Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ Gazette Plus is committed to supplying credible information as it happens. It makes the Ethiopian Press Agency (EPA) 80+ years young.

The EPA is a pan-African media entity that has been in the media landscape for over 80 years.

የተቀናጀ የሞባይልና የዌብ መተግበሪያዎችን "ከጋዜጣ ኘላስ'' ያግኙ‼️ የፕሬስን ምርት እና አገልግሎቶች በቴሌብር እና በሲቢኢ ብር አማካኝነት በቀጥታ  ግብይት የሚከናወንበት ነው፡፡ ከሚሰጣቸ...
10/09/2025

የተቀናጀ የሞባይልና የዌብ መተግበሪያዎችን "ከጋዜጣ ኘላስ'' ያግኙ‼️

የፕሬስን ምርት እና አገልግሎቶች በቴሌብር እና በሲቢኢ ብር አማካኝነት በቀጥታ ግብይት የሚከናወንበት ነው፡፡ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ከብዙ በጥቂቱ፦

✍️ የትንታኔ ዜናዎችና አርቲክሎችን

✍️ ፖድካስት እና መልቲሚዲያ አማራጮች በነፃ

✍️ ሕትመቶች (ePapers) *በክፍያ

✍️ ክፍት የሥራ ቦታዎች * በነፃ እና በክፍያ

✍️ የጨረታ ማስታወቂያዎች *በነፃ እና በክፍያ

✍️የቆዩ ጋዜጣዎች እና ፎቶግራፎች *በክፍያ

✍️ ልዩ ልዩ የደንበኝነት (subscription) አማራጮች ያሉት

በሞባይል መተግበሪያ ያሉ አገልግሎቶች ሁሉም በዌብ አፕም ይገኛል።

👉 Android version- https://shorturl.at/wGf8j

👉For IOS coming soon.

👉 Web App address - www.press.et

የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ማጠቃለያ መርሃግብር በጉባ ተካሄደ+++++++++++++++  | የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ማጠቃለያ መርሃግብር የህዳሴ ግድብ በተገነባበት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ተ...
10/09/2025

የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ማጠቃለያ መርሃግብር በጉባ ተካሄደ
+++++++++++++++

| የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ማጠቃለያ መርሃግብር የህዳሴ ግድብ በተገነባበት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ተካሄዷል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምርቃት መርሃግብር በትናንትናው ዕለት ግድቡ በሚገኝበት ጉባ ላይ ተከናውኗል።

ከዚሁ ጎን ለጎን በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታልሞ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሄድ የቆየው የዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በጉባ ግርጌ ተካሄዷል፡፡

የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን፤ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም መካሄዱ የሚታወስ ነው።

ይህንን ተከትሎ ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በተካሄደው የአንድ ጀንበር መርሀግብር 700 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ 714 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ከእቅዱ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡ በዚህም 29 ነጥብ 7 ሚሊየን ሰዎች መሳተፋቸውንም በወቅቱ ተገልጿል።

በህዳሴው ግድብ ምረቃ መርሃግብር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ ሚንስትሮች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮችና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
+++++++++++++++++++

የጉባ ሰማይ በህዳሴ ዋዜማ++++++++++++Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
08/09/2025

የጉባ ሰማይ በህዳሴ ዋዜማ
++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

“ኢትዮጵያ ህዳሴን ለገደበችበት ካሳ መጠየቅ አለባት”- ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ (ዶ/ር)+++++++++++++++++++++  | የህዳሴው ግድብ ግንባታ ጠቃሚነቱ በተለይ ለታችኛዎቹ ተፋሰስ ሀ...
08/09/2025

“ኢትዮጵያ ህዳሴን ለገደበችበት ካሳ መጠየቅ አለባት”

- ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ (ዶ/ር)
+++++++++++++++++++++

| የህዳሴው ግድብ ግንባታ ጠቃሚነቱ በተለይ ለታችኛዎቹ ተፋሰስ ሀገራት በመሆኑ ኢትዮጵያ በራሷ ፋይናንስ ግድቡን ለገደበችበት ካሳ መጠየቅ አለባት ሲሉ ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

