መረጃ ቲዩብ - Mereja Tube

መረጃ ቲዩብ - Mereja Tube ፈጣን ፣ ታአማኒነት ያላቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ወደ እናንተ እናደርሳለን።
ቤተሰባችን ይሁኑ
(2)

የኮሜድያን ማርቆስ (ቁራሌው) ልጅ ተመረቀችብዙዎቻችን ቁራሌው እያልን የምንጠራው ኮሜዲያን ማርቆስ ዛሬ ልጁን ከኒው ጀኔሬሽን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በድግሪ አስመርቋል።ጓደኛችን ማርቂ እንኳን ደስ ...
27/07/2025

የኮሜድያን ማርቆስ (ቁራሌው) ልጅ ተመረቀች

ብዙዎቻችን ቁራሌው እያልን የምንጠራው ኮሜዲያን ማርቆስ ዛሬ ልጁን ከኒው ጀኔሬሽን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በድግሪ አስመርቋል።

ጓደኛችን ማርቂ እንኳን ደስ አለህ
via ዋልተንጉስ ዘሸገር

27/07/2025

ባለ50ሚሊዬን ብር የሎተሪ እድለኛዋ ሰይፍዬ ላገኝህ እፈልጋለሁኝ የት ነው ያለህው?

ጋዛ በሮቿን ሙሉ በሙሉ ለሰበአዊ እርዳታ ከፍታ ምግብ ማስገባት ጀመረችዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ባሳደረው ጫና ምክንያት አሁን ጋዛ በሮቾአን ከፋፍታ ለህዝቦቿ የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶችን የያዙ ...
27/07/2025

ጋዛ በሮቿን ሙሉ በሙሉ ለሰበአዊ እርዳታ ከፍታ ምግብ ማስገባት ጀመረች

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ባሳደረው ጫና ምክንያት አሁን ጋዛ በሮቾአን ከፋፍታ ለህዝቦቿ የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶችን የያዙ መኪኖች ወደግዛቷ በመግባት ላይ ናቸው:በሞት አፋፍ ላይ ላሉ ዜጎቿ የሰበአዊ እርዳታን ለማደል።

የዓለማችን አውዳሚው ጦርነት በጋዛ ያሉ ንፁሃንን ከቤት ንብረታቸው ከማፈናቀል በተጨማሪ ብዙሃኑን ለከፋ ርሃብ
እረሃብና ስደት ዳርጎአቸዋል።

የነዳጅ ዋጋ ባለበት ቀጥሎአልከሀምሌ 20/2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ሥራ ላይ የሚውል የነሐሴ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ ሆነ  የነሐሴ ወር የነዳጅ ምርቶች የችር...
27/07/2025

የነዳጅ ዋጋ ባለበት ቀጥሎአል

ከሀምሌ 20/2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ሥራ ላይ የሚውል የነሐሴ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ ሆነ

የነሐሴ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሀምሌ 20/2017 ዓ.ም ምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የቤንዚል፣ የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲንና የአውሮፕላን ነዳጅ ምርቶች የመሽጫ ዋጋ በነበረበት የሚቀጥል ሲሆን ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 127.22 ብር እና ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 124.55 ብር ብቻ እንዲሸጥ በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎችም በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጥብቅ አሳስቧል፡፡

27/07/2025

ልብ የሚነካው የእናት ዘፈን

652 ህጻናት በናይጄሪያ በምግብ እጥረት ህይወታቸው አለፈበናይጄሪያ ሰሜናዊ ክፍል በምትገኘው ካትሲና  ግዛት፣ ባለፉት ስድስት ወራት ቢያንስ 652 ህጻናት በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሳቢያ መሞ...
27/07/2025

652 ህጻናት በናይጄሪያ በምግብ እጥረት ህይወታቸው አለፈ

በናይጄሪያ ሰሜናዊ ክፍል በምትገኘው ካትሲና ግዛት፣ ባለፉት ስድስት ወራት ቢያንስ 652 ህጻናት በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሳቢያ መሞታቸውን ድንበር የለሽ የሃኪሞች ድርጅት (ኤምኤስኤፍ) ገለጸ፡፡

የፈረንሳዩ የበጎ አድራጎት ድርጅት ባለፈው አርብ ባወጣው መግለጫ፤ የህጻናቱ ሞት የተከሰተው ከዓለም አቀፍ ለጋሾች የገንዘብ ድጋፍ በመቀነሱና በካትሲና ግዛት ውስጥ ባለው የአመጽና የጸጥታ ችግር ምክንያት መሆኑን አስታውቋል፡፡

