Ethiopian News ዜና ዘ ኢትዮጵያ

Ethiopian News ዜና ዘ ኢትዮጵያ ትኩስ ዜናዎች የሚቀርቡበት የመረጃ ድር

"መንግሥት በሕዝቡ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በራሱ ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ ጭምር ስጋትን ለመፍጠር በሚል የሚወስደው እርምጃ ሊሆን ይችላል" አደም ካሴ።"በአሁኑ ወቅት ሕዝቡ ታጣቂዎችን ይፈራል፤ በተጨ...
16/09/2025

"መንግሥት በሕዝቡ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በራሱ ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ ጭምር ስጋትን ለመፍጠር በሚል የሚወስደው እርምጃ ሊሆን ይችላል" አደም ካሴ።

"በአሁኑ ወቅት ሕዝቡ ታጣቂዎችን ይፈራል፤ በተጨማሪም ይጠብቀኛል የሚለውን መንግሥትንም ይፈራል" ያሬድ ኃይለ ማሪያም።

"ይህ ድርጊት በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ሥርዓት አልበኝነት መኖሩን የሚያሳይ ምልክት ነው" ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የሕግ ባለሙያ።

እነዚህ አስተያየቶች እየተደጋገመ የመጣውን ዜጎችን ከሕግ ውጪ አፍኖ በኃይል የመሰወር ድርጊትን በተመለከተ የተሰነዘሩ ናቸው። ትኩረታቸውም ክስተቱ በሕዝቡ ውስጥ ስጋት የሚፈጥር እየሆነ መሄዱ ላይ ነው።

በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች ውስጥ በታጣቂዎች የሚፈፀሙ እገታዎች የዕለት ከዕለት ክስተት ወደ መሆን እየደረሱ ነው። ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ አንጻራዊ ደኅንነት ያለባት ብትሆንም ከስጋት ግን ነጻ አይደለችም።

አዲስ አበባ ውስጥ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ የመብት ተከራካሪዎች፣ ጋዜጠኞች እና ተራ ዜጎች በማይታወቁ ኃይሎች ተይዘው ለቀናት ወይም ለሳምንታት ተሰውረው የሚቆዩበት ሁኔታ አነጋጋሪ ሆኗል።

ሰዎች የፀጥታ ኃይል ነን በሚሉ ታጣቂዎች ነገር ግን የሕግ ሥርዓትን ባልተከተለ ሁኔታ ከቤታቸው፣ ከሥራ ቦታቸው እና ከመንገድ ላይ ታፍነው መወሰዳቸው ፍርሃት እና ግራ መጋባትን ፈጥሯል።

የፖሊስ እና የመከላከያ የደንብ ልብስ ወይም ሲቪል በለበሱ ሰዎች የሚፈጸመው አስገድዶ የመሰወር ክስተት የተደጋገመ ከመሆኑ በተጨማሪ የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትም "የማያውቁት" መሆኑ የበለጠ አሳሳቢ ሆኗል።

ቢሆንም ግን የሚታፈኑት ሰዎች በሥራቸው እና በእንቅስቃሴኣቸው የሚታወቁ መሆናቸው ድርጊቱ በመንግሥት አካላት እንደተፈጸመ ይታመናል። ታጋቾቹም ከቀናት ወይም ከሳምንታት በኋላ ሲለቀቁ መሰወራቸው ከመንግሥት አካላት ጋር የተያያዘ መሆኑን ይናገራሉ።

ይህ እየተደጋገመ ያለ እና በፖለቲካው፣ በሲቪል ማኅበረሰብ እና በጋዜጠኝነት ሙያ ላይ ያሉ ሰዎችን ላይ ያነጣጠረው አፈና የሚፈጸመው ምን ለማሳካት ነው? ወደ የትስ ሊያመራ ይችላል?

ውስጥ ሥርዓት አልበኝነት እንዲሰፍን የሚያደርግ ክስተት ነው" ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

አደም ካሴ በበኩላቸው እንዲህ ዓይነቱ አፈና እና መሰወር በተበራከተ ቁጥር "ሕገ ወጥነት እና የዘፈቀደ አካሄድን በማስፋፋት አደገኛ ሁኔታን የሚፈጥር ድርጊት ነው" ብለዋል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው የሕግ እና የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች ይህ እየተደጋገመ የመጣው ከሕግ ውጪ ሰዎችን የመሰወር ድርጊት ሕግ እና ሥርዓትን በማፍረስ፣ ሥርዓት አልበኝነትን ሊያስከትል እንደሚችል በአጽንኦት አስጠንቅቀዋል።

አፈናውን የሚፈጽመው ማን ነው?
"በፀጥታ ኃይሎች" ታፍነው ወዳልታወቁ ስፍራዎች የተወሰዱ ሰዎች እና ይህንን የተመለከቱ የዓይን እማኞች እንደሚሉት ከአለባበስ እና ከንግግራቸው የመንግሥት ኃይሎች መሆናቸውን ይናገራሉ።

ነገር ግን የሚፈልጉትን ሰው ለመያዝ የሚከተሉት መንገድ በአገሪቱ ሕግ ከሚፈቀደው ውጪ ከመሆኑ በተጨማሪ፣ የያዟቸውን ሰዎች የሚወስዱበት ቦታም በመደበኝነት የሚታወቁ እስር ቤቶች ወይም የማቆያ ስፍራዎች አይደሉም።

