Mihretab G/Hiwot

Mihretab G/Hiwot Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mihretab G/Hiwot, Digital creator, Addis Ababa.

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሣዊ ትምህርቶች በዲጂታል
ለሁሉም ምእመናን እንዲዳረስ
ፎለው ላይክ ሸር ማረጉን እንዳትረሱ
ስንል በትህትና እንጠይቃለን
ወስብኃት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክቡር ኣሜን

10/07/2025

AI-Powered Manufacturing: ’s Intelligent Factories
BMW is harnessing AI not only in its vehicles but also within its manufacturing plants.

10/07/2025


==========

የድንግል ማርያም እናት ቅድስት ሐና በሥርዓት አድጋ አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግሥት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት የዘር ሐረግ ከሆነው ከቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት፡፡ ቅዱሳኑ ኢያቄምና ሐና ተጋብተው ቢኖሩም ልጅ ስላልነበራቸው ወደ ቤተመቅደስ እየሔዱ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው ይለምኑት ነበር፡፡ ለቤተ መቅደስ መብዓ ሲያቀርቡም ለሊቀ ካህናቱ “እግዚአብሔር ብዙ ተባዙ በማለት የፈቀደውን ሕግ በእናንተ ላይ እንዳይፈጸም አድርጎ ልጅ የከለከላችሁ ኃጢአተኛ ብትሆኑ ነውና መብዓችሁን አልቀበልም” ብሎ ሳይቀበል ይመልሳቸው ነበር፡፡ ቅዱሳኑ እያዘኑ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ ዛፍ ሥር ተቀመጠው ሳለ እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲያጫውቱ ተመልክተው “ለወፎች እንኳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ለእኛ የምትሰጠን መቼ ነው?” ብለው እጅግ አምርረው አለቀሱ፡፡

“ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴትም ብንወልድ ውሃ ቀድታ መሶበ ወርቅ ሰፍታ፣ መጋረጃ ፈትላ፣ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን” ብለው ተሳሉ፡፡ ሊቀ ካህናቱም “እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ፤ ስዕለታችሁን ይቀበልላችሁ፤ የልቦናችሁን አሳብ ይፈጽምላችሁ” አላቸው። ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው፣ ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ኢያቄም ሰባቱን ሰማያት ሰንጥቃ ነጭ ወፍ ወርዳ በራሱ ላይ ስትቀመጥ ማየቱን ለሚስቱ ነገራት። ሐናም ነጭ ርግብ ወርዳ በማኅጸኗ ስትተኛ ማየቷን ነገረችው፡፡

እነርሱም እንዲህ ያለ ራእይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም። ይልቁንም ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን ብለው ሱባኤ ገቡ። አልጋ ለይተው፣መሬት ላይ ወድቀው እስከ ሰባት ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ ሰባት ቀን መልአኩ ተገልጦ ከሰው የበለጠች፣ ከመላእክት የከበረች፣ ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ በሩካቤ ሥጋ ተገናኙ ብሎቸው ተገናኙ። ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡ እመቤታችን እንደ ተፀነሰች ለቅድስት ሐና የአጎቷ ሞቶ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ደረሰች። እርሷም አስከሬኑን እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል አፈፍ ብሎ ተነሥቶ "ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሐየ ጽድቅ፤ ለአብ ሙሽራው፣ ለወልድ ወላዲቱ፣ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሃ ቤቱ፣ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ" ብሎ ሰገደላት፡፡ አይሁድም ይህ ተአምር ሲደረግ ቀንተው "ሳሚናስ ምን አየህ?” ቢሉት "ከሐና ማኅጸን የምትወለደው ሕፃን ሰማይ ምድርን አየርን የፈጠረውን አምላክ ትወልዳለች በማለት መላእክት ሲያመሰግኗት ሰማሁ" አላቸው፡፡
"እኔንም ከሞት ያነሣችኝ እርሷ ናት" አላቸው፡፡ አይሁድም "በል ተወው ሰማንህ" ብለው ለማጥፋት የሚችሉበትን ተንኮል መሽረብ ጀመሩ፡፡ ሐና በእርጅናዋ ጊዜ መጸነሷን የተመለከቱ ዘመዶቿ ተደስተው እየሔዱ ይጠይቋት ነበር፡፡ እመቤታችን ግንቦት አንድ ቀን ተወለደች፡፡ ሦስት ዓመት ሲሆናትም ታኅሣሥ ፫ ቀን ቤተ መቅደስ ገባች።

እምቤታችን በቃል ኪዳኗ ትጠብቀን። አሜን!!