በአፍሪካ ቀንድ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሃይድሮ ፖለቲካ ተንታኝ ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከግድቡ ግብጽና ሱዳን ከፍተኛ ተጠቃሚ በመሆናቸው ኢትዮጵያ ግድቡን ለብቻዋ መገደብ አልነበረባትም።

የህዳሴ ግድብ ከሌሎች ጥቅሞቹ ባሻገር ግብጽ ውስጥ በከፍተኛ ትነት የሚባክን ውሃን አስቀርቷል ያሉት ኢንጂነር ጥላሁን፤ በዚህም በቀጠናው ተጨማሪ የውሃ ሀብት እንዲኖር ማስቻሉን ጠቁመዋል፡፡

እንደ ኢንጂነር ጥላሁን ገለጻ፤ ግድቡ መገንባቱ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሚደርስባቸው አደጋ ማስቀረት ችሏል፤ ለአብነትም ጎርፍ እና የመሳሰሉት ማንሳት ተገቢ ነው፡፡ በዚህም በዓመት ከሦስት እስከ አራት ጊዜ ያለምንም አደጋ ማምረት እንዲችሉ እድል ፈጥሯል፡፡

ኢንጂነር ጥላሁን አክለውም፤ ግድቡ ከዚህ በተጨማሪም የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች አሉት ያሉ ሲሆን ሀገራቱ አሁንም የዓባይ ተፋሰስ እንዲለማ ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ውሃ ሲጨምር ሌሎች ሀገራት ላይ መጨመሩ የግድ መሆኑን ገልጸው፤ ህዳሴ በትነት የሚባክነው ውሃ የሚቀንስ በመሆኑ በድርቅ ጊዜ ለቀጠናው ከፍተኛ እፎይታ የሚፈጥር ነውም ብለዋል፡፡

በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++++++

GGazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢትዮጵያ
#ህዳሴ #ግድብ #ግብጽ #ሱዳን #ተፋሰስ #ዓባይ #አፍሪካ

በአገር ውስጥ ያልተለመዱ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አኩሪ እምርታዊ ድሎች ተመዝግበዋል++++++++++++++++++++++  | በአገር ውስጥ ያልተለመዱ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አኩሪ እምር...
08/09/2025

በአገር ውስጥ ያልተለመዱ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አኩሪ እምርታዊ ድሎች ተመዝግበዋል
++++++++++++++++++++++

| በአገር ውስጥ ያልተለመዱ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አኩሪ እምርታዊ ድሎች መመዝገባቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ጷጉሜ 3 - የዕምርታ ቀን - "ዕምርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው ዕለት እየተከበረ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ በኢንዱስትሪዎች ከዚህ በፊት እንደ አገር ብዙም ያልተለመዱ አዳዲስ ምርቶችን የማምረት ጅማሮዎች እየታዩ ነው።

በአገር ውስጥ የሚመረቱ ማምረቻ ማሽነሪዎች ከአገር ውስጥ ገበያ አልፈው ወደ ውጭ ገበያ ለማቅረብ የተዘጋጁ አምራቾች አሉ ያሉት አቶ መላኩ፤ ከሚታወቁ የምርት ዓይነቶች ለየት ያሉ ምርቶችን ማመረት ወደ ሚቻለበት እየደረሰ ነው ብለዋል፡፡

ፋብሪካዎች ብረትን ከዜሮ የአይረን ኦር ጀምሮ እስከ መለዋወጫ ማምረት የደረሰ አቅም መፈጠሩን ጠቅሰው፤ ከፍተኛ የእወቀትና የቴክኖሎጂ አቅም የታየባቸው የማምረት ሂደቶች መፈጠራቸውን ገልጸዋል፡፡

