ZenaPlus

ZenaPlus News and in-depth analysis on Ethiopia, the Horn of Africa and World on YouTube.

በታጣቂዎች ታግተው የነበሩት የኢፌድሪ አየር ኃይል አዛዥ ወንድሞች ከወራት እገታ በኋላ ተለቀቁበኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታግተው ቆይተው የነበሩ የኢፌድሪ አየር ኃይል አዛዥ ጀነራል ይልማ መርዳሳ...
28/07/2024

በታጣቂዎች ታግተው የነበሩት የኢፌድሪ አየር ኃይል አዛዥ ወንድሞች ከወራት እገታ በኋላ ተለቀቁ

በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታግተው ቆይተው የነበሩ የኢፌድሪ አየር ኃይል አዛዥ ጀነራል ይልማ መርዳሳ ሁለት ወንድሞች ከወራት እገታ በኋላ ተለቀቁ።
ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለዜናፕላስ እንደተናገሩት፤ ታግተው ከነበሩት ሁለት የጀነራሉ ወንድሞች መካከል አንዱ ከአንድ ወር በፊት የተለቀቀ ሲሆን ሌላኛው ወንድም ደግሞ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ተለቋል።

ቦረና መርዳሳ ኛጳ እና በቀለ መርዳሳ ኛጳ ከሦስት ወራት በፊት ወሊሶ አካባቢ ከሚገኘው ከመኖሪያ መንደራቸው በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት ነበር የታገቱት።
ጀነራሉ የታገቱባቸውን ወንድሞቻቸውን ለማስቀለቀቅ ገንዘብ ከመክፈላቸው በተጨማሪ፤ የእገታውን ኦፕሬሽን የመሩ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ኮማንደር ቤተሰብ አባላትን አሳስረው እንደነበረ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ተናግረዋል።

እንድ ምንጮች ከሆነ ቦረና መርዳሳ የተባሉት ታላቅ ወንድም ባለፈው ሳምንት የተላቀቁ ሲሆን በቀለ መርዳሳ ግን ከስድስት ሳምንታት በፊት ነበር የለቀቁት። በአጠቃላይ ለሁለቱን ግለሰቦች ነጻ ለማውጣት 4 ሚሊየን ብር የማስለቀቂያ ገንዘብ መከፈሉ ተገልጿል።

በመንግሥት ኃይሎች ቢሾፍቱ ከተማ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ተይዘው የነረቡት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት ቤተሰቦች እንዲሁ ከእስር ተለቀዋል።
የእገታ ወንጀል በተበራከተበት የኦሮሚ ክልል ከተራው ዜጋ እስከ የመንግሥት ባለስልጣናት ቤተሰቦች የመታገት ዜና መስማት አዲስ ነገር አይደለም።

ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የነበሩት ኢ/ር ታከለ ኡማ ወላጅ አባት ከአምቦ ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ መንደር ታግተው በሽምግልና እና በክፍያ ተለቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ወላጆች በታጣቂዎች ታግተው እንደነበር የሚጠቁሙ ሪፖርቶች ሲወጡ ነበር።

የጀነራል ይልማ መርዳሳ ወንድሞች እገታ

የጀነራል ይልማ መርዳሳ ወንድሞች ቦረና መርዳሳ እና በቀለ መርዳሳ ከመታገታቸው በፊት ደቡብ ምዕራሽ ሸዋ አመያ ወረዳ በምትገኘው መኖሪያ መንደራቸው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመንግሥት ኃይል ሰፍሮ ነበር።

ከሦስት ወራት በፊት ሚያዚያ 6/2016 ዓ.ም. ንጋት ላይ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት የአየር ኃይል አዛዡ ወንድሞች በሚኖሩበት መንደር ላይ ድንገተኛ ጥቃት ከፈቱ።
ታጣቂዎቹ ትምህርት ቤት ላይ ሰፍሮ የነበረ የመንግሥት ጦር ላይ ድንገተኛ ጥቃት ከከፈቱ በኋላ የጀነራሉን ወንድሞች ለመያዝ ወደ መኖሪያ መንደራቸው አምርተው ነበር።

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እንደሚሉት በዕለቱ በአንድ መንደር ይኖሩ ከነበሩት ሦስት የጀነራሉ ወንድሞች መካከል አንዱ ከታጣቂዎች ጋር ተታኩሶ ተገድሏል።
ቦረና እና በቀለ የተባሉት የይልማ መርዳሳ ታላቅ ወንድሞች ግን እጅ ሰጥተው በታጣቂዎቹ ታግተው ተወስደው ነበር።

የሁለቱን ወንድማማቾች እገታ ተከትሎ ለኦሮሞ ነጻነት ግንባር ቅርበት ያላቸው የማሕበራዊ ገጾች ከታጋቾቹ ጋር የተገደረገ ቃለ መጠይቅ ቪዲዮ ማሕብራዊ ሚዲያ ላይ አውጥተዋል።

ሁለቱ ወንድማማቾች በቪዲዮ የሚናገሩት ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ስለ ቤተሰቡ እና እገታውን በተመለከተ ከተናገሩት ጋር ተመሳሳይ ነው።

ሁለቱ ግለሶበች ቪዲዮ ምን ይላሉ

ዘለገ ባለው የቪዲዮ ቃለ ምልልስ ቦረና መርዳሳ ልጆችን ጨምሮ አጠቃላይ 23 የቤተሰብ አባላት በአንድ አካካቢ ተሰባስበው እንደሚኖሩ ይናገራሉ።
“እኛ ገበሬዎች ነን። የማሕብረሰብ አካል ነን። ከመንግሥት ጋር ምንም አይነት ግንኑነት የለንም” ይላሉ።

