የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት The B/G/R/State Militia Office

የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት
The B/G/R/State Militia Office, News & Media Website, Benishangul Gumuz, Addis Ababa.

ብሔራዊ አገራዊ  ክብርን ማስከበር እና የሀገር ሉዐላዊነትን መጠበቅና ማስጠበቅ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታ እንደሆነ ተገለጸ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጥቅምት 18/20...
28/10/2024

ብሔራዊ አገራዊ ክብርን ማስከበር እና የሀገር ሉዐላዊነትን መጠበቅና ማስጠበቅ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታ እንደሆነ ተገለጸ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም (አሶሳ) ለ 2017 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የሀገር መከላከያ ምልመላ እየተካሄደ ነው። ምልመላውን በተሳካ ሁኔታ በማከናወን ክልሉ የተሰጠውን ኮታ መሸፈን እንዲችል ትዕዛዝ ተላልፏል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ መከላከያ ሰራዊት የ2017 በጀት አመት የመጀመርያ ዙር ምልመላ ጀምሯል፣ በዲሲፕሊን፣ በታማኝነት እና በጠንካራ ደረጃ የክልሉ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና ባለሙያዎች ይህንን ሂደት እንዲደግፉና እንዲቆጣጠሩ ስምሪት ተሰጥቷል።

የክልሉ ሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም መንገሻ በዞኖችና ወረዳዎች የሚሰማሩ አመራርና ባለሙያዎችን ለምልመላው ስኬታማነት የማስተባበር ጥረቶችን እንዲመሩ መመሪያ ሰጥተው በሥርዓት የተሞላ አካሄድ ማከናወን እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ክቡር አቶ ቢንያም መንገሻ እንዳሉት ብሔራዊ አገራዊ ክብርን ማስከበር እና የሀገር ሉዐላዊነትን መጠበቅና ማስጠበቅ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታ እንደሆነ ገልፀው አሁን ላይ የሚደረገው ምልመላ የኮታ ጉዳይ ሳይሆን የኢትዮጵያን የአንድነት፣ የዲሲፕሊን እና የማይናወጥ የሀገር ፍቅር እሴቶችን የሚያንፀባርቅ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት ለማፍራት ያለንን አገራዊ ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳያል። በጋራ፣ የወደፊት ሰላምና ደህንነትን እንገነባለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

መረጃው የክልሉ ሠላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ ነው።

የዞኑን ሰላም አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለማስቀጠል በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።የአሶሳ ዞን የህግ ማስከበር ግብረ- ሀይል ባምባሲ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ ከ...
26/10/2024

የዞኑን ሰላም አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለማስቀጠል በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።

የአሶሳ ዞን የህግ ማስከበር ግብረ- ሀይል ባምባሲ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ ከዘጠኙ ወረዳ ከተዋቀረው ግብረ-ሀይል ጋር በመሆን በባለፉት ሶስት ሳምንታት የዞኑን ሰላም ለማስቀጠል የሰራቸውን የፀጥታና የህግ ማስከበር ስራ ገምግሟል።

ጥቅል ሪፖርቱ በዞኑ ሰላም ግንባታና ፀጥታ መምሪያ በፀጥታ ዘርፍ ቡድን መሪ በአቶ ይምረው አለባቸው የቀረበ ሲሆን ከሪፖርቱ በተጨማሪ በ2017 አንደኛ ዙር የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ምልመላ ዙሪያ ውይይት ተደርጓበታል።

በሌላ በኩል ከልመናና ተረጅነት አስተሳሰብን ማስወገድ ለብልጽግና ፓርቲ ጉዞ ያለው ፋይዳ የሚል መነሻ ሰነድ እና በክልሉ ሰላም ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋም እየተሰራ ባለው ገቢ አሰባሰብ ስራ በሚመለከት ተግባራዊ ለማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በኩል ገለጻ ተደርጓል።

የአሶሳ ዞን ዋና አስዳዳሪ አቶ እንድሪስ መሀመድ፦ የዞኑን ሰላም ለማስቀጠል በተዋረድ የተዋቀረው ህግ የማስከበር ግብረ-ኃይል በሶስት ሳምንት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ሰፊ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

በተለይ ህገ- ወጥ የሰውና መሳሪያ ዝውውር መከላከልና መቆጣጠርን ጨምሮ በህግ ማስከበርና ወንጀል ቁጥጥር ረገድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ለአብነት አንስተዋል።