ኢንዱስትሪዎችን የማምረት ተግዳሮቶች በመፍታት በኩል ከፍተኛ መደላድል መፈጠሩን በመግለጽ፤ ለመለዋወጫ የሚወጡ ወጪዎችን እያስቀረ መሆኑንና በዘርፉ ያለውን ተወዳዳሪነት እያሳደግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የቢጂአይ ኢትዮ ኢንዱስትሪያል ኤንድ ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን ባለቤትና መስራች ኢንጂነር ቢጂአይ ናይከር በበኩላቸው፣ በአገሪቱ የኢንዱስትሪና ግብርና አገልግሎትን ለማሳለጥ ፋብሪኬሽን ኢንጂነሪንግ የግድ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ከሚያመርቷቸው የማሽነሪ ምርቶች መካከል በግብርናው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰው፤ እስካሁን ድረስ ወደ 110 ፋብሪካዎች ተመርተው ባንኮች፣ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት፣ ግለሰቦች ኢንቨስተሮችና የእርሻ ባለቤቶች እየተጠቀሙባቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከውጭ ይገቡ የነበረውን የሚያስቀሩና በአገር ውስጥ ተመርተው የሚቀርቡ ተኪ ምርቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ቴክኖሎጂው ለብዙ እንስሳት በአጭር ጊዜና በአነስተኛ ጉልበት መኗቸውን እያቀነባበሩ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

የቴክኖሎጂ ሽግግር አገሪቱ በያዘችው ወደ ኢንዱስትሪ የመሄድ ጉዞ የራሱን ጠጠር የሚያቀብል ስራ ነው ያሉት ኢንጂነር ቢጂአይ፣ ከ300 በላይ ሰዎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል።

መንግሥት የአገር ውስጥ ኢንቨስተሩ ዝግጁነት እንዲኖረው ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ነገር ግን የመሰረተ ልማትና የፋይናንስ ድጋፉ በፋብሪኬሽን ዘርፉ እንደሚስተዋል ገልጸዋል፡፡

በማርቆስ በላይ
++++++++++++++++++
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢትዮጵያ #ኢንቨስትመንት #ኢንተርፕረነርሺፕ #ቴክኖሎጂ #ኢኮኖሚ

የካርል ቡሽቢ ታላቅ ተልዕኮ+++++++++++  | አብዛኛዎቻችን በአቅራቢያችን ወደሚገኙ ቦታዎች ስለመራመድ እናማርራለን። ነገር ግን እ.ኤ.አ ከ1998 ጀምሮ ለሶስት አስር ዓመታት ያለማቋረጥ...
07/09/2025

የካርል ቡሽቢ ታላቅ ተልዕኮ
+++++++++++

| አብዛኛዎቻችን በአቅራቢያችን ወደሚገኙ ቦታዎች ስለመራመድ እናማርራለን። ነገር ግን እ.ኤ.አ ከ1998 ጀምሮ ለሶስት አስር ዓመታት ያለማቋረጥ እየተራመደ ያለ ሰው መኖሩን ብንነግራችሁስ?

በዓለም ታላቅ ተጓዦች ዝርዝር ውስጥ የቀድሞ የፓራሹት ወታደር ካርል ቡሽቢ የተባለ እንግሊዛዊ የሚጠቀስ ሲሆን፤ የሚታወቀውም በድፍረት እና በድንቅ አቅም ነው ።

ካርል ቡሽቢ መነሻውን በቺሊ ፑንታ አሬናስ በማድረግ ወደ ትውልድ ከተማው እንግሊዝ ሃል ለመጓዝ ተልእኮውን እ.ኤ.አ በ1998 ጀመረ።

መኪና፣ ጀልባ፣ አውሮፕላን ወይም ብስክሌት ሳይጠቀም በእግሩ ብቻ የሚጓዝ ሲሆን፤ ይህም ማለት አሜሪካን፣ እስያን፣ አርክቲክን እና አውሮፓን ጨምሮ ከ58 ሺህ ኪ.ሜ በላይ በእግር ብቻ መሄድ ማለት ነው። ጉዞው “የጎሊያድ ጉዞ” ተብሎ ይጠራል፡፡

ካርል በጉዞ በመካከለኛው አሜሪካ ጫካዎች፣ በረዷማ በሆነው የቤሪንግ ስትሪት እና ሳይቤሪያን ጨምሮ ከ20 በላይ ሀገሮችን በእግር ተራምዷል፡፡ በበረዶ፣ በምድረ በዳ፣ በደን ውስጥ በመንቀሳቀስ ድንቅ ታሪክ ሰርቷል፡፡

