Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ Gazette Plus is committed to supplying credible information as it happens. It makes the Ethiopian Press Agency (EPA) 80+ years young.

The EPA is a pan-African media entity that has been in the media landscape for over 80 years.

ኩባ ከአዲስ አበባ -  ሀቫና ቀጥታ በረራ እንዲኖር  ፍላጎት እንዳላት ገለጸች+++++++++++++++++  |  ኩባ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጎልበት ከአዲስ አበባ- ሀ...
04/11/2025

ኩባ ከአዲስ አበባ - ሀቫና ቀጥታ በረራ እንዲኖር ፍላጎት እንዳላት ገለጸች
+++++++++++++++++

| ኩባ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጎልበት ከአዲስ አበባ- ሀቫና ቀጥታ በረራ እንዲኖር ፍላጎት እንዳላት በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ሜይሊን ሱዋሬዝ አልቫሬዝ ገለጹ፡፡

አምባሳደሯ ከኢፕድ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት ኩባ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጎልበት ከአዲስ አበባ- ሀቫና ቀጥታ በረራ እንዲኖር እየሰራች ነው፡፡

የቀጥታ በረራው መጀመር የሀገራቱን የአሰርት ዓመታት የዲፕሎማሲ ትብብር ወደ ጠንካራ የኢኮኖሚና የባህል ተሳትፎ የሚያሳድግ ይሆናል፡፡

ጅማሮው የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ የሆነችውን አዲስ አበባን ከካሪቢያን የባህል ማዕከል ጋር ለማገናኘት ያለመ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ሜይሊን፤ አገራቸው ለፕሮጀክቱ ያላትን ቁርጠኝነት በመጥቀስ በዚህ ረገድ ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ በርካታ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ እንቅስቃሴዎችን እንደምታስተናግድ የተናገሩት አምባሳደሯ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመሆን የሚጀመረው የቀጥታ በረራ ኩባን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚያስችላትም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የቀጥታ በረራው መጀመር ከሁለትዮሽ ግንኙነት ያለፈ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በመጥቀስ፤ ለሁለቱ አገራት ብቻ ሳይሆን አጠቃለይ ለቀጣናዊ ትብብርም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል

በግርማቸው ጋሻው
+++++++++++++++
#ኩባ #አየርመንገድ

ቀድመው የሚደርሱ  ሰብሎችን በሜካናይዜሽን ለመሰብሰብ እየተሰራ ነው+++++++++++++++++++  | የሜካናይዜሽን አማራጮችን በመጠቀም ቀድመው የሚደርሱ የመኸር ሰብሎችን ያለምንም የምርት ...
03/11/2025

ቀድመው የሚደርሱ ሰብሎችን በሜካናይዜሽን ለመሰብሰብ እየተሰራ ነው
+++++++++++++++++++

| የሜካናይዜሽን አማራጮችን በመጠቀም ቀድመው የሚደርሱ የመኸር ሰብሎችን ያለምንም የምርት ብክነት ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ለጋዜጣ ፕላስ እንደተናገሩት፤ በ2017/18 የምርት ዘመን ቀድመው የሚደርሱ ሰብሎችን በወቅቱ በሜካናይዜሽን ለመሰብሰብ እየተሰራ ይገኛል፡፡

ለዚህም የሜካናይዜሽን አገልግሎት የማመቻቸትና አማራጮችን የመለየት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡

ክልሎችም የደረሱ ምርቶችን የመለየትና የሚያስፈልጉ ግብአቶችን እንዲያቀርቡ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የመኸር ሰብሎች የመሰብሰቢያ ወቅት በየአካባቢው የተለያየ መሆኑ የሜካናይዜሽን አማራጮችን ለመጠቀም አመች እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡

በመኸር ከተዘሩ አዝርቶዕች መካከል በስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚመርቱት ቀድመው ይደርሳሉ ያሉት መሪ ስራ አስፈፃሚው፤ ከቀናት በኋላ ቀደመው የሚደርሱ ሰብሎችን የመሰብሰብ ስራ ይጀመራል ብለዋል፡፡

