Ewunet Media

Ewunet Media like በማድረግ መረጃዎችን በፍጥነት ማግኘት ይችላሉ

⭕️ለቸኮለ ማለዳ! ረቡዕ ጥቅምት 20/2017 ዓ፣ም  ዕለታዊ ዜናዎች1፤ የሱማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ዓሊ ሞሐመድ አደን የተባሉ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ዲፕሎማት በ72 ሰዓታት ከአገሪቱ እንዲወ...
30/10/2024

⭕️ለቸኮለ ማለዳ! ረቡዕ ጥቅምት 20/2017 ዓ፣ም ዕለታዊ ዜናዎች

1፤ የሱማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ዓሊ ሞሐመድ አደን የተባሉ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ዲፕሎማት በ72 ሰዓታት ከአገሪቱ እንዲወጡ ትናንት አዟል።

ሚንስቴሩ፣ ዲፕሎማቱ ከዲፕሎማሲ ተልዕኳቸው ጋር አብሮ የማይሄድ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ነበር በማለት ከሷል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ በዲፕሎማቱ መባረር ዙሪያ ያለው ነገር የለም።

2. የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ፣ "ተቀራርቦ መነጋገርን የመሰለ ነገር የለም" በማለት ከሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል በጋራ ከተነሱት ፎቶ ጋር በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጌታቸው፣ ከሩቅ የሚመጣ ሰው አያስፈልግም በማለት ኹለቱን የሕወሓት ቡድኖች ለማገናኘት ጥረት በማድረግ ላይ የሚገኙ አካላትን አመስግነዋል። ጌታቸው ከደብረጺዮን ጋር በምን ጉዳዮች ላይ እንደተነጋገሩ፣ መቼና የት እንደተገናኙ ወይም የትኞቹ አካላት እንዳቀራረቧቸው ግን አልገለጡም።

3፤ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት፣ ካለፈው ስምንት አጋማሽ ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ግንባሮች ከመንግሥት ኃይሎች ጋር በተካሄዱ ግጭቶች 102 የመንግሥት ወታደሮችንና በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ማርኬያለኹ ሲል አዲስ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

አማጺው ቡድን በመንግሥት ኃይሎች ላይ ወታደራዊ ድል ተቀዳጅቻለኹ ያለው፣ ድሬ ኢንጪኒ፣ ደራ፣ ወረ ጃርሶ፣ አመያ፣ ዩብዶ፣ ጉቴ፣ ቦጂ፣ ቡኖ በደሌ፣ ሳሲጋ፣ አባይ ጮመን፣ ሀርጡማ ፉርሴ፣ ኤልዋዬ፣ ገላና፣ ሱሮ ቡርጉዳ፣ በቾ እና ቦራ በተባሉ የግጭት ግንባሮች ነው። ቡድኑ ግጭት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች፣ የግንኙነት መስመሮች እንደተቋረጡ መኾኑንም ጠቅሷል። መከላከያ ሠራዊት በበኩሉ፣ በቡድኑ ላይ መጠነ ሰፊ የኃይል ርምጃ እየወሰደ መኾኑን ገልጧል።

4፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘቡ 2 ነጥብ 6 ትሪሊዮን መድረሱን አስታውቋል።

ባንኩ፣ በሩብ ዓመቱ ውስጥ 121 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ብድር መስጠቱንም ገልጧል። በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ባንኩ 640 ሚሊዮን የገንዘብ ዝውውር በዲጂታል አማራጮች መካሄዱንና ይህም ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር የ46 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን አውስቷል። በባንኩ የዲጂታል የክፍያ አማራጮች የ3 ነጥብ 1 ትሪሊዮን ብር ግብይት እንደተፈጸመም ተገልጣል። [ዋዜማ]

⭕️ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ለምን “ዝምታን” መረጡ?የተወካዮች ምክር ቤት የ2017 ዓ.ም. የሥራ ዘመኑን እንደሚጀምር አስታውቆ ሁለት ቀናት ሲቀሩት ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በማኅበ...
07/10/2024

⭕️ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ለምን “ዝምታን” መረጡ?
የተወካዮች ምክር ቤት የ2017 ዓ.ም. የሥራ ዘመኑን እንደሚጀምር አስታውቆ ሁለት ቀናት ሲቀሩት ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በማኅበራዊ ገጻቸው ላይ ያጋሩት መልዕክት ግራ መጋባትን ፈጥሮ ባለፉት ቀናት መነጋገሪያ ሆኗል።

ፕሬዝዳንቷ ምን እንደገጠማቸው እና ለምን ያንን ግልጽ ያልሆነ መልዕክት አሁን ማስተላለፍ ፈለጉ የሚለው ምላሽ አላገኘም።

ጉምቱዋ ዲፕሎማት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ወደ ፌደራል መንግሥቱ የፕሬዝዳንትነት ሥልጣን መንበር የመጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሥልጣን መያዛቸውን ተከትሎ ነበር። በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአገር ውስጥ እና ከውጪ ከፍተኛ ድጋፍ ባስገኘላቸው እና በርካታ ሴቶችን ወደ አመራርነት ባመጣው ውሳኔ ነው ፕሬዝዳንቷ የተሾሙት።

ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለርዕሰ ብሔርነት ሲታጩ በናይሮቢ እና በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግሥታት ኃላፊ እና ተወካይ ሆነው ከዋና ፀሐፊ በመከተል ከፍተኛ ሥልጣን ከነበራቸው የድርጅቱ ሰዎች መካከል አንዷ ነበሩ።

ከስድስት ዓመት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ወደ ሥልጣን ያመጣው ፖለቲካዊ ለውጥ ዲፕሎማቷ ሳህለ ወርቅን ብቻ ሳይሆን በርካታ በዓለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያውያንን የሳበ ከመሆኑ በተጨማሪ ብዙዎች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ፈቃደኛ እንደነበሩ ይታወሳል።

በመጪው የካቲት 75 ዓመት የሚሆናቸው ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ ታሪክ በአምባሳደርነት ከተሾሙ ሴት ዲፕሎማቶች መካከል ከቀዳሚዎቹ የሚመደቡ ሲሆኑ፣ የሁለት ልጆች እናት ናቸው።

የሳህለ ወርቅ በአዲሱ አስተዳደር ለሥልጣን መታጨት ከተሰማ በኋላ በርካቶች ለአሥርታት በዓለም ዙሪያ በሠሩበት፣ ልምድ እና ዕውቀትን ባዳበሩበት በዲፕሎማሲው መስክ ሊሾሙ እንደሚችሉ ሲገምቱ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊሆኑ እንደሚገባም ሃሳብ ሲሰነዝሩ ነበር።

በዚህም የተነሳ በርዕሰ ብሔርነት ሲሾሙ ቦታው ጉልህ ኃላፊነት እና ሥልጣን የሌለው ነው በማለት የተቹ የነበሩ ሲሆን፣ ሌሎች ደግሞ የፕሬዝዳንትነቱን መንበር በመጠቀም የአገሪቱ ምልክት በመሆን በሴትነታቸው እና በልምዳቸው ጠቃሚ ተግባራትን የሚያካነውኑበት ዕድል ሊኖር ይችላል ማለታቸው ይታወሳል።
ፕሬዝዳንቷን ያስከፋቸው ምንድን ነው?
ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ቅዳሜ መስከረም 25/2017 ዓ.ም. በኤክስ ገጻቸው ላይ የታዋቂውን ድምጻዊ የማህሙድ አህመድን የዘፈን ስንኞች በመጥቀስ ያሰፈሩት ግልጽ ያልሆነ መልዕክት በማኅበራዊ ሚዲያ ተከታዮቻቸው ዘንድ ግራ መጋባትን ፈጥሯል።

ቢሆንም ግን ከዘፈኑ ግጥም ውስጥ የመዘዙት ሃሳብ እና ያሰፈሩት መደምደሚያ ግን ፕሬዝዳንቷ "እንደከፋቸው" እና “መሄጃ መውጫ” እንደጠፋቸው፤ ለዚህም መልሳቸው “ዝምታ” መሆኑን ይጠቁማል። በአጭር ጽሁፋቸው ማጠቃለያ ላይም ይህንን የዝምታ አማራጭ “ለአንድ ዓመት” እንደሞከሩት ገልጸዋል።

ቢሆንም ግን ርዕሰ ብሔሯ ዝምታን አማራጭ እንዲያደርጉ ያስገደዳቸው መገፋት ከየትኛው ወገን እንደገጠማቸው እና ምን እንደሆኑ በግልጽ ያሉት ነገር የለም። ጽህፈት ቤታቸውም ፕሬዝዳንቷ በግል ገጻቸው ላይ ስላሰፈሩት መልዕክት ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ገልጿል።

ቢቢሲ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ቀናት ላይ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ከሥልጣን የመልቀቅ ሃሳብ እንዳላቸው የሚገልጽ መረጃ አግኝቶ በቅርብ ከሚያውቋቸው ሰዎች ለማጣራት ያደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። ቢሆንም ግን አሁን ያጋሩት ጽሁፍም ቢሆን ከሥልጣን ስለመልቀቅ የሚያመለክተው ነገር የለም።

ከፕሬዝዳንቷ ጽሁፍ በኋላ ቢቢሲ፤ የቅርብ ወዳጆቻቸው ስለገጠማቸው ነገር የሚያውቁት ነገር ካለ በሚል ሁለት ሰዎችን ጠይቋል። ፕሬዝዳንቷ ባለፉት ዓመታት በዙሪያቸው በሚከናወኑ ነገሮች በተለይም በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱት ጦርነቶች ደስተኛ አለመሆናቸውን እንደሚያውቁ ከመናገር ውጪ በእርግጠኝነት ይህ ነው ለማለት እንደማይችሉ ገልጸዋል።

ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉት በቅርብ ከሚያውቋቸው ሰዎች መካከል አንደኛው እንዳሉት ፕሬዝዳንቷ በተለያዩ ሥነ ሥርዓቶች ላይ በሚያደርጓቸው ንግግሮች የተነሳ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደስተኛ አለመሆናቸውን የሚያመልክት መልዕክት በተዘዋዋሪ እንደሚደርሳቸው አውቃለሁ ብለዋል።