በአብዛኛው ጉዞው በረዶ፣ ወንዞች እና የየብስ መንገዶች ያሉት ስለሆነም በእግር መሄድ የሚችለው በክረምት መጨረሻ እና በፀደይ መጀመሪያ ላይ ብቻ ነው።

በ2022 ወደ አውሮፓ የሚመለስበት መንገድ በሩሲያ- ዩክሬን ጦርነት ተጨናግፎ የነበረ ሲሆን፤ ኢራንን ለማለፍ አማራጭ ስላልነበረው ከ299 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆነውን የዓለም ትልቁን የካስፒያን ባህር ለመዋኘት መርጧል፡፡
ካርል በጉዞ ወቅት ተይዟል፣ ቪዛውን ተከልክሏል ብሎም ታግዶ ያውቃል።

አልፎ ተርፎም የስፖንሰርሺፕ ኪሳራ ደርሶበታል፣ አደገኛ አየር ንብረት እና የዱር እንስሳት በመንገዱ አጋጥመውታል፡፡ ግን የእግር ጉዞውን የሚያቆመው ምንም ነገር አልነበረም፡፡

ጉዞው 12 ዓመት እንደሚወስድ አስቦ የነበረ ቢሆንም ለ27 ዓመታት ያህል ተጉዟል፡፡ በእነዚህ ጊዜያት በሀገራት ያሉ ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተለውጠዋል፤ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ተፈጥረዋል፤ ወረርሽኝ፣ በርካታ ጦርነቶች እና ትርምሶችን አልፈዋል፡፡

ካርል ቪዛ እስኪደርስ እየጠበቀ አሁን ሜክሲኮ የሚገኝ ሲሆን፤ በቀጣይም ቱርክን አቋርጦ አውሮፓ ለመግባት አቅዷል።

ለ27 ዓመታት ከቺሊ ወደ እንግሊዝ የሚያደርገው ታሪካዊ ጉዞውን ሊጨርስ 3 ሺህ 218 ኪሎ ሜትር ብቻ ቀርቶታል፡፡

የዓለም ረዥሙን የእግር ጉዞ በመጓዝ እ.ኤ.አ 2026 መስከረም ወር ተልዕኮውን እንደሚያሳካም ይጠበቃል።

የካርል ቡሽቢ ድፍረት፣ ቆራጥነት፣ ተስፋ እና ያሰበውን ለመፈጸም ያወጣው ኃይል የአይበገሬነት ምሳሌ ሆኖ ተወስዷል።

በማህሌት ብዙነህ
++++++++++++++++++++++++


#ኢትዮጵያ
#ጉዞ #ተጓዥ

ህዳሴ ግድብን ከአዲስ አበባ መቆጣጠር የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተገጥሟል+++++++++++++++++++++++++++  | ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከአዲስ አበባ መቆጣጠር የሚያስችል ቴ...
06/09/2025

ህዳሴ ግድብን ከአዲስ አበባ መቆጣጠር የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተገጥሟል
+++++++++++++++++++++++++++

| ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከአዲስ አበባ መቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ኃይል ማመንጫ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለጹ፡፡

ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ከጋዜጣ ፕላስ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ግድቡ አዲስ አበባ ሆኖ ሁሉንም ነገር መቆጣጠር የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የተላበሰ ‘አውቶማትክ’ የኃይል ማመንጫ ነው፡፡

መንግስትን በመወከል የግድቡን ግንባታ ሲያስተዳድር የቆየው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሆኑን የገለጹት ስራ አስኪያጁ፤ በቀጣይም ግደቡ በኢትዮጵያዊያን ሙሉ አቅም እንደሚተዳደር ጠቁመዋል፡፡

የግድቡ ዩኒቶች የሚያመነጩትን ኃይል ለማንቀሳቀስና ለመጠገን እንዲያስችል ከግንባታው ጅማሮ አንስቶ ኢትዮጵያዊን ባለሞያዎችን በመመደብ ምን የት እንደተተከለ እንዲሁም በየትኛው መስመር እንደሄደ እንዲያውቁ መደረጉን ጠቅሰው፤ ግድቡ ትልቅ ኃይል ማመንጫ በመሆኑ ለባለሞያዎቹ አስፈላጊው ስልጠና መሰጠቱን ኢንጂነር ክፍሌ ተናግረዋል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጥቂት አካላት አይደለም ያሉት ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊያንና ተውልደ ኢትዮጵያውያ አሻራ ያረፈበት የማንነት መገለጫ ዓርማ መሆኑን አያይዘው ገልጸዋል፡፡