አሁን ላይ ያለው ሰላም ወደ ኋላ እንዳይመለስ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በተለይ የህግ በላይነትን ከማረጋገጥና ህገ-ወጥ የጦርና የሰው ዝውውር ከመከላከል እንዲሁም የፀጥታ መረጃን ከማጠናከር ጀምሮ በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን እንደ ዞን ከተረጅነት አስተሳሰብ ለመውጣት የተጀመረውን ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አመራሩ ለጉዳዩ ትርጉም ሰጥቶ ቁርጠኛ ሁኖ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብሔራዊ ተጠባባቂ ሀይል ጽ/ቤት ኃላፊ ኮለኔል ታምራት ኤርጴሳ በበኩላቸው፦የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት የሃገር ዳር ድንበርን፣ አንድነትን፣ ሰላምን እና የኢትዮጵያዊያንን ክብር ለማስጠበቅ የተቋቋመ ሃይል መሆኑን አስታውሰዋል።

በመሆኑም የ2017 የአንደኛ ዙር የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል ምልመላ ከጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ,ም ጀምሮ ምዝገባ እንደሚጀመር ገልጸው ወጣቱ የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊትን በመቀላቀል ለሀገር አንድነትና ሉዓላዊነት መከበር የድርሻውን እንድወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

ዞኑ የልማት ኮሊድር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና የውጭ ዜጎች የሚንቀሳቀሱበት በመሆኑ የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት ህብረተሰብ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ጥብቅ የሆነ የክትትልና የቀጥጥር ስራ እየተሠራ እንደሚገኝ በመግለጽ ህብረተሰቡ ህጋዊ ስርዓትን በመከተል ለሀገርን ሰላምና ለዜጎች ደህንነት የበኩሉን ኃላፊነት እንድወጣ ያሳሰቡት ደግሞየአሶሳ ዞን የህግ ማስከበር ግብረ-ኃይል ሰብሳቢ ኮለኔል ወልዴ ለማ ናቸው።መረጃው የአሶሳ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነው።

"በፈተናዎች ውስጥ እየተገነባ የመጣ ሠራዊት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሚከበረው 117ኛው የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!እንደሚታወቀው ጀግናው የሀገር ...
25/10/2024

"በፈተናዎች ውስጥ እየተገነባ የመጣ ሠራዊት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሚከበረው 117ኛው የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!

እንደሚታወቀው ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን በየዘመናቱ የተቃጡብንን የውጭ ወረራዎች በብቃት በመመከት እና የውጭ ተልዕኮ አስፈፃሚ ተላላኪዎችን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ሉዓላዊነታችንን ያስከበረ፤ ክብራችንንም ከፍ ያደረገ ድንቅ ሠራዊት ነው።

ይህ ድንቅ ሠራዊት የተለያዩ ዓለም-አቀፍ የሠላም ማስከበር ተልዕኮዎችን ተቀብሎ በብቃት በመፈፀም በታሪክ መዝገብ ላይ ደማቅ አሻራውን ያሳረፈ፣ የሀገራችንን የተፅዕኖ ፈጣሪነት እና የተደማጭነት አቅም ከፍ ያደረገ ምርጥ ሠራዊት ነው።

ሠራዊታችን ስለ ሀገር ሉዓላዊነት እና ስለ ዜጎች ክብር ሲባል ለሚከፍለው እጅግ ውድ መስዋዕትነት ያለንን የላቀ አክብሮት እና ገደብ የለሽ ምሥጋና በራሴ፣ በክልሉ መንግሥት እና ህዝብ ስም እየገለፅኩኝ ለሠራዊታችን ያለንን የማይናወጥ አጋርነት የበለጠ አጠናክረን እንደምናስቀጥል በዚህ አጋጣሚ ለማረጋገጥ እወዳለሁ!!

የላቀ ክብር እና ምሥጋና ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን!!!

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ ስምሪት ሪፖርት ግምገማ አደረገ።(ጥቅምት 14/2017ዓ.ም አሶሳ) የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት እና የአሶሳ ዞን ሚሊሺያ ጽ/ቤት በጋራ በመሆን በአሶ...
24/10/2024

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ ስምሪት ሪፖርት ግምገማ አደረገ።

(ጥቅምት 14/2017ዓ.ም አሶሳ) የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት እና የአሶሳ ዞን ሚሊሺያ ጽ/ቤት በጋራ በመሆን በአሶሳ ዞን እና በመተከል ዞን ስር ባሉ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳድሮች በተሰጠው ስምሪት በዛሬው ዕለት የማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማ ተደርጓል ።