በታደሠ ብናልፈውና በማህሌት ብዙነህ
++++++++++++++++++++++++++++
#ግብርና #ሜካናይዜሽን

የቦይንግና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት እያደገ መጥቷል+++++++++++++++++++++++++  | የቦይንግ ኩባንያና  የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች እያደገ መም...
02/11/2025

የቦይንግና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት እያደገ መጥቷል
+++++++++++++++++++++++++

| የቦይንግ ኩባንያና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች እያደገ መምጣቱን የቦይንግ አፍሪካ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አምባሳደር ሄኖክ ተፈራ ገለፁ።

ማኔጅንግ ዳይሬክተሩ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለፁት፤ የቦይንግና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች እያደገ መጥቷል።

ኢትዮጵያ ለቦይንግ ኩባንያ የአፍሪካ መቀመጫነት የተመረጠችበት ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የረዥም ጊዜ አጋር በመሆኑና ኢትዮጵያም የአፍሪካ ወሳኝ የአቪዬሽን ማዕከል በመሆኗ ነው ብለዋል።

ቦይንግ የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ዕድገት ለመደገፍ ከትምህርት ጀምሮ በርካታ ድጋፎች እየሰጠ መሆኑንና፤ የአቪዬሽን ኢንጂነሪንግ ትምህርት እንዲስፋፋ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ባሻገር ወደ አውሮፕላን ምርት ለመግባት እየሰራ ይገኛል አምባሳደር ሄኖክ፤ በዚህም ለቦይንግ አውሮፕላኖች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን በስፋት እንዲያመርት በአቅም ግንባታን ጨምሮ ትብብር እየተደረገ ስለመሆኑ አንስተዋል።

አምባሳደር ሄኖክ ጨምረው እንዳብራሩት የቦይንግና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት 70 ዓመታትን የተሻገረ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድም በአፍሪካ ዋንኛው የቦይንግ ተጠቃሚ እንደ መሆኑ አብሮ በመሥራት ያሉትን ችግሮች በጋራ በመወጣት እስከዛሬ በውጤታማነት መዝለቅ ተችሏል ብለዋል።

በክብረአብ በላቸው
+++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣፕላስ #አየርመንገድ #ቦይንግ #አቪዬሽን

ጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት መብት መንፈግ አይችሉም+++++++++++++++  | ጎረቤት ሀገራት 'ወደ ባሕር አላሳልፍም' በማለት የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ዓለ...
01/11/2025

ጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት መብት መንፈግ አይችሉም
+++++++++++++++

| ጎረቤት ሀገራት 'ወደ ባሕር አላሳልፍም' በማለት የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ዓለም አቀፍ መብት መንፈግ እንደማይችሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁር ብሩክ ኃይሉ (ፕ/ር) ገለጹ፡፡

በዓለም አቀፍ ሕጎች ጎረቤት ሀገራት ወደ ባሕር አላሳልፍም የማለት መብት የሌላቸው መሆኑን ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።

የቀድሞ ዲፕሎማት፣ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁር ብሩክ (ፕ/ር) እንዳሉት፤ በዩናይትድ ኔሽን ኮንቬንሽን በአንቀጽ 69/123 እስከ 127 ባሉ ንዑስ አንቀጾች ኢትዮጵያ ለባሕር በር ጥያቄዋ ምላሽ የማግኘት መብት አላት። ጎረቤት ሀገራትም አላሳልፍም የማለት መብት የላቸውም፡፡

ከ34 ዓመታት በፊት ከ2 ሺህ ኪ.ሜ በላይ የባሕር በር የነበራት ኢትዮጵያ ጥቂት ኪሎ ሜትሮች መውጫ መንገድ መጠየቋ ከሕግ አግባብ ውጪ አለመሆኑን ፕሮፌሰር ብሩክ በአጽንዖት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተያይዘን እንደግ የሚል ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ የባሕር በር እጦት ሀገሪቱን ለበርካታ ችግር ዳርጓታል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የባሕር በር ከሌላቸው የዓለም ሀገራት መካከል ከፍተኛ የህዝብ ብዛት ያላት ሀገር መሆኗንም ነው የጠቀሱት፡፡