ቦረና የመንግሥት ሠራዊት አባላት ለጀነራሉ ቤተሰቦች ጥበቃ ለማድረግ የቤተሰብ አባለቱ በሚኖሩበት አካባቢ መስፈራቸውን ይናገራሉ።

ሁለቱ ወንድማማቾች ይህ ቃለ መጠይቅ የሰጡት በምን አይነት ጫና ውስጥ ሆነው እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም በቪዲዮ ላይ የሚናገሩት ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ከሰጡት አስተያየት ጋር የሚቃረን አይደለም።

“ለምን እንደመጡ (የመንግሥት ጦር) የምናውቀው ነገር የለም። ጥበቃ እንዲያደርጉልን አልጠየቅንም። . . . ለምን እንደተመደቡ እኛ ምንም አናውቅም። እኛ ትዕዛዝ መስጠት እንችልም። ይህ ጦር እዚህ መስፈሩ ለእኛ ምንም ፋይዳ የለውም ብለን ተናግረናል። ወድማችንንም አስጠይቀናል (ይልማ መርዳሳ) እሱም አጥጋቢ ምላሽ አልሰጠንም። ከማሕብረሰቡ ተለይተን እኛ እንደ የጦሩ አካል ነው የምንታየው። ሰው አይጠጋንም። ሰው ሞቶ ቀብር መሄድ እንችል። ከሰው ተለይተን ነው ስንኖር የኖርነው” በማለት ቦረና መርዳሳ ይናገራሉ።

ጀነራል ይልማ መርዳሳ ምንም እንኳ የአገሪቱ ከፍተኛ ጦር አዛዥ ቢሆኑም በወንድም ደረጃ የሚገኙ የቅርብ ዘመዶች በበግብርና በእጅ ሙያ እየሰሩ የሚተዳደሩ መሆናቸውን ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ይናገራሉ።

የግለሰቦቹን እገታ በተመለከተ ከታጣቂ ቡድኑም ሆነ ከአየር ኃይሉ አዛዥ አስተያየት ለመቀበል ያደረግነው ጥረት መልስ አላገኘም።

ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ልታስቆም ነውየኤርትራ የትራንስፖርት እና ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር አየር መንገዱ በኤርትራውያን ተጓዦች ላይ በሚያደርሰው በደል ምክንያት አየር መንገዱ ...
24/07/2024

ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ልታስቆም ነው

የኤርትራ የትራንስፖርት እና ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር አየር መንገዱ በኤርትራውያን ተጓዦች ላይ በሚያደርሰው በደል ምክንያት አየር መንገዱ ወደ አሥመራ የሚያደርገውን በረራ እንዲቋረጥ ተወስኗል ብሏል።

ከአውሮፓውያኑ መስከረም 30/2024 በኋላ አየር መንገዱ ወደ ኤርትራ በረራ እንዳያደርግ እንደታገደ የአገሪቱ መንግሥት አስታውቋል።

‼️ኢትዮጵያ ሲገቡ የታዩት ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ምንድን ናቸው?⭐️⭐️ከትናንት ሐምሌ 15 2016 ዓ.ም. ማሕብራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት የተሰራጩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ብረ...
23/07/2024

‼️
ኢትዮጵያ ሲገቡ የታዩት ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ምንድን ናቸው?
⭐️⭐️
ከትናንት ሐምሌ 15 2016 ዓ.ም. ማሕብራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት የተሰራጩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ብረት ለበስ ወታደራዊ ተሸከርካሪዎች በባቡር ተጭነው ኢትዮጵያ ሲገቡ አሳይተዋል።

ስለነዚህ ብረት ለበስ ተሸከርካሪዎች ምን ይታወቃል? የሚመረቱት የት ነው?
እነዚህ ወታደራዊ ተሸከርካሪዎች Calidus MCAV-20 ወይም በአጭሩ MCAV-20 በመባል ይታወቃሉ።
የሚመረቱት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ነው። Calidus (ካሊደስ) መቀመጫውን በአቡ ዳቢ ያደረገ ወታደራዊ መሳሪያዎችን የሚያመርት ግዙፍ ኩባንያ ነው።
ዩኤኢ ለመጀመሪያ ጊዜ MCAV-20 ያስተዋወቀችው እአአ 2021 (የካቲት 2013 ዓ.ም.) በአቡ ዳቢ ከተማ በተካሄው ዓለም አቀፍ የመከላከያ ኤግዚብሽን እና ኮንፍረንስ ላይ ነበር።
ይህ ወታደራዊ ተሸከርካሪ ለገበያ ከቀረበ የሦስት ዓመታት ዕድሜ ብቻ ነው ያለው። ከዚህ በተጨማሪም በበርካታ የጦር አውድማዎች ላይ ስላልተፈተነ የMCAV-20 ውጤታማነትን መገምገም ቀላል ላይሆን ይችላል።

