Addis Techno View አዲስ ቴክኖ ቪው

Addis Techno View አዲስ ቴክኖ ቪው Review Technology and recommendation As Ethiopian For Ethiopian To Make Ease Life Through Technology!!

‹‹ደደብነት ያለማወቅ ችግር ሳይሆን የስብዕና መቃወስ፣ የሞራል ማጣት ነው››(Stupid people are more dangerous than evil ones)(እ.ብ.ይ.)አለማወቅ ምንም አይደል፤...
29/01/2023

‹‹ደደብነት ያለማወቅ ችግር ሳይሆን የስብዕና መቃወስ፣ የሞራል ማጣት ነው››
(Stupid people are more dangerous than evil ones)
(እ.ብ.ይ.)

አለማወቅ ምንም አይደል፤ በማወቅ ይደመሳሳል፡፡ አለመማርም ችግር የለውም ቀለም በመቁጠር ድል ይነሳል፡፡ አለማወቅ መረጃ አለማግኘት ነው፡፡ አለመማር ስራዬ ብሎ የኑሮን ቀለም፣ የህይወትን ፊደል አለመቁጠር ነው፡፡ አለመማር ወደመረጃው ዓለም የሚወስደውን መንገድ አለመጀመር ነው፡፡ አለማወቅ አለማሰብ መቻል አይደለም፡፡ አለመማርም የሃሳብ እጦት ባለቤት መሆን አይደለም፡፡ የተማረውም ያልተማረውም ያስባል፤ ልዩነቱ የሚያስበው ነገር የተለያየ መሆኑ ነው፡፡ የተማረ ሁሉ በሃሳቡ የሰለጠነ ነው ማለት አይቻልም፡፡ አንዳንድ ሰው በአለባበሱና በአበላሉ የሰለጠነ ይመስላል፤ በአስተሳሰቡ ግን ኋላ የቀረ ነው፡፡ መሰልጠን ፋሽን መከተል የሚመስለው አያል ነው፤ መዘመን የዘመኑን መረጃ ማነብነብ ብቻ የሚመስለው መዓት ነው፡፡ እውነተኛ ዘመናዊነት ግን ዓለሙ ያቀረበልህን መረጃና ዕውቀት መመዘን፣ ማጥናት፣ መተንተን፣ ጥቅምና ጉዳቱን መለየት፤ ደካማና ጠንካራ ጎኑን ማውጣት፣ እንዲሁም የራስን ሃሳብ አክሎ አዲስ በጎ አተያይ መፍጠር መቻል ነው፡፡ ዘመናዊነት ዘመኑ የደረሰበት የአስተሳሰብ ወለል ላይ መድረስ ነው፡፡ መሰልጠን ግን ዘመኑን መቅደምም ሊሆን ይችላል፡፡ የሰለጠኑ ሐገራት ሰለጠኑ የሚባሉት በጊዜው የነበራቸውን ችግር ስለቀረፉ ብቻ ሳይሆን ወደፊት ሊፈጠሩ የሚችሉ ስጋቶቻቸውን ቀድመው አውቀው ለእሱ መፍትሄ ማበጀት በመቻላቸው ነው፡፡

ሰው ሁሌም የሕይወት ተማሪ ነው፡፡ ከጥፋቱ የሚማር፣ ከሌሎች ውድቀትና ስኬት ቀለም የሚቆጥር፣ በመደበኛ ትምህርት ራሱን የሚገነባ ሰው ብልህ ሰው ነው፡፡ ሰው አስተዋይ ከሆነ በዕድሜው ከሚያየው ያውቃል፤ ከሚሰማውም ይማራል፡፡ ሰው አዋቂ ሆኖ፣ ፊደል ቆጥሮ፣ ቀለም ለይቶ፣ የትተረፈረፈ መረጃ ኖሮት፣ በትምህርቱ ዓለም ብዙ ተጉዞ፣ ስምና ዝና፤ ሃይልና ስልጣን ይዞ ማሰብ፣ ማሰላሰል፣ ማመዛዘን፣ ማስተዋል ካልቻለ ግን ደደብነት ይወርሰዋል፡፡ ድድብና አዕምሮንም ልብንም መጠቀም አለመቻል ነው፡፡ ሰው በዓይኑ ያየውን፣ በጆሮው የሰማውን፣ ከዚህ ቀደም በንባብ ያወቀውን፣ በጥናት የደረሰበትን ሃሳብና ዕውቀት በልቡ አመላልሶ፣ በሕሊናው አብላልቶ፣ ክፉና ደጉን ለይቶ በሰናይ ተግባር ላይ ካላዋለው፤ በጎ ውሳኔ ላይ ካላደረሰው እሱ ያልተማረ ሳይሆን የተማረ ደደብ ነው ማለት ነው፡፡ ደደብነት የሚገፈፈው በመንፈሳዊ ዕውቀት ሲሰለጥኑ፣ በሰውነት ሲዘምኑ፣ ስሜትን ሲገሩ፣ ለሐገር ለወገን የሚጠቅም ችግር ፈቺ ሃሳብ አስበው ሲተገብሩ ነው፡፡

የዚህ ዘመን ትልቁ ችግር ያልተማሩ ሰዎች ቁጥር መበራከቱ ሳይሆን አዋቂ የተባሉ፣ የተማሩ መሃይማን እጅግ እየበዙ መምጣታቸው ነው፡፡ የክፉ ሰዎች ክፋት ሳይሆን የደደቦች ጥፋት ነው ሐገራችንን የሞት አፋፍ ላይ ያቆማት፡፡ ክፉዎችን መከላከል ትችላለህ፤ ደደቦችን ግን አትችልም፡፡ ደደቦችን በመልክ ለይተህ አታውቃቸውም፡፡ ከቤተሰብህ፣ ከጓደኞችህ፣ ከባልንጀሮችህ፣ ከመምህራኖችህ፣ ከሃይማኖት አባቶችህ፣ ሐገርህን ከሚመሩት ባለስልጣኖችህ መካከል ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ክፉዎችን በአነጋገራቸው፣ በአስተያየታቸው፣ አንዳንዴም በዓይናቸው ልታውቃቸው ትችላለህ፡፡ ክፉዎች ትንሽም ቢሆን አጥንተው ነው ሊያጠቁህ የሚፈልጉት፡፡ ደደቦች ግን ‹‹የፈሪ ብትር ሆድ ይቀትር›› እንዲል ቢሂሉ ጥፋታቸው ደመነፍሳዊ ነው፡፡ አዎ ደደቦችን አደጋ ካደረሱ በኋላ ነው የምታውቃቸው፡፡

ጀርመናዊው የስነመለኮት ሊቅ የነበረው ዳያትሪክ ቦንኹፈር (Dietrich Bonhoeffer) በሃያኛው ክፍለዘመን በጀርመን የጨለማ ታሪክ ውስጥ ተጠቃሽ ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው ጀርመን በህዝብ ተቃውሞ ስትናጥና ተቃዋሚዎች የንፁሃንን ንብረትና የንግድ ሱቆች በድንጋይ ሲሰባብሩ ዓይቶ ፊትለፊት በአደባባይ የሕዝብን ድርጊት ያወገዘ ሰው ነበር፡፡ በኋላም ሒትለርን ለማስገደል ካሴሩት ሰዎች አንደኛው ነህ ተብሎ ተከስሶ እ.ኤ.አ. በወርሃ ሚያዚያ 1945 ዓ.ም. በስቅላት የተቀጣ ሰው ነው፡፡ ይሄ የሉተራን ቤተክርስቲያን ፓስተር የነበረ ሰው ‹‹የደደብነት ንድፈ ሃሳብ (Theory of Stupidity)›› በሚል ሃሳቡ ይታወቃል፡፡ ‹‹ደደብ ሰዎች ከክፉ ሰዎች የበለጠ አደገኞች ናቸው›› ይላል፡፡ ይሄንንም ሲያብራራ ‹‹ክፉ ሰዎችን ፊትለፊት ሃይል በመጠቀም መከላከል ይቻላል፤ ደደቦችን ግን ለመከላከል አቅመቢስ እንሆናለን፡፡ ምክንያቱም ጆሯቸው ምክንያታዊነትን ላለመስማት ደንቁራል፡፡›› ይለናል፡፡ ሰውየው በዚህ አላበቃም፡፡ ‹‹ደደብነት ያለማወቅ ችግር ሳይሆን የሞራል ማጣት ነው›› ‹ብዙ ምሁራን አሉ ነገር ግን ደደቦች ናቸው፡፡ አንዳንዶች በአዕምሮ ዕውቀታቸው ደንዝዘው ደንቁረዋል፡፡›› በማለት ይተነትናል፡፡

አዎ ትምህርታቸው ያላነቃቸው፤ ማወቃቸው ያልጠቀማቸው፣ መማራቸው ያላሰለጠናቸው፤ ለወገናቸው ጠብ የሚል መላ ያልፈጠሩ ጠብደል ደደቦችን ዩንቨርስቲ ይቁጠራቸው፡፡ እያወቁ የማያውቁ፣ እያዩ የማያዩ፣ እየሰሙ የማይሰሙ የደነዘዙ አድርባይ ምሁራን እልፍ ናቸው፡፡ የዳቦ እውቀታቸው ጨጓራቸው ጋ እንጂ ልባቸው ጋ አይደርስም፡፡ ጥናትና ምርምራቸው ከአንገት በታች ነው፡፡ ጥበባቸው ከርስን መሙላት፣ የዓይን አምሮትን ማርካት፣ ቁስ ማግበስበስ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ በላይ ድድብና ከወዴት ይገኛል??

ወዳጄ ሆይ... ተወዳጁ አሜሪካዊው ፀሐፊ ማርክ ትዌይን ‹‹ከደደቦች ጋር አትከራከር፡፡ ከደረጃህ አውርደው ከነሱ ተርታ ያሰልፉሃል›› እንዳለው የልብ ዕውቀት ከሌላቸው ሰዎች ጋር እሰጣ-ግባ ውስጥ አትግባ፡፡ እነሱ ሁሉን የሚያውቁ የሚመስላቸው ሞራልና ስነምግባር የሌላቸው አውሬዎች ናቸው፡፡ አንተ ግን በልብህም በአዕምሮህም የበቃህ ሁን፡፡ በሕሊናህም በመንፈስህም ሰልጥን፡፡ በስሜትህም በአዕምሮህም ብሰል፡፡ አለማወቅህን በዕውቀት ደምስሰው እንጂ የተማረ የአዋቂ ደደብ አትሁን!

ቸር ጊዜ!

_____________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
እሁድ ጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.

