Ethio-Mereja

Ethio-Mereja One day. . .

ህወሓት የትግራይን ወጣቶች ለአል ቡርሃን ጦር ሽጧል !!ህወሓት ማለት የትግራይን ህዘብ ለሚፈልገው ዓላማና የፖለቲካ ትርፍ ከተጠቀመ በኋላ ዞር ብሎ የማያይ የትግራይ ህዘብ ታሪካዊ ጠላት ነው።...
04/04/2026

ህወሓት የትግራይን ወጣቶች ለአል ቡርሃን ጦር ሽጧል !!

ህወሓት ማለት የትግራይን ህዘብ ለሚፈልገው ዓላማና የፖለቲካ ትርፍ ከተጠቀመ በኋላ ዞር ብሎ የማያይ የትግራይ ህዘብ ታሪካዊ ጠላት ነው። የትግራይ ወጣቶችን ላለፉት ሃምሳ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ዓመታት የአፈሙዝ እራት በማድረግ የትግራይ እናቶች ካለልጅ እንዲቀሩ ፣ የትግራይ አባቶችንም ያለ ጧሪ ቀባሪ ያስቀረ የአረመኔዎች ስብስብ ነው ህወሓት። አሁንም ድመት መልኩሷ አመሏን አትረሳ ነውና ነገሩ ፣ ህወሓት በትግራይ እናት ልጆች የራሱን ከርስ እየሞላ ይገኛል ፤ ህወሓት የትግራይ ወጣቶችን በግዳጅ በማፈስ ለሱዳኑ አልቡርሃን ጦር በዶላር እየሸጠ እንደሚገኝ ታውቋል።

የትግራይ ወጣቶች ራሳቸውን ከህወሓት ለማስመለጥ ሲሉ ተሰደዋል ፣ በማያቁት ሃገር ሄደዋል ፤ ይሁን እንጂ ህወሓት ለትግራይ ህዝብ ወረርሽኝ በመሆን የትግራይን ወጣቶች በለጋ እድሜያቸው የበላ ስብሰበ ነው ፤ ይሄ አልበቃ ያለው ህወሓት የትግራይን ወጣቶች በመሸጥ ሆዱን እየሞላ ፣ ኪሱን እያደለበ ይገኛል።

" አንድ እግሬን ያጣውለትን ስልጣን በዮሀንስ ንጉሱ አማካኝነት ለህወሓት አሳልፌ አልሰጥም " ባዬ ቀናውጎንደር ውስጥ ለህወሓት ስስ ልብ ባላቸው እና ፀረ ህወሓት የሆነ አቋም ባላቸው ታጣቂዎች...
04/04/2026

" አንድ እግሬን ያጣውለትን ስልጣን በዮሀንስ ንጉሱ አማካኝነት ለህወሓት አሳልፌ አልሰጥም " ባዬ ቀናው

ጎንደር ውስጥ ለህወሓት ስስ ልብ ባላቸው እና ፀረ ህወሓት የሆነ አቋም ባላቸው ታጣቂዎች አማካኝነት የተፈጠረው የስልጣን ሽኩቻ እየተንከባለለ አሁን ላይ መሳሪያ ሊያማዝዝ የሚችል ደረጃ ላይ ደርሷል። ይህ መገፋፋት እየተንከባለለ አሁን ላይ ሊፈነዳ የቻለው ጎንደር አካባቢ የሚንቀሳቀሰውን ታጣቂ የህወሓት በጎንደር መኪል የሆነው ዮሀንስ ንጉሱ በጨረባ ምርጫ እንዲመራ በመመረጡ ምክንያት ነው። በዚህ የተበሳጨው ባዬ ቀናው ደግሞ የሀብቴ ወልዴ ምክትሉ እኔ ሁኞ ሳለ ስልጣኑን ለዮሀንስ ንጉሱ መሰጠጡ ህወሓት ውስጣችን ምን ያህል ሰርጎ እንደገባ የሚያሳይ ስለሆነ ይህን ደግሞ እኔ በፍፁም አልቀበልም ሲል ተናግሯል።

አያይዞም እኔ አንድ እግሬን ጭምር ያጣውለትን ስልጣን እንደ ዮሀንስ ንጉሱ ባሉ የህወሓት ወኪሎች አማካኝነት ለህወሓት አሳልፌ አልሰጥም በማለት እነሱ ላይ ቃታ ለመሳብ ዝግጅቱን እንደጨረሰ አሳውቋል። በቅርቡም ጎንደር ውስጥ እንደ ዮሀንስ ንጉሱ፣ሀብቴ ወልዴ፣ሳሙኤል ባለድል ባሉ የህወሓት በጎንደር ወኪሎች እና እንደ ባየ ቀናው፣ደረጀ በላይ፣ሰለሞን አጠናው ባለው ፀረ ህወሓት አቋም ባላቸው ታጣቂዎች አማካኝነት ሞቅ ያለ በተኩስ የታጀበ ደርቢ መጀመሩ አይቀሬ ነው።

" ዘመነ፣ሀብቴ እግሬን በሴራ አሳጡኝ አሁን ደግሞ ስልጣኔን በሴራ አያሳጡኝም " ባዬ ቀናውዘመነ ካሴ ሀብቴ ወልዴ የጎንደር ፋኖ መሪ ሁኖ ወደፊት እንዲመጣ በህወሓት በተሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ...
04/04/2026