ይህ ደግሞ በሚያዙት ሰዎች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ ከባድ ሥነ ልቦናዊ ጫናን የሚያስከትል ነው።

የታፈኑት ሰዎች የት እና በማን እጅ መሆናቸውን የማያውቁ ቤተሰቦች ለመደበኛዎቹ የፀጥታ ተቋማት ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚሰጣቸው ምላሽ "የምናውቀው ነገር የለም" የሚል መሆኑ ደግሞ ተስፋ መቁረጥ ያነግሳል።

ያሬድ ኃይለማሪያም ከአንድ የፀጥታ ኃላፊ ጋር ይህንን ጉዳይ በተመለከተ በነበራቸው ንግግር መደበኛው የፖሊስ እና የፀጥታ ኃይል ታገቱ ስለተባሉት ሰዎች ከመስማት ባሻገር የሚያውቁት ነገር እንደሌለ እንደነገሯቸው ገልጸዋል።

በዚህም የተነሳ አፈናውን እና ስወራውን የሚፈጽም የተለየ ኃይል እንዳለ እንደሚያምኑ የሚጠቅሱት ያሬድ፣ እነሱም "ታፋኞቹን ወዳልታወቀ ቦታ ወስደው ለቀናት ካቆዩ በኋላ ጥያቄ እና መነጋገሪያ ሲሆኑ መንገድ ላይ ወይም ፖሊስ ጣቢያ አምጥተው ይጥሏቸዋል" ይላሉ።

ማንነታቸው የማይታወቁ፣ ፊታቸውን የሚሸፈኑ፣ የፖሊስ ወይም የወታደር የደንብ ልብስ የሚለብሱ፣ በመንግሥት ወይም በግል ተሽከርካሪ የሚንቀሳቀሱ ሰዎች የሚፈጽሙት አፈና ግራ መጋባትን በመስከተል ስጋትን ይፈጥራሉ።

ያሬድ እንደሚሉት የመንግሥት አካል መሆናቸው ቢታወቅ እንኳን ሕጋዊውን ሥርዓት ስለማይከተሉ በሕዝቡ ውስጥ በተቋማት ላይ ያለውን ዕምነት የሚያሳጣ "አደገኛ የሆነ የመንግሥታዊ ሥርዓት ውድቀት ማሳያ ነው።"

እነዚህ ሁሉ ድርጊቶች አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ውስጥ ሲከሰቱ የመንግሥት አካላት ዝምታን መምረጣቸው ደግሞ ግራ አጋቢ ሆኗል።

ይህ ደግሞ የመንግሥት እጅ እንዳለበት እና ይሁንታውን የሰጠው ድርጊት ነው የሚያስብል ከመሆኑ በተጨማሪ በሕጋዊ ተቋማት ሚና እና ተቀባይነት ላይ ተስፋ መቁረጥ እያስከተለ መሆኑን ያሬድ ኃይለማሪያም ይናጋራሉ።

ይህንን እገታ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ እየፈጸሙ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስን አስፈሪ አድርገውታል። ተመሳሳይ ስጋት በከተሞች ውስጥ መኖሩ ደግሞ ዜጎች ደኅንነት እንዳይሰማቸው ያደርጋል።

"በአሁኑ ወቅት ሕዝቡ ታጣቂዎችን ይፈራል፤ በተጨማሪም ይጠብቀኛል የሚለውን መንግሥትንም ይፈራል" የሚሉት አቶ ያሬድ፣ "ሕገወጥ ቡድኖች ሲያፍኑ መፍትሔው መንግሥት ነው ይባል ነበር። አፋኙ መንግሥት ሲሆን ወደ የት ይኬዳል?" ሲሉ ይጠይቃሉ።

ቢቢሲ እንደዘገበው

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች የርሀብ አድማ አደረጉበአማራ ክልል የፀጥታ ችግር ጋር በተገናኘ በሽብር ተጠርጥረው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የ...
15/09/2025

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች የርሀብ አድማ አደረጉ

በአማራ ክልል የፀጥታ ችግር ጋር በተገናኘ በሽብር ተጠርጥረው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች 'የፌደራሉ መንግስት በአማራ ሕዝብ ላይ እየፈፀመ ነው' ያሉትን ግድያ፣ እስር እና ወከባ በፅኑ በመቃወም የርሀብ አድማ ማድረጋቸው ተሰምቷል።

የፖለቲካ እስረኞቹ ጠበቆች እንደተናገሩት በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማት ስም በርካታ ዜጎች ተፈናቅለው ሜዳ ላይ በፈሰሱበት፣ የከተማዋ ወጣቶቾ በሕገ- ወጥ መንገድ ታፍሰው የት እንደገቡ ባልታወቀበት፣ ከ300 በላይ የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ፍትሕ በእስር ቤት ታጉረው በሚገኙበት በአሁኑ ወቅት "አዲስ ዓመት ገና አልጠባም" በሚል ከጷግሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በርሀብ አድማ ላይ ይገኛሉ።

በቂሊንጦ፣ በቃሊቲ፣ በአባ ሳሙኤል፣ በዝዋይ፣ በአዲስ አበባ እና በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤቶች ከ300 በላይ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ከአማራ ክልል የፀጥታ መደፍረስ ጋር በተገናኘ ታስረው ይገኛሉ ሲሉ ጠበቆቻቸው ተናግረዋል።

“ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ተሰርቷል፤ የሚቀሩ እባጮች ነበሩ አሁን እነርሱን ነው ቆርጠው ያወጡለት” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ የቅርብ ሰውለሁለት ዓመት ከአንድ ወር በእስር የሚገኙት የህዝብ...
13/09/2025

“ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ተሰርቷል፤ የሚቀሩ እባጮች ነበሩ አሁን እነርሱን ነው ቆርጠው ያወጡለት” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ የቅርብ ሰው

ለሁለት ዓመት ከአንድ ወር በእስር የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ሰሞኑን ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ማድረጋቸውን ቤተሰባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ሰው በሰጡን ቃል፣ “ ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ተሰርቷል፤ የሚቀሩ እባጮች ነበሩ አሁን እነርሱን ነው ቆርጠው ያወጡለት ” ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም የቀዶ ህክምና አድርጎ እንደነበር ያስታወሱት እኝሁ የአቶ ክርስቲያን ቤተሰብ፣ “እባጭ ነበረው፤ ያኔም ያን ነበር ቆርጠው ያወጡለት፤ ግን የሚቀር እባጭ ነበር ” ሲሉ የአሁኑን ቀዶ ህክምና ምክንያት አስረድተዋል፡፡

በእስር ቤት ቆይታቸው " ለአንጀት ድርቀት ህመም በመዳረጋቸው " ከዚህ ቀደም ቀዶ ጥገና ማድረጋቸውን ያስታወሱት እኝሁ አካል፣ ያኔ ሙሉ ለሙሉ ቀዶ ህክምናው ተደጎላቸው ቢሆን ኖሮ “ እዛው ተኝቶ ሊከታተል ስለማይችል ከፍተኛ ጉዳት ይደርስበት ስለነበር ጊዜያዊ ሰርጀሪ ነበር የተሰራለት ” ብለዋል።

“ የሰው ልጅ አይደለም ቀዶ ህክምና የማያክል ነገር ተሰርቶና ታሞ እስር ቤት ሆኖ እቤት ተኩኖም ያስቸግራል” ብለው፣ “ሰዎች፣ የሰባዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ሂደው ቢያዩአቸው፤ ጠያቂ ቤተሰብ የሚደርስበትን ግፍም ቢመለከቱ” ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ሰሞኑን በመቅረዝ ሆስፒታል ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ከተደረገላቸው በኋላ ተቆርጦ የወጣው እባጭ ለካንስር ቅድመ ምርመራ እንደተላከና ውጤቱ ለቀጣይ ሳምንት እየተጠበቀ እንደሆነ ተመልክቷል፡፡

የፍርድ ቤት ሂደቱ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲጠይቃቸውም፣ “ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከመጋረጃ ጀርባ አቶ ክርስቲያን ላይ ምስክር አሰማለሁ ብሎ ነበር አቃቢ ህግ በዚህ መሰረት ከመጋረጃ ጀርባ ያሰሙ በሚል ተፈቅዶላቸዋል ” ሲሉ መልሰዋል።

የምስክር ቃል ከመጋረጃ በስተጀርባ እንዲሰማም ለጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ/ም ቀጠሮ መሰጠቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ:- ቲክቫህ ኢትዮጵያ

የአማራና ኦሮሚያ አጎራባች ወረዳዎች በዓባይ ወንዝ በጋራ የሚያከብሩት የሩፋኤል በዓል ጳጉሜን 3 ዓመታዊው የሩፋኤል በዓል የሚከበርበት ቀን ነውበዕብራይስጥ 'ሩፋ' ጤና፣ ፈውስ፣ መድኃኒት፣ ቸ...
08/09/2025

የአማራና ኦሮሚያ አጎራባች ወረዳዎች በዓባይ ወንዝ በጋራ የሚያከብሩት የሩፋኤል በዓል

ጳጉሜን 3 ዓመታዊው የሩፋኤል በዓል የሚከበርበት ቀን ነው

በዕብራይስጥ 'ሩፋ' ጤና፣ ፈውስ፣ መድኃኒት፣ ቸር፣ መሐሪ ማለት ሲሆን÷ 'ኤል' ደግሞ አምላክ ወይም እግዚአብሔር የሚል ትርጉም አለው። በዚህ መሰረት ሩፋኤል 'እግዚአብሔር ፈዋሽ ነው' ማለት ነው።

ጳጉሜን 3 ቀን የሚከበረው ዓመታዊው የሩፋኤል በዓል መነሻ ሐይማኖት ነው፡፡ በሐይማኖቱ አስተምህሮ መሰረት የሩፋኤል ቀን የሰማይ መስኮቶች ይከፈታሉ።

በዕለቱ የሚዘንብ ዝናብና የሚፈሱ ወንዞች ሁሉ የተቀደሱ እንደሆኑ ይታመናል።

በዚህ ምክንያት ሕዝቡ በተለይም ሕጻናትና ታዳጊዎች ዝናብ ሲዘንብ ልብሳቸውን በማውለቅ 'ሩፋኤል አሳድገን፣ ሩፋኤል ከሽንብራው ማሳ አስገባን' እያሉ በሚወርደው ዝናብ እየተጠመቁ በጎዳናዎች ይቦርቃሉ።