ፕሮፌሰር ብሩክ አክለውም፤ በዓለም ታሪክ በ60 ኪሎ ሜትር ልዩነት የባሕር በር ተዘግቶባት ያለች ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ያሉ ሲሆን አጀንዳው የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ በመሆኑ ተገቢውን ምላሽ ማግኘት አለበት ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ የባሕር በር አጀንዳ የህዝብ ቁጥሯን የሚሸከም ኢኮኖሚ ለመገንባት እና ሉዓላዊነት ለማስከበር እንዲሁም ለምስራቅ አፍሪካና ለቀጣናው መረጋጋትን ለማምጣት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡

በዚህ ረገድ በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስምምነት የመውጫ በር የከፈቱና የተቀበሉ ሀገራት እንዳሉ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕግን ያከበረና ሰላማዊ መንገድን የተከተለ ነው ብለዋል፡፡

በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣፕላስ

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የህፃናት ሙዚየም ልትገነባ ነው++++++++++++++  |  ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የህፃናት ሙዚየም ልትገነባ መሆኑን ...
29/10/2025

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የህፃናት ሙዚየም ልትገነባ ነው
++++++++++++++

| ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የህፃናት ሙዚየም ልትገነባ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ስለሺህ ግርማ አስታወቀ፡፡

ሚኒስትር ዲኤታው አቶ ስለሺህ ግርማ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የህፃናት ሙዚያም ለመገንባት የሚያስችሉ እንቅስቃዎች ተጀምረዋል፡፡

በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የህጻናት (የልጆች) ሙዚየም ተከፍተው ይጎበኛሉ ያሉት አቶ ስለሺህ፣ህጻናትን ስለአገራቸው እንዲያውቁና በትምህርት ቤት የሚማሯቸውን በሙዚየሙ የሚመለከቱበትን ዕድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡

ከቼክ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር በመቀናጀት የህጻናት ሙዚየም ለመገንባት የዲዛይን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣በቅርቡ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደአገር የህጻናት ሙዚየም እንደሚገነባ ገልጸዋል፡፡

ሙዚየሙን በወዳጅነት ፓርክ አካባቢ ለመገንባታ ታቅዷል። አስፈላጊው የዝግጅት ሥራ መጠናቀቁንም ጠቁመዋል፡፡

ህጻናት ስለሳይንስ፣ ማህበራዊ ህይወት፣ ጂኦግራፊ፣ ታሪክ፣ ባህል እውቀት የሚቀስሙበት እንደሚሆን የገለጹት አቶ ስለሺህ፣ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን በተግባር የሚያዩበትን እድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡

ሙዚየሙ ህጻናት ስለአገራቸው የሚማሩባቸው አምሳያዎችን ጨምሮ፣መዝናኛና መመገቢያ ቦታዎች እንደሚኖሩት በመግለጽ፣ህጻናቱ እየነኩና እያዩ የሚማሩበት በመሆኑ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡

ለቱሪዝም ዘርፉም ጎብኚዎችን ለመሳብ እድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው፣የውጪ ምንዛሬ በመጨመር፣የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም የሚኖረው ድርሻ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የግንባታ ሥራው አጠቃላይ ሁኔታ በኢትዮጵያና በቼክ ሪፐብሊክ መንግሥት በጋራ ቅንጅት እንደሚከናወን ጠቅሰው፣ ግንባታውን ለማስጀመር መሰረታዊ የሆነ የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁንና ፕሮጀክቱ መጽደቁን ተናግረዋል፡፡

በማርቆስ በላይ

#ቱሪዝም #የቱሪስትመዳረሻ #ሳይንስሙዚየም #ቅርሶች

ሁለት የአሜሪካ ባህር ኃይል አውሮፕላኖች ተከሰከሱ++++++++++++++++++++++++  | የአሜሪካ ባህር ሃይል ሄሊኮፕተር እና ተዋጊ ጄት በደቡብ ቻይና ባህር ላይ ተከሰከሱ።የአሜሪካ ባህ...
27/10/2025