ይሁን እንጂ አምራቹ ካልደስ MCAV-20 በአስቸካሪ ቦታዎች በፍጥነት የሚንቀሳቀስ፣ የተለያየ አይነት ያላቸው ከባድ መሳሪያዎች ሊገጠምበት የሚችል፣ በተቀጣጣይ ነገር ፍንዳታ እና የከባድ መሳሪያ ፍንጣሪ በቀላሉ ሊጎዳ የማይችል መሆኑን ይገልጻል።
አምራቹ ተሸርካሪው በቀጥተኛ ውጊያ ላይ መሳተፍ ከመቻሉ በተጨማሪ የስላላ ስራዎች ለመስራት፣ ለሎጂስቲክ አቅርቦት፣ ቁስለኛ ከጦር ስፍራ ለማውጣት እንዲሁም የድንበር ጥበቃ ለማድረግ ታስቦ የተሰራ መሆኑን ይገልጻል።

እነዚህን ብረት ለበስ ተሸከርካሪዎች የዩናትድ አረብ ኤሜሬትስ ጦር ይታጠቃቸዋል። ከዩኤኢ በተጨማሪ ወታደራዊ ተሸከርካሪዎቹ በሱዳን፣ በዴሞክራቲክ ሪፓብሊኮ ኮንጎ እና በቻድ በቅርቡ ታይተዋል።
ከሱዳን ጦር ጋር እየተዋጋ የሚገኘው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ (አርኤስኤፍ) የዩኤኢ መንግሥት የአል ቡርሃን ጦርን MCAV-20 እያስታጠቀ ነው ሲል ጥቅምት 2016 ዓ.ም. መግለጫ አውጥቶ ነበር።

ከጂቡቲ ወደብ ተነስተው ወደ ኢትዮጵያ ሲጓጓዙ የታዩት እነዚህ MCAV-20 ብረት ለበስ ተሸከርካሪዎች መዳረሻቸው ሱዳን ነው የሚሉ ባይጠፉም፤ የብረት ለበስ ተሸርካሪዎቹ ባለቤት የኢትዮጵያ መንግሥት መሆኑን የሚገልጹ ግን በርካቶች ናቸው።

ተሸርካሪዎቹን በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እስካሁን የተባለ ነገር ባይኖርም የዩኤኢ መንግሥት MCAV-20 ባስተዋወቀበት ኤግዚብሽን የኢፌድሪ ጦር ኃይል ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተሳታፊ ነበር።
በወቅቱ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ወደ አቡ ዳቢ ተጉዘው ከተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ጦር ኃይሎች ምክትል ኮማንደር እና የአቡ ዳቢ ልዑል አልጋ ወራሽ ከሆኑት ሼይክ ሞሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝተው ነበር።

📷:

ስንት ፋኖ አለ? አመራሮቹስ እንማን ናቸው?በመንግሥት ኃይል ላይ ነፍጥ ያነሱ ከ7 ያላነሱ የፋኖ አደረጃጀቶች አሉ። በጎንደርአማራ ፋኖ በጎንደር - መሪ ባዬ ቀናው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ -...
22/07/2024

ስንት ፋኖ አለ? አመራሮቹስ እንማን ናቸው?

በመንግሥት ኃይል ላይ ነፍጥ ያነሱ ከ7 ያላነሱ የፋኖ አደረጃጀቶች አሉ።

በጎንደር
አማራ ፋኖ በጎንደር - መሪ ባዬ ቀናው
የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ - መሪ ሃብቴ ወልዴ

በወሎ
የአማራ ፋኖ በወሎ - መሪ ምህረት (ምሬ) ወዳጆ

በሸዋ
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ - መሪ መከታው ማሞ
የሸዋ ዕዝ - መሪ አሰግድ መኮንን (ዛሬ ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም. ለመከላከያ እጅ ስለመስጠቱ እየተገለጸ ነው)

በጎጃም
የአማራ ፋኖ በጎጃም - መሪ ዘመነ ካሴ

ጎጃም እና ሸዋ የሚንቀሳቀስ
የአማራ ሕዝባዊ ሠራዊት - መሪዎች እስክንድር ነጋ እና ማስረሻ ሰጤ።

ትውልደ ኢትዮጵያዊውን ገድለዋል የተባሉ ሁለት አሜሪካውያን ተከሰሱበአሜሪካ ፋሲል ተክለማርያም የተባለ ትውልደ ኢትዮጵያዊን ገድለዋል የተባሉ ሁለት ሴት ጥቁር አሜሪካውያን ላይ ክስ ተመሰረተ። ...
12/07/2024

ትውልደ ኢትዮጵያዊውን ገድለዋል የተባሉ ሁለት አሜሪካውያን ተከሰሱ

በአሜሪካ ፋሲል ተክለማርያም የተባለ ትውልደ ኢትዮጵያዊን ገድለዋል የተባሉ ሁለት ሴት ጥቁር አሜሪካውያን ላይ ክስ ተመሰረተ።

የዓይን እማኞች ፋሲል ተክለማርያም የተባለው ሟች የሁለቱ ሴቶች ‘ሹገር ዳዲ’ ነው ሲል ስለመመስከራቸው የፍርድ ቤት ሰነዶች አሳይተዋል።

የ19 ዓመቷ አውድሪ ሚለር እና የ22 ዓመቷ ቴይለር ግሬይ የ53 ዓመቱን ፋሲል ተክለማርያምን ከመግደላቸው በተጨማሪ የእጅ ስልኩን በመጠቀም ገንዘቡን ለመውሰድ አውራ ጣቱን ቆርጠዋል ተብለው ተከሰዋል።