በወንዞች አካባቢ በተለይም በዓባይ ወንዝ ሩፋኤል ከመንጻትና ፈውስ ጋር ተያይዞ ለረጅም ዓመታት ሲከበር ቆይቷል።

በዓባይ ወንዝ ላይ የሚከበረው በዓል ማዶና ማዶ በክረምቱ ወንዝ ሙላት ምክንያት ተራርቆ የነበረው ሕዝብ የሚገናኝበት ጊዜ በመሆኑ ልዩ ማህበራዊ ፋይዳ አለው። ሩፋኤል ዋና የመገናኛና የአንድነት በዓል እንደሆነም ይነገራል፡፡

ለአብነትም ሸዋና ጎጃም፣ ወሎና ጎጃምን፣ ጎንደርና ጎጃምን በሚያገናኙ የዓባይ ድልድይች ሥር ወይም መገናኛ ሰርጦች አካባቢ ለየት ባለ ሁኔታ በዓሉ ይከበራል፡፡

በተመሳሳይ ከዋናው የዓባይ ድልድይ ሥር የአማራና ኦሮሚያ አጎራባች ወረዳዎች የሩፋኤል በዓል በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ይከበራል።

በቅርቡ ደግሞ በባሕር ዳር ከተማ ከአዲሱ የዓባይ ድልድይ ሥር የሩፋኤል በዓል መከበር መጀመሩንም የቪዚት አማራ መረጃ ያመላክታል፡፡

በዓባይ ወንዝ ላይ የሚከበረው ሩፋኤል በወንዝ ሙላት ተለያይተው የነበሩ የሚገናኙበት እና በታላቁ ወንዝ ዳር ተቀምጠው ዓመቱን እንዴት እንዳሳለፉ የሚወያዩበት ነው፡፡

ከዚህ ባለፈም አዲሱን ዓመት በተስፋ ለመጀመር በአንድነትና በፍቅር በዓባይ ወንዝ የሚጠመቁበትና የሚታጠቡበት በዓል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

Via ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን

192 ጋዜጠኞች በእስራኤል መገደላቸውን ሲፒጄ ይፋ አደረገከነዚህም ውስጥ ቢያንስ 178ቱ ጋዜጠኞች ፍልስጤማውያን ናቸውእስራኤል በጋዛ ላይ የተቀናጀ ጥቃት ከጀመረች መስከረም 26/2016 ዓ.ም...
23/08/2025

192 ጋዜጠኞች በእስራኤል መገደላቸውን ሲፒጄ ይፋ አደረገ

ከነዚህም ውስጥ ቢያንስ 178ቱ ጋዜጠኞች ፍልስጤማውያን ናቸው

እስራኤል በጋዛ ላይ የተቀናጀ ጥቃት ከጀመረች መስከረም 26/2016 ዓ.ም. ጀምሮ 192 ጋዜጠኞች መገደላቸውን የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪው ሲፒጄ አስታውቋል።

እንደ ተቋሙ ከሆነ ቢያንስ 178 ፍልስጤማውያን ጋዜጠኞች በእስራኤል ተገድለዋል።

እስራኤል ሆን ብላ አነጣጥራ በፈጸመችው ጥቃት በቅርቡ ከተገደሉት መካከል ታዋቂው የአልጀዚራ ዘጋቢ አናስ አል ሻሪፍን ጨምሮ አምስት የአልጀዚራ ጋዜጠኞች ይገኙበታል።

ጋዜጠኞቹ በጋዛ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው አል ሺፋ ሆስፒታል ነው ነሐሴ 4/2017 ዓ.ም የተገደሉት።
የአልጀዚራዎቹ ዘጋቢዎች ሻሪፍ እና መሐመድ ቄሬህ እንዲሁም የካሜራ ባለሙያዎቹ ኢብራሂም ዛሄር፣ መሐመድ ኑፋል እና ሙአሚን አሊዋ ጥቃት በተፈጸመባቸው ወቅት በሆስፒታሉ ዋነኛ በር ለጋዜጠኞች በተዘጋጀ ድንኳን ውስጥ እንደነበሩ የመገናኛ ብዙኃኑ አስታውቋል።

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሰዎች አፈና፣ ለገንዘብ ተብሎ የሚፈጸሙ እገታዎች፣ ዝርፊያ እና ምክንያቱ ያልታወቀ የሰዎች ደብዛ የመጥፋት እና መሰወር ሁኔታዎች በፍርሃት ውስጥ እንዲገቡ እንዳደ...
23/08/2025

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሰዎች አፈና፣ ለገንዘብ ተብሎ የሚፈጸሙ እገታዎች፣ ዝርፊያ እና ምክንያቱ ያልታወቀ የሰዎች ደብዛ የመጥፋት እና መሰወር ሁኔታዎች በፍርሃት ውስጥ እንዲገቡ እንዳደረጋቸው ነዋሪዎች ገለጹ።

በቅርቡ አቶ ፊልሞን ገብረህይወት የተባለ የካሜራ ባለሙያ እና የፊላሪ ፕሮዳክሽን ባለቤት ከጠፋ ከሳምንት በላይ የሆናቸው ሲሆን እስከአሁን የት እንደደረሱ አልታወቀም።

የአቶ ፊልሞን ባለቤት ወይዘሮ ገነት እዝራ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት ለመጨረሻ ጊዜ የባለቤታቸውን ድምጽ የሰሙት እሑድ ነሐሴ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ በባጃጅ ወደ ቤቱ እየገባ በነበረበት ሰዓት ነው። “ወደ ቤት እየመጣሁ ነው አለኝ። እንደገና ደወልኩለት ነገር ግን አላነሳም በኋላ ላይ ስልኩ ጠፋ” ሲሉ ስለ ሁኔታው አስረድተዋል።