Ke atnatiose eshetu birru page የተወሰደ

 ? - ፕሌቶበመንገድህ ላይ አንዲት አሮጊት አጋጠመችህ፤ እናም ይህቺ ሴት ትንሽ፣ ግን እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነን ስጦታ ሰጠችህ - አስማተኛ ቀለበት! ይህም ቀለበት አንተን ለሌሎች እንዳትታይ...
23/05/2022

? - ፕሌቶ
በመንገድህ ላይ አንዲት አሮጊት አጋጠመችህ፤ እናም ይህቺ ሴት ትንሽ፣ ግን እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነን ስጦታ ሰጠችህ - አስማተኛ ቀለበት!
ይህም ቀለበት አንተን ለሌሎች እንዳትታይ አድርጎ ይሰውርሃል፤ ወደፈለግከው ስፍራ መጓዝ ትችላለህ፤ ማንም ሰው አንተን ማየት አይችልም።
ጥያቄውም ይህ ነው - በዚህ ቀለበት ምን ታደርጋለህ? ይህን አስማታዊ ሃይል እንዴት ትጠቀመዋለህ?
“የጋይጂ ቀለበት” ሪፐብሊክ በተሰኘው የፕሌቶ ዘመን አይሽሬ ስራ ውስጥ እናገኘዋለን። መጽሀፉ የፕሌቶ ታላቅ ወንድም ስለሆነውና ግላውኮን ጋይጂ ስለተባለ አንድ ተራ በግ ጠባቂ ታሪክ ይነግረናል።
ይህ እረኛ ከክርስቶስ መወለድ ሰባት መቶ አመታት በፊት የሊድያ ግዛት ተብላ በምትጠራው ስፍራ ይኖር ነበር። (ይህን ግዛት አሁን ላይ በቱርክ ውስጥ እናገኘዋለን።)
ፕሌቶ ታሪኩን እንዲህ ይተርከዋል፡-
ከእለታት በአንዱ ቀን በእጅጉ ሃይለኛ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በሊድያ ግዛት ውስጥ ተከሰተ። በምድር ገጽ ላይም ትልቅ መሰንጠቅ ተፈጠረ። በስንጥቁ መሃልም እረኛው ጋይጂ አንድ የተደበቀ ዋሻ ተመለከተ። በዋሻው ውስጥም ጋይጂ ከነሐስ የተሰራ የፈረስ ሐውልት አገኘ። በዚህ ሐውልት ውስጥ በከፊል የበሰበሰ የአንድ ግዙፍ ሰው ሙት አካል ይገኝበት ነበር። በአስክሬኑ የቀኝ እጅ አንደኛው ጣት ላይም ወርቃማ ቀለበት ያብረቀርቅ ነበር። እናም ጋይጂ ይህንን ቀለበት ለራሱ ወሰደው።
እረኛው ይህ ቀለበት ተራ ቀለበት እንዳልነበረ ለመረዳት ጊዜ አልወሰደበትም። በቀለበቱ አናት ላይ ያለችውን ጌጥ ሲያሽከረክራት፣ ጋይጂ ሰው እንዳያየው ሆኖ ተሰወረ። ቀለበቱ ለጋይጂ የመሰወርን ሃይል ሰጠው።
አስደናቂ የመሰወር ሃይልን እንዳገኘም፣ ይህ ተራ የበጎች እረኛ ወደ ቤተ መንግስት ቅጥር ዘለቀ። በዚያን ዕለት ምሽትም ከንግስቲቷ ጋር ተኛ። ንጉሱንም ገደለው። ንግስናንም ተቀበለ። እናም ራሱን የሊድያ ግዛት ገዢ አድርጎ ሾመ። ታሪኩ ይቀጥላል… እስቲ ልጠይቅህ…
አንተስ የመሰወር ሃይል ቢኖርህ ምን ታደርጋለህ?
በአጠገብህ ያለ ጓደኛህን ጠይቀው፤ ራስህንም ጠይቅ።
የሚያስገርም፣ የሚያስቅ አልያም የሚያሳቅቅ ምላሽን ታገኛለህ። እናስ የመሰውር ሃይል ቢሰጥህ … ባንክ ቤት አትዘርፍም? ልክ እንደ ጋይጂ ወደ ቤተመንግስት ለመግባት አትሞክርም? ከዚህም ሲከፋ ለመናገር የሚከብዱ ወንጀሎችንስ አትፈጽምም?
እረኛው ራሱን ንጉስ ካደረገ በኋላ የገጠመውን ሁሉ ፕሌቶ ያጫውተናል፡፡ ጨዋታው ደግሞ በ የተሰኘው መጽሐፍ ውስጥ ተተርኳል፡፡

source bookfor all (ከመፀሃፍት አለም)

MOVIE TYPE  GENER: CRIME, DRAMA, MOVIE.Tells the story of the rise and fall of the Baltimore Police Department's Gun Tra...
09/05/2022

MOVIE TYPE GENER: CRIME, DRAMA, MOVIE.

Tells the story of the rise and fall of the Baltimore Police Department's Gun Trace Task Force and the corruption surrounding it.
Creators
George PelecanosDavid Simon
Stars
David CorenswetMcKinley Belcher IIIDagmara Dominczyk

To see the Trailer Go to this link

https://youtu.be/_3v38PjINzw

27/04/2022
for movie trailer desires
27/04/2022

for movie trailer desires

,$ , , #2022, , # trailers #2022, trailers, trailers 2022, , upcoming #,best movie trailers, movie trailer...

11/04/2022

እንኳን ይሄ የተኮረጀ ብሽቅ ካሪኩረም ቀርቶ
ሌላም ሌላም ነገር ጥንቅር ይበል
ከሰላት ምንስ ይበልጣል ?
የተፈጠርንበት አላማ እኮ ፈጣሪያችንን ልናመልክና ልንገዛ ነው

እንዲያው ቦታውን ስለያዛችሁት ማድረግ የምትችሉት ይሔ ብቻ ነው
እስኪ የወደሙ ት/ቤቶችን የመጠገን ስራን ስራ
እኩይ ነህና መልካም ተግባር አይመጣልህም

ት/ት አንተ ተምረህ ህዝብን እንደምታስቸግረው ከሆነ ዘላለም አለሜን ሳልማር ደንቁሬ ልኑር ።
ደግነቱ ግን ት/ት አንተ እንደምትለው ለስሜት መነዳት ሳይሆን በጥልቅ የማሰብ ውጤት ሆኖ ለችግሮች የመፍትሄ አማራጭ የሚሆን እንጂ

ብርሀኑ ነጋ ተጠንቀቅ ነገር እንዳታመጣ


25/03/2022

የአንድ ማህበረሰብ ንጉስ ነበር ይህ ንጉስ 10 እጅግ አደገኛ ከሰው ባህሪ ማይገጥሙ ውሾች ነበሩት፣ እነዚህን ውሾችም ስራ አልሰራም ለሚሉት ጥፋት የሚሰሩ ሰራተኞቹን ለማስበላትና ለማሰቃየት ይጠቀምባቸው ነበር።

ታዲያ አንዱ ሰራተኛ ንጉሱ የሚሰራው ስራ ልክ አለመሆኑን ነገረው፣ ንጉሱም ይህንን ድፍረቱን ስላልወደደው ወደ ውሾቹ ጎሬ እንዲጣልና እንዲበላ ፈረደበት፣ ሰራተኛውም አዝኖ አስር አመት ሙሉ አገልግዬ ምነው እንዲህ ፈረድክብኝ ንጉስ ሆይ ባይሆን ከመበላቴ በፊት አስር ቀን ይሰጠኝ ብሎ ጠየቀ ንጉሱም ተስማማ።

በተሰጠው አስር ቀንም ወደ ውሻው ጠባቂ ዘንድ ሄዶ ውሾቹን ይመግባቸው ዘንድ ጠየቀው ጠባቂውም በጥያቄው ተገርሞ ፈቀደለት፣ በነዚህም አስር ቀናት ውስጥ ውሾቹን ያጥባቸው ምግብ ይሰጣቸውና እያሻሸ ይንከባከባቸው ጀመር።
የማይደርስ ቀን የለም ቀኑ ደረሰና በንጉሱ ትእዛዝ መሰረት በውሾቹ እንዲበላ ተጣለ፣ ንጉሱ በሚያየው ነገር ተደናገጠ እነዛ ሰዎችን በደቂቃ ውስጥ ዘነጣጥለው ሚበሉት ውሾች ጭራቸውን እየቆሉ እግሩን ሲልሱት አየ፣ በሁኔታው ተደናግጦ ውሾቼ ምን ሆነው ነው ብሎ ጠየቀ፣
ሰራተኛውም ውሾቹን ላለፉት አስር ቀናት ስንከባከባቸውና ስመግባቸው ነበር እነሱም አገልግሎቴን አልርረሱም ፣ አንተን ግን አስር አመት አገልግዬህ በመጀመሪያው ስህተቴ ሁሉንም አገልግሎቴን እረሳከው አለው፣ ንጉሱም ስህተቱን ተረድቶ ሰራተኛው እንዲለቀቅ አዘዘ።

የዚህ ፖስት መልእክትም ብዙ መልካም ነገር ያደረጉልንን ሰዎች ስህተት ሲሰሩ ስናይ በዛ ሚዛን ልንመዝናቸው አይገባም ።

Cosmos Michael እንደተረጎመው

ይናገራል ፎቶ  #0003
21/03/2022

ይናገራል ፎቶ #0003

ይናገራል ፎቶ
17/03/2022

ይናገራል ፎቶ

https://youtu.be/nFu0xkNnlBsthis is an important thing for who want improve language this is a chance prepared by w***y ...
30/09/2021

https://youtu.be/nFu0xkNnlBs

this is an important thing for who want improve language
this is a chance prepared by w***y Ethiopia
***yEthiopia language and training center

8: መሠረታዊ የእንግሊዝኛ ትምህርት ለጀማሪ https://youtu.be/lShydun-lT4 Lesson 9: እንግሊዝኛን በ...

