28/11/2025
ራሳቸውን ጫኚና አውራጅ ነን በማለት ተቋም ላይ ሁከት የፈጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
(የዎላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፤ ህዳር 19/2018ዓ.ም)
በዎላይታ ሶዶ ከተማ ዋዱ አምባ ቀበሌ ውስጥ ራሳቸውን ጫኚና አውራጅ ነን በማለት ተቋም ላይ ሁከት የፈጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የቀበሌው ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር ተገኝ ዎንጃሎ ገለፁ።
ፍፁም አየሌ፣ አማኑኤል በቀለ ፣ ታሪኩ ሞርጋ እና ጥላሁን ጮሌ የተባሉት እነኚ ግለሰቦች በቀን 19/03/2018 ዓ.ም ራሳቸውን ጫኚ እና አውራጅ ነን በማለት በዋዱ አምባ ቀበሌ ዋዱ ቀጠና 1 እንድሪያስ ያያ ሆቴል ሕንፃ ግቢ ወስጥ ሁከት ፈጥረዋል።
ግለሰቦቹ ተቋሙ ውስጥ በመግባት የቢሮ ዕቃ ለማውረድ 15,000 በመጠየቅ ሁከት መፍጠራቸውን ነበር ረ/ኢንስፔክተር ተገኝ ዎንጃሎ የተናገሩት።
በመሆኑም የተቋሙ የህግ ክፍል ለዋዱ ፖሊስ ባደረሰው ይድረሱልን ጥሪ መሠረት ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ውለው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገልጸዋል።
ኮማንደር ሀብታሙ አክለውም በተለያዩ አከባቢዎች ራሳቸውን ጫኚ እና አውራጅ ነን በማለት ህብረተሰቡን የሚያጭበረብሩ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!
MINOTETTAN NAAGOOS ASUMMATETTAN HAGGAAZOOS!