ወ/ሮ ገነት በማግስቱ ጠዋት ጉዳዩን ለፖሊስ ቢያሳውቁም ምንም አይነት መረጃ እንዳላገኙ ይናገራሉ። አለመረጋጋት በቤተሰቡ ላይ በተለይም በሁለት ትንንሽ ልጆቻቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን አክለዋል። “ከአባታቸው ጋር ይህን ያህል ጊዜ ድረስ ተለያይተው አያውቁም። ለነሱ ሁሉ ነገራቸው ነው። አሁንም ዕለት ዕለት እየጠበቁት ነው። በጣም አስቸጋሪ ነው” ብለዋል።

መሰል ክስተቶች በመቐለ ከተማ ከቅርብ ወራት ወዲህ እየተባባሱ ስለመምጣታቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ። የ30 አመቱ ግርማይ ሃፍቴ “ከጦርነቱ በኋላ በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ትግራይን ለማስተዳደር ኃላፊነት የተጣለባቸው ሃይሎች ሰላም እና ጸጥታን ከማረጋገጥ ይልቅ በውስጥ የስልጣን ሽኩቻ ውስጥ ገብተዋል” በማለት ሁኔታውን “ፍፁም ውድቀት” ሲሉ ገልጸውታል።

አያይዘውም የወጣቶች ስራ አጥነት፣ ያልተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች፣ የጸጥታ ሃይሎችን ለፖለቲካዊ ዓላማ ማስፈጸሚያነት መጠቀም እና የህግ የበላይነት አለመረጋገጡ ለጸጥታ ችግሮቹ መንሰኤ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በከተማዋ ለብዙሀኑ ነዋሪዎች ፍርሃት የዕለት ተዕለት ሕይወታቸው አካል ሆኗል። ለአብነትም የ34 ዓመቷ ሳምራዊት ታደሰ ልጇ ከቤት ውጭ እንድትወጣ ለመፍቀድ ፍርሃት እንደሚያድርባት ትናገራለች።

“ስለ አፈና እና ለገንዘብ ተብሎ ስለሚፈጸሙ እገታዎች በወሬ እንሰማለን። አንዳንዶቹ የተጋነኑ ቢሆኑ እንኳ ፍርሃቱ እውነት ነው። ልጄ ከቤት በወጣችበት ጊዜ ሁሉ በሰላም ትመለስ ይሆን ብዬ እጨነቃለሁ፤ ይሄ ደግሞ መኖር አይደለም” ስትል ተናግራለች።

ከሰሞኑ በሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ እንዳባጉና ከተማ የሰባት አመት ልጅ ከተገደለ በኋላ የፍርሃት ስሜቱ ተባብሷል።

ህጻኑ በመጀመሪያ ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ ለእናቱ ለወ/ሮ ዮርዳኖስ ጋይም ልጇ ህይወቱን ሲማጸን የሚያሳይ ቪዲዮ እንዲደርሳት ተደርጎ የማስለቀቂያ ለመክፈል ተገድዳለች።

አጋቾቹ ሁለት ሚሊዮን ብር ጠይቀው ወደ 1.7 ሚሊዮን ብር ቢልኩም የሰባት አመት ልጃቸው ተገድሎ እና አስከሬኑ ድልድይ ውስጥ ተጥሎ መገኘቱን ቢቢሲ ትግረኛ ዘግቧል።

በተመሳሳይ በከተማዋ የሚገኙ የንግድ መደብር ባለቤቶችም ኢኮኖሚያዊ ውድቀት እየገጠማቸው እንዳለ ይናገራሉ።

በመቐለ ከተማ ሱቅ በመሸጥ የሚተዳደሩት የ28 አመቱ ክብሮም አረጋዊ በከተማዋ የተንሰራፋው ዘረፋ እና ስርቆት ደንበኞቻቸውን እያሸሸ እንደሆነ ይገልጻሉ።

“ሰዎች ስለሚፈሩ ሱቆች በጣም ቀደም ብለው ይዘጋሉ። ከጦርነቱ ተርፈን ሳለ፣ የደህንነት ችግር ቀጣይነት ባለው ፍርሃት ውስጥ እንድንኖር ምክንያት መሆን አልነበረበትም ” ብለዋል።

የመቐለ ዞን ፖሊስ በበኩሉ ዘረፋ፣ ጥቃት እና ግድያን ጨምሮ በከተማዋ ወንጀሎች መበራከታቸውን አረጋግጧል።

የዞኑ የህዝብ ግንኙነትና ክትትል ሃላፊ የሆኑት ኮማንደር አበበ ገብሬ በበኩላቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጠፉ ሰዎች ሪፖርቶች ነዋሪዎችን ማሳሳባቸውን ገልጸው ነገር ግን በጊዜ ሂደት በርካታ ጉዳዮች እልባት አግኝተዋል ብለዋል።

ፖሊስ በቅርቡ አምስት ሰዎች መጥፋታቸውን ገልጾ 3 ሰዎች በእስር ላይ እንዳሉ፣ አንዱ ወደ አዲስ አበባ መጓዙን፣ ሌላኛው ደግሞ ወደ አፋር ክልል መዛወሩን አስታውቋል።