በዚህም የተነሳ ፕሬዝዳንቷ ደስተኛ እንዳልሆኑ እና በተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም በሌሎች ጥቂት ዓመታዊ ዝግጅቶች ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ከመገናኘት ባሻገር እንደ ርዕሰ ብሔር እና ርዕሰ መንግሥት በሁለቱ መካከል የቀረበ ግንኙነት እና ምክክር እንደሌለ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቷ ያጋሩትን አጭር ጽሁፍ በተመለከተም ሌላኛው የሚያውቃቸው ግለሰብ፤ ማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ እራሳቸው እንደሚጽፉ እንደሚያውቅ ጠቅሶ፣ ጽሁፉ የራሳቸው ሊሆን እንደሚችል ከመጠቆም ባለፈ ስላሰፈሩት ሃሳብ ከግምት ውጪ መናገር እንደማይችል ለቢቢሲ ገልጿል።

ግምቱም ፕሬዝዳንቷ ቅሬታቸውን በይፋ መጻፍ የፈለጉት ሰኞ መስከረም 27/2017 ዓ.ም. ከሚካሄደው የተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ጉባኤ ንግግራቸው ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል ብሏል። በየዓመቱ ምክር ቤቶቹ ሥራ ሲጀመሩ ፕሬዝዳንቷ በአጠቃላይ አገራዊ ሁኔታዎች ላይ እና የመንግሥትን ዕቅድ በሚመለከት ንግግር እንደሚያደርጉ ይታወቃል።

እንደ ቢቢሲ ምንጭ ከሆነ ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ላይ በፕሬዝዳንቷ ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የአገሪቱ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች ደስተኛ አለመሆናቸው በማንሳት ምናልባት ዛሬ ሰኞ በሚደረገው የፕሬዝዳንቷ ንግግር ዙሪያ አለመግባባት ተፈጥሮ ሊሆን ይችላል ብለዋል።

የመጨረሻቸው ይሆን?
ለውጡን ተከትሎ ባለፉት ስድስት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋባዥነት ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ጋር ሳይዛመዱ ባላቸው ዝና እና ብቃት ወደ አገሪቱ የተለያዩ የሥልጣን መንበሮች የመጡት ባለሙያዎች በተለያዩ ምክንያቶች ቀስ በቀስ ከመድረኩ እየራቁ ነው። የቀሩት ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ብቻ ናቸው ማለት ይቻላል።

ቁልፍ በሚባሉ የኃላፊነት ስፍራዎች ላይ ከነበሩት መካከል የሚጠቀሱት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት መዓዛ አሸናፊ እንዲሁም የሰብአዊ መብት ኮሚሽነሩ ዳንኤል በቀለ በራሳቸው ምክንያት ቦታቸውን ባለፉት ዓመታት በየተራ መልቀቃቸው ይታወሳል።

ከእነዚህ ተሿሚዎች ጋር ወደ አገሪቱ የርዕሰ ብሔርነት የሥልጣን መንበር የመጡት ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቷ ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ቀጣይዋ ተሰናባች ሊሆኑ እንደሚችሉ አብረዋቸው የሠሩ እና በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች ይናገራሉ። ባለፉት ዓመታት "በተለይም ጦርነቶች በሚካሄዱባቸው እና ጥቃቶች በሚፈጸሙባቸው ጊዜያት ሐዘናቸው ከባድ እንደነበረ" ቢቢሲ ያናገራቸው የቅርብ ሰዋቸው ይገልጻሉ።

በተለይ በምክር ቤቶች መክፈቻ እና በአንዳንድ ዓመታዊ ሥነ ሥርዓቶች ላይ ብቻ ከሚያገኟቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ያላቸው ግንኙነት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑ ፕሬዝዳንቷ ተነጥለው በኢዮቤሊዩ ቤተ መንግሥት እንዲቀሩ እና በመንግሥት ውስጥ ለሚካሄዱ ነገሮች ባዳ ሳያደርጋቸው እንደማይቀር ምንጩ ይናገራሉ።

በትግራይ የተካሄደው ጦርነት በተለይ በሴቶች ላይ ያደረሰው ጉዳት በእጅጉ እንዳሳዘናቸው በተደጋጋሚ እንደሚናገሩ የሚገልጹት የቢቢሲ ምንጭ፣ ከዚያም ጋር በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል የሚካሄዱት ግጭቶችም በጣሙን እንደሚያሳስባቸው እና በቶሎ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያገኙ ይሻሉ ብለዋል።

ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ በአንድ ወቅት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ ዛሬ የሚሠሩት እስከ ዛሬ በሙያ ሕይወታቸው የገነቡትን እና ያካበቱትን ልምድ እንዳይንድባቸው እንደሚጠነቀቁ ተናግረዋል።