በአማን ረሺድ
+++++++++++++++++++++


#ፕሮጀክት #አፍሪካ #ግድብ #ዓባይ #ህዳሴ #ንጋት #ኤሌክትሪክ #ወንዝ #ኢትዮጵያ #ተፋሰስ

እሁድ ጷጉሜ 2 2017 ዓ.ም ቀይ የጨረቃ ግርዶሽ ይከሰታል+++++++++++++++++++++የጨረቃ ግርዶሹ በመላው ኢትዮጵያ እንደሚታይ ይጠበቃል፡፡ ጨረቃ ቀይ ሆና እንደምትታይም ይጠበቃል።ክ...
05/09/2025

እሁድ ጷጉሜ 2 2017 ዓ.ም ቀይ የጨረቃ ግርዶሽ ይከሰታል
+++++++++++++++++++++

የጨረቃ ግርዶሹ በመላው ኢትዮጵያ እንደሚታይ ይጠበቃል፡፡ ጨረቃ ቀይ ሆና እንደምትታይም ይጠበቃል።

ክስተቱን ለመመልከት ምንም መመልከቻ መሳሪያ ሳያስፈልግ በዐይን መመልከት የሚቻል ሲሆን፤ በዐይን ላይ ምንም ጉዳት እንደማያስከትል ተገልጿል።
++++++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ጨረቃ #ግርዶሽ #ኢትዮጵያ

"ልምድ በሌለው ኮንትራክተር ምክንያት መንግስት 450 ሚሊዮን ዩሮ ካሳ ከፍሏል"- ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ++++++++++++++++++++++++++  | በታላቁ የኢትዮጵ...
04/09/2025

"ልምድ በሌለው ኮንትራክተር ምክንያት መንግስት 450 ሚሊዮን ዩሮ ካሳ ከፍሏል"

- ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ
የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ
++++++++++++++++++++++++++

| በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ ስለሀይድሮ ኤሌክትሪክ ምንም አይነት ልምድ በሌለው ኮንትራክተር ምክንያት መንግስት 450 ሚሊዮን ዩሮ ካሳ ከፍሏል ሲሉ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለጹ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ከጋዜጣ ፕላስ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱን ረጅም ጊዜ ያቆየው እና ትልቅ መሰናክል የተፈጠረው ምንም አይነት ልምድ የሌለው ኮንትራክተር ትልቁንና ውስብስቡን የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ስራ እንዲሰራ መደረጉ ነው።
የበለስ ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክትን ለመገንባት የፈጀው 460 ሚሊየን ዩሮ መሆኑን ለማሳያነት ያነሱት ኢንጂነር ክፍሌ፤ ህዳሴ ግድብ ላይ ልምድ የሌለው ኮንትራክተር እንዲሠራ መደረጉ አንድን የኤሌክትሪክ ኃይል ጣቢያ መገንባት የሚያስችል ኪሳራ አድርሷል ብለዋል፡፡

ኮንትራቱ ከተፈረመ ከሁለት ወራት በኋላ የሲቪል ስራውን የወሰደው ኮንትራክተር በግድቡ መሰረት ላይ ልል ድንጋይ እንዳጋጠመው እና ድንጋዩን አውጥቶ መሠረቱን በኮንክሪት ለመሙላት ተጨማሪ ሶስት ዓመት እንደሚወስድበት ገልጾ እንደነበር ስራ አስኪያጁ አስታውሰዋል፡፡