አንድ የ16 አመት አዳጊ ደግሞ ማይፀብሪ ላይ የታገተ በማስመሰል ከወላጆቹ 500,000 ብር የማስለቀቂያ ሲጠይቅ መገኘቱን አመልክቷል።

ሆኖም የአቶ የፊልሞን ገብረህይወት ጉዳይ እስከአሁን ድረስ እልባት አለማግኘቱን ኮማንደር አበበ አረጋግጠዋል።

“ፖሊስ ጉዳዩን በንቃት እየተከታተለ ነው” በማለት ነዋሪዎች ከህግ አስከባሪዎች ጋር እንዲተባበሩ እና አጠራጣሪ ድርጊቶችን ሲመለከቱም ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ለብዙዎች መሰል ከጸጥታ አካላት የሚነገሩ ቃሎች እና የዋስትና ንግግሮች ለአጭር ጊዜ የሚቆዩ ተደርገው ነው የሚወሰዱት።

የአቶ ፊልሞን መጥፋት ቤተሰቡን ጭንቀት ውስጥ ከመክተቱም በላይ በከተማዋ ያንዣበበውን የደህንነት ስጋት የፍርሃት ስሜት በጉልህ ያመላክታል ተብሏል።

አንድ የማህበረሰብ አባል”ነዋሪዎች ከተስፋ በላይ ይፈልጋሉ፤ ፀጥታና እና መረጋጋትን ለመመለስ ተጨባጭ እርምጃ መወሰድ አለበት” ሲሉ ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል።

አኃዛዊ መረጃዎችም የቀውሱን ጥልቀት ያሳያሉ።

ለአብነትም የመቀሌ ከተማ ፖሊስን ጠቅሶ የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ እንደዘገበው ከነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም አንስቶ እስከ ሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ 12 ሴቶች ተገድለዋል፣ 80 ሴቶች ተደፍረዋል፣ 10 ሰዎች ሲታገቱ 178 በሚሆኑት ላይ ደግሞ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል።

አዲስ ስታንዳርድ በሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ባወጣው የትንታኔ ዘገባውም በፕሪቶሪያ ስምምነት የሁለት ዓመቱ ጦርነት ቢያበቃም ትግራይ አሁንም ከፍርሃት: ለገንዘብ ተብለው ከሚደረጉ የእገታ ተግባራት እና የክልሉን አዝጋሚ የሆነ የማገገም ሂደትን አደጋ ላይ ከሚጥሉ ወንጀሎች ጋር እየታገለች እንደምትገኝ አመልክቷል።

የወንጀል ድርጊቶቹ የህዝቡን ሰላም ከማደፍረስ አልፎ ህዝቡ በጸጥታ ተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ እንዲሸረሽር አድርጓል።

የፊልሞን ጉዳይ እልባት ባላገኘበት በአሁኑ ወቅትም የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች የሰላም ተስፋቸው በደህንነት ስጋት ተሸፍኖባቸው ቤተሰብ እና የንግድ ድርጅቶችም በፍርሀት እንዲሁም እርግጠኛ ባልሆነ ሁኔታ እና ውዥንብር ውስጥ ሆነው ህይወትን ለመግፋት እየታገሉ ናቸው።

ዘገባው የአዲስ ስታንዳርድ ነው

በአማራ ክልል በወሊድ ምክንያት ከሁለት መቶ በላይ እናቶች ህይወት አለፈየክልሉ ጤና ቢሮ እንደገለፀው በአማራ ክልል 274 እናቶች በወሊድ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል፡፡የእናቶችን ሞት መንስኤ...
23/08/2025

በአማራ ክልል በወሊድ ምክንያት ከሁለት መቶ በላይ እናቶች ህይወት አለፈ

የክልሉ ጤና ቢሮ እንደገለፀው በአማራ ክልል 274 እናቶች በወሊድ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል፡፡

የእናቶችን ሞት መንስኤ በጥናት ለማረጋገጥ ተሞክሯል ሲሉ የክልሉ ጤና ቢሮ የእናቶች ወጣቶች እና ህፃናት ዳይሬክተር መልሰዉ ጫንያለው ተናግረዋል፡፡

ከ75 በመቶ በላይ የሚሆኑት እናቶች በወሊድ ጊዜ በሚያጋጥም የደም መፍሰስ እንደሚሞቱ ታውቋል ብለዋል፡፡

በተለይ በክልሉ የፀጥታ ችግር ባለባቸዉ አካባቢዎች የጤና ተቋማት መዘጋት የአደጋው አባባሽ ምክንያት ነው ብለዋል፡፡

አምቡላንሶች በተፈለገዉ ልክ ተንቀሳቅሰዉ እንዳይሰሩ እክል እንደተፈጠረም አቶ መልሰዉ አንስተዋል፡፡

ጭምብል ባደረጉ ሰዎች  ታፍነው የነበሩት ጋዜጠኞች ተለቀቁ የሪፖርተር ጋዜጣ ባልደረባ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ ጭምብል ባደረጉ ሰዎች  ታፍኖ ከነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ደብዛው ጠፍቶ የነበ...
23/08/2025