የዋሽንግተን ፖሊስ ትውልደ ኢትዮጵያዊው በሁለቱ ሴቶች በርካታ ቦታ በስለት ተወግቶ የተገደለው መጋቢት 27/2016 ዓ.ም.መሆኑን ገልጾ፤ ሰነዶችን አሰባስቦ ሐምሌ 4/2016 ዓ.ም. በሁለቱ ሴቶች ላይ ክስ መመስረቱን አስታውቋል።

ሟቹ ከመገደሉ በፊት ወይም ሕይወቱ እንዳለፈ የቀኝ እጁ አውራ ጣት ተቆርጦ መወሰዱን የገለጸው ፖሊስ፤ ተጠርጣሪዎቹ የጣቱን አሻራ ተጠቅመው ከስልኩ ገንዘብ ወጪ ሲያደርጉ ነበር ብሏል።

ፖሊስ ሟቹ ተገድሎ በተገኘበት አፓርታማ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የተፈጸመውን “ወንጀል ለመደበቅ እና ማስረጃ ለማጥፋት ማጽጃ ኬሚካሎች ጥቅም ላይ ውለዋል” ብሏል።

በአፓርታማ ሕንጻው ላይ የተገጠሙ ሲሲቲቪ ካሜራዎች የግድያ ወንጀሉ ከተፈጸመ በኋላ ሁለቱ ሴቶች ከሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ጋር ወደቤቱ በመግባት የሟች አስክሬን ካለበት ቤት ንብረት ዘርፈው ሲወጡ አሳይተዋል።

“ስልክ፣ ታብሌት ኮምፒዩተር የመሳሳሉ ንብረቶች አሁንም እንደጠፉ ናቸው” ያለው ፖሊስ፤ ሁለቱ ተከሳሾች ከሟቹ ጋር ጾታዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ከዓይን እማኞች አረጋግጫለሁ ብሏል።

የ19 ዓመቷ አውድሪ ሚለር እና የ22 ዓመቷ ቴይለር ግሬይ በፋሲል ተክለማርያም የግድያ ወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው ገልጿል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሱዳን ገቡጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባልተጠበቀው ጉብኝት ሱዳን መግባታቸው ተገለጸ። ሱዳን ትሪቢዩን የተባለው ለአገሪቱ ጦር ቅርበት ያለው የሱዳን መገናኛ ...
09/07/2024

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሱዳን ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባልተጠበቀው ጉብኝት ሱዳን መግባታቸው ተገለጸ።

ሱዳን ትሪቢዩን የተባለው ለአገሪቱ ጦር ቅርበት ያለው የሱዳን መገናኛ ብዙሃን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ፖርት ሱዳን ሲደርሱ በአገሪቱ ጦር መሪ ጀነራል አብዱል ፋታህ አል ቡርሃን አቀባበል ሲደረግላቸው የሚያሳይ ምስል ይዞ ወጥቷል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጉዞ ዓላማ አልተገለጸም። በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እንዲሁ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጉብኝት በተመለከተ የተባለ ነገር የለም።

ይህ ጉብኝት ሱዳን ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት ከገባች ወዲህ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሱዳን ያቀኑ የመጀመሪያው መሪ ያደርጋቸዋል።

ጀነራል አብዱል ፋታህ አል ቡርሃን የሚመሩት ጦር በጀነራል ሞሐመድ ዳጋሎ ሔሜቲ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር መዋጋት ከጀመረ ዓመት አልፎታል።

በጦርነቱ ምክንያት ከሱዳን መዲና ካርቱም ለመሸሽ የተገደደው የጀነራል አል-ቡርሃን ጦር ዋና መቀመጫውን ፖርት ሱዳን ካደረገ ሰነባብቷል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አሥመራ ገቡየሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼይክ ሞሐሙድ ለሥራ ጉብኝት ኤርትራ ገቡ።  የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አሥመራ ሲደርሱ በኤርትራው አቻቸው ኢሳያስ አፈወርቂ ደማቅ አቀ...
08/07/2024

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አሥመራ ገቡ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼይክ ሞሐሙድ ለሥራ ጉብኝት ኤርትራ ገቡ።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አሥመራ ሲደርሱ በኤርትራው አቻቸው ኢሳያስ አፈወርቂ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው የኤርትራ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ሐስን በአሥመራ ቆይታቸው በሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነቶች ላይ ይመክራሉ ተብሏል።

የኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ የባሕር በር ስምምነትን ተከትሎ የአዲስ አበባ እና ሞቃዲሹ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እጅጉን ከሻከረ በኋላ ፕሬዝዳንት ሐሰን በቀጠናው ወደሚገኙ አገራት የሚያደርጉት ጉዞ በርክቷል።

ፕሬዝዳንቱ ከኢትዮጵያ ጋር ወዳጅነቷ ወደተቀዛቀዘው ኤርትራ ሲጓዙ ይህን በስድስት ወራት ውስጥ ሦስተኛው ነው።

“የእገታ መብዛት የሕግ የበላይነት መዳከም ውጤት ነው”በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢትዮጵያ የታጋቾች ቁጥር መበራከት በአገሪቱ የሕግ የበላይነት መዳከም ውጤት ነው አሉ።አ...
08/07/2024

“የእገታ መብዛት የሕግ የበላይነት መዳከም ውጤት ነው”

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢትዮጵያ የታጋቾች ቁጥር መበራከት በአገሪቱ የሕግ የበላይነት መዳከም ውጤት ነው አሉ።

