06/01/2026
A little about "Christmas" (ገና)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና በመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩ አብይ በዓላት አንዱ የጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል "ገና" ነዉ።
"ገና" የሚለዉ ቃል ከጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ የተወረሰ ቃል እንደሆነና ትርጉሙም "ልደት" ማለት እንደሆነ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሐይማኖት አባቶች ይናገራሉ።
"ገና" የሰዉን ልጆች በጥንተ ተፈጥሮ የፈጠረው የእግዚአብሔር ልጅ (ኢየሱስ) ሰዉን ለማዳን ሰዉ ሆኖ የተፈጠረበት ቀን ሲሆን፣ በዓለ ልደት በየአመቱ የሚከበረው ታህሳስ 29 እና በዘመነ ዮሐንስ ግን የሉቃስ ጳጉሜ ስድስት ቀን ስለምትሆን ልደቱ ታህሳስ 28 ይዉላል።
በዚህ እለትም የገና በዓልን የምታከብረው ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የእስክንድርያ ቤተክርስቲያንም በደማቅ ስታከብር፣ በግብፅ፣ ኤርትራ፣ (በተለይ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች)፣ ሶሪያ፣ ህንድ፣ አርመን፣ ግሪክ እና ሩሲያ ያሉ ክርስትያኖች ገናን በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 (በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ደግሞ ታኅሣሥ 28) በደማቅ መልኩ ያከብሩታል።
👉 ኖቾ መልቲሚዲያም በማረሚያ ቤት ላሉት እና በተለያዩ የአለም ክፍሎች ለሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የገና በዓል እንዲሆን ይመኛል!
✍️ እስራኤል ግርማ (Ezra)
ምንጭ:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ 200 ዓ.ም። እና የተለያዩ........
ኖቾ መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን፣ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ።
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በተለያዩ የማህበራዊ ድህረ-ገፆቻችን ያገኙናል።
YouTube - http://www.youtube.com/
Tiktok - www.tiktok.com/
Telegram - https://t.me/+d0wR-A2xqk45YmQ0
page – Nocho Multimedia Production