ጭምብል ባደረጉ ሰዎች ታፍነው የነበሩት ጋዜጠኞች ተለቀቁ

የሪፖርተር ጋዜጣ ባልደረባ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ ጭምብል ባደረጉ ሰዎች ታፍኖ ከነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ደብዛው ጠፍቶ የነበረ ሲሆን የታፈነበት ዕለት ነሐሴ 7 ነበር። ትናንት ዓርብ ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓም ምሽት ከሶስት ሰዓት በኋላ ተለቋል።

በአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 FM ራዲዮ የቅዳሜ ገበያ ፕሮግራም አዘጋጅ ጋዜጠኛ አብዱል ሰመድ መሀመድም በተመሳሳይ መለቀቁ ታውቋል።

ጋዜጠኛ ዮናስ ከታገተበት የተለቀቀው 10ኛ ቀኑ ላይ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ አብዱል ሰመድ ደግሞ ከ12 የእገታ ቀናት በኋላ ነው።

ጋዜጠኞቹ በማን ታፍነው እንደተወሰዱ፣ የት አካባቢ እንደቆዩም ሆነ አካላዊ ጉዳት ይድረስ አይድረስባቸው አልታወቀም።

በጋዜጠኞችም ሆነ በሌሎች ታዋቂ ሰዎች እገታ ጉዳይ መንግስት ያለው ነገር የለም።

የፕሬስ አባላት ላይ ማነጣጠር እና ማስፈራራት ተቀባይነት የለውም አሉ የአሜሪካ ሴናተሮች 17 የአሜሪካ ሴናተሮች ያሉበት ቡድን እስራኤል ጋዜጠኞች ጋዛ እንዲገቡና ጥበቃ እንዲደረግላቸው ጫና እ...
21/08/2025

የፕሬስ አባላት ላይ ማነጣጠር እና ማስፈራራት ተቀባይነት የለውም አሉ የአሜሪካ ሴናተሮች

17 የአሜሪካ ሴናተሮች ያሉበት ቡድን እስራኤል ጋዜጠኞች ጋዛ እንዲገቡና ጥበቃ እንዲደረግላቸው ጫና እንዲያደርጉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮን ተማጽነዋል።

"ዩናይትድ ስቴትስ የሚዲያ ድርጅቶችን ማገድ እና ሳንሱር ማድረግ ብሎም በፕሬስ አባላት ያነጣጠሩ ጥቃቶች ወይም ማስፈራራት ተቀባይነት የሌለው ነው እስራኤል ይህንኑ ድርጊቷ እንድታቆም ግልጽ ማድረግ አለባት" ሲሉ የዴሞክራቲክ ሴናተሮቹ በመግለጫቸው ተናግረዋል።

"የእስራኤል መንግስት በጋዛ ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞችን እንዲጠብቅ እና አለም አቀፍ ሚዲያዎች ወደ ግዛቱ እንዲገቡ እንዲፈቅድ ግፊት እንድታደርጉ እናሳስባለንም" ብለዋል። ባለፈው ሳምንት በተፈፀመው የእስራኤል ጥቃት ዘጋቢ አናስ አል ሻሪፍን ጨምሮ አራት የአልጀዚራ ጋዜጠኞችን እና ሁለት ሌሎች ጋዜጠኞችን መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን ይህም አለም አቀፍ ቅሬታን አስነስቷል።

የሴናተሮቹ ደብዳቤ ጥቃቱን ያወገዘ ሲሆን “ለዚህ ጥቃት ወታደራዊ ዓላማ መሆኑን አሳማኝ ማብራሪያ ባይኖርም፣ እስራኤል በጋዛ ያለውን የስቃይ መጠን ለዓለም ያሳዩ ጋዜጠኞችን ኢላማ አድርጋ መግደሏንና ይህም የዓለም አቀፍ ሕግን መጣስ መሆኑን በይፋ ማመን አለባት" ብለዋል። ከደብዳቤው ፈራሚዎቹ መካከል የማሳቹሴትስ ሴናተር ኤልዛቤት ዋረን፣ የቨርጂኒያ ሴናተር ቲም ኬይን እና ሌሎች 13 የዲሞክራቲክ ሴናተሮች እንዲሁም የቬርሞንት ሴናተር በርኒ ሳንደርስ ይገኙበታል ተብሏል።

17.5 በመቶ እንዲሆን የቀረበው የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ባለበት እንዲቀጥል ተወሰነየገንዘብ ሚኒስቴር በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ማሻሻያው የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ ይ...
19/08/2025

17.5 በመቶ እንዲሆን የቀረበው የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ባለበት እንዲቀጥል ተወሰነ

የገንዘብ ሚኒስቴር በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ማሻሻያው የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ ይቀጥላል ብሏል

ነባሩ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ከምጣኔ ውጭ ሌሎች ማሻሻያዎችን በማካተት ከ30 ዓመታት በኋላ ተሻሽሎ በ2017 በጀት አመት ስራ ላይ መዋሉን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከነበረው ከ12 በመቶ በላይ ድርሻ በየዓመቱ በተከታታይ እየቀነሰ ከ7 በመቶ በታች መድረሱን ጠቅሶ፥ ከዚህ ጠቅላላ ቅናሽ 44 በመቶው የተጨማሪ እሴት ታክስ ድርሻ እንደሆነ አመልክቷል፡፡

የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ህጉ አሁን ካለው የኢኮኖሚ ሁኔታ የቀጣይ ዓመታት ለውጦች ጋር እንዲጣጣም በማድረግ በመካከለኛ ዘመን የገቢ ስትራቴጂው መሰረት ተሻሽሎ በ2017 በጀት ዓመት ስራ ላይ እንዲውል ተደርጓል ብሏል ገንዘብ ሚኒስቴር፡፡