ስለሰላም እና ስለ ሴቶች በተደጋጋሚ ሲናገሩ የሚደመጡት ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ የፕሬዝዳንትነት ዘመናቸው አስቸጋሪ ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው ታሪክ ሲወሳ “ኢትዮጵያ በእንደዚህ ዓይነት መከራ ውስጥ ስታሳልፍ ሴት ፕሬዝዳንት ነበረች ተብሎ መገምገሜ አይቀርም። ምን ማድረግ እችል ነበር የሚለው ሌላ ጥያቄ ነው። ነገር ግን ይህንንም መቀበል አለብኝ” ብለዋል።

ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ወደ ሥልጣን የመጡበት የኋላ ታሪክ አገሪቱን ከሚመሩት የፖለቲካ ልሂቃን የተለየ በመሆኑ በአገሪቱ ሕዝቦች መካከል ያለው የብሔር መለያየት እንዲለዝብ እና ለጋራ አገር በአንድነት እንዲቆም በርከት ባሉ አጋጣሚዎች ላይ መክረዋል።

ባለፈው ዓመት የካቲት ወር መጀመሪያ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ከፍተኛ የአገሪቱ ባለሥልጣናት እንዲሁም የተለያየ አገራት ዲፕሎማቶች በተገኙበት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ሲመረቅ ዓድዋ የዘመቱ ኢትዮጵያውያን የተሰባሰቡት በሃይማኖት እና በብሔር ተመራርጠው አለመሆኑን የተናገሩት ፕሬዝዳንቷ “አገርን ማዳን ከልዩነታችን በላይ ነው” ሲሉ ማሳሰባቸው ይታወሳል።

የአገሪቱ ክልሎች ፕሬዝዳንቶች እና ባለሥልጣናት በታደሙበት በዚያ ዝግጅት ላይ ከርዕሰ ብሔሯ ቀድመው ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የነበሩ ሲሆን፣ ይህም የፕሮቶኮል ጥያቄ በአንዳንዶች ዘንድ እንዲነሳ አድርጎ ነበር።

ፕሬዝዳንቷም ወደ መድረክ በተጋበዙበት ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ከንቲባዋ ካሉት ውጪ የሚሉት ነገር እንደሌለ በመናገር በአገሪቱ የሚከሰቱ ልዩነቶችን ለመፍታት ጠመንጃ ማንሳት መለመዱን “. . . ወንድም ወንድሙ ላይ መነሳት አገር ኩራት አይደለም” በማለት “በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን አለመግባቶች በሰከነ መንገድ ተነጋግሮ መፍታት” አስፈላጊ መሆኑን መልዕክት አስተላልፈዋል።

በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚያጋጥሙት ቀውሶች ፕሬዝዳንቷን በዋናነት የሚያሳስቡ ጉዳዮች መሆናቸውን የሚገልጹት ሌላኛዋ የቅርብ ሰው፣ በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ሁኔታዎቹ ከመርገብ ይልቅ እየተባባሱ መሄዳቸው ከአንድ ዙር የሥልጣን ዘመናቸው መጠናቀቅ በኋላ በፕሬዝዳንትነት ላይቀጥሉ እንደሚችሉ ይናገራሉ።

በተለይ ባለፈው ዓመት በተለያዩ አጋጣሚዎች 2017 ጥቅምት ወር የመጨረሻቸው መሆኑን የሚያመለክቱ ነገሮችን ለቅርብ ሰዎቻቸው ጠቆም ያደርጉ ነበር። በእርግጥም የፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ የመጀመሪያ ዙር ስድስት ዓመት የሥልጣን ዘመን የሚያበቃው በመጪው ጥቅምት ወር ነው።

በፕሬዝዳንትነት ተሰይመው ከሚያገኙት በላይ በመንግሥታቱ ድርጅት የነበራቸው ቦታ የሚያስገኝላቸው ጥቅምን ትተው ወደ ሥልጣን የመጡት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ “ለዚህ ያበቃችኝን አገሬን በማገልገል ውለታዋን የምመልስበት አጋጣሚ ነው” ብለው ያምኑ እንደነበር የሚገልጹት ምንጫችን ምኞታቸውን ምን ያህል አሳክተዋል የሚለውን ግን እርግጠኛ አይደሉም።

ባለፉት ዓመታት መሥራት የሚፈልጉትን ያህል አለማሳካታቸውን በተዘዋዋሪ መረዳት ይቻላል የሚሉት ላለው ምንጭ ምናልባትም አሁን “ሆድ እየባሳቸው” ዝምታን የመረጡት ከዚህ በላይ መቀጠል ስለማይችሉ ጥቅምት ወርን እየጠበቁ ስለሆነ ይሆናል ይላሉ።

የሪፐብሊኩ አራተኛዋ ፕሬዝዳንት
ኢሕአዴግ ሥልጣን ይዞ አዲስ ፌደራላዊ አወቃቀር እና ሕገ መንግሥትን ለአገሪቱ ከቀረጸ በኋላ በነበሩት 30 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅን ጨምሮ አራት ፕሬዝዳንቶችን ወደ ሥልጣን አምጥቷል።

ከፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ውጪ ያሉት ሦስቱ ወንዶች ከመሆናቸው በተጨማሪ የኋላ ታሪካቸው በአንድ ወይም በሌላ መልኩ በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ የነበራቸው ናቸው። በተለይም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የገዢው ኢህአዴግ አካል የሆነው የኦህዴድ አባላት ነበሩ። መቶ አለቃ ግርማ ወ/ጊዮርጊስም እንዲሁም ከገዢው ፓርቲ ውጪ እምብዛም የማይታወቅ ፓርቲ አመራር ነበሩ።

አራተኛዋ የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ከቀደምቶቻቸው በተለየ በዲፕሎማሲው መስክ ለረጅም ዓመታት ከመሥራታቸው በተጨማሪ ከየትኛውም የፖለቲካ ቡድን ጋር የሚታወቅ ግንኙነት አልነበራቸውም። በተጨማሪም በአገሪቱ ታሪክ በፕሬዝዳንትነት ተሰይመው ሥልጣን የየዙ የመጀመሪያዋ ሴት ናቸው።

ይህ የአገሪቱ ፕሬዝዳንትነት ሥልጣን ግን ከአገር ምልክትነት ባለፈ ጉልህ ውጤት የሚኖረው ውሳኔን ለማሳለፍ የሚያስችል ኃላፊነት በሕገ መንግሥቱ አልተሰጠውም። በዚህም ሳቢያ የአምባሳደር ሳህለ ወርቅ ፕሬዝዳንት መሆን ያላቸውን የዲፕሎማሲ ሙያ እና ልምድ ያባክነዋል ብለው የተቆጩ ጥቂቶች አልነበሩም።

በሕገ መንግሥቱ ፕሬዝዳንቷ በዋናነት የተሰጣቸው ኃላፊነት በሌሎች የመንግሥት አካላት የተላለፉ ውሳኔዎችን ዕውቅና መስጠት ነው። በዚህም የተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቃቸው ሕጐች እና ስምምነቶችን በነጋሪት ጋዜጣ ማወጅ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርቧቸውን አምባሳደሮች እና መልዕክተኞችን መሾም እንዲሁም ከፍተኛ ወታደራዊ ማዕረጎችን መስጠት ነው።

በተጨማሪ ደግሞ የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽኑን ምክር ቤቶችን የጋራ ስብሰበባ በንግግር መክፈት፣ የውጭ አገራት አምሳደሮችን እና የልዩ መልዕክተኞችን የሹመት ደብዳቤ መቀበል፣ ኒሻኖች እና ሽልማቶችን መስጠት እንዲሁም የቀረቡ ሕጋዊ የይቅርታ ጥያቄዎችን መቀበል ይጠቀሳሉ ነው።

እንኳን አደረሰን
26/09/2024

እንኳን አደረሰን

🛑ጀማሪ ክሊኒካል ነርስBMY MEDICAL TECHNOLOGIES PLCFull Time ራስ ደስታ ሆስፒታል አጠገብ - ገተር ሕንፃJOB OVERVIEWSalary Offer NegotiableExperi...
19/08/2024

🛑ጀማሪ ክሊኒካል ነርስ
BMY MEDICAL TECHNOLOGIES PLC
Full Time ራስ ደስታ ሆስፒታል አጠገብ - ገተር ሕንፃ
JOB OVERVIEW
Salary Offer
Negotiable
Experience Level
Junior
Total Years Experience
0 (Zero Experience)
Date Posted
August 18, 2024
Deadline Date
August 29, 2024
JOB REQUIREMENT
ተፈላጊ የትምህርት ደረጃና የሥራ ልምድ:ከታወቀ የጤና ተቋም በክሊኒካል ነርስ በዲፕሎማ/በዲግሪ የተመረቀ/ችና በሙያው 0 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት፣
ብዛት:5
ጾታ፡- ወንድ/ሴት

HOW TO APPLY
ማሳሰቢያ፡-

አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር /10/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ማመልከቻ፣ የትምህርት እና የሥራ ልምድ ማስረጃዎች የማይመለስ ፎቶ ኮፒ እና ኦርጅናል በመያዝ በአካል በሰው ኃይል አስተዳደር ቢሮ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 -11፡30 ቅዳሜ 6፡ሰአት መመዝገብ ይቻላል፤
ከላይ ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ ቦታዎች በጤና ተቋም የተገኘ የሥራ ልምድ ተመራጭ ይሆናል፡
አድራሻ፡ የመመዝገቢያና የሥራ ቦታ፡ራስ ደስታ ሆስፒታል አጠገብ – ገተር ሕንፃ ለበለጠ መረጃ 09-47-85-85-85/ 9560

SHARE THIS JOB

🇪🇹እንኳን ወደ እውነት ሚድያ በሰላም መጣችሁ🇪🇹 በውስጥ መስመር ከፈለጉን

‼️ስራ በዜሮ አመት አባይ ባንክ✅CUSTOMER SERVICE OFFICERS (CSO) - ||  ✅JOB OVERVIEW  👉Salary Offer : As per Company Scale 👉Experien...
30/07/2022

‼️ስራ በዜሮ አመት አባይ ባንክ

✅CUSTOMER SERVICE OFFICERS (CSO) - ||

✅JOB OVERVIEW

👉Salary Offer : As per Company Scale
👉Experience Level: Junior
👉Total Years Experience:0
👉Date Posted: July 31, 2022
‼️Deadline Date: August 5, 2022

‼️ JOB SUMMERY

👉The CSO attends customer inquiries, handless payments and collections, works on deposit mobilization and searches for potential customers, checks, signs and counter signs on tickets, ensures that correct receipts and advices are issued to customers for all transactions, balances daily cash positions.

