All in one place

All in one place Wellcome to all in one place ❤❤
👉news
👉technology
👉enjoyment
👉blog

“ ባርሴሎና እና ሜሲን አመሰግናለሁ “ ዴምቤሌ የባሎን ዶር አሸናፊው ተጨዋች ኡስማን ዴምቤሌ ከሽልማቱ በኋላ የቀድሞ ክለቡን ባርሴሎና ማመስገን እንደሚፈልግ ገልጿል። “ ባርሴሎና ማመስገን እ...
23/09/2025

“ ባርሴሎና እና ሜሲን አመሰግናለሁ “ ዴምቤሌ

የባሎን ዶር አሸናፊው ተጨዋች ኡስማን ዴምቤሌ ከሽልማቱ በኋላ የቀድሞ ክለቡን ባርሴሎና ማመስገን እንደሚፈልግ ገልጿል።

“ ባርሴሎና ማመስገን እፈልጋለሁ “ ያለው ዴምቤሌ “
እንዲሁም ሊዮኔል ሜሲን ማመስገን እፈልጋለሁ ከእሱ ብዙ ተምሬያለሁ “ ሲል ተናግሯል።

የተበረከተለት ሽልማት በቡድን ስራ የመጣ መሆኑን የገለፀው ዴምቤሌ “ የቡድን አጋሮቼን በጣም ማመስገን እፈልጋለሁ “ ብሏል።

“ የትውልድ መንደሬን ከልብ አመሰግናለሁ ወደዛ የመሄድ አጋጣሚ ሳገኝ የአካባቢው ሰው እዚህ እንድደርስ ረድቶኛል “ ዴምበሌ

21/09/2025

What are you doing live alone??

የእንግሊዝ ፕርሚየ ሊግ በ5ኛ ሳምንት በጉጉት የሚጠበቀው የእንግሊዝ ፕርሚየ ሊግ  አርሰናል ከማንችስተር ሲቲ በኢሚሬትስ ስታዲየም ያገናኛል ። ማን ያሸንፍ ይሆን ግምታቹ አስቀምጡ ።እሁድ ምሽ...
20/09/2025

የእንግሊዝ ፕርሚየ ሊግ
በ5ኛ ሳምንት በጉጉት የሚጠበቀው የእንግሊዝ ፕርሚየ ሊግ አርሰናል ከማንችስተር ሲቲ በኢሚሬትስ ስታዲየም ያገናኛል ። ማን ያሸንፍ ይሆን ግምታቹ አስቀምጡ ።
እሁድ ምሽት 12:30 ጨዋታው ይጀመራል ።
https://t.me/allinoneplace21

የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል ! የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል። በዚህም መሰረት የባርሴሎናው የፊት መስመር ተጨዋች ማርከስ ራሽፎርድ የሳምን...
20/09/2025

የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል !

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት የባርሴሎናው የፊት መስመር ተጨዋች ማርከስ ራሽፎርድ የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች በመባል መመረጥ ችሏል።

ማርከስ ራሽፎርድ ባርሴሎና ኒውካስል ዩናይትድን ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት የማሸነፊያ ግቦችን በማስቆጠር የጨዋታው ኮከብ ነበር።
Via tikvahesport

https://t.me/allinoneplace21

አትሌት ቢኒያም መሀሪ ለፍፃሜ አልፏል ! በሁለተኛው ምድብ የወንዶች 5000ሜ ማጣሪያ ውድድር የተሳተፈው አትሌት ቢኒያም መሀሪ ለፍፃሜ በቅቷል። አትሌት ቢኒያም መሀሪ ውድድሩን  #በአንደኝነት...
19/09/2025

አትሌት ቢኒያም መሀሪ ለፍፃሜ አልፏል !