07/09/2021

እሸቱ ብሩ ይትባረክ እንዲህም ይላል

“አዲስ ዓመት” አዲስ እኔ”ነት ነው!
(New year is the philosophy of self optimism)
(እ.ብ.ይ.)
ሰው ሁልጊዜ አዲስ ይሆን ዘንድ እንዲችል አዲስ ዓመትን ፈጠረ፡፡ ሰው ከራሱ ጋር ይታረቅ ዘንድ፣ እቅዱ ከግቡ እንዲስማማ፤ ውጫዊና ውስጣዊ ሕይወቱ እንዲጣጣም አዲስ ዓመት ወሳኝ ድርሻ አለው፡፡ የአዲስ ዓመት አፈጣጠሩም ሰው ለራሱ ቀና ለመሆን ከመነጨ ውስጣዊ ጉጉቱ ነው፡፡ የዛሬው ሰውም ለራሱ እንኳ ቀና መሆንን ባልቻለበት የእድሜ ዘመኑ አንዲቷ ቀን አዲስ ዓመት ትሆነው ዘንድና ለራሱና ለወገኑ መልካምና ቅን ያስብባት ዘንድ አባቶቹና ቅድመ አያቶቹ አዲስ አመትን ሰሩለት፡፡
አዲስ ዓመት የሰው ልጅ ራሱን የሚያሻሽልበት፣ ያለፈውን ሕይወቱን ገምግሞ ደካማውን ሽሮ ጠንካራውን ይዞ እንዲቀጥልበት ለራሱ የፈጠረው የቀን ቀጠሮ ነው፡፡ ተፈጥሯዊ ቀኑ ያው ከሌላው ቀን የተለየ አይደለም፡፡ እንደማንኛውም ቀን ይነጋል፤ እንደማናኝውም ምሽት ይመሻል፡፡ ነገር ግን ለቀኑ ስያሜ በመስጠት በቀኑ አማካኝነት ራስን መለወጥ፣ አስተሳሰብን ማደስ፣ አኗኗርን ማስተካከል ማሰብ ማሰላሰል በሚችለው በሰው ልጅ ታሪክ የተለመደ ወግ ነው፡፡ ምክንያት ፈልጎ ወይም ፈጥሮ አንድ ነገር ማድረግ ሰው የሰለጠነበት ልማዱ ነው፡፡ ዛሬም እንደጥንቱ በሰሜናዊው የሃገራችን ክፍል ሰው አይደለም ለደስታው ቀርቶ ለሐዘኑም ጭምር ደረቱን ለመድቃት፣ ፊቱን ለመንጨት እንኳ ቀድሞ የተረዳውን/የሰማውን የወዳጁን ወይም የዘመዱን ሞት እርሙን ለማውጣት ሲል ቀን ቀጥሮ ከዘመድ አዝማዱ ጋር ተሰባስቦ በቀጠሮ ለቅሶ ሐዘን ይቀመጣል፡፡ አዲስ ዓመትም አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ዕቅድ፣ ከበፊቱ የተለየ የሕይወት መንገድ የሚጀመርበት የቀን ቀጠሮ ነው፡፡
አዎ አዲስ አመት ሰው ለራሱ ቀና የሚያስብበት፣ አዲስ ቃል የሚገባት ዕለቱ ነው፡፡ ይሄ ቀን ደግሞ መጪው ጊዜ መልካም እንዲሆን፤ ኑሮው እንዲሳካ፣ ጎጆው እንዲሞላ፣ መንፈሱ እንዲረካ፣ አዕምሮው እንዲሰላ፣ ነፍስያው እንዲጠግብ፣ የውስጡም የውጪውም ሕይወቱ እንዲያምር ሀ ብሎ ስራ የሚጀምርበት ዕለት ነው፡፡ በርግጥ ብዙዎቻችን አዲስ ዓመትን ከአለባበስ፣ ከመብልና ከመጠጥ ጋር ብቻ የምናያይዝ ነን፤ እንዲሁም ከወዳጅ ዘመድ ጋር ተገናኝቶ ለመጫወት ብቻ ቀኑን የምናሳልፍ ጥቂት አይደለንም፡፡ ከቤተሰብ ጋር ሆኖ አምሮና ደምቆ በፍቅርና በደስታ አዲስ ዓመትን ማሳለፍ የሚያስደስት ቢሆንም እውነተኛ የአዲስ ዓመት ትርጉሙ ግን አዲስ ሰውነት፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ለውጥ፣ አዲስ የሕይወት መንገድ የምናበጅበት፣ ለራሳችን ቀና አስተሳሰብ የምንቀይስበት ዕለት ነው፡፡
የስቶይክ ፍልስፍና አራማጆች እንደሚመክሩት የሰው ልጅ ጭንቀቱና ትኩረቱ መሆን ያለበት መቆጣጠር በማይችላቸው በውጫዊ ኩነቶች ሳይሆን በቀላሉ ሊያስተዳድራቸው በሚችላቸው በውስጣዊ ሕይወቱ መሆን አለበት ይላሉ፡፡ የሰውነት ጓዳ ጎድጓዳውን ሳይሞላ ቤቱን በቁስ የሚሞላ ሰው የአዕምሮ ድሃ ነው፡፡ ሕይወቱን ለመብላት ብቻ የሚያኖራት እውነተኛ ደስታ የለውም፡፡ ሆድን ከመሙላት በላይ አዕምሮን በማጥገብ ነው የሕይወት እርካታ የሚገኘው፡፡ የሰው ልጅ በእንጀራ ብቻ አይኖርም እንዲል ቅዱስ ቃሉ፡፡
ሰው ለአዲስ ዓመት አዲስ እቅድ ሲያዘጋጅ ገንዘብ ለማግኘት ብቻ ብሎ ሳይሆን ገንዘብ እንዴት መስራትና በምን አግባብ ሐብት ማከማቸት እንደሚችል የሚያውቅ ጭንቅላት መፍጠር እንዳለበትም ጭምር ካልሆነ እቅዱ ትርጉም አይሰጥም፡፡ ገንዘቡ ግንዛቤ ከሌለው አደጋ ነው፡፡ አዲስ ዓመት በቁስ ሃብታም የመሆን ጉዳይ ብቻ አይደለም፡፡ አዲስ ዓመት በአዲስ አስተሳሰብ የመንፈስ ባለፀጋ የዕውቀት ባለሐብት ለመሆን እቅድ ካልተያዘበት ዋጋ የለውም፡፡ ሰውነትን የማያበለጽግ እቅድ ግቡን ቢመታም ህይወትን አስደሳች አያደርግም፡፡
ወዳጄ ሆይ..... የአዲስ ዓመት ፍልስፍናህን ገምግመው፡፡ አንተ ራስህን ለመለወጥ ቆርጠህ ካልተነሳህ አዲስ ዓመት አንተን አይለውጥህም፤ ቀኑ በራሱ ጥንትም ማንንም ለውጦ አያወቅም፤ ወደፊትም አይለውጥም፡፡ አዲስነት በሃሳብ መለየት ብቻ ሳይሆን በግንዛቤ መበልጸግ፣ በጥበብ መጎልመስ፣ ራስን በመቆጣጠር መርቀቅም ጭምር መሆኑን ተረዳ፡፡ አዲስነት የትናንቱን ድካም፤ ያለፈውን አጉል ልማድ መድገም ሳይሆን አዲሱን ኑሮ በአዲስ ሰውነት፣ በሰለጠነ አስተሳሰብና በቀናነት መጀመር ነው፡፡ አዎ! አዲስ ዓመት ከአዙሪት ሕይወትህ ነጻ የምትወጣበት፤ ከአጉል ልማድ እስርህ ሐርነት የምታገኝበት የነፃነት ቀንህ ነው፡፡ አዲስ ዓመት ለራስህ፣ ለወገንህ፣ ለሐገርህ ቅን አስበህ በጎውን የምትከውንበት የስራ ዘመንህም ነው፡፡ አዲሱ ዓመት ሰላም የሞላበት፣ ፍቅር የበዛበት ይሆን ዘንድ ከራስህ ጋር ውል የምትፈፅምበት የቃልኪዳን ዕለትህም ጭምር ነው፡፡ አዲሱን ዓመት በአዲስ ሰውነት ካልተቀበልከው አዲሱ ዓመትህ ያረጃል፣ አንተም በአዲስ ዓመት ከበርቻቻ ትርጉም ታጣለህ፡፡
አዲስ ዓመት የአዲስ ሕይወት ጅማሮ፤ የቀናነት አስተሳሰብ የመጀመሪያው ክፍለጊዜ ነው፡፡
መልካም አዲስ ዓመት!
ቸር ዘመን!
____________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
ዕለተ ማግሠኞ ጰጉሜ ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም.

21/08/2021

አስተሳሰብህን ጠርጥር! ፖለቲካህን ጠርጥር! ራሱ ጥርጣሬህንም ቢሆን ጠርጥር!
(Be skeptical even of your skepticism)
(እ.ብ.ይ.)

አባቶቻችን ‹‹ጠርጥር ገንፎም አለው ስንጥር››፣ ‹‹ያልጠረጠረ ተመነጠረ›› እያሉ ጥርጣሬ እውነትን ማግኛ፤ ከክፉ ወጥመድ ማምለጫ መንገድ አድርገው በምሳሌውም በተረቱም ያስተምሩናል፡፡ መጠርጠር በቅን ልቦና ከሆነ መድረሻው እውነትና እውቀት ነው፡፡ ስሜትን መጠርጠር ከደመነፍስ ውሳኔ ያድናል፡፡ አቋምን መጠርጠር ከመውደቅና ከመደናቀፍ ይጠብቃል፡፡ ሃሳብን መጠርጠር ከግራመጋባት ይመልሳል፡፡ አዙሮ ማየት፣ መለስ ብሎ መመልከት፣ አራት ዓይና መሆን ጥርጣሬን ማስወገጃ፣ ግራ መጋባትን ማጥሪያዎች ናቸው፡፡ መጠርጠር የምርምር መስመር ነው፡፡ ዓለሙን የጠረጠሩ የዓለሙን አስከፊ ሁኔታ ለውጠዋል፡፡ የኖርንበትን አስተሳሰብ የጠረጠሩና ዙሪያ ገባውን አመለካከት የመዘኑ የተሻለ እውቀትና ማንነት ላይ ደርሰዋል፡፡ ዓለም እዚህ ዝማኔ ላይ የደረሰችው እውነት ባይሆንስ፣ ልክ ባይሆንስ፣ የምንከተለው መንገድ የተሳሳተ ቢሆንስ ብለው ሁኔታውን፣ መንገዱን፣ ውስጡን ባጠኑ ጥልቅ አሳቢያን ነው፡፡

የምዕራቡ ዓለም ፍልሰፍና ከተወለደ ሁለተኛ ሚሊንየሙን አሳልፏል፡፡ ነገር ግን ዘመናዊው ፍልስፍና ከጥንታዊው ፍልስፍና ዕድሜ ጠገብነት አንጻር በንፅፅር ሲታይ ዕድሜው ገና ለጋ ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ የጥንታዊው ፈላስፎች ምድብ መገኛ ሐገር ግሪክ ስትሆን በጊዜው ከነበሩት ፈላስፎች መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሱት እነሶቅራጦስ፣ ፕሌቶ፣ አርስጣጢሊስ እና ሌሎችም ናቸው፡፡ የሁለተኛው የፈላስፎች ምድብ መነሻውን ሰሜን አውሮፓ ያደረገ ሲሆን ተጠቃሽ ተዋናዮቹም የነበሩት ዴስካርቴ፣ ሆብስ፣ ሰፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሊቤንዝ፣ ሂዩም፣ ሩሶ፣ ቮልቴርና ሌሎችም ናቸው፡፡ እነዚህ የዘመናዊውን ፍልስፍና ለዓለሙ ያስተዋወቁ፣ የስነክዋክብቱን፣ የጨረቃውን፣ የትዕይንተ ዓለሙን ፍልስፍና ከሰማይ አውርደው የሰውነትን ፍልስፍና ወደሰው ልጅ ልቦና የዶሉ፤ የተኛውን አዕምሮ የቀሰቀሱና ጨለማውን ዘመን በዕውቀት ብርሃን የገፈፉ፤ የሃሳብ አብዮት ያስነሱ፣ ለምን፣ አንዴት ብለው የጠየቁ የሃሳብ አብዮቶኞች ናቸው፡፡ በሁለቱም ምድብ የነበሩት ፈላስፎች ፍልስፍናን ለገንዘብ ጥቅም ሳይሆን ለእውነት፣ ለመንፈስ ደስታ የተፈላሰፉባት፣ ለዕውቀት የረቀቁባት፣ ቁሳዊ ችግርን ለመፍታት ሳይንስን ፀንሰው የወለዱባት፤ እውነትን ፈላጊዎች፣ ጥበብን አሳዳጆች፣ ዕውቀትን አጥማጆች ነበሩ፡፡ ያለምንም ቁሳዊ ክፍያ ሕሊናቸውን በዕውቀት አጥግበው፤ ለጥበብ ሲሉ ነፍሳቸውን እስከመስጠት የደረሱ አስቦ አዳሪዎች፣ ሰርቶ አሳዪዎች ናቸው፡፡ 18ኛው ክ/ዘመን ያበቀለው የዕውቀት ብርሃን (Enlightnment) እነዴስካርቴ በ17ኛው ክ/ዘ የዘሩትን ነው፡፡ ዓለም የዛሬዋ ስልጣኔ ላይ እንድትደርስ ዋጋ የከፈሉ ጥልቅ አሳቢያን ክብር ይገባቸዋል፡፡