መንግስታዊ ያልሆነው ድርጅት እንዳለው፤ ባለፈው ሰኔ ወር መጨረሻ ላይ በሆስፒታል ውስጥ ገብተው የታከሙትን 10ሺ ህጻናት ጨምሮ ወደ 70ሺ የሚጠጉ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ያለባቸው ህጻናት ካትሲና ግዛት ውስጥ ከሚገኙት የኤምኤስኤፍ ቡድኖች የህክምና አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

ይሁን እንጂ በሰሜን ናይጄሪያ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን የመከላከልና ህክምና ፍላጎት እጅግ በጣም ብዙ በመሆኑ አፋጣኝ የድጋፍ ማሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ድርጅቱ አሳስቧል።

ሮይተርስ እንደዘገበው፤ በናይጄሪያ በሰሜን ምስራቅ በተከሰተው አመፅ ለአንደ ነጥብ 3 ሚሊዮን ሰዎች የምግብና የተመጣጠነ ምግብ እርዳታ ለማቆም እንደሚገደድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ኤጀንሲ አስታወቋል፡፡

አድማስ ዩኒቨርስቲ ከ6,ሺህ በላይ ተማሪዎች አስመረቀ  👉 ከሰባ በመቶ በላይ ሴቶች ናቸው አድማስ ዩኒቨርስቲ ላለፋት 26 ዓመታት በመደበኛና በርቀት ትምህርት፣ በድግሪ፣ በዲፕሎማና በሰርተፊኬ...
27/07/2025

አድማስ ዩኒቨርስቲ ከ6,ሺህ በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

👉 ከሰባ በመቶ በላይ ሴቶች ናቸው

አድማስ ዩኒቨርስቲ ላለፋት 26 ዓመታት በመደበኛና በርቀት ትምህርት፣ በድግሪ፣ በዲፕሎማና በሰርተፊኬት በርካታ ተማሪዎችን አስመርቆ፣ በሀገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ የሚፈለገውን የተማረ የሰው ሀይል አሰልጥኖ በማቅረብ ረገድ የበኩሉን ድርሻ እንዳበረከተ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሞላ ፀጋይ የገለፁ ሲሆን በዛሬው ዕለት ከ6,000 በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል ከእነዚህ ውስጥ ከ71 ፐርሰንቱ በላይ ሴቶች መሆናቸውም ተነግሯል፡፡

ዶ/ር ሞላ አክለውም ዩኒቨርስቲው ከዚህ በፊት የርቀት ትምህርት በመንግስትም ሆነ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዳይሰጥ ለሶስት ዓመታት ከተከለከለ በኃላ እንደገና ተፈትሾ፣ ጥራታቸው ተረጋግጦ በርቀት ትምህርት እንዲያሰለጥኑ ከተፈቀደላቸው ግንባር ቀደም ተቋማት አድማስ አንዱ ነው ብልዋል፡፡

በዚህ ዓመትም የአዲስ አበባ የሥራና ክህሎት ቢሮ በዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም ነበራቸው ካላቸው 13 ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ዩኒቨርሲቲውን በአንደኛ ደረጃ አስቀምጦታል፡፡

ዩኒቨርሲቲያችን፣ ከመደበኛው የመማር _ ማስተማር _ ጎን _ ለጎን፣ _ አጫጭር ስልጠናዎችና የማማከር አገልግሎቶች በመስጠት፣ ሀገር አቀፍና አለም አቀፍ ጥናትና ምርምሮች በማካሄድ ውጤቱን ለህብረተሰቡ በማሳወቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን ሀገር አቀፍ የተማሪዎች የጥናት እና ምርምር ሲምፓዚየምን እስከ አሁን ለሰባተኛ ጊዜ እንዳካሄደ ተገልፆአል። አድማስ ዩኒቨርስቲ ከሃገር ውጭም በሶማሊላንድና በፑትላንድም ዩኒቨርስቲ ከፍቶ በማስተማር ላይ ይገኛል።

የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫን በናይጄሪያ  አሸናፊነት ተጠናቀቀበሞሮኮ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የሰነበተው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ሌሊት ሰባት ሰአት አካባቢ ተጠናቋል። ሞሮኮዎች በቺዝላን ቼባክና ፣ በሳ...
27/07/2025

የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫን በናይጄሪያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

በሞሮኮ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የሰነበተው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ሌሊት ሰባት ሰአት አካባቢ ተጠናቋል።

ሞሮኮዎች በቺዝላን ቼባክና ፣ በሳና ምሶዴ ሁለት ግቦች 2 ለ 0 ሲመሩ ቆይተው በስተመጨረሻ 3 ለ 2 ተሸንፈዋል።

የናይጄሪያን ሶስት ግቦች ኤስቴር ኦኮሮንኮ ፣ ፎላሻድና ጄኒፈር ኢቼጊኒ አስቆጥረዋል።

ሞሮኮ ለሁለት ተከታታይ ግዜያት ለአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ደርሳ ስትሸነፍ ናይጄሪያ ለ10ኛ ግዜ ዋንጫውን አንስታለች።

Via_አራዳ ኤፍ ኤም

የሀዋሳ የቀድሞው ከንቲባ ስለታቸውን አስገቡ ምስክርነትም ሰጡ"ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አውጣኝ አልኩት ጸሎቴን ሰምቶ አወጣኝ"......"የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ምስክርነት !!!***የሐዋሳ...
27/07/2025

የሀዋሳ የቀድሞው ከንቲባ ስለታቸውን አስገቡ ምስክርነትም ሰጡ

"ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አውጣኝ አልኩት ጸሎቴን ሰምቶ አወጣኝ"......"የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ምስክርነት !!!
***
የሐዋሳ ከተማ የቀድሞ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ በሐሰት በተከሰሱበት የክስ መዝገብ 13 ዓመት ተፈርዶባቸው ወደ ወህኒ ሲወረወሩ በእስር ቤት ሆነው ለቅዱስ ገብርኤል ጸሎት ልመናንን አቀረቡ።

"በአዉደ ምህረትህ ቆሜ ስለክብርህ መስከርያለሁና ለቂርቆስና እየሉጣ የደረስክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አንተ ድረስልኝ ! የኔ እዉነት ተቀብሮ እንዳይቀር እርዳኝ" ሲል ተለማመኑት።

እነሆ መላእከ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል በግፍ እና በበደል ለተገፉት ፈጥኖ መድረስ ባህሪው ነው እና ሰኔ 12 የዓመቱ ሚካኤል ቀን የባህራንን የሞት ደብዳቤ የሻረ አምላክ ከተፈረደባቸው የ 13 ዓመት የሐሰት እስራት ፍርድ በይግባኝ ነጻ ተብለው በሠላም ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቀሉ።

እነሆ ድንቅ ታምር ያደረገላቸው እና ጸሎት ልመናቸውን የሰማውን ቅዱስ ገብርኤል በአውደ ምህረት ቆመው ትላንት አመስግነዋል። ስለታቸውንም 5000 ብር አስገብተዋል።

27/07/2025

ኑ ለእግዚያብሄር በጋራ ሆን በአንድነት እንዘምር !!

በ2025 የቶኪዮ የአለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ስም ዝርዝር  በወፍ በረር✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)📌44 አትሌቶች በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያ...
27/07/2025

በ2025 የቶኪዮ የአለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ስም ዝርዝር በወፍ በረር

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

📌44 አትሌቶች በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያን ወክለው ይሳተፋሉ

📌ጀግናዋ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በሁለት ውድድሮች ሀገሯን ትወክላለች

📌ቀደም ሲል ይፋ እንዳደረግነው ታምራት ቶላ ከቶኪዮው አለም ሻምፒዮና ውጪ ሆኗል

📌ከነገ(ሠኞ) ጀምሮ በሆቴል ተሰባስበው ልምምድ ይጀምራሉ

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ትናንት(ቅዳሜ)ባደረገው ስብስባ እ.ኤ.አ ከSeptember 13 አስከ 21/2025 በጃፓን ቶኪዮ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው 20ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ሀገራቸውን የሚወክሉ አትሌቶች ስም ዝርዝር እጃችን ገብቷል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ገና ይፋ ያላደረገውና እጃችን እንደገባው የቶኪዮ 2025 የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተሳታፊዎች ዝርዝር መረጃ መሠረት 27 ሴቶችና 17 ወንዶች በድምሩ 44 አትሌቶች መመረጣቸውን ማረጋገጥ ችለናል።

ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ቀደም ሲል በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና ሀገራቸውን ሊወክሉ፣100% ሊመረጡ ይችላሉ ብላ ያመነችባቸውን አትሌቶች በመስፈርቱና በባለሙያ ታግዛ ያቀረባች ሲሆን ምርጫዋም ከ95% በላይ እንደ ግምታችን የተሳካ ሆኖ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ኮሚቴ ከፍተኛ ጥንቃቄ በማድረግ በመስፈርቱ መሠረት ከመረጠ በኃላ በቃለ-ጉባኤ ተፈራርሞ ለስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ካቀረበ በኃላ ከምሽት 11:30 ጀምሮ ብረርቱ ውይይትና ክርክር ካደረገ በኃላ ውሳኔውን እንዳሳለፈ ነው የተሠማው።በተለይ አትሌት ጉዳፍ ካላት ወቅታዊ ብቃትና ሚኒማ አንፃር በሁለት ርቀት ትሩጥ?አትሩጥ?የሢለው ክርክር ያስነሳ ሲሆን ቀደም ሲል በቃለ-ጉባኤ ጭምር አንድ አትሌት በአንድ ርቀት ብቻ ነው የሚሮጠው ብለን ነበር በሚል የሃሳብ ልዩነቶች እንደነበሩ ከምንጮቻችን ሠምተናል።

እስከአሁን በተገኘውና በተረጋገጠው መረጃ መሠረት ጀግናዋ አትሌት ጉዲፍ ፀጋይ በሁለት ርቀቶች ማለትም የወቅቱ የ10ሺ ሻምፒዮን በመሆንዋ በግብዣ በ10ሺ እንዲሁም በ5ሺ እንድትሮጥ የተወሠነ ሲሆን በቀጣይ ከአትሌቷና ከአሠልጣኟ ጋር በሚደረግ ውይይት 5ሺ ቀርቶ በተጠባባቂነት በተያዘችበት በ1500 ሜትር ልትሳተፍ የምትችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል ተብሏል።

በመጨረሻም የመጨረሻ ምዝገባ (Final Conformation) ሲካሄድ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ት አትሌቶች ከተመረጡበትና ከሚወዳደሩት የውድድር ምድብ ተጨማሪ ሁለቴ እንዲሮጡ በተጠባባቂነት እንዲመዘገቡና ፌዴሬሽኑ በመጨረሻ ባለው የመወሠን ስልጣን ወይም እንደሚያመጡት ሜዳልያ አይነት በድጋሚ እንዲሮጡ ውሳኔ ላይ ደርሷል ስራ አስፈፃሚው፡-

በዚህም መሠረት
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ5000 ሜትር፣ አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በ1500 ሜትር እና አትሌት ቢኒያም መሀሪ በ10,000 ሜትር እሰከዛ በተጠባባቂነት እንዲያዙ ሆኗል።

ፌዴሬሽኑ ገና ይፋ ያላደረገውና እጃችን በገባው መረጃ መሠረት በተለያዩ ርቀቶች በወንድም በሴትም ሀገራቸውን የሚወክሉ አትሌቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መሆናቸው ተረጋግጧል፤

ከነገ ሠኞ ጀምሮ ወደ ሆቴል እንዲገቡና ልምምዳቸውን እንዲያደርጉም ተወስኗል፤እጃችን በገባው የዕጩ አትሌቶቾ ምርጫ መሠረት:

📌በሴቶች 5,000ሜትር

🏃‍♀,1.ጉዳፍ ፀጋይ ⏰ 14:04:41 በሚኒማ

🏃‍♀,1.ፍሬወይኒ ሀይሉ⏰ 14:19:33 በሚኒማ

🏃‍♀2.ብርቄ ሐዬሎም ⏰ 14:24:20 በሚኒማ

🏃‍♀3.ጫልቱ ዲዳ ⏰14:27:11 በሚኒማ
-------------------------------------------------
👉🏃‍♀4.(ተጠባባቂ) አለሽኝ ባወቀ ⏰ 14:27:33 በሚኒማ
-----------------------------------------------
📌በወንዶች 5,000ሜ

🏃‍♂1.ቢኒያም መሀሪ⏰ 12:45:93 በሚኒማ

🏃‍♂2.ኩማ ግርማ ⏰ 12:46:41 በሚኒማ

🏃‍♂3.ሐጎስ ገብረህይወት ⏰ 12:46:82 በሚኒማ
-----------------------------------------------
👉ተጠባባቂዎች
-------------------------------------------------
🏃‍♂4.መዝገቡ ስሜ ⏰ 12:49:80 በሚኒማ