✅JOB REQUIREMENT

• Educational Level and work Experience: Minimum BA degree in Accounting or Business Management or Management or Banking and Finance or Economics and/or related Departments.

• Graduate year: Only Graduates of 2021and 2022.
• CGPA:2.75 and above for Female and 3.0and above for Male
• Age: below 30 years
• Writing and speaking of Somali and Affan Oromo language is desirable

‼️Place of Work: Branches under Dire Dawa District areas include: Somali reginal State of Ethiopia Western and Eastern hararge Dire Dawa City

⚠️HOW TO APPLY

‼️Application Dead line: August 05, 2022 Interested & qualified applicants fulfilling the above criteria can apply through Online via www.abaybank.com.et. Only short listed candidates will be contacted.
=====================
✅YouTube ቻናላችንን ይከታተሉ
👇
https://youtu.be/M_5e2uxf4HQ

✅ ሀሳብ አስተያየት ወይም ጥቆማ ካላቹህ ይላኩልን

መረጃው በቅንነት ሼር ያድርጉላቸው 🙏
=====================

የክልልነት ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ጉዳዩን የአመጽና የሁከት መነሻ ለማድረግ በሚሞክሩ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋ...
15/07/2022

የክልልነት ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ጉዳዩን የአመጽና የሁከት መነሻ ለማድረግ በሚሞክሩ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ

👉የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ መንግሥት በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በተለያዩ ጊዜያት የሚነሱ የክልልነት ጥያቄዎችን በሀገሪቱ ሕግና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እየሠራ ይገኛል፡፡

👉ነገር ግን አንዳንድ አካላት ይህንን ሂደት በሚቃረን መንገድ ሕጋዊ ጥያቄዎችን ሽፋን በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር በህቡዕ ዝግጅት ማድረጋቸውን የጋራ ግብረ ኃይሉ ባደረገው ክትትል ስለተደረሰበት ተገቢው እርምጃ ይወስዳል፡፡

👉መግለጫው እንዳብራራው፤ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት በስሩ የሚገኙ ዞኖችን በአዲስ መልክ ለማዋቀር እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ ጌዲኦም በአዲስ መልክ ከሚዋቀሩ ዞኖች አንዱ ሲሆን፤ የኅብረተሰቡን ተሳትፎ በተጨባጭ ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ሰሞኑን የማወያያ ሰነዶች ተዘጋጅተው የዞኑ ነዋሪ እየመከረበት ይገኛል፡፡

👉ይሁንና የጌዲኦ ዞን የክልልነት ጥያቄ መፍትሔ የማይሰጠው ከሆን ጥያቄያችንን በኃይል እናስፈጽማለን የሚሉ አካላት በህቡዕ ተደራጅተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጧል፡፡

👉በህቡዕ የተደራጁት አካላት የጥፋት እቅዶቻቸውን ለማሳካት ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች በመክፈት የተዛቡና የፈጠራ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን ያመለከተው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ ማኅበረሰቡንም በተሳሳቱ መረጃዎች ለማደናገር እየሞከሩ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

👉እነዚህ አካላት ያደራጇቸው ግለሠቦችና ቡድኖች ቤት ለቤት ጭምር እየተንቀሳቀሱ ቅስቀሳ እያደረጉ እንደሚገኙ ይህም በደኅንነትና በጸጥታ አካላት እንደተደረሰበት አመልክቷል፡፡

👉የጋራ ግብረ ኃይሉ ለዚህ እኩይ ዓላማ የተደራጁና የተሰለፉ ግለሠቦችንና ቡድኖችን በደኅንነትና በጸጥታ መዋቅሩ አማካኝነት ለይቶ ክትትል እያደረገባቸው መሆኑን በማስገንዘብ፤ ከጥፋት ተልዕኳቸውም እንዲቆጠቡ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

👉ይህን ተላልፈው በሚገኙ ላይም ተገቢውን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያስጠነቅቃል፡፡

👉አብዛኛው የዞኑ ኅብረተሰብ የጥፋት ተልዕኮ ያነገቡ አካላት ህቡዕ እንቅስቃሴ ተገቢ አለመሆኑን በማመን ለጸጥታና ደኅንነት አካላት ጥቆማ በመስጠት የሁከትና ብጥብጥ ተልዕኮው እንዲከሽፍ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የጠቆመው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫው፤ በቀጣይም ከእንደዚህ አይነት የጥፋት ሴራ እራሱን በማቀብ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት ለመንግሥት አካላት መረጃ በመስጠት የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቋል፡፡

የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል

ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም

‼️ሐሙስ ሰኔ 9/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች✅ወደ ትግራይ ገንዘብ ለመላክ እስከ 50 በመቶ ይከፈል የነበረው ኮሚሽን ሰሞኑን ወደ 25 በመቶ እንደወረደ ዋዜማ መረዳት ችላለች። 👉የገንዘብ መ...
16/06/2022

‼️ሐሙስ ሰኔ 9/2014 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

✅ወደ ትግራይ ገንዘብ ለመላክ እስከ 50 በመቶ ይከፈል የነበረው ኮሚሽን ሰሞኑን ወደ 25 በመቶ እንደወረደ ዋዜማ መረዳት ችላለች።

👉የገንዘብ መላኪያው ኮሚሽን የቀነሰው የአስተላላፊዎች ቁጥር ስለጨመረ እንደሆነ ገንዘብ ላኪዎች ለዋዜማ ተናግረዋል።

👉 የገንዘብ ላኪዎችን መብዛት ተከትሎ፣ መንግሥት በአማራ ክልል ቆቦ እና በአፋር ክልል ሠመራ የሚገኙ ገንዘብ አስተላላፊዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል ጀምሯል። Link- https://bit.ly/3mTG5nc

✅ አምራች ኢንዱስትሪዎች ከማምረት አቅማቸው 49 በመቶውን ብቻ እየተጠቀሙ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚንስቴር ለፓርላማው ባቀረበው የ10 ወራት ሪፖርት ላይ መናገሩን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግቧል።

👉በበጀት ዓመቱ መግቢያ 46 በመቶ የነበረውን የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም በዓመቱ መጨረሻ ላይ 60 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ እንደነበር የጠቀሰው ሚንስቴሩ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከ49.2 በመቶ በላይ ማሳደግ እንዳልተቻለ ገልጧል።

👉 የውጭ ምንዛሬና የግብዓት እጥረት እና የጸጥታ ችግር የዘርፉን የማምረት አቅም እንዳዳከሙት እና በቅርቡ በተተገበሩ መፍትሄዎች ግን 118 ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት እንደተመለሱ ተገልጧል።

✅ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ጉዳት ከደረሰባቸው 190 አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች መካከል 22ቱ የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ እስካሁን ሥራ አለመጀመራቸውን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግቧል።

👉 የኢንዱስትሪ ሚንስቴር የ10 ወራት ሪፖርቱን ለፓርላማው ባቀረበበት ወቅት፣ በአማራና አፋር ክልሎች ከሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች 65ቱ በሙሉ አቅማቸው፣ 103ቱ ደሞ በከፊል ምርት እንዲጀምሩ መደረጉ ተገልጿል። ሚንስቴሩ

👉 ሥራ ያልጀመሩ ፋብሪካዎች የሚፈልጉትን ድጋፍ በዝርዝር አጥንቶ ለሚመለከተው አካል አቅርቧል።

✅ የአማራ ክልል ዳኞች ማኅበር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ትናንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላይ፣ "ዳኞች አንደኛ ደረጃ ሌቦች ናቸው" በማለት ለተናገሩት ያልተገባ ንግግር ማስተካከያ እንዲያደርጉ ዛሬ ባሰራጨው ደብዳቤ መጠየቁን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግቧል።

👉ልዩ ጥናትና ማስረጃ በሚፈልግ ጉዳይ ላይ ዐቢይ ዳኞችን በጅምላ በሌብነት መፈረጃቸው ተገቢ አይደለም ያለው ማኅበሩ፣ ንግግራቸው ሕዝብ በፍርድ ቤቶች ላይ ያለውን አመኔታ የሚያሳጣ፣ የፍርድ ቤቶችን ገጽታ የሚያበላሽ እና የምስጉን ዳኞችን ሞራል የሚጎዳ እንደነ ገልጧል።

✅ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የሕግ ባለሙያዎች ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ማክሰኞ'ለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው አንገብጋቢ አገራዊ ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ እና ማብራሪያ አልሰጡም በማለት እንደተቹ ሪፖርተር አስነብቧል።

👉 የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ራሄል ባፌ፣ ዐቢይ ለጥያቄዎች በቀጥታ መልስ መስጠት አለመስጠታቸውን ተችተዋል።

✅ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 51 ብር ከ8017 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 52 ብር ከ8377 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል።

👉 የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 59 ብር ከ8199 ሳንቲም፣ መሸጫው 61 ብር ከ0163 ሳንቲም ሆኗል።

👉በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ54 ብር ከ2985 ሳንቲም ሲገዛ እና በ55 ብር ከ3845 ሳንቲም ሲሸጥ ውሏል።

✅ ሱዳን ከሕዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ውሃ ሙሌት በፊት በዘላቂ የውሃ ክፍፍል እና በግድቡ ደኅንነት ዙሪያ የሦስትዮሽ ስምምነት ላይ እንዲደረስ መጠየቋን ዘ ኢስት አፍሪካን ዘግቧል።

