Dominant News

Dominant News Dominant Records

Dominant News is a digital news channel delivering global headlines, war updates, politics, trending stories, and youth-focused reports — on YouTube, TikTok, and Facebook.

https://youtu.be/qDFK2qWcUGc
05/06/2026

https://youtu.be/qDFK2qWcUGc

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

https://youtu.be/VFPfb1_9wCc
05/06/2026

https://youtu.be/VFPfb1_9wCc

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

የአለልኝ አዘነ ገዳዮች ተብለው የ16 እና 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ግለሰቦች፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።" የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ...
05/06/2026

የአለልኝ አዘነ ገዳዮች ተብለው የ16 እና 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ግለሰቦች፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።"

የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ውሳኔ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ሀዘን እና ድንጋጤ ዳርጓል

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ማህበረሰብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዘነው እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ ሰርስሮ የገባው የሟች አለልኝ አዘነ የፍትሕ ሂደት፣ አሁን ላይ አሳዛኝ እና አነጋጋሪ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

ባለፈው ጊዜ በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና ሉንጎ ሉቃስ፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የሟች ቤተሰቦች አረጋግጠዋል።

ይህ ውሳኔ ቤተሰቡን ከዚህ ቀደም ከነበሩበት ሀዘን ባሻገር፣ ለከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ እና ብስጭት ዳርጓቸዋል። የቤተሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ወንጀሉ ተፈጽሞ፣ ጥፋተኞች ተለይተውና በፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ሰበብ እንዲህ በነፃ መለቀቃቸው ተቀባይነት የሌለው እና የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያጠይቅ ሆኖ አግኝተውታል።

በችሎቱ ውሎ ወቅት የነበረው ውጥረት፣ የቤተሰቡ ለቅሶ እና ሰቆቃ፣ እንዲሁም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የነበራቸው የመጨረሻ ተስፋ መሟጠጡ መላውን የፍትህ ናፋቂ ማህበረሰብ በእጅጉ አሳዝኗል።

ቤተሰቡ እንደገለጸው፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቦታ እርባምንጭ ሆኖ ሳለ፣ የፍርድ ሂደቱ ወደ ወላይታ ሶዶ ተዛውሮ የወሰደው ቅርፅና ውጤት ለቤተሰቡ ድርብ ስቃይ ሆኗል።

ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ እንደሚችል እየተነገረ ነው። በተለይም የወንጀል ድርጊት ተረጋግጦ በነበረበት መዝገብ ላይ እንዲህ ያለ የይግባኝ ውሳኔ መሰጠቱ፣ በፍትሕ ተቋማት ላይ ያለው የመተማመን ቀውስ እንዲባባስ ማድረጉ አልቀረም።

የሕግ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት፣ ጉዳዩ በሰብአዊ መብት እና በሕግ የበላይነት መርህ መሠረት በሰፊው ሊጤን የሚገባው ሆኗል።

የሟች ቤተሰብ አባላት በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ይገኛሉ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው እንዲቆም እና የፍትሕ ጥያቄውን እንዲያቀናጅ ጥሪ አቅርበዋል።

©️ቤተሰብ

ጉርሻ Page

ለኮሪደር ልማት አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበረ የኤሌክትሪክ ገመድ የሰረቀ ግለሰብ በፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ ተያዘ።***አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ በረ...
05/06/2026

ለኮሪደር ልማት አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበረ የኤሌክትሪክ ገመድ የሰረቀ ግለሰብ በፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ ተያዘ።
***
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ በረከት አረጋ የተባለ ግለሰብ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመው በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ጉስቋም ቅድስት ማርያም አካባቢ ከምሽቱ 4:00 ሠዓት ላይ ነው።

ተጠርጣሪው በሠዓቱ ለኮሪደር ልማት ተዘርግቶ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብል በመጋዝ ቆርጦ በመውሰድ በውሃ ፍሳሽ መውረጃ ቱቦ ውስጥ ገብቶ ለመሰወር ቢሞክርም በወቅቱ ስራ የነበሩ የፖሊስ አባላት ተከትለው በመግባት ሁለት ሰአት በፈጀ ፍለጋ ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጦር ስር በማዋል አስፈላጊው ምርመራ እየተጣራበት መሆኑን የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ገልጿል ።

ወንጀል ፈፃሚው በወቅቱ ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር እንዲውል ህብረተሰቡ ከፖሊስ ጋር በመሆን አስፈላጊውን ትብብር ማድረጉ የሚያስመሰግን ተግባር ነው ያለው ፖሊስ ህዝብ ሲተባበር ወንጀል ፈጻሚዎችን በቀላሉ ለህግ ማቅረብ እንደሚቻልም አመላክቷል ብሏል።

የክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያም ከአስተዳደሩ ጋር በመነጋገር የፍሳሽ መውረጃ ትቦ ውስጥ ገብተው ተጠርጣሪውን ለያዙት አባላት ማበረታቻና ሽልማት እንደሚሰጥም አሳውቋል።
*
ዘገባ፦ ም/ሳጅን ሳምሶን ሠለሞን
*

Via : Addisababapolice

05/06/2026

Address

Addis Ababa

Website

https://www.youtube.com/@DominantNews, https://www.youtube.com/@DominantS

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dominant News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dominant News:

Share