Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ Gazette Plus is committed to supplying credible information as it happens. It makes the Ethiopian Press Agency (EPA) 80+ years young.

The EPA is a pan-African media entity that has been in the media landscape for over 80 years.

እስራኤልና ሃማስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ደረሱ++++++++++++  | በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ሲደረግ የቆየው ድርድር በስምምነት ተጠናቋል።በእስራኤል እና በሃማስ መካከል በተካሄ...
09/10/2025

እስራኤልና ሃማስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ደረሱ
++++++++++++

| በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ሲደረግ የቆየው ድርድር በስምምነት ተጠናቋል።

በእስራኤል እና በሃማስ መካከል በተካሄደው ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ሸምጋዮች ሁለቱ ወገኖች በጋዛ ሰርጥ ያለውን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ሐሙስ ማለዳ ላይ አስታውቀዋል ሲል ሪወተርስ ዘግቧል።

የተኩስ አቁሙ ዛሬ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን፤ በ72 ሰዓታት ውስጥ የእስረኞች ልውውጥ እንደሚደረግም ታውቋል።

በስምምነቱ የመጀመርያ ምዕራፍ ከሁለቱም ወገን እስረኞች ይለቀቃሉ ሲሉ የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ቃል አቀባይ በኤክስ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።

ሃማስ በህይወት ያሉ የእስራኤል 20 እስረኞች በአንድ ጊዜ ይፈታሉ፤ በአምስት አቅጣጫ ወደ ጋዛ ሰርጥ ሰብዓዊ እርዳታን የጫኑ መኪኖች መግባት ይጀምራሉ ተብሏል በስምምነቱ ላይ።

ሃማስን ትጥቅ ማስፈታትና የጋዛ ሰርጥን ማን ያስተዳድር የሚለው ጉዳይ ሁለተኛው የድርድር ምዕራፍ ተደርጓል።

ሁለተኛው ምዕራፍ ድርድር ከመጀመርያው አፈፃፀም በኋላ እንደሚቀጥል አል አረቢያ ዘግቧል።

የሐማስ ተጨማሪ የልዑካን ቡድን ማምሻውን በምክትል ዋና ጸሃፊው እየተመራ ግብፅ ገብቷል።

ልዑካኑ ጦርነቱን በዘላቂነት ለማስቆም በሚደረገው ድርድር ላይ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።

በአረቡ ሙህየ
+++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

ሆስፒታሉ 60 በመቶ የህክምና ኦክስጅን ፍጆታውን በራሱ እየሸፈነ ነው  +++++++++++++++++++  | ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 60 በመቶ የህክምና ኦክስጅን ፍጆታውን በራሱ ...
08/10/2025

ሆስፒታሉ 60 በመቶ የህክምና ኦክስጅን ፍጆታውን በራሱ እየሸፈነ ነው
+++++++++++++++++++

| ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 60 በመቶ የህክምና ኦክስጅን ፍጆታውን በራሱ እየሸፈነ መሆኑን አስታወቀ።

የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አብርሀም እሸቱ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የሆስፒታሉ 40 በመቶ የሚሆኑ ታካሚዎች የሳንባና ተያያዥ ህመም ተጠቂዎች ናቸው፡፡

በዚህም የተነሳ አብዛኛዎቹ ታካሚዎች የህክምና ኦክስጅን የሚፈልጉ በመሆናቸው ሆስፒታሉ የኦክስጅን አቅርቦቱን ለማሻሻል የተለያዩ ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል፡፡

ሆስፒታሉ በግቢው ውስጥ የኦክስጅን ማምረቻ በመትከል ኦክስጅን እያመረተ መሆኑን ገልጸው፤ በአሁኑ ሰዓትም 60 በመቶ የሚሆነውን የኦክስጅን ፍጆታ በራሱ እየሸፈነ መሆኑ ጠቅሰዋል፡፡

ከዚህ በተጨማም በስሊንድር የሚቀርበው ኦክስጅን በቱቦ ወደ የክፍሎቹ እንዲደርስ ማድረግ በመቻሉ ብክነትን እንዳስወገደ አብራርተዋል።