አምባሳደር ማሲንጋ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በኦሮምያ እና አማራ ክልሎች የሚታገቱ ሰዎች ቁጥር መጨመር የግጭቶች መራዘም ወንጀለኞችን እንደሚያበረታቱ እና የሕግ የበላይነትን እንደሚያዳክሙ ማሳያ ነው ብለዋል።

አምባሳደሩ በአሜሪካ ኤምባሲ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በወጣው መልዕክታቸው ባለፈው ሳምንት ከ100 በላይ ተማሪዎች እና መንገደኞች መታገታቸውን ገልጸዋል።

ባሳለፍነው ሳምንት ከአማራ ክልል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ባሕር ዳር ከተማ የተነሱ ከአንድ መቶ በላይ መንገደኞች በሦስት አውቶብሶች ወደ አዲስ አበባ እየተጓዙ ሳለ ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብር ጉራቻ አካባቢ መታገታቸው ይታወሳል።

Image: Department of States

25/06/2024

ኬንያውያን ወጣቶች የአገሪቱን ፓርላማ ጥሰው ገቡ

የኬንያ መንግሥት ያጸደቀውን የቀረጥ ሕግ በመቃወም በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ፓርላማውን ጥሰው ገቡ።

ፖሊስ በከፍተኛ ቁጥር የወጡ ተቃዋሚዎችን ለመበተን ጥይት ተኩሶ ቢያንስ 10 ወጣቶችን ገድሏል።

ወጣቶቹ ፓርላማው ዛሬ ያጸደቀው የቀረጥ ሕግ ኑሮ ያስወድዳል በሚል ሲቃወሙት ቆይተዋል።

የፓርላማው በር በወጣት ተቃዋሚዎቹ ሲወድቅ፤ በምክር ቤቱ የነበሩ የሕዝብ እንደራሴዎች ሕይወታቸውን ለማዳን ወደ ሕንጻው ምድር ቤት ሲሯሯጡ እንደነበረ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

የኢትዮጵያ እና ኬንያ አትሌቶች ቻይናዊ ሯጭ ውድድር እንዲያሸንፍ አድርገዋል ተብለው ምርመራ ተከፈተባቸውየቤይጂንግ ግማሽ ማራቶን አዘጋጆች ኢትዮጵያዊው አትሌት ደጀኔ ኃይሉ እና ሌሎች ሁለት ኬ...
15/04/2024

የኢትዮጵያ እና ኬንያ አትሌቶች ቻይናዊ ሯጭ ውድድር እንዲያሸንፍ አድርገዋል ተብለው ምርመራ ተከፈተባቸው

የቤይጂንግ ግማሽ ማራቶን አዘጋጆች ኢትዮጵያዊው አትሌት ደጀኔ ኃይሉ እና ሌሎች ሁለት ኬንያውያን ሆን ብለው ቻይናዊው ሂ ጄይ እንዲያሸንፍ አድርገዋል በሚል ምርመራ ጀመሩ።

ቻናውያን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሂ ጄይን ማሸነፍ “አሳፋሪ” ሲሉ ተችተውታል።

ጉዳዩ የውድድሩ አዘጋጆችን ትኩረት የሳበው አትሌቶቹ ሂ ጄይን እንዲያሸንፍ ሲረዱት የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ድረ-ገጽ ላይ በሰፊው ከተዘዋወረ በኋላ ነው።

ውድድሩ የተካሄደው ትናንት እሁድ ሲሆን፣ ውድድሩን ሊያጠናቅቅ ሲቃረብ፣ ኬንያውያኑ ሮበርት ኬተር እና ዊሊ ምናንጋት እንዲሁም ደጀኔ ኃይሉ ቻይናዊው ሂ ጄይ ውድድሩን ቀድሞ እንዲጨርስ ፍጥነታቸውን ሲቀንሱ እና አልፏቸው እንዲሄድ ምልክት ሲሰጡት ይታያሉ።

ሶስቱ የምስራቅ አፍሪካ አትሌቶች ቻይናዊው ወደ ውድድሩ ማጠናቀቅያ እንዲገሰግስ በእጃቸው ምልክት ሲያሳዩት በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ የታየ ሲሆን፣ አልፏቸው ከሄደም በኋላ እነርሱ በዝግታ ሲሮጡ ተስተውሏል።

የውድድሩ አዘጋጆች ለፈረንሳዩ የዜና ወኪል ኤኤፍፒ ጉዳዩን አስመልክተው “ምርመራ እያደረግን ነው፤ የምርመራችንን ውጤት እንዳጠናቀቅን ለሕዝብ ይፋ እናደገርጋለን” ብለዋል።

ኢራን እስራኤል ላይ የአየር ጥቃቶችን ከፈተችኢራን በእስራኤል ላይ የሰው አልባ አውሮፕላኖች እና የሚሳኤል ጥቃቶችን ከፈተች።ኢራን እስራኤል ከዛሬ 12 ቀናት በፊት በሶሪያ በሚገኝ ቆንስላ ጽ/...
14/04/2024

ኢራን እስራኤል ላይ የአየር ጥቃቶችን ከፈተች
ኢራን በእስራኤል ላይ የሰው አልባ አውሮፕላኖች እና የሚሳኤል ጥቃቶችን ከፈተች።

ኢራን እስራኤል ከዛሬ 12 ቀናት በፊት በሶሪያ በሚገኝ ቆንስላ ጽ/ቤቷ ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ ይህንን ጥቃት መክፈቷን አስታውቃለች።

ኢራን ቆንስላዋ ጥቃት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት እና ስትዘጋጅ ቆይታለች።

