Dominant News

Dominant News Dominant Records

Dominant News is a digital news channel delivering global headlines, war updates, politics, trending stories, and youth-focused reports — on YouTube, TikTok, and Facebook.

ዜና: በነገው ዕለት አዲስ አበባ ይገባሉ ተብለው የሚጠበቁት የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር በሁለቱ የኢትዮጵያ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደርጋሉ ተባለከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢ...
15/12/2025

ዜና: በነገው ዕለት አዲስ አበባ ይገባሉ ተብለው የሚጠበቁት የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር በሁለቱ የኢትዮጵያ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደርጋሉ ተባለ

ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝተው በ #ኢንቨስትመንት እና በ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ ተጠቁሟል

ህንድ በመጪው የፈረንጆቹ 2026 የብሪክስ ጉባዔን በሊቀመንበርነት ለመምራት በዝግጅት ላይ ባለችበት ወቅት፣ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ታሪካዊ የተባለለትን ጉብኝት ከታህሳስ 7 እስከ 8/2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚያደርጉ የኤዥያን ኒውስ ኢንተርናሽናል ዘግቧል።

ከጉብኝቱ ቀደም ብሎ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ትኩረት በሚሰጥባቸው የሁለትዮሽ ግንኙነት ጉዳዮች ማለትም በኢንቨስትመንት፣ በግብርና፣ በማዕድን ልማት፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት እና በሳይበር ደህንነት ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ በጉብኝታቸው ወቅት በተጨማሪም በኢትዮጵያ በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ላይ ንግግር እንደሚያደርጉም ይጠበቃል።

አምባሳደር ራይ፣ ጉዞውን የሁለትዮሽ ትብብርን የሚያጠናክርና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማሻሻያ እንዲሁም የብሪክስ አጀንዳዎችን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ቅንጅት የሚያጎለብት “በጣም ታሪካዊ ወቅት” ሲሉ ገልጸውታል።

አያይዘውም “ህንድ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየ፣ ጥልቅና ወዳጃዊ ግንኙነት ያላቸው ሁለት የስልጣኔ ሀገራት ናቸው” ያሉ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ባለፉት 15 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን የሚጎበኙ የመጀመሪያው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ ብለዋል።

Via : Addis Standard Amharic

እዞም ውልቀሰባት ዝኽሰሱሎም ዝርዝር ገበናት------እዚኦም፡ ዘቤታዊ ዓመጽ፡ ብተደጋጋሚ ሰኺርካ መኪና ምዝዋር፡ ምዝማት፡ ምጭዋይ ህጻናት፡ ምፍርራሕ ግብረሽበራ፡ ብብረት መጥቃዕቲ ምፍጻም፡ ዝ...
14/12/2025

እዞም ውልቀሰባት ዝኽሰሱሎም ዝርዝር ገበናት
------
እዚኦም፡ ዘቤታዊ ዓመጽ፡ ብተደጋጋሚ ሰኺርካ መኪና ምዝዋር፡ ምዝማት፡ ምጭዋይ ህጻናት፡ ምፍርራሕ ግብረሽበራ፡ ብብረት መጥቃዕቲ ምፍጻም፡ ዝተሰርቀ ንብረት ምቕባል፡ ትእዛዝ ቤትፍርዲ ዘይምኽባርን ዘይሕጋዊ ዝውውር ገንዘብን ይርከብዎም።

እዚ ብምኒስትሪ ድሕነት ሃገር ዝተዘርግሐ ኰይኑ፡ ኣካል ናይቲ ኣብታ ሃገር ኣብ ልዕሊ ዘይሕጋውያን ስደተኛታት ዝካየድ ዘሎ ሰፊሕ ስጕምቲ እዩ።

Via : BBC

"አዲስ ዜና! ተወዳጁ አርቲስት ጋሽ ሰለሞን በቅርቡ በተካሄደው የመኪና ሽልማት እንዳሸነፉ የሚታወቅ ሲሆን ብሩክ ሪል እስቴትም መኪናውን ለማስረከብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።አርቲስቱም ...
13/12/2025