ሁለት የአሜሪካ ባህር ኃይል አውሮፕላኖች ተከሰከሱ
++++++++++++++++++++++++

| የአሜሪካ ባህር ሃይል ሄሊኮፕተር እና ተዋጊ ጄት በደቡብ ቻይና ባህር ላይ ተከሰከሱ።

የአሜሪካ ባህር ኃይል የሁለቱም ክስተቶች መንስኤ እየተመረመረ መሆኑ ተነግሯል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተከሰቱትን አደጋዎች እጅግ ያልተለመዱ ሲሉ የገለፁ ሲሆን፤ የአደጋው መንስኤ የነዳጅ ችግር ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።

የአደጋው መንስዔ ተጠርቶ ይፋ እንደሚደረግ ተናግረው፤ በረራውን ሲያደርጉ የነበሩ የባህር ኃይሉ አባለት መትረፋቸውን ገልፀዋል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በበኩሉ አደጋውን ለማጣራት ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

በቻይና እና በበርካታ ደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት የተከበቡት የደቡብ ቻይና ባህር ክፍሎች በበርካታ የአካባቢው መንግስታት የይገባኛል ጥያቄ የሚቀርብባቸው ቢሆንም፤ ቤጂንግ በሁሉም የስትራቴጂክ የውሃ መስመር ላይ የባለቤትነት መብት ያለት መሆኑን ትናገራለች።

ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ቻይና በእነዚህ አከራካሪ ደሴቶች ላይ ወታደራዊ ተቋማትን በመገንባት የግዛት ይገባኛል ጥያቄዋን አጠናክራለች። ዘገባው የሲኤንኤን ነው።

በክብረአብ በላቸው
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣፕላስ #አሜሪካቻይና #ዓለምአቀፍ

ስለኢትዮጵያ የትርክት ለውጥ ለማምጣት እየሰራ የሚገኝ መድረክ ነው+++++++++++++++++++  | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት(ኢፕድ) የሚያዘጋጀው የስለኢትዮጵያ መድረክ በዋናነት በሰላምና ኢ...
25/10/2025

ስለኢትዮጵያ የትርክት ለውጥ ለማምጣት እየሰራ የሚገኝ መድረክ ነው
+++++++++++++++++++

| የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት(ኢፕድ) የሚያዘጋጀው የስለኢትዮጵያ መድረክ በዋናነት በሰላምና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት የትርክት ለውጥ ለማምጣት እየሰራ መሆኑን የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ።

ሶስተኛው ምዕራፍ የመጀመርያ ዙር የስለኢትዮጵያ መድረክ በዛሬው እለት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ከተማ “ሰላም ለኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል ርዕስ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ መክፈቻ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኢፕድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መሳፍንት ተፈራ እንደገለጹት ተቋሙ ባለፉት ሶስት አመታት ስለኢትዮጵያ በሚል መድረክ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የትርክት ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ውይይቶችን አካሂዷል።

በዚህም በተለይ በሰላምና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመው፣ ስለኢትዮጵያ የትርክት ለውጥ ያመጡ በርካታ ጉዳዮች መነሳታቸውን ገልጸዋል።

በስለኢትዮጵያ ትልቁን ቦታ የሚሰጠው ሰላምና አብሮንት ነው ያሉት አቶ መሳፍንት ሰላም በሌለበት የሚሰራ ነገር ሁሉ ቀለቡ ጠላት ነው ብለዋል።

ኢፕድ ባለፉት 84 ዓመታት በጋዜጦቹ ሀሳብ ሲዘራ እና እውቀትን ሲገነባ መኖሩን የጠቀሱት አቶ መሳፍንት፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በአዳዲስ የህትመት ውጤቶችና በዲጂታል ሚዲያዎችም ተደራሽነቱን ማስፋቱን ተናግረዋል።

ከነዚህም ውስጥ በልጆቻችን ላይ ለመስራት ሁለት የልጆች መጽሄቶችን እያሳተምን ነው ያሉት አቶ መሳፍንት፣ ይህም በከፍተኛ ሁኔታ ህብረተሰቡ ጋ እየደረሰ ነው ብለዋል።