ከዘመናዊው ፈላስፎች መካከል አንደኛው ሰው ዴስካርቴ ነው፡፡ ይህ ሰው እውነትን የሚፈልግበት መንገድ የተለየ ነበር፡፡ የፍራንሲስ ቤከን አባባል የእሱ የፍልስፍናው መመሪያ ሆኗል፡፡ ፍራንሲስ ቤከን፡-

‹‹በእርግጠኝነት የጀመረ ሰው በጥርጣሬ ይጨርሳል፡፡ ነገር ግን በጥርጣሬ የጀመረ በእርግጠኝነት ይጨርሳል፡፡ (If man will begin with certainties, he shall end in doubts, If he will be content to begin with doubts, he shall end in certainties)›› ይላል፡፡

የዴስካርቴ ፍልስፍና የፍራንስስ ቤከን ግልባጭ ነው፡፡ ጠርጣራነቱ እውነትን የሚፈልግበት አዋጭ መንገዱ ነው፡፡ ስሜቱን አያምንም፡፡ ስሜታችን አሳሳች ነው ብሎ ነው የሚያስበው፡፡ በማሕበረሰቡ እምነትና አመለካከት ላይ አመኔታ የለውም፡፡ ባህሉንም፣ ሃይማኖቱንም ወግ ልማዱንም ይጠረጥራል፡፡ የራሱን ሃሳብ እንኳን እንደወረደ አያምነውም፡፡ ከእኛ አስተሳሰብ ውጪ በእኛ ላይ ሃይል ያለው ማንም የለም ይላል፡፡ ያልተጠረጠረና ያልተመነጠረ አስተሳሰባችን ነው አሁን ላለንበት የክፋት ጥግ፣ የማንነት ቀውስ፣ የውርደት ደረጃ ያደረሰን ሲል ይናገራል፡፡

እውነት ነው! ባህላችን፣ አኗኗራችንና ወግ ልማዳችን እንድናስብ ሳይሆን ዝም ብለን እንድንቀበል ነው የሚገፋፋን፡፡ ልናራግፋቸው የሚገቡን የተጫኑብን የመንፈስ ሸክሞች ብዙ ናቸው፡፡ ስነልቦናችን ልክ አይደለም፡፡ አስተሳሰባችን የጠራ አይደለም፡፡ ማሕበረሰባችን ምን፣ ለምን፣ እንዴት ብሎ መጠየቅ አላስለመደንም፡፡ ወይ መቀበል አልያም መቃወም ነው የተማርነው፡፡ ስንቀበል እንዴት፤ ስንቃወም ለምን ብለን አንጠይቅም፣ ምክንያታችንን አናስቀምጥም፣ ማስረጃችንን አናቀርብም፡፡ ዓለሙ የጋተን በግድ ማመንን ወይም በሃይል ማሳመንን ነው፡፡ በታሪካችን ጀግና የሚባለው ጉልበተኛው ነው፡፡ ዘመደ ብዙን እንፈራለን፤ ብቸኛውን እናስፈራራለን፡፡ ደሃ አደጉን እንበድላለን፤ ለባለ ገንዘቡ እናደላለን፡፡ ሰውን በነፃና በእኩል ደረጃ መውደድ አልተለማመድንም፡፡ አሁንም ባለጡንቻው ይሾማል፣ ይሸለማል፣ ይፈራል፣ ይታፈራል፣ ይገበርለታል፡፡ ዛሬም ጦርነት የሃሳብ ልዩነቶቻችን መፍትሄ እንደሆነ ነው፡፡ ያለነፍጥ በሃሳብ ለመሸናነፍ የተዘጋጀን አይደለንም፡፡ በዘመናዊው ዓለም ውስጥ የምንኖር ኋላ ቀር ህዝቦች ሆነናል ብል ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ ባለስልጣኑን አንጠረጥርም፤ ፖለቲካችንን አንጠረጥርም፤ ካድሬውን አንጠረጥርም፣ ሴራውን አንፈትሽም፡፡ ርዕዮታችን ሰልባጅ ነው፡፡ በልካችን የተሰፋ ፖሊሲም ሆነ ስትራቴጂ የለንም፡፡ እቅዳችን የሚሳካው በሪፖርት እንጂ በተግባር አይደለም፡፡ የምናምነውን መዝነንና መርምረን አናምንም፡፡ ወገንተኝነት ያጠቃናል፡፡ አድሏዊነት አጥፍቶናል፡፡ የምንቃወመው፣ የምንጠላው፣ የምንወደውም በጅምላ ነው፡፡ በግል የምንወስንበት ደረጃ ላይ አልደረስንም፡፡ ተማርን የምንል ብንኖርም መማራችን በተግባር አልታየም፡፡ ሃሳባችን መሬት ላይ መውረድ አልቻለም፡፡

ወዳጄ ሆይ.... ዴስካርቴ፡- ‹‹ጥርጣሬ የጥበብ መገኛ ነች! (Doubt is the origin of wisdom)›› እንዲል መጠርጠር የሚገባህን ሁሉ ጠርጥር፡፡ አዎ ፍቅርህንም ቢሆን ጠርጥር፡፡ ጠብህንም ጠርጥር፡፡ ፖለቲካህንም ጠርጥር፤ ፍልስፍናህን ጠርጥር፤ ስሜትህንም ጠርጥር፡፡ ከሁሉ ይልቅ ሃሳብህን ጠርጥር፡፡ ዕውቀትህንም ጠርጥር፡፡ አሁን የያዝኩት እውቀት፣ እውነትና እምነት ልክ ነውን ብለህ መዝን፡፡ አጉል ጥርጣሬ እንዳይሆን ራሱ ጥርጣሬህንም ቢሆን ጠርጥር! ጠርጥር ስልህ መርምር እያልኩህ እንደሆነ አትዘንጋ፡፡ አንተነትህን ፈትሽ! ሕይወትህን ፈትሽ! ስሜትህን ፈትሽ፣ መንፈስህን ፈትሽ! የአስተሳሰብ ማዕከልህን፣ የአመለካከት ድንበርህን ፈትሽ!

‹‹ጠርጠር እንዳታጥር፤
ጥርጣሬህንም ጠርጥር፣
ወደኋላ እንዳትነጥር፡፡
ፈትሽ እንዳትቆሽሽ!
ሞራልህ እንዳይሟሽሽ፤
ሩጥ መርሽ...
ከሐሰቱ ሽሽ፡፡››

ቸር ጥርጣሬ!

____________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
ዕለተ እሁድ ነሐሴ ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም.

