Ever Light

Ever Light Updates on different situations You can get what you want,if you put here.

በህዳሴ ግድብ የሚሰማሩ የባህር ዳርቻዎች ጥበቃ የፖሊስ ምልምል አባሎች ተመረቁ =====================የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጋር በመ...
29/08/2025

በህዳሴ ግድብ የሚሰማሩ የባህር ዳርቻዎች ጥበቃ የፖሊስ ምልምል አባሎች ተመረቁ
=====================
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሚሰማሩ የባህር ዳርቻዎች ጥበቃ የፖሊስ ምልምል አባሎችን በመሰረታዊ ባህርተኝነት አሰልጥኖ አስመርቋል።
በባቦጋያ ማሪታይም እና ሎጂስቲክስ አካዳሚ በተካሄደው የምረቃ መርሐ ግብር የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንዳሉት፤ ስልጠናው በዓለም አቀፍ መስፈርቶች መሰረት የተከናወነ ነው።
የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው በማለት ገልጸው፤ የፌዴራል ፖሊስ እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት ግድቡን ከጅማሮው አንስቶ ሲጠብቁ ቆይተዋል ብለዋል።
በለውጡ መንግስት አማካኝነት ግድቡን ከነበረበት ውድቀት በማዳን ለስኬት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።
የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ድርጅቱ ሀገር እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እና በአካዳሚው በኩል ባህርተኞችን ለዓለም ገበያ እያበቃ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በሁሉም መስክ እያንሰራራች ያለችውን ኢትዮጵያ ወደኋላ የሚመልሳት ኃይል እንደሌለ ተናግረዋል።
የባቦጋያ ማሪታይም እና ሎጂስቲክስ አካዳሚ ዲን ሲራጅ አብዱላሂ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ስልጠናው ዘመኑን የዋጀ ዓለም አቀፍ ይዘቱን የጠበቀ እንደሆነ ገልጸው፤ ሰልጣኞች አስፈላጊውን እውቀትና ባህሪ ታጥቀዋል ብለዋል።
በመርሀ ግብሩ ለስልጠናው መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ እና በስልጠናው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ እውቅና መሰጠቱንም ኢዜአ ዘግቧል።

© FMC

 #የወርቅ ሽልማት አሸናፊዋ አዲስ አበባ ከተማ ===========================የአዲስ አበባ ከተማ "ብሉምበርግ ኢኒሽዬቲቭ ፎር ግሎባል ሮድ ሴፍቲ" በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ባዘጋጀ...
28/08/2025

#የወርቅ ሽልማት አሸናፊዋ አዲስ አበባ ከተማ
===========================

የአዲስ አበባ ከተማ "ብሉምበርግ ኢኒሽዬቲቭ ፎር ግሎባል ሮድ ሴፍቲ" በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ባዘጋጀው በዓይነቱ የመጀመሪያ በሆነው ፍጥነትን ማሰተዳደር ዓለም አቀፍ ውድድር የወርቅ ሽልማት አሸናፊ ሆነች።

አዲስ አበባ ከተማ ለሽልማት ከታጩ ስምንት ከተሞች መካከል አንደኛ በመውጣት ነው የወርቅ ሽልማት ተሸላሚ የሆነችው።

ከውድድሩ መስፈርቶች መካከል የመንገድ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት እና የትራፊክ ደኅንነትን በመጠበቅ ረገድ ከተሞች ሥራ ላይ የሚያውሏቸው ስትራቴጂዎች ተግባራዊነት ተጠቃሽ ናቸው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ “ብሉምበርግ ፍላንተሮፒስ ኢንሼቲቭ ፎር ግሎባል ሮድ ሴፍቲ ባዘጋጀው የመንገድ ደኅንነትን ማስተዳደር ላይ ከተማችን ባስመዘገበችው ተጨባጭ ውጤት፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ የወርቅ ሽልማት አሸናፊ በመሆኗ ታላቅ ክበር ተሰምቶናል" በማለት በሽልማቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