የሀገር ውስጥ ኮንትራክተር በዘርፉ እንዲበቃ፤ በጥሩ እሳቤ የፕሮጀክቱን ግንባታ ቢጀምርም ነገር ግን መንግስት በቂ ዝግጅት ሳይደረግ ለኮንትራክተሩ እንዲሰጥ መወሰኑ ትልቅ ስህተት እንደነበር በቁጭት ተናግረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ እንደተጀመረ አካባቢ ህጻናት ቁርሳቸውን ትተው፤ እናቶች ከመቀነታቸው ያላቸውን ገንዘብ ሰጥተው እንዲሁም ህዝቡ በአጠቃላይ ተሳትፎ ሲሰራ እንደነበር ያወሱት ሥራ አስኪያጁ፤ በቂ መረጃ ለህዝቡ ባለመሰጠቱ የኢትዮጵያዊያንን ሞራል በእጅጉ እንደጎዳ ጠቁመዋል፡፡
ሀገራዊ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፕሮጀክቱ የገጠሙትን ችግሮች በመገምገም እና የኮንትራት ይዘቱ እንዲቀየር በማድረጋቸው ፕሮጀክቱ ነብስ መዝራት መቻሉን ተናግረዋል፡፡

መንግስት ከቦርድ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ድረስ ሪፎርም ካደረገ በኋላ የፕሮጀክቱ ስራ ሲጀመር ስራውን ለማስቆም የተፋሰሱ ሀገራት የተልዕኮ ጦርነት መጀመራቸውን ኢንጂነር ክፍሌ ገልጸዋል፡፡

በአጠቃላይ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በመንግስትና በህዝብ ርብርብ በርካታ መሰናክሎችን በማለፍ ለመጠናቀቅ እንደበቃ ግልጸዋል፡፡

በአማን ረሸድ
+++++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢትዮጵያ
#ዓባይ #ህዳሴ #ተፋሰስ #አፍሪካ #ፕሮጀክት #ኤሌክትሪክ

“ህዳሴ ዓድዋን የደገመ ‘የዚህ ትውልድ አርበኝነት’ ውጤት ነው”- ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ++++++++++++++++++++++++++  | ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዓድዋን የደገመ የዚህ...
04/09/2025

“ህዳሴ ዓድዋን የደገመ ‘የዚህ ትውልድ አርበኝነት’ ውጤት ነው”

- ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን
++++++++++++++++++++++++++

| ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዓድዋን የደገመ የዚህ ትውልድ የአርበኝነት ውጤት ነው ሲሉ የጥንት ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለጹ፡፡

ፕሬዝዳንቱ የህዳሴ ግድብ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መሸጋገሩን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ግድቡ በተለያዩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች አልፎ ለዚህ መብቃቱ ትውልዱ በጋራ ባደረገው የአርበኝነት ተጋድሎ መሆኑ ተናግረዋል፡፡

ልጅ ዳንኤል አክለውም፤ ዓድዋ ድል ሲነሳ ከጫፍ ጫፍ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ የጻፉት ደማቅ ቀለም ነው ያሉ ሲሆን፤ ህዳሴም የዚህ ዘመን ትውልድ የአያቶቹንና የቅድመ አያቶቹ ፈለግ በመከተል ተረባርቦ ዳግም ያቆመው አደዋ ነው ብለዋል፡፡

ህዳሴ ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን ለቀጠናውም ጭምር አዲስ ተስፋ የሚያጭር ነው ያሉት ልጅ ዳንኤል፤ የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማጎልበት መሰረተ ልማት የሚያስፋፋ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

እንደ ልጅ ዳንኤል ገለጻ፤ የህዳሴ ግድብ ለዚህ ደረጃ ያደረሰው ጉሊት የሚሸጡ እናቶች ከመቀነታቸው፣ በላባቸው የሚተዳደሩ አባቶች ከኪሳቸው ባሰባሰቡት ገንዘብ ነው፡፡ ከህዳሴው ግድብ ውጤት በመነሳትም ለሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክት መትጋት ያስፈልጋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የህዳሴው ግድብ ለዚህ ክብር እንዲበቃ የአመራሩ ሚና ቀላል እንዳልነበር አስረድተዋል፡፡