17/07/2021

ማንበብ ያልለወጠው ትውልድ!
(እ.ብ.ይ.)
(Re)
በእኛ ሐገር ከሚያነቡት ይልቅ የማያነቡት እንደሚበልጡ ምንም ምርምርም ሆነ ክርክር አያሻውም፡፡ ብዙዎቻችን አናነብም፡፡ ብናነብ እንኳን ያነበብነውን አናሰላስለውም፡፡ ባናሰላስለው እንኳን ካነበብነው መጽሐፍ ቁምነገሩን መርጠንና ዘግነን ከሃሳባችን ጋር አናስታርቀውም፡፡ የንባብ ቁምነገሩ ለሕይወታችን እንዲጠቅም ለማድረግ አንሞክርም፡፡ ከንባብ ባገኘነው ጠቃሚ ሃሳብ ውስጣችንን ለማደስ ልምምድ አናደርግም፡፡ ቁምነገሩን ባንቆነጥር እንኳን ራሳችንን ለማየት በንባብ ያገኘነውን ሃሳብ ከራሳችን ሕይወትና አመለካከት ጋር አናስተያየውም፡፡ ሃሳቡን በሃሳባችን ለመሞረድ አንጥርም፡፡ አንብበናል ለማለት እንጂ ለመለወጥ የምናነብ በጣም ጥቂቶች ነን፡፡
አዎ! አንብበዋል የምንላቸው የ60ዎቹ ትውልድ እንኳን ስለማንበባቸው በመልካም ተግባር፣ በሚታይ ስራ አላረጋገጡልንም፡፡ ማንበብ አንድን አንባቢ በመልካም መሠረት ላይ አቁሞ ተግባሩን ሠናይ ካላደረገው ማንበቡ ፋይዳ የለውም፡፡ ማንበብ ራስን እንደመመልከቻ መስታወት ሆኖ አዲስ አስተሳሰብን የምንፈጥርበት ሂደት ነው፡፡ ማንበብ ብቻውን የመጨረሻው ግብ አይደለም፡፡ ግቡ አዲስ አስተሳሰብ ፈጥሮ ራስን በአዲስና በተሻለ አስተሳሰብ መለወጥ መቻል ነው፡፡ አዲስነት ከተለመደው ውጪ እንግዳ የሆነ ሃሳብ ብቻ ሳይሆን የነበረውንም ኋላ ቀርና ጠቃሚ ያልሆነ አስተሳሰብ የሚያሻሽልና የሚለውጥ ማለት ነው፡፡ ለውጥ ተፈጥሯዊ ግዴታ ነው፡፡ ሰው በአካላዊው ተፈጥሮው እንደየዕድሜው ይለዋወጣል፡፡ ነገር ግን ብዙዎቻችን መንፈሳዊ አካላችንን ለመለወጥ ዝግጅቱ የለንም፡፡ ላያችን ይለወጣል እንጂ ውስጣችን ባለበት ተገትሮ ቆሟል፡፡ ተፈጥሮ አካላችንን ሲለውጥ፤ እኛ ደግሞ መንፈሳዊ ማንነታችንን መለወጥ ይኖርብናል፡፡ ይሄም የሚሆን ነው በማንበብ ነው፡፡ ማንበብ ስንል መፅሐፍን፣ ተፈጥሮን፣ ትናንትን፣ ራስን፣ የወደፊት ሕይወትን፣ ወዘተ ማለታችን ይታወቅ፡፡ ራስን መለወጥ አንድ ነገር ቢሆንም የመለወጥ ግቡ ተለውጦ መቅረት ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ይለወጡ ዘንድ መብራት መሆንም ጭምር ነው፡፡ ለውጡ ተለውጦ ለዋጭ መሆን አለበት፡፡ ለሌሎች ብርሃን ሆኖ የለውጥን ዳና ማስመር ይጠበቅበታል፡፡ ለውጥ ማለት ለውጡ ሐገራዊ እንዲሆን መልፋትም ጭምር ነው፡፡ ብሔራዊ ለውጥ ወደፊት ያራምዳል፡፡ ጥቂቶች ተለውጠው ብዙሃኑ ወደኋላ ከቀረ ሐገርን ለመለወጥ ይከብዳል፡፡ ሐገር ማለት ሰው ነውና እንዲል ገጣሚው!
ዛሬ አንብበው ራሳቸውን የለወጡ አርአያ የሆኑ አንባብያን እጥረት አለብን፡፡ መፅሐፍ የሚሸከሙ (Book carriers) እንጂ አንብበው የሚለወጡና የሚለውጡ የለውጥ ወኪሎች (Change agents) እምብዛም ናቸው፡፡ ኑሯቸውን የለወጡ ይገኙ ይሆናል እንጂ ሰውነታቸውን ከፍ ከፍ ያደረጉ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ምሁርነታቸውን ለምስቅልቅል ፖለቲካ ያዋሉና ማንበባቸውን ለአድሏዊ ፖለቲካ የሚጠቀሙበት ፖለቲከኞች የፖለቲካ ፓርቲ ይቁጠራቸው፡፡ ዘንድሮ ማወቃቸውን በጽንፈኝነት የሚያረጋግጡልን መዓት አንባቢዎች ሞልተውናል፡፡ ማንበባቸው ፅንፈኝነታቸውን አንዲያውጁ ረዳቸው እንጂ ሰውነታቸው ላይ የጨመረው ምንም ደግ ነገር የለም፡፡ ለሌላው ማሰብ የቻሉ አንባቢዎችና ተመራማሪዎችን ማግኘት ብርቅ ሆኖብናል፡፡ አንብበን ያልተለወጥን ትውልድ ከሆንን ራሳችን ለራሳችን አደጋዎች ነን፡፡ ማንበብ ያልለወጠው ትውልድ ዳፋው በራሱና በሐገሩ ላይ ነው፡፡ የችግሩ ምንጭም የችግሩ ገፈት ቀማሹም ራሱ ነውና፡፡
አንዳንዴ የ60ዎቹን ትውልድ ውቀስ ውቀስ ይለኛል፡፡ እጅን ሌላ ላይ መጠቆም አልወድም፡፡ ነገር ግን የዛ ዘመን ትውልድ የነበሩት ወጣቶች አንባቢዎች ነበሩ፡፡ በንባብ ልምዳቸው የሚቀናባቸው ቢሆኑም መሬት ላይ ጠብ ያለ ነገር ባለማምጣታቸው ያስቆጩናል፡፡ ብዙ አንብበዋል፣ ብዙ ተመራምረዋል፣ የማርክሲዝም፣ የካፒቲሊዝም፣ የኮሚኒዝም፣ የብዙ ኢዝም ፅንሰሃሳቦችን ኮምኩመዋል፡፡ እርስበርስ በፖለቲካ ርዕዮት ዓለም ተቆራቁሰዋል፡፡ ክርክሩ፣ ጭቅጭቁ፣ የፖለቲካ ልዩነቱ ማንበባቸውንና ዕውቀታቸውን ፈትኖ የነበረ ቢሆንም ሐገራችን ላይ ያነበሩት የፖለቲካ ሥርዓት ግን ችግራችንን የሚቀርፍ አልሆነም፡፡ መስዋዕት የሆኑለትንና የተዋደቁለትን ርዕዮት በተግባር አልለወጡትም፡፡ እነሱም እርስበራሳቸው አሳዳጅና ተሳዳጅ፣ ገዳይና ሟች ሆነዋል፡፡ ሕዝባቸውም የሥርዓታቸው ተጨቋኝ ሆኗል፡፡ ጭቆናን ለመታገል የወጡ ጨቋኞች ሆነው ተመልሰዋል፡፡ በብሶት ወደግንባር በረሃ የወረዱ ብሶተኞች ሌሎች ብሶተኞችን ፈጥረዋል፡፡ በሃሳብ ለመታገል የቆረጡ በጥይት ምላሽ አግኝተዋል፡፡ የሃሳብ አብዮት አስነስተው የመሳሪያ አብዮት በልቷቸዋል፡፡ አሳዛኝ ትውልድ!
ዛሬም ስለሰብዓዊ መብት፣ ስለእኩልነት፣ ስለንግግር ነፃነት፣ ስለፕሬስ ነፃነት ወዘተ ድምፃችንን እያሰማን ነው፡፡ የአንባቢነት ማረጋገጫው ፍሬው ነውና ፍሬውን አጥተናል፡፡ ዛሬም የዲሞክራሲ ረሀባችን አልታገሰም፡፡ የእኩልነት ጥማችን አልረካም፡፡ አሁንም ጉልበትና አምባገነንነት እየቆራረጠን ነው፡፡ ታዲያ ማንበባችን ቁምነገሩ ወዴት አለ??????? በማንበብ ድል ያልተመታ ፈላጭ ቆራጭነት በምን ሊሸነፍ ይችላል???? ሃሳብ ያልረታው አድሏዊነት፣ ዕውቀት ያላገደው ተረኝነት እንዴት በእኩልነት ሊተካ ይችላል???? እኔንጃ!
ማንበብ ያልለወጠው ትውልድ ታዲያ ምን ሊለውጠው ኖሯል?? ያለፈውም የአሁኑም ትውልድ ያነባል እንጂ አልተለወጠም፡፡ እናነባለን እንጂ ሐገራዊ መፍትሄ ለማምጣት እውቀት አልፈጠርንም፡፡ አነባበባችን ይሁን የምናነበው መፅሐፍ አላውቅም መልካሚቱንና ትክክለኛዋን ጥበብን እንድናገኝ አላስቻለንም፡፡ የተደበቀውን የአያቶቻችንን ጥበብ ለመግለጥ የሚያስችል አዕምሮ አልቀረፅንም፡፡ አርአያ የሆነ ትውልድ አጥተናል፡፡ መጪውም ትውልድ መነሻ እንዲያጣ እያደረግነው ነው፡፡ የምዕራባውያኑን እውቀት እናነበንበዋለን እንጂ አልኖንበትም፡፡ ታዲያ ከየቱ ነን???????
እውነቱን ለመናገር በገዛ አስተሳሰባችን ታመናል፡፡ ከራሳችን ጋር ሆድ ተባብሰናል፡፡ ከራሳችንም ከሌላውም ጋር ለመታረቅ የሚያስችል ለሁላችንም ተስማሚ ሃሳብ አልፈጠርንም፡፡ በጎራ ተከፋፍለን፣ በጎጥ ተለያይተን፣ በአስተሳሰብ ተጠፋፍተን ኑሮ አይሉት ነገር እያለን የለንም፡፡ እውነተኛ ማንበብማ ለውጦ ለዋጭ ነበር፡፡ ብልህ አንባቢ ትውልድ ራሱን ለውጦ ሐገሩን ይለውጣል፡፡ አንብቦ ያልተለወጥ ትውልድ ግን ለራሱም፣ ለሐገሩም ዕዳና አደጋ ነው፡፡ እንለወጥ ዘንድ እናንብብ የዕለቱ መልዕክት ነው!
ቸር የሚለውጥ ንባብ!
___________________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
ሠኞ ሐምሌ ፰ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም.

17/06/2021

ፍላጎታችን አይሰልጥንብን ◈
==========================
ኢኮኖሚክስ ላይ"
water & Diamond paradox "የሚባል እሳቤ አለ።
ለኑረት ወሳኙ ነገር ውሀ ነው ነገር ግን ርካሽ ነው ፣
አልማዝ ለህላዌ የሚያበረክተው ድንቡሎ የለም ።
ግን ውድ ነው።
ለዚህም ይመስላል
አንስታይን
"The important things are always simple "
ማለቱ ዘግይቶም ቢሆን የሚገባህ እውነት ነገሮችን
በውድና ርካሽ የሚፈርጀው አስተሳሰብ እንጂ የነገሩ ወሳኝነት አለመሆኑን ነው

እርግጥ ማህበረሰባዊ ስምምነቶች ለተፈጥሮ ህግ ከመገዛት
ይልቅ መንጋነትን ያበረታሉ ።
ለምሳሌ ◆ ዋናው ቁምነገር አብሮነትና ፍቅሩ ቢሆንም ውዱ ግን ሰርጋችን ነው ።
◆ ጠቃሚው ውበት ፀጥታ ቢሆንም የምንከፍለው ግን
ለሚበጠብጠን ጩኸት ነው
◆ ጤናችን ያለው ንፁህ ውሀ ውስጥ ቢሆንም ብዙ የምንከፍለው ግን ለመታመሚያችን አልኮል ነው ። ወዘተ...
እልፍ ርቀት ሮጠህ ስታበቃ ቆም ብለህ "ለዚህ ጉዳይ ይሔን
ያህል ዋጋ መክፈል ነበረብኝን ?" ብለህ ብትጠይቅም መሮጥህን ግን አታቆምም።
በዙሪያህ ያሉ ነገሮች ጡዘትህን እንጂ ቆምታህን አያበረቱም ።
ይልቁንስ በውድድር እንድትቆይ ይገፉሀል ።
ከጓደኛህ ትወዳደራለህ ፣ከጎረቤትህ ትወዳደራለህ ፣ ከባልደረባህ ትወዳደራለህ ፣ ከንግድ አቻዎችህ ትወዳደራለህ ።
እናም ማቆሚያ በሌለው ዙረት ውስጥ ትዳክራለህ ።
ዛሬ የሆነ ነገር ለማግኘት ትሮጣለህ ደርሰህ ስትይዘው
ይቀልብሀል ። ነገ ሌላ ለመጨበጥ ትዘረጋለህ ደርሰህ ስታየው
ለዚህ ነው በሬዬን ያረድኩት ያስብልሀል ።
እንደገና ሌላ ሩጫ ፣
እንደገና ሌላ መባከን ፣ እንደገና ሌላ ፍለጋ.......
እጅህ ላይ ያለው ካላስደሰተህ እርግጠኛ ሁን ሊመጣ
ያለውም አያረካህም ፣ በርህ ላይ ባለው አበባ ሳትፈነድቅ በገነት
ውበት አትመሰጥም ። ደስታን ከውጭ ከመፈለግ በላይ ጉድለት
የሚመስለኝ ይህ ነው ። እየፈለጉ መቀጠልን ማቆም ባይቻል
በደረሱበት አለምቃቃት ትልቅ ጉዳት ነው። የደረስክበት ደግሞ
አሁን ነው ፣ ይህ ቅፅበት ፣ አሁንና እዚህ.....
አንዳንዶች "የኔ ቀን ነገ ናት " እንላለን ።
እንዴት ሰው እርግጠኛ ከሚሆንበት ዛሬ ይልቅ የማያውቀው ነገ ላይ የደስታውን
ውበት ያንጠለጥላል ? ደስታ ኑረትን ግድ ይላል እኮ ... ነገ እንትን ሳገኝ እደሰታለሁ የምትል ከሆነ ለመደሰት ቀጠሮ እየሰጠህ ነው ፣ ከዛም በላይ ደስታህን በነገሩ መኖር አለመኖር ላይ እየመሰረትክ ነው ።
ደግሞስ ለደስታ ምን ያህል ነው የሚበቃን ? ስንት ብር ፣
ስንት መኪና ፣ ምን ያህል ቁስ ? በዙሪያህ ብዙ ያላቸው
ተነጫናጮችና ምንም የሌላቸው ደስተኞች አሉ እኮ እናም ደስታ
ውስጣዊ እንጂ ቁሳዊ ወይም ሰበባዊ አይደለም ።
ሆኖም በተግባባንበት መንገድ ለመደሰት ስንት ያስፈልገናል ? ምንም አይበቃንም ።
ምናልባትም ምድርን የሚያህል ሀብት ቢኖረን እንኳን ሌላ ፕላኔት ማሰሳችን አይቀርም ።