እንደ አሜሪካ እና ዩናይትድ ኪንግደም ያሉ የእስራኤል ወዳጅ ሀገራት ኢራን ጥቃት እንዳትፈጽም ሲያስጠነቅቁ ቆይተዋል።

ዛሬ ለሊቱን በተሰማው ዜና ግን ኢራን እንደዛተች አልቀረችም። ከዒላማቸው በመጋጨት ጉዳት በሚያደርሱ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሚሳኤሎች
እስራኤልን ማጥቃት ጀምራለች።

እስካሁን ድረስ ከ300 በላይ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃቶችን እንደሰነዘረች ተሰምቷል።

የአሜሪካ ጦር እና የዩኬ አየር ኃይሎች እስራኤልን እየተከላከሉ ሲሆን እስራኤል 99 በመቶ የሚሆነው ጥቃት ማክሸፏን ይፋ አድርጋለች።

#ኢራን #እስራኤል

የአዲስ አበባ ፖሊስ ክትትል ሳደርግባቸው የቆየዋቸውን የፋኖ አባላት ዛሬ ሚያዚያ 4 2016 በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክር ተኩስ ከፍተዋል ብሏል። የከማው ፖሊስ የፋኖ አመራርን ጨምሮ ሦስት ግ...
12/04/2024

የአዲስ አበባ ፖሊስ ክትትል ሳደርግባቸው የቆየዋቸውን የፋኖ አባላት ዛሬ ሚያዚያ 4 2016 በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክር ተኩስ ከፍተዋል ብሏል።

የከማው ፖሊስ የፋኖ አመራርን ጨምሮ ሦስት ግለሰቦችን ለመያዝ ነበር ኦፕሬሽን ያደረገው።
በዚህም ከተማው ፖሊስ እና በሦስት የፋኖ ፖሊስ አባላት መካከል ለውውጥ ተደርጓል።
በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት ሲገደሉ ሁለት የፖሊስ አባላት ደግሞ ቆስለዋል።

የፋኖ አባላቱን በመጫን አልተባበርም ያሉ አንድ በአካባቢው የነበሩ ግለሰብ በፋኖ አባል መገደላቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

የተኩስ ልውውጥ በተከሰተበ አካባቢ የነበሩ የዓይን እማኞች ለዜና ፕላስ እንደተናገሩት ሁለት በአካባቢው የነበሩ ሰዎች በጥይት ተመትተው ቆስለዋል።

የተኩስ ልውውጡ የተፈጸመው ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች ወደ ቦሌ መድኃኒያለም በሚያስወጣ መንገድ ላይ ነው።

ዛሬ ቦሌ አካባቢ በነበረ የተኩስ ልውውጥ የፋኖ አመራር መገደሉን ፖሊስ አስታወቀየአዲስ አበባ ፖሊስ ዛሬ በቦሌ ሚሌኒየም አካባቢ ከታጣቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ገለጸ።እንደ ፖሊስ ...
12/04/2024

ዛሬ ቦሌ አካባቢ በነበረ የተኩስ ልውውጥ የፋኖ አመራር መገደሉን ፖሊስ አስታወቀ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዛሬ በቦሌ ሚሌኒየም አካባቢ ከታጣቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ገለጸ።

እንደ ፖሊስ መረጃ ከሆነ በተኩስ ልውውጡ የሰው ሕይወት ሲያልፍ የተወሰኑ የፖሊስ አባላት ቆስለዋል።

ፖሊስ የፋኖ አባላት ናቸው ያላቸው ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ “በአዲስ አበባ የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው እየተንቃሰቀሱ” እንደነበር ገልጿል።

ፖሊስ ዛሬ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ ከታጣቂዎቹ ጋር ባደረገው የተኩስ ልውውጥ የፋኖ መሪ ነው የተባለው ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሕይወቱ ማለፉን እና አንዳርጌ ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል ብሏል።

አቤኔዘር ጋሻው አባት የተባለው የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ታጣቂዎቹ በሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ መክፈታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አክሎ አስታውቋል።

አቶ በቴ የተገደሉት በበርካታ ጥይት ጭንቅላታቸውን ተመትተው መሆኑ ተገለጸየኦሮሞ ነጻነት ግንባር የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ የተገደሉት በበርካታ ጥይት ጭንቅላታቸውን ተመትተው መሆኑ ተ...
11/04/2024

አቶ በቴ የተገደሉት በበርካታ ጥይት ጭንቅላታቸውን ተመትተው መሆኑ ተገለጸ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ የተገደሉት በበርካታ ጥይት ጭንቅላታቸውን ተመትተው መሆኑ ተገለጸ።
ቢቢሲ የአቶ በቴ ኡርጌሳን አስክሬን የመረመሩ ባለሙያ እና የቤተሰብ አባል ጠቅሶ እንደዘገበው በአስክሬናቸው ላይ ቢያንስ 11 ጉዳቶች ታይተዋል።

ስማቸው ያልተጠቀሰ የሕክምና ባለሙያ የአቶ በቴ ጭንቅላት ላይ አምስት በጥይት ምት የተፈጠሩ ጉዳቶችን መመልከታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
“ጭንቅላቱ ላይ አምስት ቁስለት፣ ወገቡ ላይ ሦስት ቦታ፣ በግራ ጎኑ አንድ ትልቅ ጉዳት፣ ከወገቡ ወደታች እና ታፋው ላይም ተጨማሪ አንዳንድ ጉዳት በአጠቃላይ 11 የሚሆኑ ቁስለቶች ታይተዋል።” ሲሉ ይህ ባለሙያ ተናግረዋል።

