙሉ ' እንዘጋዋለን ' የሚል ነገር የለም ' በተሻለ ግልጽነት እና ተጠያቂነት የአሜሪካንን ጥቅም ባስጠበቀ መንገድ የሚሰሩ ሚዲያዎች እናደርጋለን ' የሚል መረጃ ነው የምንሰማው ይህ ማለት እንዘጋዋለን የሚል ትርጉም የለውም ሆኖ እስከምናየው ግን እርግጠኞች አይደለንም።

ነገር ግን ተመልሶ ወደ ስርጭት ቢመለስስ በየሃገሩ ያለው አገልግሎት ይቀጥላል ወይ የሚለው አሳሳቢ ነው ሚዲያው ቀጥሎ እነዚህ አገልግሎቶች ካልቀጠሉ ለእኛ ትርጉም የለውም " ብለዋል።

በሀገሪቱ አብዛኛው ቦታ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋረጠ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው ብሏል ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግ...
07/12/2024

በሀገሪቱ አብዛኛው ቦታ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋረጠ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው ብሏል

ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግር የተነሳ በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።

ችግሩን በመፍታት የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው ብሏል።

የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቆ፤ ያሉትን መረጃዎች በፍጥነት የሚያሳውቅ መሆኑንም ገልጿል።

01/12/2024

#ማስታወሻ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማሕበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሰሞኑን በስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደው የመጽሐፍ ምረቃ ላይ መዝሙር በሚያቀርቡ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች አጠገብ ቆመው በቪድዮ መታየታቸው አነጋግሯል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ከዚህ ቀደም እንደዚህ ተናግረው ነበር👇

ሶማሊያ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት አገሪቱን ለቅቀው እንዲወጡ አዘዘች።
31/10/2024

ሶማሊያ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት አገሪቱን ለቅቀው እንዲወጡ አዘዘች።

Somalia, Ethiopia, diplomat expulsion, current events.

Heaven Awot was sexually assaulted, mutilated and killed by her mother’s landlord Getnet Baye last August in the north-w...
19/08/2024

Heaven Awot was sexually assaulted, mutilated and killed by her mother’s landlord Getnet Baye last August in the north-western city of Bahir Dar in Amhara region.

Read full story👇

I have lost my Heaven, justis for heaven, r**e, killed. ethiopia, Amhara, Tigray

“የመንግስት መዋቅር በሌቦች ተጠልፏል”- ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ የኢዜማ የፓርላማ አባልየህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27፤ 2016 እያካሄደ ባለው መደበኛ ስብሰባ፤ የፓርላማ አ...
04/07/2024

“የመንግስት መዋቅር በሌቦች ተጠልፏል”- ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ የኢዜማ የፓርላማ አባል

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27፤ 2016 እያካሄደ ባለው መደበኛ ስብሰባ፤ የፓርላማ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር አብርሃም በርታ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ይስተዋላል ስላሉት “የሀብት ብክነት” እና “ሙስና” ጠይቀዋል።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የምትገኝበት የሙስና ችግር “እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል” ያሉት ዶ/ር አብርሃም፤ ሙስና በሀገሪቱ “ከዓመት ዓመት እየጨመረ መምጣቱን” ዓለም አቀፍ ተቋማት በሚያወጣቸው ሪፖርቶች ጭምር ይፋ መደረጉን አመልክተዋል። የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በቅርቡ ለፓርላማ ባቀረበው ዓመታዊ ሪፖርትም፤ “ከፍተኛ የሆነ የሃገር ሀብት ብክነት እንዳለ” በዝርዝር በማስረጃ አስደግፎ ማቅረቡንም ጠቅሰዋል።

“በኦዲተር ሪፓርት መሰረት በየመስሪያ ቤቶቹ ከፍተኛ የሆነ የጥሬ ገንዘብ ጉድለት ይታያል። ገንዘብ ያለማስረጃ ወጪ በማድረግ ይጠቀማሉ። ምንም አይነት ማስረጃ ሳያቀርብ በወጪ ይመዘግባሉ። ከፋይናንስ መመሪያና ደንብ ውጪ የገንዘብ ክፍያ ይፈጸማል” ሲሉ የፓርላማ አባሉ ተናግረዋል። መንግስት ሙስናን ለመዋጋት “ይህ ነው የሚባል መፍትሄ እየሰጠ አይደለም” ሲሉም ተችተዋል።

“የህዝብና የመንግስት ሃብት በዘረፉ ሙሰኛ ባለስልጣናት ላይ መቀጣጫ የሚሆን እርምጃን ከመውሰድ ይልቅ ተጨማሪ ሹመትና የቦታ ዝውውር በመስጠት መንግስት ሙሰኞችን አብሮ አቅፎ ይኖራል ማለት ይቻላል። ከዚም የተነሳ የመንግስት መዋቅር በሌቦች ተጠልፏል” ሲሉ ዶ/ር አብርሃም ወንጅለዋል።

ምንጭ:- ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

“I concede and therefore I will not sign the 2024 finance bill and it shall subsequently be withdrawn,” Ruto said in a t...
26/06/2024

“I concede and therefore I will not sign the 2024 finance bill and it shall subsequently be withdrawn,” Ruto said in a televised address on Wednesday. “The people have spoken.”

News, analysis, Entertainment from Ethiopia & worldwide, multimedia & interactive, opinions, documentaries.

Assange and US officials have been engaged in a legal dispute for the past 14 years because they believe Assange leaked ...
26/06/2024

Assange and US officials have been engaged in a legal dispute for the past 14 years because they believe Assange leaked confidential documents that could have endangered lives.

News, analysis, Entertainment from Ethiopia & worldwide, multimedia & interactive, opinions, documentaries.

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News ዜና ዘ ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share