"አዲስ ዜና! ተወዳጁ አርቲስት ጋሽ ሰለሞን በቅርቡ በተካሄደው የመኪና ሽልማት እንዳሸነፉ የሚታወቅ ሲሆን

ብሩክ ሪል እስቴትም መኪናውን ለማስረከብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

አርቲስቱም ሽልማቱ እውን እንዲሆን ላደረጉት ለሁሉም ውድ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ታላቅ ምስጋና አቅርቧል።

"ይህን ሁሉ እንዲሳካ ላደረጋችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ፈጣሪ ይስጥልኝ!" ብለዋል።

ነገር ግን ጋሽ ሰለሞን ከሽልማት አሰጣጡ ሂደት ጋር በተያያዘ አንድ ልብ የሚነካ ውሳኔ አስተላልፈዋል።

"እኔ ግን የዚህ ነገር ትልቅ ጀማሪና ጠንሳሽ ውድ ልጄ አዶናይ በተገኘበት ብቻ የመኪና ሽልማቱን ለመቀበል ወስኛለሁ።"

በመጨረሻም አርቲስቱ "እግዚአብሔር ልጆቿንና ህዝቦቿን ይባርክ!" በማለት መልካም ምኞቷቸውን ገልፀዋል።"

Via ጉርሻ page

ውድ ዋጋ ያላቸው ስልኮች ላይ ትኩረት በማድረግ የቅሚያ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ከ30 አይፎን ስልኮችን ጋር በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን  የአዲስ አበባ ፖሊስ ...
13/12/2025

ውድ ዋጋ ያላቸው ስልኮች ላይ ትኩረት በማድረግ የቅሚያ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ከ30 አይፎን ስልኮችን ጋር በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 4:00 ሰዓት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሲ.ኤም. ሲ 5 መቶ ቤቶች አካባቢ አንድ ግለሰብ የዋጋ ግምቱ 100ሺ ብር የሚያወጣ ኤስ 23 አልትራ ሳምሰንግ ሞባይል እንደተቀሙ ለሲ. ኤም.ሲ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታሉ፡፡

ፖሊስ ጣቢያው የተፈፀመውን ወንጀል መነሻ በማድረግ በቴክኖሎጂ ጭምር በመደገፍ ባደረገው ክትትልና ወንጀሉ ከተፈፀመበት ስፍራ ባሰባሰበው መረጃ መሰረት በማድረግ ባደረገው ክትትል ወንጀሉ በተፈፀመ በሁለተኛው ቀን የግል ተበዳይን ሞባይል ስልክ የቀሙትን ምስጋናው አለማየሁ፣ ሄኖክ ወርቁ እና ኢዮብ ወርቁን በቁጥጥር ስር ያውላል።

በቀጣይነት በተሰራ ምርመራን የማስፋት ተግባርም በክፍለ ከተማው ወረዳ 3 አያት ዞን አምስት ኮንዶሚኒየም 3ኛ ፎቅ ላይ ምስጋናው አለማየው የተባለው ተጠርጣሪ ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት በህግ አግባብ በተደረገ ብርበራ የግል ተበዳይን ስልክ ጨምሮ 41 ስማርት ስልኮች ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ለውጡን ተከትሎ ፖሊስ በስራው አጋዥ የሆኑ ልዩ ልዩ ቴክኖሎጂዎችን ስራ ላይ ማዋሉን ገልጾ በቴክኖሎጂ በመደገፍ በተደረገ ክትትል ወንጀል ፈፃሚዎቹን በቀላሉ በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለ አስታውቆ ከዚህ በፊት ስልክ የተሰረቀባቸው ግለሰቦች ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ ስልካቸውን እንዲለዩ መምሪያው ጥሪውን አስተላልፏል።