ዕውቅናው ከተማዋ ፍጥነትን ለማስተዳደር እና የመንገድ ደኅንነት ለማሻሻል እየወሰደች ያለውን ጠንካራ ቁርጠኝነት ዳግም የሚያረጋገጥ እንደሆነም ነው ከንቲባዋ የጠቀሱት።

በዕውቅናው የተገኘው የ100 ሺህ ዶላር ሽልማት፤ በቀጣይ የከተማዋ መንገዶች ደኅንነታቸው የተጠበቀ፣ ጤናማ፣ ለነዋሪው ተስማሚ፣ ምቹ እና አካታች እንዲሆኑ የሚያስችሉ የማሻሻያ ሥራዎችን ለመሥራት ተጨማሪ እገዛ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

የብሉምበርግ ኤል.ፒ. እና የብሉምበርግ ግብረ-ሠናይ ድርጅት መሥራች፤ የዓለም ጤና ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና ጉዳቶች አምባሳደር እንዲሁም የኒውዮርክ ከተማ 108ኛው ከንቲባ የሆኑት ማይክል አር ብሉምበርግ፥ በፍጥነት ማሽከርከር በሀገራቸው በየዕለቱ 1 ሺህ 600 ሰዎች ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ተናግረዋል።

"ብሉምበርግ ኢኒሽዬቲቭ ፎር ግሎባል ሮድ ሴፍቲ" በዓለም ላይ ባሉ ሀገሮች ውስጥ ካሉ አጋር ድርጅቶች ጋር ሕይወትን ለማዳን ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል በትብብር በመሥራት ላይ ይገኛልም ነው ያሉት።

28/08/2025

ክቡር ጠ/ሚንስትር ዓብይ አህመድ ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ያስተላለፉት መልዕክት

በኢትዮጵያ በዓመት እስከ 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ*********************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵ...
28/08/2025

በኢትዮጵያ በዓመት እስከ 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ
*********************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ በዓመት እስከ 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረጉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህብዊ ትስስር ገጻቸው፤ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በዳንጎቴ ኢንደስትሪ ኩባንያ መካከል የማዳበሪያ ኮምፕሌክስ ባለአክሲዮን የኢንቨስትመንት ስምምነት ተፈራርመናል ብለዋል።
Source:- EBC

28/08/2025

የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት በድል ተጠናቋል። የህዳሴ ግድብ ኮንትራክተር የሆነው ሳሊኒ ኮስትራቶሪ (በአዲሱ ስያሜው WeBuild Group) የግንባታ ማሽነሪዎቹን ወደ ሁለተኛው የዓባይ ወንዝ ግድብ 24/7 እያጓጓዘ ይገኛል።

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ መሠረተ ልማቶች ግንባታ ላይ አሻራውን ያኖረው ዊቢውልድ ግሩፕ በቅርብ ቀን በይፋዊ ሥነሥርዓት የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የሚያስረክብ ይሆናል። ኩባንያው የግልገል ጊቤ 1፣ ጊቤ 2፣ ጊቤ 3 እንዲሁም የጣና በለስ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ ያደረገ ሲሆን የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየሰራ ይገኛል።

በዓባይ ወንዝ ላይ በአንድ ጊዜ የሁለት ግዙፍ ግድቦችን ለማስጀመር ፋይናንስ ማፈላለግን ጨምሮ አስፈላጊው ቅድመ-ዝግጅት ተጠናቋል::
Getnet Almaw

Hagern yemigeneba ሀቅ ነው
27/08/2025

Hagern yemigeneba ሀቅ ነው

ውሃ ላይ የሚያርፉና የሚነሱ አውሮፕላኖች ወደ አገልግሎት ሊገቡ ነው  ውሃ ላይ የሚያርፉና የሚነሱ አውሮፕላኖች ወደ አገልግሎት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን...
27/08/2025

ውሃ ላይ የሚያርፉና የሚነሱ አውሮፕላኖች ወደ አገልግሎት ሊገቡ ነው

ውሃ ላይ የሚያርፉና የሚነሱ አውሮፕላኖች ወደ አገልግሎት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።