ተግባሩ የኦክስጅን አቅርቦት ብክንት እንዳይፈጠር ከማድረጉም ባሻገር በትራንስፖርትና መሰል ወጪዎች ምክንያት ይቆራረጥ የነበረን ኦክስጅን በወጥነት ለማዳረስ የረዳ መሆኑ ገልጸዋል፡፡

መስከረም ሰይፉ
++++++++++++++++++++++++++++

የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ አስተማማኝ ደርጃ ላይ ደርሷል+++++++++++++++++++++  | የኢትዮጵያ የባሕር  በር የማግኘት ጥያቄ አስተማማኝ ደርጃ ላይ  ደርሷል ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዜዳ...
06/10/2025

የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ አስተማማኝ ደርጃ ላይ ደርሷል
+++++++++++++++++++++

| የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ አስተማማኝ ደርጃ ላይ ደርሷል ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዜዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ተናገሩ።

6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው፡፡

ንግግር ያደረጉት ፕሬዜዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፤ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ ከፍ ወደ አለ ደርጃ የተሻገረበት ነው ብለዋል።

የባሕር በር ፍትሕዊ ተጠቃሚነታችንን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያገኘበት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ሀገራችን በድንበር ተሻጋሪ ሀብት ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ስተቀበል፤ አስተማማኝ የባሕር በር የማግኘት መብቷን ማረጋገጥ ይኖርባታል ሲሉ ጠቁመዋል፡፡
++++++++++++++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

05/10/2025
 #ኢሬቻ አበባ በሆነችው አዲስ አበባ++++++++++++++++
04/10/2025

#ኢሬቻ አበባ በሆነችው አዲስ አበባ
++++++++++++++++

በአፋር ክልል በ900 ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምገባ ሊጀመር ነው +++++++++++++++++  | በክልሉ 900 ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምገባ ሊጀመር መሆኑን የአፋር ክልል ትምህርት ቢ...
01/10/2025

በአፋር ክልል በ900 ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምገባ ሊጀመር ነው
+++++++++++++++++

| በክልሉ 900 ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምገባ ሊጀመር መሆኑን የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

በትምህርት ቢሮው የመማርና ማስተማር ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁመድ አብደላ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ በተያዘው የ2018 የትምህርት ዘመን 372 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ገበታ ላይ ይገኛሉ።

በክልሉ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች 900 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ለመመገብ በዝግጅት ላይ ናቸው ብለዋል።

በተማሪዎች የምገባ ፕሮግራሞች የማኅበረሰቡ ተሳትፎ እንደተጠበቀ ሆኖ ተቋማትም የበኩላቸውን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በጥናት የተለዩ የትምህርት ሰብራቶችን ለመጠገን የመምህራንን አቅም ማሻሻልን ጨምሮ በተማሪዎች የምገባ ፕሮግራሞች ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ሊሰሩ መታቀዱን አብራርተዋል።

የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ የትምህርት ጥራት ችግሮችን ለመቅረፍ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በትኩረት እንደሚሠራም አያይዘው ገልጸዋል።

በአፋር ክልል የሚታየው የተማሪዎች ውጤት ማነስ ዘርፉ ላይ እንደ ትልቅ ችግር እንደሚነሳ ጠቁመው፤ ይህን ችግር ከመሠረቱ ነቅሎ ለመጣል የባለድርሻ አካላት ትብብር እና ርብርብ ስለሚያስፈልግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በካሚል መሐመድ (ሠመራ)
+++++++++++++++++++++++


#አፋር #ትምህርት #ምገባ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር  ኳታርን ይቅርታ ጠየቁ++++++++++++++++++++  | የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሀገራቸው በዶሃ የሃማስ መሪዎች ላይ ባደረሰችው ጥቃት ...
30/09/2025

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኳታርን ይቅርታ ጠየቁ
++++++++++++++++++++

| የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሀገራቸው በዶሃ የሃማስ መሪዎች ላይ ባደረሰችው ጥቃት በኳታር ዜጋ ለፈጸመችው ግድያ ኳታርን ይቅርታ ጠየቁ።