ምክንያቱም ደስታ ከብዛትም ሆነ ከነገሮች ጋር አይቆራኝም ።
"የሰው ልጅ ፍላጎት ገደብ የለውም " በሚል ከንቱ ስብከት
እየተነዱ ያለኝ ይበቃኛል ማለት እንደሚከብድ ግልፅ ነው ።
.
ያም ሆኖ በፍላጎታችን ላይ የምንሰለጥን እንጂ ፍላጎት የሚሰለጥንብን
እንዳልሆንን ጠቃሚ ይመስለኛል ። አግበስባሽነት በማግኘት ላይ እንድትመሰጥ እንጂ ባለህ ነገር ደስታ እንድትፈጥር እድል
አይሰጥህምና .....
Source :book for all Facebook group

30/05/2021

ስሜት ማጣት ራሱ ስሜት ነው! (የባዶነት ስሜት!)
(እ.ብ.ይ.)

መኖር ስሜት ነው፡፡ ትዳር ስሜት ነው፡፡ ጓደኝነት ስሜት ነው፡፡ አብሮ ማሳለፍ፣ አብሮ መኖር ስሜት ነው፡፡ መብላት መጠጣት ስሜት ነው፡፡ ፍቅር ስሜትም ውሳኔም ነው፡፡ ጥላቻም ስሜት ነው፡፡ ሰላም ስሜት ነው፡፡ ሰላም ማጣትም ስሜት ነው፡፡ ሐዘን ስሜት ነው፤ ደስታም ስሜት ነው፡፡ ርሃብ ስሜት ነው፤ ጥጋብም ስሜት ነው፡፡ መጠማት ስሜት ነው፤ ጥምን መቁረጥም ያው ስሜት ነው፡፡ መብላት መጠጣት የርሃብን ስሜት አስታግሶ የእርካታ ስሜትን ማምጣት ነው፡፡ የጥጋብ ስሜትም ያው ስሜት ነው፡፡ የመራብም ሆነ የጥጋብ ስሜት ሁለቱም ገፊ ስሜቶች ናቸው፡፡ ስሜቶቹ የሚፈልጉትን ካላገኙ አደጋ ያመጣሉ፡፡ ሰው ሲርበው ብዙ እንደሚያደርገው ሁሉ ሲጠግብም ጥጋቡ አያስቀምጠውም፡፡ ‹‹ካልጠገቡ አይዘሉ፤ ካልዘለሉ አይሰበሩ›› እንዲል የሐገራችን ብሒል፡፡

አንዳንድ ጊዜ በሁሉም ነገሮች ስሜት ታጣለህ፡፡ ባዶነት ይሰማሃል፡፡ ስሜት ማጣትም በራሱ ስሜት ቢሆንም ባዶነትህ ግን ያሳስብሃል፡፡ ጣዕም አልባ ሕይወት፤ አልጫ አልጫ የሚል ኑሮ ጨው አልባ ስሜት ነው፡፡ ባይጣፍጥም፣ ባይጥምም ስሜት አለው፡፡ ባያስደስትም፣ ባያረካም ደስ ባይልም ስሜት ነው፡፡ ደስ አለመሰኘቱን ያወቅከው በዛው ስሜትህ ነውና፡፡ የመኖር ስሜቱ ያወዛግብሃል፡፡ ወዳጅነት፣ ዝምድና፣ ወዘተ ማህበራዊ ግንኙነቶች ስሜት ታጣባቸዋለህ፡፡ የዓለም ትርጉሙ ስሜት አልሰጥ ይልሃል፡፡ የሕይወትህ ዓላማ፣ የመኖርህ ምክንያት ትርጉሙ፣ ስረ-ስሜቱ ይምታታብሃል፡፡ ራሱን ስሜትህን ስሜት ባጣ ስሜትህ ሆነህ ስታጠናው ውሉ ግራ ይገባሃል፡፡ ባዶነትን ስትመረምረው፣ አለመሙላትን ስታውቀው ለምን ትላለህ፡፡ ስሜት አልባ ስሜት ይሉሃል ይሄ ነው!

ጥላቻ ስሜት ነው፡፡ ብዙ ሰው በተለይ በዚህ ዘረኝነት ባረበበት ጊዜ ሰውን ዝም ብሎ ይጠላል፡፡ የሚጠላው በዕውቀቱ ሳይሆን በስሜቱ ነው፡፡ እያወቀ የሚጠላ፣ ተምሮ የሚያወግዝ የበዛበት ዘመን ነው፡፡ እርግማኑ የመነጨው፣ ጥላቻው የተፀነሰው ከስሜቱ ማህፀን እንጂ ከእውቀቱ ማህደር አይደለም፡፡ አንዳንድ ሰው ለጥላቻው ምክንያት ይደረድራል፡፡ ምክንያቱ ግን ከጠዪው ስሜቱ እንጂ ከአዋቂው አዕምሮው አይደለም፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ከህሊናው ጋር ተጣልቶ ከስሜቱ ጋር የተወዳጀ ነው፡፡ የሚፈልገው መጥላትን ብቻ ስለሆነ ለጥላቻው ትርጉም አልባ ሰበብ ይዘበዝባል፡፡

አንዳንድ ስሜት ደግሞ አለ በውስጥህ የሚርመሰመስ፡፡ ለመውጣት ጊዜ የሚጠብቅ፡፡ አንዳንድ ጊዜ አልቅሰህም ሆነ ስቀህ፤ ጮኸህም ሆነ ተመስጠህ የማታወጣው ስሜት በውስጥህ ይተራመሳል፡፡ ተናግረህ የማትገልጸው፤ ፅፈህ የማታወጣው፣ ፀልየህ የማትገልጠው ድብቅ ስሜት በስውር መንፈስህ ላይ ረብብቦ ስሜት ያሳጣሃል፡፡ ለቅርብህ ሰው፣ ለወዳጅህ፣ ለወላጅህ፣ ለነፍስ አባትህ፣ ለሐኪምህ የማትነግረው ስሜት አልባ ስሜት ሊሰማህ ይችላል፡፡ ለቅሶ የሀዘን ስሜትህን የምትገልጽበት መንገድ ቢሆንም አልቅሰህ የማይወጣልህ ስሜት አለ፡፡ ሳትበደል፣ ሳትከፋ፣ ምንም ሳታጣ፣ ምንም ሳትሆን ስሜት አልባ የምትሆንበት ወቅት አለ፡፡ ከደስታም፣ ከሐዘንም ያልሆነ የባዶነት ስሜት በውስጥህ ይሰነቀራል፡፡ በሰው ተከብበህ፣ በወዳጅ ዘመድ ታጥረህ ነገር ግን የብቸኝነት ስሜት የሚያንከላውስህ ቀን አለ፡፡ ቀኑ ያው ቀን ነው፤ ነገር ግን ስሜትህ ቀንህን ይለዋውጠዋል፡፡ የተለወጠው ስሜትህ አንተንም፣ ቀንህንም፣ ሕይወትህንም፣ አስተሳሰብህንም፣ አኗኗርህንም ያመሰቃቅለዋል፡፡ የተመሰቃቀለ ሕይወት የስሜት ማጣት ውጤት ነውና፡፡ ስሜት ያጣው ስሜትህን ከመረመርከው ግን ልትሰለጥንበት ትችላለህ፡፡ ባዶነትህን በእውነት፣ በምክንያት፣ በዕውቀት፣ በጥበብና በእምነት ለመሙላት ከተፍጨረጨርክ ግን ስሜቱ አዲስ ሕይወት ይሰጥሃል እንጂ አያጠፋህም፡፡

አንዳንድ ሰው የኑሮውን ስሜት ለማሟላት ሲል በአቋራጭ መንገድ ይነጉዳል፡፡ ዋሽቶም ቢሆን፣ አጭበርብሮም ቢሆን ያሻውን ለማሳካት ስሜቱን ለማስታገስ ሲል ወደውሸቱ ዓለም ይገሰግሳል፡፡ አቋራጩ መንገድ ተሳክቶለት የፈለገውን ቢያገኝ እንኳን ባገኘው ነገር ስሜት ያጣል፡፡ ፍላጎቱ የስሜቱ ወኪል ሆኖ ጉዳዩን ቢያስጨርስለትም እደሰትበታለሁ ያለው ስሜቱ ግን ያልጠበቀው ይሆናል፡፡ መፈለጉና የፍላጎቱን ለማግኘት የሚያደርገው መፍጨርጨር የፈለገውን ሲያገኝ ትርጉም ያጣበታል፤ ስሜቱም ስሜት አልባ ይሆንበታል፡፡ ፍላጎቱንም ሲጨብጥ ዋጋ ያጣበታል፡፡ እንኳን ዋሽተህና አጭበርብረህ ቀርቶ እውነተኛ ሆነህና በጎ ሰርተህ እንኳን ጥሩ ስሜት ላይሰማህ ይችላል፡፡

ጀርመናዊው ፈላስፋ ሾፐንሐወር፡-

‹‹የምትዋሸው በፍላጎትህ እንጂ በዕውቀትህ አይደለም፡፡ ስለዚህም ማወቅህ እንዳትዋሽ ካላደረገህ ፍላጎትህ የዕውቀትህ አዛዥ ሆኗል ማለት ነው፡፡ ለዚህ ነው ሃይማኖቶች በላይኛው ቤት ዋጋ ታገኝበታለህ የሚሉት የእውቀትህን ሳይሆን የፍላጎትህን ስራ ነው፡፡ ማመንዘር ብትፈልግ በእውቀትህ ሳይሆን በፍላጎትህ ነው፡፡ ጥላቻንም ብናይ ሰው በዕውቀቱ አይጠላም፤ በፍላጎቱ እንጂ፡፡›› ይላል፡፡

ወዳጄ ሆይ .. ምን ያህል ሊቅ ብትሆን ስሜትህን መግራት ካልቻልክ ፊደል መቁጠር ከማይችለው ብታንስ እንጂ በምንም አትሻልም፡፡ ዕውቀትህን ስሜትህ ካሸነፈው ዋጋ የለህም፡፡ ፍላጎትህ ጥበብህን ድል ከነሳው የፍላጎትህ ባሪያ ሆነህ ዕድሜህን ትጨርሳለህ፡፡ ምን ያህል ስምና ዝና ቢኖርህ ፍላጎትህን መቆጣጠር፣ ደመነፍስህን ማስተዳደር ካልቻልክ ምንም ነህ፡፡ ባዶነትህን ካልሞላህ እንደጎደልክ ትኖራለህ፡፡ ስሜትህ እንዳሻው እንጂ አንተ እንዳሻኸው አትሆንም፡፡ የሥሜት ማጣት ስሜት የአንተነትህ ጌታ ይሆናል፡፡ ማወቅህ ስሜትህ ላይ ካልሰለጠነ፤ ዕውቀትህ ፍላጎትህን ካልተቆጣጠረ፣ ስምና ዝናህ ስሜትህን ካልገራ እንደብረት ድስት ሲጥዱህ ቶሎ ትግላለህ፤ ሲያወርዱህም ቶሎ ትቀዘቅዛለህ፡፡ አንተ ግን ክቡር ሰው ነህ ከብረድስትም በላይ!! ስለዚህ ሰው ሁን!