“በሌላም በኩል የኢኮኖሚ ጉዳይ አንዱ የትኩረት ስራችን ነው። ኢኮኖሚ መሰረታዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዘመን ኢኮኖሚ በሚል በአብዛኛው ጎልማሶችን ማዕከል ያደረገ ስራ እየሰራን እንገኛለን” ሲሉም አክለዋል።

በሌላ በኩል ወጣቶችን ማዕከል ያደረገ የዲጂታል ዘርፍ በማቋቋም እንዲሁም ጥልቅ ትንታኔዎችን የሚያካትት የሞባይልና የድረገጽ መተግበሪያን በማልማት የትርክት ግንባታ ላይ በትኩረት እየሰራን ነው ብለዋል።

በመክፈቻ መድረኩ ላይ የጌዲኦ አባገዳዎች፣ የጋሞ አባቶች እና የጋሞ የሀገር ሽማግሌዎች በጋራ የምረቃ ስነስርዓት ያከናወኑ ሲሆን የጌዲኦ የባህል ቡድንም ባህላዊ ሙዚቃ አቅርበዋል።

ማርቆስ በላይ

ማርቆስ በላይ
++++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢፕድ #ስለኢትዮጵያ

ትራምፕ ከካናዳ ጋር የሚያደርጉት የንግድ ድርድር አቋረጡ++++++++++++++++  | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከካናዳ ጋር የሚያደርጉት የንግድ ድርድር በፀረ-ታሪፍ ማስታወቂያ ...
24/10/2025

ትራምፕ ከካናዳ ጋር የሚያደርጉት የንግድ ድርድር አቋረጡ
++++++++++++++++

| የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከካናዳ ጋር የሚያደርጉት የንግድ ድርድር በፀረ-ታሪፍ ማስታወቂያ ምክንያት ማቋረጣቸውን አስታወቁ፡፡

በካናዳ ኦንታሪዮ ግዛት መንግስት ድጋፍ የተላለፈው ይህ ማስታወቂያ ታሪፉ እያንዳንዱን አሜሪካዊ ይጎዳል በሚል ትራምፕ በካናዳ ላይ የጠሉትን ታሪፍ የሚተች ነው፡፡

ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፃቸው ማስታወቂያው ሀሰተኛ መሆኑን በመግለፅ የንግድ ድርድሩ ወዲያው መቋረጡን አስታውቀዋል፡፡

የትራምፕ አስተዳደር በካናዳ ገቢ ምርቶች ላይ 35 በመቶ ቀረጥ የጣለ ሲሆን፤ ታሪፉ እንደ ተሽከሪካሪና ብረታ ብረት ባሉ የኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ይነገራል። የዘገበው የቢቢሲ ነው፡፡

በማህሌት ብዙነህ
++++++++++++++++
#አሜሪካ #ካናዳ

በሚሊዮን የሚቆጠሩ የውሃ ውስጥ ጊንጦች ወደ ባህር ዳርቻ እየፈለሱ ነው+++++++++++++++++++++++  | 10 ሚሊዮን የሚደርሱ የውሃ ውስጥ ጊንጦች (ክራብስ) ከጫካ ጉድጓዶቻቸው ወደ ...
23/10/2025

በሚሊዮን የሚቆጠሩ የውሃ ውስጥ ጊንጦች ወደ ባህር ዳርቻ እየፈለሱ ነው
+++++++++++++++++++++++

| 10 ሚሊዮን የሚደርሱ የውሃ ውስጥ ጊንጦች (ክራብስ) ከጫካ ጉድጓዶቻቸው ወደ ሚራቡበት የባህር ዳርቻ እየፈለሱ መሆኑ ተገለጸ።

ፍልሰቱ በየዓመቱ የሚደረግ ሲሆን 100 ሚሊዮን የሚሆኑ ክራብሶች ገና ፍልሰት እንደሚያደርጉም ተገልጿል።

በአውስትራሊያ የክሪስማስ ደሴት ብሔራዊ ፓርክ ተጠባባቂ ሥራ አስኪያጅ አሌክሲያ ጃንኮውስኪ እንደተናገሩት፤ በህንድ ውቅያኖስ ውስጥ ባለችው አነስተኛ የአውስትራሊያ ደሴት ላይ እስከ 200 ሚሊዮን የሚደርሱ ክራብሶች አሉ።