#ተዋህዶ #ኦርቶዶክስ #ድንግል #ማርያም

10/07/2025

ባዓታ ለማሪያም *3*

የባዓታ ለማሪያም ረድኤት በረከቷ ምልጃና ፀሎቷ አይለየን @🙏🙏🙏

10/07/2025

❗ ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 በዚህች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ወርሃዊ በዓል ነው ምክንያቱም እርሷ ለእግዚአብሔር የስዕለት ልጅ ነበረችና።

🔷👉 ታዲያ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት ነው ብለን ብቻ ማለፍ ሳይሆን እንዴት እንደገባች ማወቅ ያስፈልጋልና አጠር አድርገን እንመለከታለን።

🔴👉 የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወላጅ እናት ቅድስት ሐና ትባላለች። እናታችን ቅድስት ሐናም አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግሥት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት።

🔴👉 እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፤ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሂደው ሲጸልዩ ሲያዝኑ ዋሉ። ሀዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ፡- ኢያቄም፡- "አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ጸሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ ለዐይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ/ች ወንድ ወይም ሴት ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ። ሐናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ፤ ስማኝ ለዐይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማኅጸኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች።

🔷👉 እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ዐይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች። ከሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ፣ ቤተ እግዚአብሄርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ (ውሃ) ቀድታ፣ መሶብ ወርቅ ሰፍታ፣ መጋረጃ ፈትላ፣ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ። ዘካርያስም እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላችሁ ብሎ አሳረገላቸው።

🔷👉 ከዚያም በኋላ ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱኑ ራዕይ ዐይተው ነገር አግኝተው አደሩ። ራዕዩም ኢያቄም “ርኢኩ በህልምየ እንዘ ይትረኀው ሰባቱ ሰማያት - ፯ቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ” አላት ፤ ወፍ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነጭነቱ ንጽሐ ባሕሪው ነው፤ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ ዐየሁ ማለቱ፤ አምላክ የኢያቄምን ( የሰውን) ባሕርይ ባሕርይ እንዳደረገው ሲያጠይቅ ነው፤ ፯ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባሕርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩ መንግሥቱ ናቸው።

🔴👉 ሐናም እኔም አየሁ አለችው፤ ምን አየሽ ቢላት፤ “ዖፍ ጸዓዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርዕስየ ወቦአት ውስተ ዕዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርስየ - ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ ስትተኛ አየሁ” አለችው። ርግብ የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት። ነጭ መሆንዋ ንጽህናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ድንግልናዋ ነው። ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕጸኔ ስትተኛ አየሁ ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መጽነሷን ነው። ይህንኑም ራዕይ ያዩት ሐምሌ ፴ (ሠላሳ) ዕለት ነው።

🔷👉 እነሱም እንዲህ ያለ ራዕይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም፤ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆ

07/07/2025
07/07/2025

በማህፀን ቅኔ

በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ
በተራራማ አገር በኤፍሬም ከተማ
ዮሐንስ ይናገር በረሃ ያደገው
ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው
አዝ
የእናቱ ማህፀን የቅኔ እርስት ሆነች
ድንግል የአምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች
በሀሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ
ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ
አዝ
በድንግል ማህፀን ስላየ ጌታውን
ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን
ትንቢቱ ሲፈፀም በሆዷ ሲነግስ
ሰገደ ለአምላኩ የስድስት ወር ፅንስ
አዝ
ጀመረ ስብከቱን ገና ሳይወለድ
ተፈጥሮ መች ቻለ ነብዩን ለማገድ
አፉ ተከፈተ በታላቅ ምስጋና
በእናቱ ማህፀን ድምፅን አሰማና
አዝ
የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት
ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት
ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ
አዝ
የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት
ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት
ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ

ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mihretab G/Hiwot posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share