ስምሪቱ በዋናነት ያተኮረው በ1ኛ ሩብ ዓመት የሚከናወኑ ተግባራቶችን በመለየትና በቸክሊስት በማስደገፍ የታችኛውን መዋቅር ድጋፍና ክትትል በማድረግ የተቋሙን የአፈፃፀም ደረጃ የተሻለ ለማድረግ ያለመ ነው።

በስምሪቱ ወቅትም የሚሊሺያ አባላቶች በስነ_ምግባርና በስነ ልቦና የታነፁ እንዲሆኑ ከማድረጉም ባሻገር በየተቋሙ የሚስተዋሉ የአፈፃፀም ክፍተቶችን ለማስተካከል በቂ ግንዛቤ የተሰጠበት ስምሪት እንደነበርም በቀረበው ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል ።

እንዲሁም በሪፖርት ግምገማው ወቅት ከተነሱት ነጥቦች መካከል ወረዳ ላይ ባለው የጽ/ቤቱ መዋቅሮች የሚሰጠው ትኩረት በቂ ባለመሆኑ የሚመለከታቸው ባለ ድርሻ ለተቋሙ ልዩ ትኩረት በመስጠት የበኩላቸውን ድርሻም እንዲወጡ ጠቁመዋል ።

በመተከል ዞንም በነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ ቸክሊስት በቂ ግንዛቤ የተፈጠረበትና ወደ ተሻለ ስራ ሊያስገባ የሚችል መሆኑን በቀረበው ሪፓርት ለመረዳት ተችሏል ።

የተሰጠው ስምሪት የተቋማቱ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን የሚሞላና በቀጣይ ወደ ስራ ሊያስገባ የሚችል ድጋፍና ክትትል እንደነበር ተገልጿል ።

በዕለቱም የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ እስማኤል አብዱረህማን እና ስምሪት የተሰጣቸው እንዲሁም ባለ ድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የተስተዋሉ የአፈፃፀም ክፍተቶችንና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት የጋራ አቅጣጫ በማስቀመጥ የሪፓርቱ ግምገማው ተጠናቋል ።

ጥቅምት 14/2017ዓ.ም
አሶሳ

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ።ጥቅምት 13/02/2017ዓ.ም አሶሳ የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት በ2017ዓ.ም በጀት ዓመት በ1ኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተ...
23/10/2024

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ።

ጥቅምት 13/02/2017ዓ.ም አሶሳ
የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት በ2017ዓ.ም በጀት ዓመት በ1ኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራቶችን ሪፖርት በማጠናከር በዛሬው ዕለት ግምገማ አድርጓል።

የ1ኛ ሩብ ዓመቱ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በጽ/ቤቱ የዕቅድ ዝግጅት ዳይሬክቶሬት በሆኑት በአቶ ታደሰ አለሙ አማካኝነት ቀርቦ የማኔጅመንት አባላቱ በቀረበው ሪፓርት ላይ ውይይት አድርገዋል።

በዕለቱም የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ እስማኤል አብዱረህማን የተገኙ ሲሆን ተቋሙ በቀጣይ በሚሰራባቸው የትኩረት ነጥቦችና ቅድሚያ በሚሰጣቸው አንኳር ነጥቦችን በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል ።

ጥቅምት 13/02/2017ዓ.ም

አሶሳ

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት እና የአሶሳ ዞን ሚሊሺያ ጽ/ቤት ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን በተዘጋጀው ቸክሊስት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።መስከረም 24/2017ዓ.ም አሶሳ የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ያዘ...
04/10/2024

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት እና የአሶሳ ዞን ሚሊሺያ ጽ/ቤት ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን በተዘጋጀው ቸክሊስት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።

መስከረም 24/2017ዓ.ም አሶሳ የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ያዘጋጀውን ቸክ ሊስ ወደ ወረዳ ለማውረድ ከአሶሳ ዞን ሚሊሺያ ጽ/ቤት ጋር በመሆን ግምገማ አድርገዋል።

የስምሪቱ ቡድን መሪ የሆኑትየክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት የፀጥታ መረጃ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አልባቅር ሙሳ የተዘጋጀውን ቸክሊስት በማቅረብ ለሚሰማሩ የክልሉ እና ለዞኑ ባሙያዎች ገለፃ አድርገዋል።
በዕለቱም የዞኑ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱረዛቅ አሻይብ የቀረበው ቸክሊስት ወቅታዊና ሊያሰራ የሚችል መሆኑን አስረድተዋል።