በቀጣይ ከዚህ ፕሮጀክት ሀገር በምትፈልገው መልኩ መጠቀም እንድትችል ሁሉም በየፊናው የራሱን ሚና መወጣት እንዳለበት ገልጸው፤ ትውልዱ ይበልጥ የአርበኝነት ስራ ለመስራት እርስ በእርስ ከመጎሻሸም ወጥቶ ፊቱን ወደ ልማት ማዞር እንዳለበትም መክረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ የቀድሞ ትውልድ ቁጭት የገረሰሰ የአሁኑ ትውልድ ድል ያበሰረ እንዲሁም የመጪው ትውልድ ተስፋ በመሆኑ መላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++++++


#ኢትዮጵያ #ህዳሴ #አባይ #ግድብ #ዓባይ #ንጋት

03/09/2025
ተማሪዎች ያለምንም ሌላ መመዘኛ በያዙት ድግሪ ውጭ ሀገር ስራ ሊያገኙ ነው++++++++++++++++++++++++  | ተማሪዎች ያላቸውን ድግሪ ተጠቅመው ያለምንም ሌላ መመዘኛ የውጭ ሀገር ስራ...
02/09/2025

ተማሪዎች ያለምንም ሌላ መመዘኛ በያዙት ድግሪ ውጭ ሀገር ስራ ሊያገኙ ነው
++++++++++++++++++++++++

| ተማሪዎች ያላቸውን ድግሪ ተጠቅመው ያለምንም ሌላ መመዘኛ የውጭ ሀገር ስራ እንዲያገኙ ለማድረግ ዕውቅና አግኝቻለሁ ሲል የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ በአራት የትምህርት መርሀግብሮች ዓለምአቀፍ እውቅና አገኝቷል።

ያገኘውን ዕውቀና አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ደረጃ እንግዳ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በአፕላይድ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ማለትም በባይዮ ቴክኖሎጂ፣ በምግብ ሳይንስና በአመጋግብ ስረዓት፤ በኬሚካል ኢንዱስትሪና በጅኦሎጂ ዓለም አቀፍ ዕውቅና አግኝቷል።

ዩኒቨርሲቲው ያገኘው ዕውቅና በተለያዩ መርሃግብሮች የተመረቁ ተማሪዎች ያለምንምን መመዘኛ በውጭ ሀገራት ስራ እንዲያገኙ ያደርጋል ብለዋል።

ተማሪዎች የተመረቁበትን ድግሪ ይዘው በውጭ ሀገር ስራ መቀጠር አይችሉም ነበር፤ ከዚህ በፊት በሚቀጠሩበት ሀገር መመዘኛ መፈተን ግዴታ ነበር፤ አሁን የተገኘው ዕውቅና በድግሪያቸው ቀጥታ ስራ እንዲቀጠሩ የሚያደርግ ነው ሲሉ አብራርተዋል።

የተማሪዎቻችን ድግሪ ዓለም አቀፍ ዕውቅናን ያገኘ ባለመሆኑ የውጭ ሀገር ኢንዱስትሪዎች ወደ ሀገር ውሰጥ ሲገቡ የራሳቸውን የተማረ የሰው ሀይል ይዘው ነው የሚመጡት፤ ዕውቅናው ይህንን ችግር ይፈታል ሲሉ ገልጸዋል።

ተማሪዎች ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው የድግሪ የትምህርት ማሰረጃ መያዛቸው በሀገር ውስጥ ባሉ የውጭ ድርጅቶች እንዲቀጠሩ ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል። ዕውቀናው የትምህርት ስብራትን የሚጠግን ነውም ብለዋል።

ዓለም አቀፍ ዕውቅና የተገኘባቸውን የትምህርት ፕሮግራሞች ለውጭ ተማሪዎች ለመስጠት እየተሰራ ነው፤ የውጭ ተማሪዎች መማራቸውም ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ገቢ ያስገኛል ሲሉ ገልጸዋል።

ዕውቅናው እ.ኤ.አ ከ2023 ዓም የተመረቁትንም እንዳሚያጠቃልል አስረድተዋል።

በኢንጀሪንግ ትምህርት በዘጠኝ የትምህርት ፕሮግራሞች ዓለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት መሰራቱን ገልጸው፤ ዘርፎቹ በቀጣይ ህዳር ወር ዕውቅና ያገኛሉ ብለዋል።

በታደሠ ብናልፈው
+++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢትዮጵያ

Address

Arada Sub City Wereda 09
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share