የአቶ በቴ ኡርጌሳ ቤተሰብ አባል የሆኑ ግለሰብ ረቡዕ ጠዋት ከነዋሪዎች ባገኙት መረጃ መሠረት፣ ሁለት ሰዓት አካባቢ አስከሬኑን ማንሳታቸው እና አካላቸው ብዙ ቦታዎች ላይ ቆስሎ መመልከታቸውንም ገልጸዋል።

ለአቶ በቴ ግድያ እስካሁን በይፋ ተጠያቂ የሆነ አካል የለም።
የክልሉ መንግሥትም በአንዳንድ ወገኖች ለግድያው መንግሥት ተጠያቂ መደረጉን አጥብቆ አውግዟል።

አሜሪካ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ ተጽእኖ ፈጣሪዎች የግድያ ወንጀሉ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ጠይቀዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ በቴ ተገድለው የተገኙባት የመቂ ከተማ ከንቲባ አቶ ዲልቦ ኡርጌሳ ግድያው የተፈጸመው ምናልባት በቤተሰብ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ሊሆን ይችላል ሲሉ መላ ምት ሰንዝረዋል።

የአቶ በቶ ኡርጌሳ ወንድም የሆኑት ሚሎ ኡርጌሳ ግን በቤተሰብ መካከል ምንም አይነት ግጭት አለመኖሩን ተናግረው ይህን እንደምክንያት እየተነሳ ያለው ወንጀሉን ለመሸፋፋን ስለተፈለገ ነው ሲሉ ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።

#በቴ #በቴኡርጌሳ

ስለ አቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ እስካሁን የምናቀውየኦነግ የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ በትውልድ ከተማቸው መቂ ትናንት ሰኞ ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም. እኩለ ለሊት ላይ ተገድለው አስክሬናቸው...
10/04/2024

ስለ አቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ እስካሁን የምናቀው

የኦነግ የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ በትውልድ ከተማቸው መቂ ትናንት ሰኞ ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም. እኩለ ለሊት ላይ ተገድለው አስክሬናቸው ተጥሎ ተገኝቷል።

ግድያው የተፈጸመባቸው አርፈውበት ከነበረው ሆቴል ተይዘው ከወጡ በኋላ ነው።
አስክሬናቸው መቂ እና ባቱ ከተማ አቅራቢያ ተጥሎ መገኘቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
ለግድያው እስካሁን በይፋ ተጠያቂ የተደረገ አካል የለም።

ፓርቲያቸው ኦነግ አቶ በቴ በጥይት ተመትተው ስለመገደላቸው ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
የክልሉ መንግሥት የአቶ በቴን ግድያ በተመለከተ እስካሁን ያለው ነገር የለም።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) እና ኦነግ በአቶ በቴ ግድያ ዙሪያ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

ግድያውን ተከትሎ ሊከሰት የሚችልን የጸጥታ መደፍረስ ቀድሞ ለመከላከል እንደ አምቦ እና ሻሸመኔ ባሉ የኦሮሚያ ከተሞች የክልሉ ፖሊስ እና አድማ ብተና ኃይሎች በብዛት ሲንቀሳቀሱ መታየታቸው ነዋሪዎች ለዜና ፕላስ ተናግረዋል።

በመቂ እና በዙሪያዋ የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጠዋል።
አቶ በቴ ወደ መቂ የተጓዙት ከከተማዋ አቅራቢያ የሚገኝ የፓፓያ እርሻቸውን ለመመልከት መሆኑን ቢቢሲ የቅርብ ኳደኛቸውን ጠቅሶ ዘግቧል።

በኦሮሚያ የተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ ተጽእኖ ፈጣሪ የነበሩት አቶ በቴ የአራት ልጆች አባት ነበሩ።

#በቴ #በቴኡርጌሳ

ሰበር ዜና!!አቶ በቴ ኡርጌሳ ተገድለው አስክሬናቸው ተጥሎ ተገኘየኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ተገድለው አስክሬናቸው ተጥሎ ተገኘ።ምንጮች አቶ...
10/04/2024

ሰበር ዜና!!
አቶ በቴ ኡርጌሳ ተገድለው አስክሬናቸው ተጥሎ ተገኘ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ተገድለው አስክሬናቸው ተጥሎ ተገኘ።
ምንጮች አቶ በቴ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን በምትገኘው መቂ ከተማ የተገደሉት ትናንት ሰኞ ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም. እኩለ ለሊት ላይ ነው።
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ የሕዝብ ግንኑነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ “በቴ የሆነውን ማመን አቅቶኛል” ሲሉ ጽፈዋል።

አቶ በቴ መቂ ከተማ አርፈው ከነበረበት የሆቴል ክፍል ውስጥ ተይዘው እንዲወጡ ከተደረጉ በኋላ ተገድለው አስክሬናቸው መንገድ ላይ ተጥሎ መገኘቱን ቢቢሲ የቅርብ ጓደኛቸውን ጠቅሶ ዘግቧል።

አቶ በቴ በፖለቲካ ተሳትፏቸው ምክንያት በተደጋጋሚ ለእስር ሲዳረጉ የቆዩ ፖለቲከኛ ሲሆኑ ከጥቂት ሳምንታት በፊትም ከአንድ ፈረንሳይዊ ጋዜጠኛ ጋር በአዲስ አበባ በቁጥጥር ስር ውለው ለሁለት ሳምንታት ያክል በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ከሁለት ሳምንታት በፊት ነበር ነጻ የወጡት።