የስምሪት ቡድኑም በተዘጋጀው ችክ ሊስት መሠረት የሚሰማሩ አካላት ተጨባጭ ስራ ሰርተው እንዲመጡ አሳስበዋል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አንኳር ነጥቦች በመለየት ለባለሙያዎች የስራ ስምሪት ሰጠ።አሶሳ መስከረም 23/216ዓ.ም ጽ/ቤቱ በ2017ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድ በመነሳት ...
03/10/2024

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚሊሺያ ጽ/ቤት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አንኳር ነጥቦች በመለየት ለባለሙያዎች የስራ ስምሪት ሰጠ።

አሶሳ መስከረም 23/216ዓ.ም ጽ/ቤቱ በ2017ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድ በመነሳት ትኩረት በሚፈልጉና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ተግባራቶች ለይቶ በማውጣትና በቸክ ሊስት በማካተት በጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ እስማኤል አብዱረህማን አማካኝነት ኦረንቴሽን በመስጠት ለጽ/ቤቱ ባለሙያዎች የስራ ስምሪት ተሰጥቷል ።

ባለሙያዎቹ ወደ ዞንና ወረዳዎች በሚሄዱበት ወቅት በተዘጋጀው ቸክሊስት መሠረት ውጤታማ ስራ ሰርተው እንዲመጡና ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለስራው ውጤታማነት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት በ2ኛ ሩብ ዓመት በሚከናወኑ አንኳር ነጥቦች ላይ ውይይት አደረገ።አሶሳ (መስከረም 21/01/2017ዓ.ም) የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ እስማኤል አብዱረህማን እና ...
01/10/2024

የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤት በ2ኛ ሩብ ዓመት በሚከናወኑ አንኳር ነጥቦች ላይ ውይይት አደረገ።

አሶሳ (መስከረም 21/01/2017ዓ.ም) የክልሉ ሚሊሺያ ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ እስማኤል አብዱረህማን እና ማኔጅመንት አባላት በቀጣይ ሩብ ዓመት ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ በሚሰራቸው አንኳር ነጥቦች ላይ ውይይት አድርገዋል ።

በ2017ዓ.ም ከዓመታዊ የተቋሙ ዕቅድ በመነሳትና በ2ኛ ሩብ ዓመት በሚከናወኑ ተግባራትን ነቅሶ በማውጣት ለተቋሙ ሁለንተናዊ ለውጥና የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የሚረዳ መሆኑን የማኔጅመንት አባላቱ በመወያየት ዕቅዱን እስከታችኛው የጽ/ቤቱ መዋቅሮች ተደራሽ በማድረግ አፈፃፀሙን በትኩረት መከታተል እንደሚገባ አመላክተዋል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ እስማኤል አብዱረህማን እንደገለፁት ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ሁለንተናዊ ለውጥና የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ እንዲችል የባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ በመሆኑ በቅንጅትና በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ገልፀዋል።

በመጨረሻም በቀጣይ ሩብ ዓመት የሚከናወኑ አንኳር ተግባራቶችን ከዓመታዊ እቅዱ ላይ ነቅሶ በማውጣት እስከታችኛው መዋቅር በድጋፍና ክትትል ለማውረድ የጋራ መግባባት በመያዝ ውይይቱ ተጠናቋል ።

መስከረም 21/01/2017ዓ.ም

አሶሳ

ግብፅ አፍሪካን ሊያምስ ከሚችለው ድርጊት ተቆጥባ ወደ ትክክለኛው መስመር እንድትመለስ ኢትዮጵያ ጠየቀችበዓባይ ጉዳይ ኢትዮጵያ ለግብጽ ምላሽ እና መፍትሔ ሰጥታለች።ግብፅ የኢትዮጵያን በተፈጥሮ ...
30/09/2024

ግብፅ አፍሪካን ሊያምስ ከሚችለው ድርጊት ተቆጥባ ወደ ትክክለኛው መስመር እንድትመለስ ኢትዮጵያ ጠየቀች

በዓባይ ጉዳይ ኢትዮጵያ ለግብጽ ምላሽ እና መፍትሔ ሰጥታለች።

ግብፅ የኢትዮጵያን በተፈጥሮ ሀብቷ ተጠቅማ የመልማት መብቷን የሚጋፋ አቋም ስለመያዟ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ምክትል ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ በድርጅቱ 79 ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር አስታውቀዋል።