ኔታንያሁ የኳታርን ሉዓላዊነት በመጣስ ለፈጸመችው ድርጊት የኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ መሀመድ ቢን አብዱራህማን ቢን ጃሲም አልታኒን ይቅርታ ጠይቀዋል።

እስራኤል ዳግም እንደዚህ አይነት ጥቃት እንደማትፈፅም ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ማረጋገጣቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

የኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ መሀመድ ቢን አብዱራህማን ቢን ጃሲም አልታኒ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ኔታንያሁ በዋይት ሀውስ በተገናኙበት ወቅት በጋራ ባደረጉት ጥሪ ይቅርታውን እንደተቀበሉ ዘገባው ጠቁሟል።

እስራኤል በሴፕቴምበር 9 በዶሃ እየተካሄደ ባለ የተኩስ አቁም ድርድር ወቅት በሃማስ መሪዎች ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ አምስት ዝቅተኛ የሃማስ አባላት እና አንድ የኳታር የጸጥታ ባለስልጣን መግደሏን ዘገባው አስታውሷል።

በአማን ረሺድ
++++++++++++++++++++
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#እስራኤል #ኳታር

የማዕድን አልሚዎችን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችል አሠራር ሊዘረጋ ነው+++++++++++++++++++++++  | ማዕድን አልሚዎች ያለባቸውን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ በቀጥታ ነዳጅ እን...
29/09/2025

የማዕድን አልሚዎችን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችል አሠራር ሊዘረጋ ነው
+++++++++++++++++++++++

| ማዕድን አልሚዎች ያለባቸውን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ በቀጥታ ነዳጅ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ እንደሚገኝ ማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።

ጉዳዩ በተለይ ልዩ አነስተኛ ማዕድን አልሚዎችን የሚመለከት መሆኑም ተነግሯል።

የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ በ2017 በጀት ዓመት ከፍተኛ የማዕድን ምርት የተገኘው ከልዩ አነስተኛ ማዕድን አልሚዎች ነው።

ይህንን ለማበረታታት በተያዘው ዓመት አልሚዎቹ ያለባቸውን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ አሠራር ይዘረጋል ብለዋል።

አሠራሩ አምራቾቹ በቀጥታ ነዳጅ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሚሆን ገልጸዋል።

ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በውጤቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ማዕድናት በሀገር ውስጥ መተካት እና የውጭ ምንዛሪ ማዳን እንደሚቻል አመላክተዋል።

በዓመለወርቅ ከበደ

+++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ማዕድን #ኢንዱስትሪ

በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ለመቀየር መመሪያ እየተዘጋጀ ነው++++++++++++++++++++++++++++  | በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ለመቀየር ስታ...
28/09/2025

በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ለመቀየር መመሪያ እየተዘጋጀ ነው
++++++++++++++++++++++++++++

| በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ለመቀየር ስታንዳርድ ፀድቆ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በኢፕድ ለምትታተመው ዘመን ኢኮኖሚ እንደገለጹት፤ በነዳጅ የሚሠሩና አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ተሽከርካሪዎች ዕጣ ፈንታቸው ወደ ኤሌክትሪክ መቀየር ነው።

ለዚህም የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ መቀየሪያ ስታንዳርድ ጸድቆ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

የኤሌክትሪክ መኪና በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ ባለበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያም ከ100 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን ወደ ገበያው ማስገባት ችላለች ያሉት ኃላፊው፤ በመጪዎቹ 10 ዓመታት ወደ ሀገር ውስጥ ከሚገቡ ተሽከርካሪዎች መካከል 95 በመቶ የሚሆኑትን የኤሌክትሪክ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት የኤሌክትሪክ መኪና ምርትን ለማፋጠን፣ የነዳጅ ወጪን ለመቀነስ እና አረንጓዴ ከባቢን ለመገንባት አቅዶ እየሠራ ሲሆን፤ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥም ከ500 ሺህ በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑ ገልጸዋል።

በፍሬህይወት አወቀ

++++++++++++++++

#ትራንስፖርት #ኤሌትሪክመኪና

የዓለም የእህል ዘርን የሚጠብቀው ካዝና+++++++++++++++++++++  | ካዝናው ‘ስቫልበርግ ሲድ ዞልት’ የሚል ስያሜ ያለው ሲሆን በኖርዌይ መንግሥት ስር በምትገኘው ኖርዌጂያን ደሴት ላ...
27/09/2025