በሁለተኛው ምድብ የወንዶች 5000ሜ ማጣሪያ ውድድር የተሳተፈው አትሌት ቢኒያም መሀሪ ለፍፃሜ በቅቷል።

አትሌት ቢኒያም መሀሪ ውድድሩን #በአንደኝነት በማጠናቀቅ ለፍፃሜ መድረስ ችሏል።

በመጀመሪያው የተካፈለው አትሌት ሀጎስ ገብረህይወት 6️⃣ኛ ደረጃ ይዞ በማጠናቀቅ ለፍፃሜ አልፏል።

ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ኩማ ግርማ ውድድሩን አቋርጧል።

የወንዶች 5000ሜ ፍፃሜ ውድድር የፊታችን እሁድ ከቀኑ 7:05 የሚካሄድ ይሆናል።


All in one place

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋት ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ መቀመጧን ጥናት አመለከተ‼️ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔትን ነጸነት በመገደብ ከአፍሪካ በአንደኛ ...
17/09/2025

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋት ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ መቀመጧን ጥናት አመለከተ‼️

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔትን ነጸነት በመገደብ ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን በብሉምስበሪ አሳታሚ ላይ የታተመ የጥናት መጽሐፍ አመላከተ።

“የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ” በሚል ርእስ በፊሊሽያ አንቶኒዮ እና ቶኒ ሮበርትስ የተጠናውና መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ባደረገው ብሉምስበሪ አሳታሚ ድርጅት ላይ በመጸሐፍ መልክ ታትሞ የወጣው ጥናት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 በአህጉረ አፍሪካ በሀገራት የተፈጸመውን የኢንተርኔት መዘጋት ገምግሟል።

በዚህም በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 ባሉት በለፉት ዘጠኝ ዓመታት 193 የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ አህጉር መመዝገቡን ገልጿል።

በተጠቀሱት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ በተፈጸሙ የኢንተርኔት መዘጋት ድግግሞሽ መጠኖች ሀገራትን በደረጃ ያስቀመጠው ጥናቱ ኢትዮጵያን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ሰላሳ ጊዜ ኢንትርኔት የዘጋች በሚል ከ55ቱ የአፍሪካ ሀገራት በአንደኛ ደረጃ አስቀምጧታል።


All in one place

የዛሬ ተጠባቂ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ! 1:45 አትሌቲክ ቢልባኦ ከ አርሰናል 4:00 ጁቬንቱስ ከ ዶርትመንድ 4:00 ሪያል ማድሪድ ከ ማርሴይ 4:00 ቶተንሀም ከ ቪያሪያል 4:00 ቤኔፊ...
16/09/2025

የዛሬ ተጠባቂ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች !

1:45 አትሌቲክ ቢልባኦ ከ አርሰናል

4:00 ጁቬንቱስ ከ ዶርትመንድ

4:00 ሪያል ማድሪድ ከ ማርሴይ

4:00 ቶተንሀም ከ ቪያሪያል

4:00 ቤኔፊካ ከ ቃራባህ


All in one place

 የ2018 ትምህርት ዘመን ሰኞ መስከረም 05 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚጀመር ይታወቃል፡፡ በዲጂታል ዘመን በተማሪ ህይወት ላይ ትልቅ ተፅእኖ ከሚያሳድረው አንዱ ማህበራዊ ሚድያ ሲሆን እንደ ፦...
15/09/2025



የ2018 ትምህርት ዘመን ሰኞ መስከረም 05 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚጀመር ይታወቃል፡፡

በዲጂታል ዘመን በተማሪ ህይወት ላይ ትልቅ ተፅእኖ ከሚያሳድረው አንዱ ማህበራዊ ሚድያ ሲሆን እንደ ፦
- ቲክቶክ
- ኢንስታግራም
- ፌስቡክ
- X
- ቴሌግራም እና መሰል መተግበሪያዎችን ያለ አግባብ መጠቀም ትኩረትን ይቀንሳል ፣ የአካዳሚክ አፈጻጸምን ያዳክማል ፣ ጭንቀትና መሰል አሉታዊ የሆኑ ውጤቶችን ያመጣል።

ተማሪዎች ማህበራዊ ሚድያን ያለ አግባብ ሲጠቀሙ የሚገጥሟቸው ዋና ዋና ፈተናዎች ምንድን ናቸው ?