👉 ቢኒያም መሀሪና ዮሚፍ ቀጄልቻ አነሱም አሠልጣኞቻቸውም እንዲቀያየሩ ማለትም ዮሚፍ በ5ሺ ቢኒያም መሀሪ በ10ሺ እንዲወዳደሩ ስለሚፈለግ የውድድር ርቀትና የቦታ ልውውጥ ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል።

📌በሴቶች 10,000ሜ

🏃‍♀ጉዳፍ ፀጋይ ⏰ 29:05:92 Wild Card(ቀጥታ ተጋባዥ)

🏃‍♀,1.መዲና ዒሣ ⏰ 29:25:00 በሚኒማ

🏃‍♀,2.ፎቴን ተስፈዬ⏰ 29:47:71 በሚኒማ

🏃‍♀3.ፅጌ ገብረሠላማ ⏰ 29:48:34 በሚኒማ
---------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
------------------------------------------------
🏃‍♀ 4.አይንአዲስ መብራቱ ⏰30:09:05 በሚኒማ
---------------------------------------------------------
📌በወንዶች 10,000ሜ

🏃‍♂1.ዬሚፍ ቀጄልቻ⏰ 26:31:01 በሚኒማ

🏃‍♂2.በሪሁ አረጋዊ ⏰26:31:13 በሚኒማ

🏃‍♂3.ሰለሞን ባረጋ ⏰26:34:93 በሚኒማ
-----------------------------------------
👉ተጠባባቂ
-------------------------------------------
🏃‍♂4.ቢንያም መሀሪ ⏰26:37:93 በሚኒማ
----------------------------------------------
ቢሆኑም ቢኒያም መሀሪና ዮሚፍ ቀጄልቻ አነሱም አሠልጣኞቻቸውም እንዲቀያየሩ ዮሚፍ በ5ሺ ቢኒያም በ10ሺ እንዲወዳደሩ ስለሚፈለግ የቦታ ልውውጥ ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል።

📌በወንዶች ማራቶን

🏃‍♂1.አትሌት ደሬሳ ገለታ በሚኒማ

🏃‍♂2.አትሌት ታደሰ ታከለ በሚኒማ

🏃‍♂3.አትሌት ተስፋዬ ድሪባ በሚኒማ
-----------------------------------------
👉ተጠባባቂ
-------------------------------------------
አትሌት ጭምዴሳ ደበሌ በሚኒማ
---------------------------------------------
📌በሴቶች ማራቶን

🏃‍♀አማኔ በሪሶ በ Wild Card ቀጥታ ተሳታፊ

🏃‍♀1.አትሌት ትዕግስት አሰፋ በሚኒማ

🏃‍♀2.አትሌት ስቱሜ አሰፋ በሚኒማ

🏃‍♀3.አትሌት ያለምዘርፍ የኃላው በሚኒማ
---------------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
-----------------------------------------------------
🏃‍♀4.አትሌት ትዕግስት ከተማ በሚኒማ
-------------------------------------------------------
📌በ3ሺ መሠናክል ወንዶች በሚኒማ

🏃‍♂1.ሳሙኤል ፍሬው 8:05:61 በሚኒማ

🏃‍♂2. ለሜቻ ግርማ 8:07:01 በሚኒማ

🏃‍♂3.ጌትነት ዋለ 8:07:57 በሚኒማ
---------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
------------------------------------------------
🏃‍♂4.አብርሃም ስሜ 8:07:92 በሚኒማ
-----------------------------------------------
📌በ3ሺ መሠናክል ሴቶችች

🏃‍♀1.ሲምቦ አለማየሁ 8:59:90 በሚኒማ

🏃‍♂2. ሎሚ ሙለታ 9:06:07 በሚኒማ

🏃‍♂3. አለምነት ዋሌ 9:06:88 በሚኒማ
---------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
------------------------------------------------
🏃‍♂4. ወሠኔ አሠፋ WR በኮታ
-----------------------------------------------
📌በ1500 ወንዶች

🏃‍♂.1. አትሌት መለሠ ንብረት WR በኮታ

🏃‍♂.2. አትሌት ኤርሚያስ ግርማ WR በኮታ

🏃‍♂.3. አትሌት ወገኔ አዲሱ WR በኮታ
---------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
------------------------------------------------
🏃‍♂4. አትሌት አብዲሳ ፈይሳ WR በኮታ
-----------------------------------------------
📌በ1500 ሴቶች