የአቶ በቴ ግድያን ተከትሎ በመቂ ከተማ የቴሌኮም አገልግሎት ተቋርጦ ይገኛል።

በኦሮሞ የተቃውሞ ፖለቲካ እና በኦነግ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆኑት አቶ በቴ ከዚህ ከቀደምም ለተደጋጋሚ እስር ሲዳረጉ ቆይተዋል።

#በቴኡርጌሳ

ኢትዮጵያውያንን አሳፍራ ወደ የመን ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ሰጥማ 38 ዜጎች ሞቱትናንት ሰኞ መጋቢት 30 2016 ዓ.ም. ከ60 በላይ ኢትዮጵያውያንን ጭና ከጅቡቲ ወደ የመን ስትጓዝ የነበረች ...
09/04/2024

ኢትዮጵያውያንን አሳፍራ ወደ የመን ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ሰጥማ 38 ዜጎች ሞቱ

ትናንት ሰኞ መጋቢት 30 2016 ዓ.ም. ከ60 በላይ ኢትዮጵያውያንን ጭና ከጅቡቲ ወደ የመን ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ሰጥማ የ38 ዜጎች ሕይወት ማለፉን በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።

ኤምባሲው በሰሜን ምስራቅ ከሚገኘው የአገሪቱ ክፍል ተነስታ ጉዞዋን ወደ የመን አቅጣጫ አድርጋ የነበረችው ጅላበ ቢያንስ 60 ኢትዮጵያውያንን አሳፍራ ነበር ብሏል።

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ድርጅት (አይኤኤም) ከሟቾቹ መካከል ሕጻናት እንደሚገኙበት ገልጾ 22 ሰዎች በሕይወት መገኘታቸውን ገልጿል።

አይኦኤም እስካሁን የደረሰቡት ያማይታወቁ ተጨማሪ 6 ሰዎች ሕይወታቸው ሳያልፍ አይቀርም ብሏል።

በየዓመቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች የኤደን ባሕረ ሰላጤን በማቋረጥ ከጅቡቲ ተነስተው ወደ ወደ መካከለኛው ምስራቅ በባሕር እና በየብስ አደገኛ ጉዞ ያደርጋሉ።

በመዳረሻቸውም ጦርነት እና ስቃይ ይገጥማቸዋል።

አይኦኤም ከእአአ 2014 ጀምሮ በዚህ የጉዞ መስመር ቢያንስ 1ሺህ ስደተኞች ሕይወታቸው አልፏል አልያም የገቡበት አይታቅም ይላል።


ምስል፡ Eth Embassy in Djibouti

በደኅንነት ስጋት ወደ ሞቃዲሹ የሚደረጉ በረራዎች ተሰረዙየቱርክ፣ ኳታር እና ፍላይ ዱባይ አየር መንገዶች ወደ ሞቃዲሹ የሚያደርጓቸውን በረራዎች በደኅንነት ስጋት ምክንያት ሰረዙ። አየር መንገዶ...
09/04/2024

በደኅንነት ስጋት ወደ ሞቃዲሹ የሚደረጉ በረራዎች ተሰረዙ

የቱርክ፣ ኳታር እና ፍላይ ዱባይ አየር መንገዶች ወደ ሞቃዲሹ የሚያደርጓቸውን በረራዎች በደኅንነት ስጋት ምክንያት ሰረዙ።

አየር መንገዶቹ ወደ ሶማሊያ መዲና ሊያደርጓቸው የነበሩትን በረራዎች የሰረዙት አሜሪካ በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሹ የሽብር ጥቃት ሊኖር እንደሚችል ማሳሰብያ ማውጣቷን ተከትሎ ነው።

በሶማሊላንድ የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን አየር መንዶቹ በረራቸውን የሰረዙት በደኅንነት ስጋት መሆኑን እየዘገቡ ይገኛሉ።

በናይሮቢ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ትናንት ሰኞ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ በሞቃዲሹ የተለያዩ ቦታዎች የሽብር ጥቃቶች ሊፈጸሙ ጠቅሶ አሳስቧል።

ትናንት ምሽትም ከፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት ቪላ ሶማሊያ በቅርብ ርቀት በሚገኙ አካባቢዎች ቢያንስ ሦስት የሞርታር ጥቃቶች ተፈጽመዋል።

ተሳፋሪዎች ወደ ሞቃዲሹ ሊያደርጉ የነበረው በረራ መሰረዙን የሚያሳይ ከአየር መንገዶች የደረሳቸውን መልዕክት በማሕበራዊ ሚዲያዎች እያጋሩ ነው።

ፍላይዱባይ የበረራ ቁጥር ከዱባይ ተነስቶ ዛሬ እኩለ ቀን ሞቃዲሹ ማረፍ ነበረበት። ከዶሃ ተነስቶ በጂቡቲ አድርጎ ሞቃዲሾ ይገባ የነበረው የኳታር አየር መንገድ ወደ አደን አዴ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ የሚያደርገውን በረራ ሰርዟል።

በተመሳሳይ የቱርክ አየር መንገድ ከኢስታንቡል ወደ ሞቃዲሾ በበረራ ቁጥር የሚያደርገውን በረራ ሰርዟል።


@ Getty Images

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ZenaPlus posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share