ውሃ ላይ የሚያርፉ አውሮፕላንኖች (አምፊቢያን ኤር ክራፍት) የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎች ላይ ለአገልግሎት እንደሚውሉ ከባለሥልጣኑ መ/ቤት የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡

አውሮፕላኖቹ ከውሃ ተነስተው መሬት ላይ ማረፍ እንዲሁም ከመሬት ተነስተውም ውሃ ላይ ማረፍ የሚችሉ ናቸው ተብሏል፡፡

via addisadmas

ሰበር ዜና - አዲስ አበባ➛በርበራ የኤሌክትሪክ ባቡር ❗️    🚆🚂በዱባዩ ዓለምአቀፍ የወደብ አገልግሎት አቅራቢ Dubai Port World - DP world አማካኝነት የለማውን የሶማሊላንዱን...
27/08/2025

ሰበር ዜና - አዲስ አበባ➛በርበራ የኤሌክትሪክ ባቡር ❗️

🚆🚂

በዱባዩ ዓለምአቀፍ የወደብ አገልግሎት አቅራቢ Dubai Port World - DP world አማካኝነት የለማውን የሶማሊላንዱን የበርበራ ወደብ ከአዲስ አበባ ጋር በፈጣን የኤሌክትሪክ ባቡር መስመር ለማስተሳሰር የሚውል $3 ቢሊዮን ዶላር የቁርጥ ቀን የልማት አጋራችን ዩናይትድ አረብ ኢሜሬትስ ያቀረበች ሲሆን ግንባታው በአዲሱ 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር አስተማማኝ መረጃ ደርሶናል።

ከበርበራ አዲስ አበባ የሚዘረጋው ፈጣን የኤሌክትሪክ ባቡር የኢትዮጵያን የወደብ አማራጭ ከማስፋት ባሻገር ዓለም በዘርፉ በደረሰበት ቴክኖሎጂ የሚዘረጋ በመሆኑ የኤክስፖርት ንግዳችንን የበለጠ የሚያቀላጥፍ ይሆናል።



የዓባይ ድል በቀይ ባህር ይደገማል !!
Getnet Almaw Tiruneh

25/08/2025

#ጀግንነት
#ሐሞት
#አቅም
#አሸንፎ የመውጣት ብቃት!!

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት የሀገር አለኝታ፡ የሀገር መከታ።

25/08/2025

የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት ማርች ባንድ በሩሲያ ጎዳናዎች ከሞገስና ሙገሳ ጋር

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) የኮምቦልቻ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የስራ እንቅስቃሴን ጎበኙየኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ...
21/08/2025

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) የኮምቦልቻ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የስራ እንቅስቃሴን ጎበኙ
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) በኮምቦልቻ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የሚገኙ ባለሃብቶች የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈሚው በጉብኝታቸው በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ በስራ ላይ የሚገኙ የሃገር ውስጥ እና የውጭ ኩባንያዎችን የምርት ሂደትና የስራ እንቅስቃሴ የጎበኙ ሲሆን ከባለሃብቶቹ ጋርም በስራ ሂደቱና አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴያቸው ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚገኙ ባለሃብቶች በስራ እድል ፈጠራ፤በውጭ ምንዛሬ፤በእውቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር እንዲሁም ተኪ ምርት በማምረት ሂደት ውስጥ ያላቸውን አበርክቶ አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ዶ/ር ፍሰሃ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚ ኮርፖሬሽኑ ስራቸውን በቅርበት እንደሚደግፍ ጠቁመው ኮባንያዎቹም እየሰሩ ያለውን ስራ እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል፡፡
በኮምቦልቻ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከ6 በላይ የሃገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ገብተው በመስራት ላይ ሲሆኑ ከ5000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም ቋሚ የሆነ የስራ እድል ፈጥረዋል፡፡

20/08/2025

Address

Bole

1000

Telephone

+251924542559

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ever Light posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share