🏃‍♀1.አትሌት ድርቤ ወልተጂ ⏰3:51:44 በሚኒሚ

🏃‍♂2. አትሌት ብርቄ ኃዬሎም⏰ 3:54:79 በሚኒሚ

🏃‍♂3..አትሌት ሳሮን በርሄ ⏰3:57:72 በሚኒሚ
---------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
------------------------------------------------
🏃‍♂4. አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ⏰4:00:69
-----------------------------------------------
📌በ800 ሴቶች
🏃‍♂1. አትሌት ፅጌ ዱጉማ⏰1:56:64 በሚኒማ

🏃‍♂2.አትሌት ንግስት ጌታቸው⏰1:57:01 በሚኒማ

🏃‍♀3.አትሌት ወርቅነሽ መሠለ⏰1:58:06 በሚኒማ
---------------------------------------------
👉ተጠባባቂ
------------------------------------------------
🏃‍♂4. አትሌት ሀብታም ዓለሙ⏰12:00:94 በሚኒሚ
-----------------------------------------------
📌በ800 ወንዶች

🏃‍♂1. አትሌት ዮሐንስ ተፈራ⏰1:44:49 በሚኒማ

🏃‍♂2. አትሌት ጄኔራል ብርሃኑ⏰1:44:49 በWR በኮታ

በመሆን ለጃፓን ቶኪዮ 2025 የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና መመረጣቸውን ማረጋገጥ ችለናል ፌዴሬሽኑም ዛሬ በይፋ ሊያሳውቅ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

ለቶኪዮው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 12 አሠልጣኞች  መመረጣቸው ታወቀ✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ትናንት(ቅዳሜ)ባደረገው ስብሰባ ከአ...
27/07/2025

ለቶኪዮው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 12 አሠልጣኞች መመረጣቸው ታወቀ

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ትናንት(ቅዳሜ)ባደረገው ስብሰባ ከአትሌቶች ምርጫ በተጨማሪ ለቶኪዮው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በየርቀቱ የሚያሰለጥኑ አሠልጣኞችን መርጦ መጨረሱን በእጃችን ከገባው መረጃ መረዳት ተችሏል።

እጃችን ከገባው የፌዴሬሽኑ የምረጫ መረጃ ከሆነ ሁለትና ከዚያ በላይ አትሌቶችን ያስመረጡ አሠልጣኞች በመስፈርቱ መሠረት ለሀገር ውክልና ጥሪ ተደርጎላቸዋል።

ለአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እጩ አሰልጣኞች ምርጫን በተመለከተ አትሌቶች በተጠባባቂነት ያስመረጡትንም ጭምር ያካተተ ሲሆን በዚህም መሠረት፡-

👉ለመካከለኛ ርቀት
አሠልጣኝ ህሉፍ ይህደጐ
9 አትሌቶችን በማስመረጥ

አሠልጣኝ ይረፉ ብርሃኑ
2 አትሌቶችንበማስመረጥ

አሠልጣኝ ጌታሁን ታደሰ
2 አትሌቶችን በማስመረጥ

👉ለ3ሺ ሜትር መሠናክል
አሠልጣኝ ተሾመ ከበደ
2 አትሌቶችን በማስመረጥ

አሠልጣኝ ፍቃዱ ግርማ
2 አትሌቶች በማስመረጥ

አሠልጣኝ ዶ/ር ንጉሴ ጌቻሞ
2 አትሌቶች በማስመረጥ

👉ለረጅም ርቀት
አሠልጣኝ ቴዎድሮስ ኃይሉ
3 አትሌቶችን በማስመረጥ

አሠልጣኝ ሁሴን ሽቦ
3 አትሌቶችን በማስመረጥ

አሠልጣኝ ቶሌራ ዲንቃ
2 አትሌቶችን በማስመረጥ

👉ለርምጃ 20 ኪ.ሜ ርቀት
አሠልጣኝ ሻ/ቃ ባዬ አሰፋ
2 አትሌቶች በማስመረጥ

👉በማራቶን ርቀት…
አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ 8 አትሌቶችን በማስመረጥ
አሠልጣኝ ሀጂ አዲሎ 3አትሌቶችን በማስመረጥ

ለቶኪዮው የአለም ሻምፒዮና የመጨረሻ ዕጩ ሆነው መመረጣቸውን ያገኘነው የተረጋገጠ መረጃ ይጠቁማል።

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መረጃ ቲዩብ - Mereja Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category