ማወቅህ ፍላጎትህን ካልገዛ፤ ጥበብህ ስሜትህን ካልተቆጣጠረ ፍላጎትህና ስሜትህ የዕውቀትህ ገዢዎች ይሆናሉ!

ቸር ጊዜ!

________________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
እሁድ ግንቦት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም.

06/05/2021

ግብህን ካላወክ የትኛውም መንገድ ይወስድሃል
“ቁም ነገሩ ከየት እንደመጣህ አይደለም፣ ዋናው ቁም ነገር ወደ የት እንደምትሄድ ማወቅህ ነው” – Brian Tracy
አንድ መንገደኛ ሰው ረጅምና አድካሚ የሆነ ጎዳናን ካለፈ በኋላ መንትያ መንገዶች ላይ ደረሰ፡፡ በዚያ የቆመን አንድ ሌላ የሀሃገሩን ሰው አየና፣ “ከእነዚህ ሁለት መንገዶች ትክክለኛው መንገድ የቱ ነው?” ብሎ ጠየቀው፡፡ ይህ የሃገሩ ሰው፣ “መሄድ የምትፈልገው ወደ የት ነው?” ብሎ ለመንገደኛው ጥያቄውን በጥያቄ መለሰለት፡፡ መንገደኛውም፣ “ወደ የት መሄድ እንደፈለኩ ገና አላወኩም” አለው፡፡ የቆመውም ሰው፣ “እንግዲያውስ፣ ሁለቱም ትክክለኛ መንገዶች ናቸው” በማለት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መለሰለት፡፡ መንገደኛው፣ “የምትሄድበትን ካላወቅህ የትኛውም መንገድ ይወስድሃል” የሚልን መልእክት ተቀብሎ፣ “መልእክቱ ገብቶኛል” በሚል ዝምታ ተዋጠ፡፡
ብዙ ሰዎች በደመ-ነፍስ ነው የሚኖሩት፡፡ ከየት ተነስተው ወደ የት መሄድ እንዳለባቸው በቅጡ አያውቁትም፡፡ ወደ የት እንደሚሄዱ ማወቅ በሕይወት ላይ ያለውን ተጽእኖ በፍጹም አስበውት አያውቁም፡፡
የግብ ጉዞ የምርጫ ጉዞ ነው - “የትኛውን ጎዳና ብመርጥ ወደ ዋናው የሕይወቴ አላማና ራእይ ያደርሰኛል” የሚል ምርጫ! ግቡን በቅጡ ያላወቀ ሰው የመጣውን ያስተናግዳል፣ ወደተከፈተለት ይገባል፣ ጊዜአዊ ደስታን በሰጠው ነገር ላይ ጊዜውን ያባክናል፡፡
ሕይወት በምርጫ የተሞላች ነች፡፡ ጠዋት በስንት ሰአት ከመኝታዬ መነሳት እንዳለብኝ ከምወስነው ውሳኔ አንስቶ ማታ በስንት ሰአት ወደመኝታዬ መሄድ አለብኝ እስከሚለው ድረስ የምንመርጠው ምርጫና የምንወስነው ውሳኔ በአላማችን ላይ ጣልቃ ይገባል፡፡
“ብዙ ሰዎች የሚያስፈልጋቸው አሳ እንዳልሆነ ሳይገባቸው እድሜ ልካቸውን አሳ ሲያጠምዱ ይኖራሉ” –Henry David Thoreau
“የምትፈልገውን ነገር ካልተከታተልከው አትጨብጠውም፡፡ ካልጠየክ መልሱ ሁልጊዜ የእምቢታ ነው፡፡ ወደፊት ካልተራመድክ ዘወትር ራስህን ባለህበት ታገኘዋለህ” – Nora Roberts
“ግቡ አልደረስ ያለ ሲመስልህ መቀየር ያለብህ ግቡን አይደለም አካሄድህን እንጂ” - Unknown Source du savoir

