05/06/2026
ሶማሊያዊው ዳኛ የዓለም ዋንጫን ለመዳኘት ወደ አሜሪካ ያቀናሉ
********
ዝነኛው ሶማሊያዊ የመሐል ዳኛ ኡመር አብዱልቃድር አርታን በ2026 በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ ጨዋታዎችን ለመምራት የሚያስችለውን የዩናይትድ ስቴትስ መግቢያ ቪዛ ማግኘቱ ተረጋግጧል።
ይህ ስኬት ለሶማሊያ ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ እግር ኳስ ትልቅ ስኬት ተደርጎ ተወስዷል።