👉 ሱዳን የሕዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ውሃ ሙሌት እና ውሃ አለቃቀቅ በአነስተኛ ግድቦቿ ላይ ሊፈጥረው የሚችለው ተጽዕኖ እንዳሳሰባት ጋዜጣው አየሁት ባለው የሱዳን መስኖ ሚንስቴር ማስታዎሻ ላይ ተገልጧል።

👉ሱዳን ድንገተኛ አደጋዎችን በጋራ ለመፍታት፣ በውሃ አሞላል፣ ውሃ አለቃቀቅ እና በግድቡ ደኅንነት ላይ የሦስትዮሽ የመረጃ ልውውጥ ባስቸኳይ እንዲጀመር ትፈልጋለች።
=====================
✅YouTube ቻናላችንን ይከታተሉ
👇
https://youtu.be/M_5e2uxf4HQ

መረጃው በቅንነት ሼር ያድርጉ

አዲስ አበባ ስቴድየም =====================✅YouTube ቻናላችንን ይከታተሉ                     👇https://youtu.be/M_5e2uxf4HQ
13/06/2022

አዲስ አበባ ስቴድየም
=====================
✅YouTube ቻናላችንን ይከታተሉ
👇
https://youtu.be/M_5e2uxf4HQ

‼️ሰበር "ድምጻዊ ዳዊት ነጋ(ዘዊደሮ) ህይወቱ አልፏል =====================✅YouTube ቻናላችንን ይከታተሉ                     👇https://youtu.be/M_5e...
12/06/2022

‼️ሰበር

"ድምጻዊ ዳዊት ነጋ(ዘዊደሮ) ህይወቱ አልፏል
=====================
✅YouTube ቻናላችንን ይከታተሉ
👇
https://youtu.be/M_5e2uxf4HQ

ለጥንቃቄ ያህል ነውሰሞውኑን የግብፅና የምዕራቡ አለም ጋዜጦች ኢትዮጵያና ግብፅ ሱዳን በኤምሬትስ አደራዳሪነት ወደ ድርድሩ ሊመለሱ ነው እያሉ ዜና እየሰሩ ነው። ይሄንን መረጃ ከነሱ ያነበቡት ...
12/06/2022

ለጥንቃቄ ያህል ነው
ሰሞውኑን የግብፅና የምዕራቡ አለም ጋዜጦች ኢትዮጵያና ግብፅ ሱዳን በኤምሬትስ አደራዳሪነት ወደ ድርድሩ ሊመለሱ ነው እያሉ ዜና እየሰሩ ነው። ይሄንን መረጃ ከነሱ ያነበቡት አንዳንድ ኢትዮጵያዊያንም እንደዚሁ ዘገባ ላይ ሲያውልት ተመልክተናል።

ጉዳዩን በተመለከተ ከመንግሥት ሰዎች ለማጣራት ሞክሬያለሁ። አንደኛ እስከ ሦስተኛ ወገን ድረስ አጣርቸ የሚከተለውን መረጃ አግኝቻለሁ።

ድርድሩ ከአፍሪካ ህብረት ውጭ እንደማይወጣና ኤምሬትስም ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር እንዲጀመር ሦስቱም አገሮች አቋርጠውት ከነበረው ሰላማዊ ድርድር እንዲመለሱ ጥረት እያደረግች እንደሆነና ይሄም ጉዳይ ስኬታማ ትሁን አትሁን የራሷ ፍላጎት ብቻ እንደሆነ የግድቡን ድርደር ከሚመራው ከፍል አረጋግጠውልኛል።

የኤምሬትስ ፍላጎት ሦስቱም አገሮች በአፍሪካ ህብረት ስር የጀመሩትን ድርድር ማስቀጥል ብቻ እንደሆነም ነው ያገኘሁት መረጃ የሚያሳየው። ከዚህ በፊት ሦስቱን አገሮች ለማደራደር ጥያቄ ያቀረቡ አገሮች ነበሩ። ከነዚህ ውስጥ ሳኡዲ አረቢያ አሜሪካ ቀዳሚዎቹ ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ህብረት ውጭ ሌላ አደራዳሪ እንደማትፈልግ በማሳወቋ ከዚህ ቀደም ከአፍሪካ ህብረት ውጭ የወጣው ድርድር ወደ አፍሪካ ህብረት መመለሱ አይዘነጋም። እናም አገራችን ዳግመኛ ዕንደዚህ አይነት ስህተቶችን እንደማትፈፅም ነው መረጃው የሚጠቁም።

ሱሌማን አብደላ

‼️ዓለም ዓቀፍ የቁርኣን ዉድድሩ ነገ ጠዋት በአዲስ አበባ ስታዲየም እንዲካሄድ ተፈቅዷል።እንኳን ደስ አላቹህ
12/06/2022

‼️ዓለም ዓቀፍ የቁርኣን ዉድድሩ ነገ ጠዋት በአዲስ አበባ ስታዲየም እንዲካሄድ ተፈቅዷል።

እንኳን ደስ አላቹህ

Address

Addis Ababa
1234

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ewunet Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share