ጋዜጠኞቹ ታፍነው መወሰዳቸው ተዘገበየታፈኑት ጋዜጠኞች ዮናስ አማረ እና አብዱልሰመድ መሐመድ ናቸውየሪፖርተር ጋዜጣ ባልደረባ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ ከነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ሥራ ባለመግ...
17/08/2025

ጋዜጠኞቹ ታፍነው መወሰዳቸው ተዘገበ

የታፈኑት ጋዜጠኞች ዮናስ አማረ እና አብዱልሰመድ መሐመድ ናቸው

የሪፖርተር ጋዜጣ ባልደረባ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ ከነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ሥራ ባለመግባቱ በእጅ ስልኩ ላይ ሲደወልለትም ሆነ ከቤተሰቦቹ ለማጣራት ሲሞከር ማግኘት እንዳልተቻለ ተቋሙ ይፋ አድርጓል።

እንደ ሪፖርተር ዘገባ ጋዜጠኛው በሥራ ላይ እያለ የገባበት በመጥፋቱ የሥራ ባልደረቦቹም ሆኑ የሚቀርቡት ጓደኞቹ በእጅ ስልኩ ላይ ቢደውሉም ማግኘት አልተቻለም።

ሪፖርተር በዘገባው "ጋዜጠኛ ዮናስ በሚኖርበት በሸገር ከተማ ኮዬ ፌጬ ኮንዶሚኒዬም በመሄድ በተደረገ ማጣራት፣ ጋዜጠኛው ረቡዕ ምሽት ፊታቸውን በጭምብል በሸፈኑ ሰዎች መታፈኑን ጥበቃዎች ነገሩኝ" ብሏል።

የጥበቃ ሠራተኞቹ ተጨማሪ መረጃ መስጠት ባለመቻላቸው፣ ጋዜጠኛ ዮናስ፣ እነማን እንደወሰዱትና የት እንደተወሰደ ማወቅ አልተቻለም ሲል አስነብቧል።

በተመሳሳይ የቅዳሜ ገበያ የራዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅ ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ ከነሐሴ 5 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ ጀምሮ ደብዛው መጥፋቱን ሰለንዳ ኤቨንትስ እና ኮሚኒኬሽን በመግለጫ ይፋ አድርጓል።
አብዱል ሰመድ መሐመድ በአሐዱ ራዲዮ የሚተላለፈው የቅዳሜ ገበያ ፕሮግራም እና በዩቲዩብ ትረካ ስራዎቹ ይታወቃል።

የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ወደ 17.5 በመቶ እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ ቀረበበኢትዮጵያ ዝቅተኛ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔን ከ15% ወደ 17.5% እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ መቅረቡ ታ...
15/08/2025

የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ወደ 17.5 በመቶ እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ ቀረበ

በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔን ከ15% ወደ 17.5% እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ መቅረቡ ታወቀ

ይህንን የግብር ምጣኔ ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የግብር ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ሊያሳድግ እንደሚችል ተነግሯል።

የገንዘብ ሚኒስቴር እና የፊስካል ጥናት ተቋም (IFS) በጋራ ባዘጋጁት አዲስ ጥናት፣ የኢትዮጵያ የ15% የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ከብዙ የምስራቅ አፍሪካ እና የደቡብ ሰሃራ አፍሪካ ሀገራት ምጣኔዎች ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ ነው።

ለምሳሌ፣ የኬንያ የ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔ 16% ሲሆን፣ የሩዋንዳና የዩጋንዳ ደግሞ 18% ነው። የደቡብ ሰሃራ አፍሪካ ሀገራት አማካይ ምጣኔም 17.5% መሆኑን አመልክቷል።

ጥናቱ አክሎም፣ የ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔን ወደ 17.5% ማሳደግ ብቻ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በተጨማሪ 0.4% ነጥቦችን ከ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሊያስገኝ እንደሚችል ጠቁሟል።

ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ፣ ከዚህ በፊት ታክስ አልተሰበሰበባቸው የነበሩ እንደ ነዳጅ ያሉ ምርቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ መሰብሰብ መጀመሩ ትልቅ አዎንታዊ እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።

"የኢትዮጵያ ታክስ-ለ-ጂ.ዲ.ፒ ምጣኔ፡ የማነፃፀሪያ ግምት እና የአፈጻጸም ትንተና" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ጥናት፣ የኢትዮጵያ የታክስ-ለ-ጂ.ዲ.ፒ ምጣኔ በ2022/23 በጀት ዓመት ወደ 7.5% ዝቅ ማለቱን ያሳያል።

ይህ ቁጥር በ2014/15 ከነበረው ከፍተኛው 12.4% ጋር ሲነፃፀር 4.9 በመቶ ነጥብ ቅናሽ አሳይቷል። ለዚህ ከፍተኛ የገቢ ቅናሽ ዋና ዋና ምክንያቶችም ዉስጥ ​መዋቅራዊ ለውጦች ፣​የፖሊሲ ልዩነቶች እና ​ዝቅተኛ የታክስ ተገዢነት መሆናቸውን በዝርዝር አስቀምጧል። ዘገባው የካፒታል ነው።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News ዜና ዘ ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share