ከእነዚህ ውስጥ ከ100 ሚሊዮን በላዩ ከጫካ ጉድጓዶቻቸው ወደ ሚራቡበት የባህር ዳርቻ ይጓዛሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።

ዓመታዊ የክራብሶቹ ፍልሰት የሚከሰተው የበጋ ዝናብን ተከትሎ መሆኑን ገልጸው ለክራብሶቹ ምቹ የመራቢያ ጊዜ መሆኑን ተናግረዋል።

በደሴቷ የሚኖሩ ሰዎች በመኪናም ሆነ በእግር ሲንቀሳቀሱ ክራብሶቹ ላይ ጉዳይ እንዳያደርሱ የተለያዩ መንገዶች ተዘግተዋል ሲል የዘገበው ዘ ዋሺንግተን ፖስት ነው።

በዳግማዊት አበበ
++++++++++++
#ክራብሶች

ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች +++++++++++++++++++++++  | ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን አስታወቀች።ሀገሪቱ ያደረገችው ...
23/10/2025

ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች
+++++++++++++++++++++++

| ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን አስታወቀች።

ሀገሪቱ ያደረገችው የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ እራሷን የመከላከል ቴክኒካል አቅሟን እያሳደገች ስለመሆኑ ግልጽ ማስረጃ መሆኑን አረጋግጣለች።

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮሪያ በሚሳኤል አስተዳደር የተካሄደውን ሙከራ፣ የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሃፊ ፓክ ጆንግ ቾን፣ የሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ጃንግ ቻንግ ሃ መምራታቸውን የኮሪያ ማዕከላዊ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

አዲሱ የጦር መሣሪያ ስርዓት ከጠላት ሊሰነዘሩ የሚችሉ ስትራቴጂካዊ ጥቃቶችን በዘላቂነት እና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመመከት እንደሚያስችል ተነግሯል።

የፒዮንግያንግ እንቅስቃሴ ጦርነትን ቀድሞ ለማስቀረት ያለመና ዓላማው ራስን መከላከል ብቻ መሆኑን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናግረዋል።

የደቡብ ኮሪያ ጦር ፒዮንግያንግ በርካታ የአጭር ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ምስራቅ ባህር መተኮሷን አስታውቋል።

አሜሪካ ሙከራው ህገ-ወጥ እና የቀጠናውን መረጋጋት የሚረብሽ ነው በማለት ያወገዘች ሲሆን፤ ሰሜን ኮሪያ የተለያዩ የሰላም ስምምነቶችን ከሚጥሱ ተጨማሪ ድርጊቶች እንዲትተቀብ ጠይቃለች።

በክብረአብ በላቸው
++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣፕላስ #ዓለምዓቀፍ #ሰሜንኮሪያ #ደቡብኮሪያ

ትራምፕ በሩሲያ ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣሉ++++++++++++++++++++++  | የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ለማስቆም እየተደረገ ባለው...
23/10/2025

ትራምፕ በሩሲያ ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣሉ
++++++++++++++++++++++

| የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ለማስቆም እየተደረገ ባለው ጥረት የተኩስ አቁም ድርድሩ ላይ መሻሻል ባለመኖሩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።

የአሜሪካ የግምጃ ቤት ሚኒስትር ስኮት ቤሴንት፤ ማዕቀቡ በሩሲያ ሁለቱ ትላልቅ የነዳጅ ኩባንያዎች ሉኮይልና ሮስኔፍት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም የሆነው የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጦርነቱን ለማስቆም ፈቃደኛ ባለመሆናቸውና ሞስኮ ለሰላም ሂደቱ ከፍተኛ ቁርጠኝነት ባለማሳየቷ ነው ብለዋል።

የአሜሪካ ግምጃ ቤት ዲፓርትመንትም ሩሲያ በዩክሬን ከሦስት ዓመታት በላይ የፈጀውን ጦርነት ከቀጠለች ተጨማሪ ርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጿል።