አያይዞም ፖሊስ ባስተላለፈው መልዕክት መኖሪያ ቤት የሚያከራዩ ግለሰቦች ሆኑ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ማህበራት የተከራዮችን ማንነት የማጣራት ኃላፊነት እንዳለባቸው ተገንዝበው ግዴታቸው በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
*
ዘገባ፦ ዋና ሳጅን አዳነ ደስታ

Via Addis Ababa Police

የ   ጸጥታ ቢሮ ከማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ቲክቶከሮች ጋር ተወያየየአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ፣ የከተማዋን ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን በሚደረገው ጥረት፣ ከማኅበራዊ ሚ...
13/12/2025

የ ጸጥታ ቢሮ ከማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ቲክቶከሮች ጋር ተወያየ

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ፣ የከተማዋን ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን በሚደረገው ጥረት፣ ከማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች እና ከቲክቶከሮች ጋር የጋራ የንቅናቄ ውይይት ማካሄዱን አስታውቋል።

ውይይቱ የተካሄደው በታኅሣሥ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲሆን፣ በዲጂታል ዘመን የተሳሳተ መረጃ ስርጭት በሚያስከትለው የጸጥታ ስጋት ላይ ትኩረት ማድረጉ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ፣በመድረኩ ላይ መልዕክት ሲያስተላልፉ፣ ወቅታዊውን ጊዜ "የድህረ-እውነት" ዘመን በማለት የገለጹት ሲሆን፣ ሚዲያው የ"አራተኛው መንግሥት" ያህል ክብደት ባለበት ሁኔታ፣ የአጠቃቀሙን አግባብነት መገምገም ወሳኝ ነው ብለዋል።

ኃላፊዋ፣ አንቂዎቹ "ለአንድ ሃገር" በመቆምና አግባብነት በሌላቸው ጉዳዮች ላይ ከማተኮር ይልቅ፣ ለትውልድ የሚጠቅሙ የጋራ አስተሳሰቦችን በማስፋፋት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

ወ/ሮ ሊዲያ አክለውም "ለትውልድ ከማይጠቅሙ ሐሳቦች ወጥተን በአዲስ አስተሳሰብ በመገስገስ የአሁኑ ትውልድ የሚመራትን ሃገር አንድ በማድረግ አኩሪ ድል በሚመሰርት መልኩ" መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

ኅላፊዋ በአሁኑ ወቅት ያለው የፖለቲካ ንግግር “የኔነትን” ስሜት ላይ ሳይሆን፣ "የእኛነትን" አስተሳሰብ ይዞ የሚሠራ፣ "ነጠላ ትርክትን ትቶ ኢትዮጵያዊነት ላይ የሚያምንና ሁሉንም ብሔር በእኩልነት የያዘ የመንግሥት አሰራር" መኖሩን ጠቁመዋል።

የሚዲያ አንቂዎቹ በቀጣይ ሕግና ሥርዓትን አክብረው በትውልዱ ላይ መሥራት እንዳለባቸው አሳስበው፣ ቢሮው ከዲጂታል አንቂዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

በውይይቱ የተሳተፉት የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች በበኩላቸው፣ በትውልዱ አስተሳሰብ ላይ የተሻለ ንቃተ-ሕሊና ለመፍጠር እንደሚሠሩ ቃል ገብተዋል። የማኅበራቸው አካል የሆኑት አንቂዎች "የተሳሳተ አስተሳሰብ" ላይ ትኩረት በመስጠት፣ ሀገራዊና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት እንደሚሰሩም ገልጸዋል።

Via : Addis Standard Amharic

13/12/2025
13/12/2025

እንዲህም ኣለ እንዴ?

13/12/2025

ምን ኣስተያየት ኣላቹህ!?