የሚጠቅም ነገር ካገኛችሁበት ተጋሩት ከቅርብ ሰዎቻችሁ ጋር

06/05/2021

ግብፃዊያን የተሠሩበት ታሪክ ስለ ዓባይ
~~~~~~~~~~~~~~~~~
በእስሌማን አባይ

ግብፆች ከጥንት ዘመን ጀምረው ስለ አባይ ይጨነቃሉ ስለ አባይ ያለቅሳሉ ስለ አባይ ያትታሉ ይህንኑም ሃተታ ለትውልድ ያስተላልፋሉ፡፡ መነሻዬን ይሄን አድርጌ ከዛሬ 1386 አመት በፊት በኸሊፋ ዑመር ቢን ኸጣብ ዘመን እንዲቆም የተደረገን አንድ ልማድ ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡

ግብፃዊያን ከጥንት ጀምረው ለአባይ (ኒል ናይል) ወንዝ በአመት አንዲት ቆንጆ ልጅገረድ ይሰዋሉ ግብሩንም የተቀበለው የአባይ ወንዝ አመቱን ሙሉ ሲፈስ በተሰጠው ግብር እንደሆነ አጥብቀው ያምናሉ፡፡ ከዘመናት ቆይታ በኋላም አምር ኢብን-አስ ግብፅን ማስተዳደር በጀመሩ በወራቶች ውስጥ ግብፃዊያን የአባይ ወንዝ መስዋት ደረሰባቸው እና ተሰብስበው ለአምር ነገሯቸው። አምርም እንዲህ አይነቱን ከባድ ነገር ብቻየን መወሰን አልችልም በማለት ለኸሊፋ ዑመር ቢን ኸጧብ ደብዳቤ ፅፈው አሳወቁ ኸሊፋውም እንዲህ አይነት ኢ-ሰባዓዊ ድርጊት መፈፀም እንደማይቻል በደብዳቤ አሳወቁ፡፡ አምርም ለግብፃውያኑ ይህንኑ ነግረው መሰዋቱ ተከለከለ፡፡

በዚያው አመትም የናይል ውሃ ቀነሰ በመቀነሱ ምክንያትም በልማድ የተተበተቡት ግብፃዊያን ግብሩን ስላለገኘ ውሃው ቀነሰብን ብለው ደመደሙ እና ወደ አምር ኢብን አስ ለሁለተኛ ጊዜ ሂደው ጉዳዮን አስረድተው መስዋቱ እንዲፈቀድ ጠየቁ፡፡
አምርም ይህንኑ ጉዳይ በደብዳቤ ፅፈው ለኸሊፋው ልከው መልስ መጠበቅ ጀመሩ፡፡ ኸሊፋ ዑመር ቢን ኸጧብ ግን የቀየሩት ውሳኔ አልነበረም ይልቁንስ አሉት መልዕክተኛውን ይችን ደብዳቤ ለአምር ኢብን አስ ስጠውና ቀዳዶ በናይል ወንዝ ውሃ ውስጥ ይጨምራት ንገረው ብለው ደብዳቤ አስይዘው መልሰው ላኩት፡፡
ደብዳቤዋ እንዲህ ትላለች
"ይድረስ የአላህ ፍጥረት ለሆንከው የናይል ወንዝ በአላህ ፍቃድ የምትፈስ ከሆነ እንደ ወትሮህ እንድትፈስልን አላህን እንለምናለን በራስህ ፈቃድ የምትፈስ ከሆነ ግን ወሃህን መያዝ ትችላለህ እኛም አንፈልግህም" የምትል ደብዳቤ ነበረች አምር ኢብን አስም ደብዳቤዋን አንብበው ከጨረሱ በኋላ እንደተባሉት አድርገው ግብፃዊያኑን የመስዋቱ ጉዳይ በፍፁም የተከለከለ መሆኑን ነግረው አሰናበቷቸው ውሳኔው ያልተዋጠላቸው ግብፃዊያንም እያጎመተመቱ ተበተኑ የአባይ (የናይል) ወንዝ ውሃም ከሳምንት በኋላ እንደወትሮው እያጓራ መፍሰስ ጀመረ፡፡
ግብፃዊያንም ከፈርኦን ጀምሮ የነበረውን ልጃገረድ የመስዋቱን ነገር በኸሊፋ ዑመር ቢን ኸጧብ ዘመን ርግፍ አድርገው አቆሙ፡፡
እናም ወገኖቸ የአባይ ወንዝን ሊያቆም የሚችል አንድም ምድራዊ ሀይል እንደሌለ አይደለም ግብፆች ማንም ያውቀዋል ይህንን እውነታ እያወቁ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ እልህ አስጨራሽ ትግል የሚያደርጉት በግድቡ ከሚያጡት የወሃ ክፍፍል በላይ የነገዋን የተሻለች ኢትዮጵያ ላለማየት እና የኢትዮጵያን ውድቀት ከመመኘት የተነሳ ጂኦ-ፖለቲካዊ ፍላጎት ነው።

#እስሌማን አባይ በቴሌግራም ቻናሉ እንደከተበው
ናይል

25/04/2021

የአዙሪት ሕይወትህን አቋርጠው ((Interrupt the cycle))
(እ.ብ.ይ.)

ዘመኑ መረጃ ሞልቶ የሚፈስበት ዘመን ነው፡፡ ቁሳዊው መረጃና ዕውቀት እንደጎርፍ ጎርፎ አጥለቅልቆናል፡፡ አንዳንዶቻችን ከመረጃው ዓለም አለት ጋር እያጋጨ ጠራርጎ ወስዶናል፡፡ ጥቂቶቻችን ምናልባት ጎርፉን ዳር ሆነን እያሳለፍነው ይሆናል፡፡ ሌሎቻችን ደግሞ አደጋነቱ አልታየን ይሆናል፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አደጋው አግጦና አፍጦ ፊትለፊታችን ቆሟል፡፡ ዛሬ ስለዓለማችን ክንዋኔዎች ለመስማት መረጃው በየሚዲያው እንደቧንቧ ውሃ እዚህም እዚያም ይንፎለፎላል፡፡ ትላልቆቹ የመረጃ ቋቶች እነጎግል ደግሞ የአንተንና የብጤዎችህን መረጃ እየተቀበሉ አባዝተው ይሸጣሉ፡፡ ሰው ለነዚህ መረጃዎች ጆሮውን፣ ዓይኑን፣ ቀልቡን፣ አዕምሮውን፣ ጊዜውን፣ ገንዘቡን፣ መንፈሱን ሁሉ አሳልፎ ሰጥቷል፡፡ ስለዓለሙ ማወቅ ባይከፋም ስለራስ ዓለም ሳያውቁ ሲሆን ግን አሳፋሪ ነው፡፡ ራሱን ሳያውቅ ሌላውን ለማወቅ የሚጥር ራሱን የሸወደ ብቻ ነው፡፡

ብዙዎቻችን የምንፈልገውን አናውቀውም፡፡ የምንሮጥለትን አንረዳውም፡፡ የተንገበገብንለትን ያን ያህል አናስተውለውም፡፡ የምንናፍቀውን ብናገኘው ልባችን በደስታ ተምነሽንሾ አያርፍም፡፡ የምንፈልገው ገንዘብ ወይም ስልጣን ሊሆን ይችላል፤ አልያም ዝና እና እውቅና ወይም ደግሞ ፍቅር ሊሆን ይችላል፡፡ ወይ ደግሞ ጥበብና ዕውቀት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዛ በኋላስ? ከማግኘታችን በኋላ ያለው ሕይወታችን ምን ይሆናል? የናፈቅነውን ስናገኝ ናፍቆታችን ይቆማል? የሮጥንለትን ስንደርስበት ሩጫችን ያበቃለታል? የቋመጥንለትን ገንዘብ ስናገኝ ተረጋግተን እንኖራለን? እውን ደስታን፣ እርካታን፣ መረጋጋትን፣ ማስተዋልን በእጃችን እናደርግ ይሆን ወይስ የሩጫ አዙሪቱ፣ የናፍቆት ድግምቱ፣ የድካም ሕይወቱ ይቀጥላል?

ትልቁ ጥያቄ የምንሮጥለትን እናውቀዋለን ወይ ነው? ቁምነገሩ ያለው የምንፈልገውን የእውነት እንፈልገዋለን ወይ የሚለው ላይ ነው፡፡ የእውነት እንፈልገዋለን ወይ የሚለው ጉዳይ ምን ማለት ነው የሚለው በደንብ ሊተነተን የሚገባው ነው፡፡ አብዛኞቻችን ማለት ይቻላል ፍላጎታችን ውጫዊ ነው፡፡ የውስጣችንን ርሃብ ትተን የውጩውን አምሮት ነው የምንሞላው፡፡ የልባችንን ምት ማዳመጥ አቁመን በዓለሙ ጫጫታ ተማርከናል፡፡ ከራሳችን ጋር መክረን የፈለግነውና የወደድነው የለም፡፡ በዚህም ምክንያት የምንሮጥለትን ስንደርሰበት አንረካበትም፡፡ ሌላ የማያልቅ ቅጥልጥል ሩጫ ይመጣብናል፡፡ የምንፈልገውን ብንጨብጠው እንኳን ውስጣዊ ደስታ የለንም፡፡ ደስታን ከውጪው ዓለም ለመሸመት ስለምንቋምጥ በገዛነው ነገር የመደሰት አቅም እናጣለን፡፡ ሰው ስላደረገው እናደርግና ደስታን ና ብንለው አይሰማንም፡፡ ወደፊት የምንጓዘው በአስተሳሰብ ወደኋላ ቀርተን ነው፡፡ አዕምሯችን ያለው ገና የጨለማው ዘመን ላይ ነው፡፡ የብርሃን ዓለም በውስጣችን አልበራም፡፡ ቦግ ያለ አስተሳሰብ ስለሌለን ጨለማ ወርሶናል፡፡ የውስጣችንን ሻማ ሳንለኩስ ነው መንገድ የጀመርነው፡፡ የሣሎኑ ሳይበራ የበረንዳው ቢበራ ያው በድንግዝግዙ መደናበር ነው፡፡ የውስጡ ብርሃን ለውጪው ዓለም ነፀብራቅ መሆኑን አለመረዳታችን ያመጣብን ጣጣ ብዙ ነው፡፡

አዎ ብዙዎቻችን በአዙሪት ውስጥ ነው ያለነው፡፡ የሕይወት አዙሪት አደንዝዞናል፡፡ ከተለመደው የሕይወት መንገድ ወጣ ብለን አዲስ መንገድ ለመስራት አንደፍርም፡፡ ደስታ፣ እርካታ፣ እርጋታ፣ ማስተዋል የሚባሉት የአዙሪት ጠላቶች ርቀውናል፡፡ በደመነፍስ እንሮጣለን፣ በስሜት እንወስናለን፣ በጥድፊያ እንኖራለን፤ ይሄንኑ አሰልቺ ሕይወት ዕለት ዕለት እየደጋገምን የመጨረሻዋ ቀናችን ስትመጣ በድካምና በበቃኝ እንሰናበታለን፡፡ ከራሳችን የአስተሳሰብ ባርነት ነፃ ሳንወጣ ሞት ያሸንፈናል፡፡ የምንፈልገውን ሳናውቅ፤ የምንሮጥለትን ሳንረዳ ፣ የነፍሳችንን ጥማት ሳናረካ፣ መንፈሳዊ ርሃባችንን ሳናስታግስ እንዲሁ የረባ ነገር ሳንሰራ እናልፋለን፡፡ አናሳዝንም????????

ዶክተር ቢያንካ ፊንከሊስቴን (Bianca Finkelstein) የተባሉ ምሁር ከእንደዚህ ዓይነቱ የሕይወት አዙሪት ለመውጣት ሶስት መላዎች አሉኝ ይላሉ፡፡ እነዚህም፡- አንደኛው አዙሪቱን ማቋረጥ (Interrupt the cycle)፣ ሁለተኛው ጠላቶቻችን መስታወቶቻችን መሆናቸውን መረዳት (Understand That Our Enemies Mirror Us)፣ ሶስተኛው ደግሞ የሚያሳምሙንን ያለፉ ታሪኮቻችን መተው (Leave Pain Stories In The Past) ናቸው፡፡

1. አዙሪቱን ማቋረጥ (Interrupt the cycle)

አዎ እስከምንነቃ ድረስ አዙሪቱ ራሱን ይደጋግማል፡፡ እሽክርክሪቱ እንዳይቀጥል ማቆም ግድ ይለናል፡፡ አዙሪቱ ደስታና ፍቅር ማሳጣት፣ የውስጣችን ርህራሄ ማሟጠጥ፣ ድካማችንን ማብዛት ነው ዋና ስራው፡፡ ሌላ ትርፍ የለውም፡፡ ካልነቃን እናልቃለን፡፡ የምንፈልገውና ካላወቅን እሽክርክሪቱን ማቆም አንችልም፡፡ ስለዚህ ፍላጎታችንን ማወቅ፣ የምንሮጥለትን ቀድመን መረዳት፣ ኑሯችንን መገምገም፤ ደስታችንን ከውስጣዊው ሕይወታችን ጋር ማያያዝ ስንጀምር የአዙሪት ገመዱን እንበጥሳለን፡፡ የእሽክርክሪት ሕይወቱን አቁርጠን ባዲስ የሕይወት መንገድ እንጓዛለን፡፡ ያም መንገድ ቀድመን የምንደርስበትን የምናውቅበትና ስንደርስበት ደግሞ የምንደሰትበት ይሆናል፡፡

2. ጠላቶቻችን መስታወቶቻችን መሆናቸውን መረዳት (Understand That Our
Enemies Mirror Us)

ብልህ ሰው የሚጠሉትን ሰዎች የሚጠቀምባቸው ነው፡፡ ከጠይዎቻችን ጥላቻቸውን ከልባቸው መፋቅ የሚያስችለን ሀይል ባይኖረንም ራሳችንን ለመመልከት መስታወታችን ልናደርጋቸው እንችላለን፡፡ ሶቅራጦስ ጨቅጫቃ ሚስቱን ያልፈታት ዓለሙን መመልከቻ መስታወት ስላደረጋት ነው፡፡ የጠላ ሰው ስለእኛ የሚናገረው በመሰለኝና በደሳለኝ ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ጊዜም እቅጭ እቅጩን ነው፡፡ እኛ ያላየነውን የጠሉን ሰዎች በጥራት ያዩታልና፡፡

3. የሚያሳምሙንን ያለፉ ታሪኮቻችን መተው (Leave Pain Stories In The Past)፡፡

‹‹መተው ነገሬን ከተተው›› እንዲል ብሒላችን የትናንትናውን መልካሙን እንጂ የሚያሳምመውን ታሪክ መውሰድ አይገባም፡፡ ባለፈው ሕይወት መብሰልሰል ለዛሬም ሆነ ለነገ ትርጉም አያመጣም፡፡ እሱን መደጋገም አዕምሮን እዛ ጊዜ ላይ መቸንከር ነው የሚሆነው፡፡ በትናንትናው ሕይወት ተገትሮ የሚቆም ሕይወቱ የቆመ ነው፡፡ ትናንት አልፏል፡፡ መልካሙን ትዝታ መድገም እንጂ ክፉዉን ማስታወስ አይገባም፡፡ ከከፋው ካለፈው ጊዜ መማር ያሻል፡፡ ከትናንት ራስን ማላቀቅ ግድ ይላል፡፡ የማይስማማን መተው ትልቁ መድሐኒት ነው!

ወዳጄ ሆይ... የምትሮጥለትን ቀድመህ እወቀው፡፡ የምትፈልገውን ነፍስህም እንደሚፈልገው አረጋግጥ፡፡ የምትፈልገውን ካገኘህ በኋላ ስለሚኖርህ ሕይወት ቀድመህ አስብ፡፡ ከትናንት ሕመምህ ራስህን አድን፡፡ የአዙሪት ሕይወትህን አቁርጠህ ባዲስ መንገድ አዲስ ሕይወት ጀምር፡፡ ፍላጎቶችህን በሙሉ ገምግማቸው፡፡ የዓለሙን ፍላጎት የራስህ ፍላጎት አታድርግ፡፡ የራስህን ፍላጎት ፈልግ፡፡ በውስጥህ ተሟጦ ሊያልቅ ያለውን ፍቅርና ርህራሄ መልሰህ ሙላው፡፡ ዘመንህን ፍጠር እንጂ በዘመኑ ቀሽም አስተሳሰብ አትወሰድ፡፡ አንተነትህን ፈልቅቀህ አግኝ! ሰውነትህን ካንተነትህ ባህር ጠልቀህ አውጣ፡፡

ቸር ጊዜ!
እሸቱ ብሩ ከገፁ ላይ እንደ ከተበው

Address

Addis Ababa

Telephone

+251993940329

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Techno View አዲስ ቴክኖ ቪው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Techno View አዲስ ቴክኖ ቪው:

Videos

Share