ዶናልድ ትራምፕ በሃንጋሪ ከፑቲን ጋር ሊያደርጉት ያቀዱትን ስብሰባ እንዳራዘሙ ከገለፁ በኋላ በዋይት ሀውስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ስብሰባውን እንደሰረዙትና ነገር ግን ወደፊት የማድረግ እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ ማዕቀቡ ለረጅም ጊዜ መቆየት እንደማይችል ተስፋ እንዳላቸው ገልፀው፤ ነገር ግን በተቋረጠው የእርቅ ድርድር አለመግባባቶች እየጨመሩ መምጣታቸውን ጠቁመዋል።

ሩሲያ እስካሁን ለአሜሪካ ርምጃዎች ምላሽ አልሰጠችም ሲል የዘገበው አልጀዚራ ነው።

በቃልኪዳን አሳዬ
++++++++++++++++++

#አሜሪካ #ዩክሬን #ሩሲያ

የለውዝ ፍሬ መጠን ያለው የሻርክ ዝርያ ተገኘ+++++++++++++++++++++++ | የአውስትራሊያ ሳይንቲስቶች የለውዝ ፍሬ መጠን ያለው የሻርክ ዝርያ ማግኘታቸውን አስታወቁ፡፡ግኚቱ ሳይንቲስ...
22/10/2025

የለውዝ ፍሬ መጠን ያለው የሻርክ ዝርያ ተገኘ
+++++++++++++++++++++++

| የአውስትራሊያ ሳይንቲስቶች የለውዝ ፍሬ መጠን ያለው የሻርክ ዝርያ ማግኘታቸውን አስታወቁ፡፡

ግኚቱ ሳይንቲስቶቹ ጥልቅ ባህርን በማሰስ ካገኟቸው ሁለት አዳዲስ ዝርያዎች መካከል መሆኑን የአውስትራሊያው የሳይንስ ኤጀንሲ ጥናት አመልክቷል፡፡

አዲሱ የሻርክ ዝርያ 40 ሴ .ሜ የሚደርስ ትላልቅ አይኖችና የሚያብረቀርቅ ሆድ ያለው ሲሆን 600 ሜትር ከውቅያኖስ ወለል በታች መገኘቱ ተመራማሪዎች ጠቁመዋል፡፡

አውስትራሊያ በዓለም ከአንድ ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ዝርያዎችና የብዝሃ ሕይወት መገኛ ስትሆን፤ አብዛኞቹ በምድር ላይ የማይገኙ በመሆኑ እስካሁንም ሳይንስ ተመራምሮ ያልደረሰባቸው እንዳሉ ተገልጿል።

እንደ ጥናቱ ገለጻ፤ አዲሱ ዝርያ የተገኘው በ2022 በተጀመረው ፍለጋ ከተሰበሰቡ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ናሙናዎች ውስጥ ነው፡፡

የአሳ ሳይንቲስትና ተመራማሪ ዊል ዋይት(ዶ/ር) አዲስ የተገኙት ዝርያዎች በሆዳቸውና በጎናቸው አብረቅራቂ ብርሃን የሚያመነጩ ናቸው ብለዋል፡፡

ሳይንቲስቶቹ ከዚህ በተጨማሪም አንድ ነጥብ አምስት ሴ.ሜ ርዝማኔ ያለውና ከባህር ጠለል በታች 122 ሜትር ገደማ የሆነ ሌላ ዝርያ ማግኘታቸው ገልጸዋል፡፡

እነዚህ አዳዲስ ግኝቶች ምግብ ለመፈለግ ከጥፍራቸው ይልቅ ጸጉራቸው የሚጠቀሙ ስለመሆናቸው ተነግሯል።

በፍለጋው እስካሁን ወደ 20 የሚጠጉ አዳዲስ ዝርያዎች በቁፋሮ የተገኙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ካርናቮን ፍላፕጃክ ኦክቶፐስ 4 ሴ.ሜት ስፋት ያለው ፍጡር ተጠቃሽ ነው፡፡

በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣፕላስ #አውስትራሊያ #ምርምር #ሳይንስ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share