የዓለም ዋንጫ ጀግና በህንድ መዲና! - ሊዮኔል ሜሲ በኮልካታ ሐውልት ቆመለት!ኮልካታ፣ ህንድ፡- የህንድ ከፍተኛ የእግር ኳስ ፍቅር በድጋሚ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ጎልቶ ታይቷል።የአርጀንቲና...
13/12/2025

የዓለም ዋንጫ ጀግና በህንድ መዲና! -
ሊዮኔል ሜሲ በኮልካታ ሐውልት ቆመለት!

ኮልካታ፣ ህንድ፡- የህንድ ከፍተኛ የእግር
ኳስ ፍቅር በድጋሚ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ጎልቶ ታይቷል።

የአርጀንቲናው አፈ ታሪክ እና የ2022 ፊፋ ዓለም ዋንጫ አሸናፊ የሆነው ሊዮኔል ሜሲ የደጋፊዎች ፍቅር መገለጫ የሆነ አዲስ ሐውልት በኮልካታ፣ ምዕራብ ቤንጋል ከተማ መቆሙ ተዘግቧል።

ይህ ያልተጠበቀ ክብር በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ በፍጥነት በመሰራጨት ትልቅ ውይይት ቀስቅሷል።

ኮልካታ ለዓመታት የህንድ የእግር ኳስ ማዕከል በመባል የምትታወቅ ሲሆን፣ የዓለም አቀፍ ክለቦችን እና ተጫዋቾችን የምትወድ ከፍተኛ ስሜታዊ የደጋፊዎች ስብስብ ባለቤት ነች። ይህ ሐውልት የከተማዋን ጥልቅ የእግር ኳስ ባህል እንደሚያንጸባርቅ የአካባቢው ዘጋቢዎች ይገልጻሉ።

ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት፣ የሜሲ ሐውልት መትከል የመንግስት ፕሮጀክት ሳይሆን፣ በተለይ በዓለም ዋንጫው ድል ማግኘቱን ተከትሎ፣ በሜሲ ደጋፊ ቡድኖች በገንዘብ ተደግፎና ተደራጅቶ የተከናወነ ነው።

ደጋፊዎች ሜሲን ለረጅም ጊዜ በትዕግስት እና በትህትና በመጓዝ ዓለም አቀፍ ክብርን በማግኘቱ ያከብሩታል፤ ይህም ለብዙ የህንድ ደጋፊዎች ትልቅ አዎንታዊ መልዕክት ያስተላልፋል ተብሏል።

የሐውልቱ ፎቶግራፎች እና ቪዲዮዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን የደረሱ ሲሆን፣ ስለ የእግር ኳስ ታላቅነት እና የአለም አቀፍ ስፖርት ባህሎች መተሳሰር ከፍተኛ ውይይት ፈጥረዋል። በጎ አስተያየት ሰጪዎች የደጋፊዎችን ፍቅር ሲያሞግሱ፣ ሌሎች ደግሞ እንዲህ ያለው ክብር የአገር ውስጥ ጀግኖችን ሊያጎላ ይገባል የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።

⚽️⚽️⚽️

🌴🌴🌴

Via : ጉርሻ page

ኤርትራ ከኢጋድ አገለለች‼የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል በ X ገፃቸው ባሰራጩት መረጃ አገሪቱ ራሷን ከኢጋድ አባል አገራት ህብረት ማግለሏን ይፋ አድርገል።ምክንያት ያሉት ነገ...
12/12/2025

ኤርትራ ከኢጋድ አገለለች‼

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል በ X ገፃቸው ባሰራጩት መረጃ አገሪቱ ራሷን ከኢጋድ አባል አገራት ህብረት ማግለሏን ይፋ አድርገል።

ምክንያት ያሉት ነገር በዝርዝር ባያስቀምጡም ኢጋድ በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራቱ ሀገሪቱን በብስጭት ለዚህ ውሳኔ እንዳበቃት ተንታኞች ግምታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።
#ዋሱመሐመድ

Address

Peter Street
Addis Ababa
M5V2H1

Website

https://www.youtube.com/@DominantNews, https://www.youtube.com/@DominantS

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dominant News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dominant News:

Share