➡️ በኦንላይን የሚጠፋው ከልክ ያለፈ ጊዜ የተማሪዎችን ትኩረት እና ምርታማነትን ስለሚቀንስ ተማሪዎችን ወደ ደካማ የአካዳሚክ አፈፃፀም ያመራል፡፡

➡️ ከፍተኛ መጠን ያለው የስክሪን ጊዜ በተማሪዎች ላይ የስነ ልቦና ጫናን ያስከትላል።

➡️ በምሽት ማህበራዊ ሚዲያን አብዝቶ መጠቀም እንቅልፍ ለመተኛት እና ጤናማ እረፍትን ለማድረግ ከባድ ስለሚሆን የማስታወስ ችግርን ያስከትላል እንዲሁም የመማር ችሎታን ይቀንሳል፡፡

➡️ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአካባቢ እና የትምህርት ቤት ስሞችን ወይም ስልክ ቁጥሮች እና መሰል የግል መረጃዎችን ማጋራት ለመጭበርበር እና ለሳይበር ጥቃት በቀላሉ ተጋላጭ ያደርጋል።

ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን ሲጀምሩ ማህበራዊ ሚዲያን አግባብ ባለው መልክ እንዲጠቀሙ መውሰድ ያለባቸው መፍትሄዎች ምንድን ናቸው ?

📇 የስክሪን ጊዜን መገደብ እና ማህበራዊ ሚዲያን ከመጠቀማቸው በፊት ለትምህርት ቤት ስራ ቅድሚያ በመስጠት ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን መቀነስ።

📇 ማህበራዊ ሚዲያን እንደ መዝናኛ ብቻ ከመመልከት ይልቅ የትምህርት መሳሪያ በማድረግ የጥናት ቡድኖችን በመቀላቀል፣ የአካዳሚክ ገጾችን በመከተልና አዳዲስ ክህሎቶችን በመማር የትምህርት ጊዜን የተሳካ ማድረግ።

📇 ከቤተሰብ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ፣ መጽሐፍ ማንበብ ወይም የስፖርት እንቅስቃሴን በማድረግ የተሻለ ማህበራዊ ህይወት ልምምድ ማዳበር።

#ማስታወሻ ፦ ትምህርት ሚኒስቴር መስከረም 05/2018 ዓ/ም ከሚጀምረው የትምህርት ዘመን ጋር በተያያዘ ተማሪዎች ስልክን ጨምሮ ማንኛውም አይነት ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ወደ ትምህርት ቤት ይዘው መምጣት እንደማይችሉ አስጠንቅቋል።

ይህ ፅሁፍ በቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።


ታንዛኒያ የማራቶን አሸናፊ ሆነች ! ልብ አንጠልጣይ የነበረው የወንዶች ማራቶን ፍፃሜውን ሲያገኝ የምስራቅ አፍሪካዊቷ ታንዛኒያ አትሌት አልፎስ ሲምቡ የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፏል።ለጀርመን የሚሮጠ...
15/09/2025

ታንዛኒያ የማራቶን አሸናፊ ሆነች !

ልብ አንጠልጣይ የነበረው የወንዶች ማራቶን ፍፃሜውን ሲያገኝ የምስራቅ አፍሪካዊቷ ታንዛኒያ አትሌት አልፎስ ሲምቡ የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፏል።

ለጀርመን የሚሮጠው አማኒ ፔትሮስ ሁለተኛ እንዲሁም ጣልያናዊው ሊያስ ኦዋኒ የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊ ሆነዋል።

ታንዛኒያ በአለም ሻምፒዮናው በርቀቱ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያዋ ሆኖ ተመዝገቧል።

የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊው አልፎንሶ ሲምቦ የአመቱ ምርጥ ሰዓቱን በማስመዝገብም ውድድሩን ጨርሷል።

የሀገራችን አትሌቶች ውድድሩን ሳይጨርሱ ለማቋረጥ ተገደዋል።

ውድድሩ ያለቀበት ሰዓት ምን ይመስላል?