የዓለም የእህል ዘርን የሚጠብቀው ካዝና
+++++++++++++++++++++

| ካዝናው ‘ስቫልበርግ ሲድ ዞልት’ የሚል ስያሜ ያለው ሲሆን በኖርዌይ መንግሥት ስር በምትገኘው ኖርዌጂያን ደሴት ላይ ይገኛል።

ታድያ ይህ ካዝና በዚች ደሴት ላይ መገንባቱ የሰው ሰራሽም ሆነ የተፈጥሮ አደጋ እንዳይደርስበት ያደርጋል።

ካዝናው ዓለም ላይ ያለ የእህል ዘር በሙሉ ምንም አይነት አደጋ ሳይደርስበት ማስቀመጥ የሚችል ሲሆን፤ የዓለም ሀገራት ያላቸውን የእህል ዘር ናሙና ወደዚህ ካዝና አስገብተዋል።

የእህል ዘር በሰው ሰራሽም ሆነ በተፈጥሮ የመጥፋት አደጋ ቢያጋጥመው ለማትረፍ ታልሞ የተገነባው ይህ ካዝና፤ ጦርነት ተነስቶ ኒውክለር ቢፈነዳ እንኳን ካዝናውን ማጥፋት እንደማይችል ይነገራል።

በአሁኑ ጊዜ ዓለም ላይ የማይገኙና የጠፉ ዘሮችም በዚህ ካዝና እንዳሉ ይገለፃል።

ካዝናው ከኔጌቲቨ 18 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ቀዝቃዛ ቦታ ላይ ስለሚገኝ በውስጡ ያሉ የእህል ዘሮች ከመቶ ዓመታት በላይ ሳይበላሹ እንዲቆዩ ያደርጋል።

ካዝናው ሙሉ በሙሉ በኖርዌይ መንግስት የሚተዳደር ሲሆን፤ ለመገንባትም ከ8 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላይ በላይ ወጪ ወቶበታል።

በበረዷማ ተራሮች ላይ የተገነባው ይህ ካዝና ወደ ታች 120 ሚትር ርቀት አለው ።

ከውጭ የሚመለከተው ሰውም መግቢያ በሩን እንጂ ከመሬት ስር ያለው የካዝናውን አካል ማየት የማይችል ሲሆን ማንኛው ሰው
ቦታውን መጎብኘት ቢፈልግ የተከለከለ ነው።

በዳግማዊት አበበ
++++++++++++++++++++++++


#ሰብል #ግብርና #ኢትዮጵያ

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርት በዘንድሮው ዓመት መስጠት ይጀምራል+++++++++++++++++++++++++++++  | በዘንድሮ የትምህርት ዘመን የኒውክሌር ምህንድስና ትም...
25/09/2025

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርት በዘንድሮው ዓመት መስጠት ይጀምራል
+++++++++++++++++++++++++++++

| በዘንድሮ የትምህርት ዘመን የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርትን በሁለተኛ ዲግሪ መስጠት እንደሚጀምር የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ የድህረ ምረቃ መርሃ ግብር ዲን ዜናማርቆስ ባንቴ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በአዲሱ የትምህርት ዘመን የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርት በሁለተኛ ዲግሪ ሊሰጥ ነው።

በሀገሪቷ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን እንደ አንድ አማራጭ የኃይል ምንጭ አድርጎ የመጠቀም ዕቅድ በመኖሩ ፕሮግራሙን መስጠት ማስፈለጉ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲዉ ትምህርቱን መከታተል የሚፈልጉ ተማሪዎችን እየመዘገበ ሲሆን ለዚህ ትምህርት ብቁ የሚሆኑትም ከዚህ ቀደም በኬሚካል ኢንጅነሪንግ፣ በመካኒካል ኢንጂነሪንግ፣ በኬሚስትሪ፣ በፊዚክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸዉ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

ሳሙኤል ወንደሰን
+++++++++
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢትዮጵያ #ኒውክሌር

Address

Arada Sub City Wereda 09
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share