እኛ የምናምነው ኢትዮጵያ በዓባይ ምክንያት ከግብፅ ጋር ጥብቅ ትስስር እንዳላት ነው ያሉት አምባሳደር ዮሴፍ ዓባይ የሁለቱን ሀገራት ሕዝቦች በልማት የሚያስተሳስር የጋራ ሀብት መሆኑን ኢትዮጵያ እንደምታምን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በማንኛውም መልኩ ግብፅን ችግር ውስጥ የሚያስገባ እና የመልማት መብቷን የሚገድብ እንቅስቃሴ እና የጥላቻ ተግባር የመፈጸም ፍላጎት እንደሌላትም አምባሳደሩ አስታውሰዋል።

በመንግስታቱ ድርጅት ጉባዔ ላይ የግብጽ ተወካይ ያሰሙት ንግግር የአንድን ሀገር የተፈጥሮ ሀብቷን ተጠቅማ የመልማት መብቷን እና ይህን የሚደነግገውን ዓለም አቀፍ መርህ የሚቃረን ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በዓባይ ወንዝ ላይ የገነባው በራሱ ጥረት እንደሆነ ጠቅሰው ግድቡ መሰረታዊ የሆነውን የመብራት አገልግሎት ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያቀርብ እንደሆነም ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈም ግድቡ በአሁኑ ጊዜ የቀጣናውን ሀገራት በኃይል አቅርቦት ማስተሳሰር መጀመሩንም ተናግረዋል።

የዓባይ ወንዝ አንድ ሦስተኛውን የኢትዮጵያ ክፍል የሚያካልል እና ከ75 በመቶ በላይ የውሃ ምንጩ ከኢትዮጵያ ቢሆንም ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት በምግብ ዋስትና እና በኃይል አቅርቦት ችግሮች ስትፈተን መኖሯን ገልጸዋል።

120 ሚሊዮን ገደማ ከሚሆነው ሕዝቧ ከግማሽ የማያንሰው በንጹህ ውሃ እጥረት እና በኃይል አቅርቦት ችግር ውስጥ እየኖረ ይህን ችግር ለመፍታት እጇን አጣምራ ትቀመጥ ማለት ፍትሃዊነት እንዳልሆነም ተናግረዋል አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ።

ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለ ህይወት መሥራት ቅድሚያ ተግባራችን ነው ያሉት አምባሳደሩ ይህን ለማድረግ ግን ኢትዮጵያ የማንንም የመልማት መብት እንደማትገፋ እና የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን በጋራ የመጠቀም መርህን እንደምታከብር ገልጸዋል።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ግን ኢትዮጵያ እና የታችኛው የናይል ተፋሰስ ሀገራት ትልቁን ድርሻ ከሚያበረክቱበት የናይል ወንዝ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ተደርገው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

ለናይል ወንዝ ጠብታ ውሃ የማታበረክተው ግብፅ የሌሎችን በውሃው የመጠቀም መብትን ስትጋፋ ከመኖሯም በላይ የጋራ አጠቃቀምን የተመለከቱ ትብብሮችን እየተቃወመች እንደሆ ነው አምሳደር ዮሴፍ የገለጹት።

ግብፅ ወንዙን የሚያመነጩትን ሀገራት በተጋፋ መልኩ በቅኝ ግዛት ውል ውሃውን ለብቻዋ ስትጠቀም መኖሯን አስታውሰው፣ ነገር ግን ኢትዮጵያ ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት ወንዙን በትብብር እና በፍትሃዊነት እንዲጠቀሙ የጀመረችውን ጥረት ትቀጥላለች ብለዋል።

ግብፅ ዘመኑ ያለፈበትን የቅኝ ግዛት ውሎችን ትታ ሁሉንም ተጠቃሚ ሊያደርግ ወደሚችለው ትብብር እንድትመጣ ጥሪ አቅርበው፣ ይህን አውነታ የምትቀበልበትና ትብብር ተጠቃሚ እንደሚያደርጋት የምትረዳበት ጊዜ ይመጣል ብለው እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የጋራ የሆነውን ሀብት ለብቻዬ ካልተቆጣጠርኩ የሚለው ያፈጀና ያረጀ አስተሳሰብ እንደማይሠራ የጠቀሱት አምባሳደሩ፣ ኢትዮጵያ ግብፅ አፍሪካን ሊያምስ ከሚችለው ድርጊት ተቆጥባ ወደ ትክክለኛው መስመር እንድትመለስ ጥሪ ታቀርባለች ብለዋል።

Address

Benishangul Gumuz
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሚሊሺያ ጽ/ቤት The B/G/R/State Militia Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share