1️⃣ኛ አልፎንስ ሲምቡ - 2:09:48
2️⃣ኛ አማኒ ፔትሮስ - 2:09:48
3️⃣ኛ ሊያስ ኦዋኒ - 2:09:53 በሆነ ሰዓት ውድድራቸውን ጨርሰዋል።
Via tikivah

ኤለን መስክ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃርነት ስፍራውን አስረከበ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር የነበረው አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤለን መስክ የቀዳሚነት ስፍራውን በኦራክል ኩባንያ መስራች ላሪ ኤሊሰን ...
10/09/2025

ኤለን መስክ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃርነት ስፍራውን አስረከበ

የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር የነበረው አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤለን መስክ የቀዳሚነት ስፍራውን በኦራክል ኩባንያ መስራች ላሪ ኤሊሰን አስረክቧል።

አጠቃላይ 385 ቢሊየን ዶላር ሀብት የነበረው ኤለን መስክ እስከ ትናንትና ድረስ 101 ቢሊየን ዶላር ሃብት በነበረው ላሪ ኤሊሰን በስምንት ቢሊየን ዶላር ተበልጦ የዓለም ቁጥር ሁለት ቱጃር ሆኗል።

ላሪ ኤሊሰን ትናንትናው ባወጣው የገቢ ሪፖርት አጠቃላይ ሀብቱ ወደ 393 ቢሊየን ዶላር ከፍ በማለቱ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር ለመባል በቅቷል።

የዳታ አስተዳደር ኩባንያ ባለቤቱ አሊሰን በዚህ ፍጥነት ተምዘግዝጎ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር መሆኑ ብዙዎችን ማስገረሙን ብሉምበርግ ዘግቧል።

የኩባንያው የአክሲዮን ዋጋ ዛሬ ማለዳ ላይ በ40 በመቶ ከፍ ማለቱም ተነግሯል።

‎All in one place

  new year Happy a new year all Ethiopians 2018E.C
10/09/2025

new year
Happy a new year all Ethiopians 2018E.C

ኖርዌይ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈች !በአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ኖርዌይ ከ ሞልዶቫ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ 11ለ1 በሆነ ሰፊ ውጤት ማሸነፍ ችላለች። በጨዋታው ኤርሊንግ ሀላንድ አምስት ጎ...
09/09/2025

ኖርዌይ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈች !

በአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ኖርዌይ ከ ሞልዶቫ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ 11ለ1 በሆነ ሰፊ ውጤት ማሸነፍ ችላለች።

በጨዋታው ኤርሊንግ ሀላንድ አምስት ጎሎችን ከመረብ ሲያሳርፍ ቴሎ አስጋርድ አራት ጎሎችን አስቆጥሯል።

ቀሪዎቹን የኖርዌይ ግቦች ማርቲን ኦዴጋርድ እና ሆርን ማህሬ ከመረብ አሳርፈዋል።

በሌላ ጨዋታ ፖርቹጋል ከ ሀንጋሪ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችላለች።

የፖርቹጋልን የማሸነፊያ ግቦች ሮናልዶ ፣ በርናርዶ ሲልቫ እና ካንሴሎ ሲያስቆጥሩ ለሀንጋሪ ቫርጋ 2x ከመረብ አሳርፏል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን 1️⃣4️⃣1️⃣ኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።

ፈረንሳይ በበኩሏ ከአይስላንድ ያደረገችውን ጨዋታ በኪሊያን ምባፔ እና ባርኮላ ግቦች 2ለ1 አሸንፋለች።

ከሰርቢያ ጋር ጨዋታዋን ያደረገችው እንግሊዝ በሀሪ ኬን ፣ ማዱኬ ፣ ኮንሳ ፣ ማርክ ጉሂ እና ማርከስ ራሽፎርድ ግቦች 5ለ0 አሸንፋለች።


TIKVAH SPORT Image
All in one place

Address

Addis
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when All in one place posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share