" ዘመነ፣ሀብቴ እግሬን በሴራ አሳጡኝ አሁን ደግሞ ስልጣኔን በሴራ አያሳጡኝም " ባዬ ቀናው

ዘመነ ካሴ ሀብቴ ወልዴ የጎንደር ፋኖ መሪ ሁኖ ወደፊት እንዲመጣ በህወሓት በተሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ባዬ ቀናውን ከጨዋታ ውጭ ለማድረግ በሴራ እግሩን እንዲያጣ እንዳደረጉት የሚታወቅ ጉዳይ ነው።ይህን እድል በመጠቀምም ሀብቴ ወልዴ የጎንደር ፋኖ መሪ እንዲሆን ማድረግ ችለዋል።

ታዲያ አሁን ላይ ደግሞ ከዚህ በፊት እግሩን አስመትተው ከጨዋታ ውጭ ያደረጉትን ባዬ ቀናውን ከስልጣን ውጭም አድርገውታል።ይህ ሊሆን ቻለው ደግሞ በሀብቴ ወልዴ ቦታ ላይ ክፍተት ስለተፈጠረ እሱን ክፍተት መያዝ የነበረበት የሱ ምክትል የሆነው ባዬ ቀናው ሁኖ ሳለ የህወሓት ቅጥረኛ የሆነው ዮሀንስ ንጉሱ ቦታውን እንዲይዘው በመደረጉ ነው።

በዚህ የዘመነ፣የሀብቴ እና የህወሓት ሴራ በከፍተኛ ሁኔታ የተበሳጨው ባዬ ቀናውም ከዚህ በፊት እነዘመነ በሰሩብኝ ሴራ እግሬን አጣው አሁን ደግሞ ሴራ ሰርተው ስልጣኔን ለማሳጣት እየሄዱበት ያለውን መንገድ በፍፁም እንደማይቀበል አሳውቋል።

ያጣውትን እግሬን ማስመለስ ባልችል ስልጣኔን ግን አይኔ እያየ ለህወሓት በጎንደር መኪል ለሆነው ዮሀንስ ንጉሱ አሳልፌ አልሰጥም በማለት ባዬ ቀናው የህወሓት ወኪል በሆኑት ሀብቴ እና ዘመነ ላይ ነፍጥ እንዳነሳ ለማወቅ ተችሏል።

ፅንፈኛው ህወሓት ለተፈናቃይ ሲደረግ የቆየው ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲቆም ውሳኔ አስተላልፏል!በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች በአንድም በሌላ መንገድ የህወሓትን አ...
04/04/2026

ፅንፈኛው ህወሓት ለተፈናቃይ ሲደረግ የቆየው ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲቆም ውሳኔ አስተላልፏል!

በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች በአንድም በሌላ መንገድ የህወሓትን አረመኔነት ሲገልፁ ቆይተዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ የቡድኑን አመራሮች ባገኙ ጊዜ ሁሉ በኛ ስም አትነግዱ በማለት ተቃውሞ ሲያሰሙ እንደቆዩም ይታወቃል፡፡ በቅርቡም ምዕራብ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች ቡድኑ ከነሱ በሀይል መዋጮ የሚሰበስብበትን ሰነድ ለእርዳታ ሰጪዎች በማጋለጣቸው ከቡድኑ ጋር አንገት ለአንገት ተያይዘው ነው የሚገኙት፡፡

ተፈናቃዩ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ከህወሓት የሚደርስበትን በደል እየገለፀ ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ ፅንፈኛው ህወሓት በበኩሉ ማንኛዉም ተፈናቃይ የህክምና እርዳታ እንዳያገኝ ሲል አሳውቋል፡፡ እንደሚታወቀው ተፈናቃይ ከዚህ በፊት በአቅራቢያው በሚገኘው የጤና ተቋም ነፃ የህክምና እርዳታ ሲያገኝ ቆይቷል፡፡

ቢሆንም ሰሞኑን ህወሓት ተፈናቃይ ከዚህ በኋላ ከፍሎ ይታከም ሲል በተፈናቃይ ላይ የሞት አዋጅ አውጇል፡፡ የምዕራብ ትግራይ ተፈናቃዮች የህክምና አገልግሎት በጤና ጣቢያ ወይም በሆስፒታል ይሰጠን በማለት ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ ሆኖም ጨካኑ ህወሓት እንኳን ጤና ጣቢያ እና ሆስፒታል በአቅራቢያው ባለው የጤና ተቋማም ከኪሱ ክፍሎ ይታከም ሲል ተፈናቃዩን ለተጨማሪ ሞት የሚዳርግ ውሳኔ ወስኗል፡፡

"ታደሠ ወረደ እና የሕወሃት አክራሪዎች እስካሉ ድረስ ትግራይ ከቀውስ አትወጣም"ጌታቸው ረዳየቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳን...
10/02/2026

"ታደሠ ወረደ እና የሕወሃት አክራሪዎች እስካሉ ድረስ ትግራይ ከቀውስ አትወጣም"ጌታቸው ረዳ

የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ እና በዙሪያቸው ያሉ የሕወሃት አክራሪዎች እስካሉ ድረስ ትግራይ ከቀውስ አትወጣም በማለት አስጠነቀቁ።

ጌታቸው ፎርቹን ጋዜጣ ላይ ባወጡት ሃተታ፣ ጀኔራል ታደሠ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት በነበሩበት ወቅት ሕወሃት ውስጥ የሚገኙ አክራሪዎችን ሲያባብሉና ጊዜያዊ አስተዳደሩን በተደጋጋሚ ቀውስ ውስጥ ሲከቱ ነበር በማለት ወቅሠዋል።

ጌታቸው፣ ጀኔራል ታደሠ በእሳቸውና በአክራሪዎቹ መካከል አሸማጋይ መስለው በመቅረብ የፓርቲው ጥገኛ አድርገዋቸው እንደነበር በመጥቀስ፣ በኋላም ጀኔራሉ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት መኾናቸው በትግራይ ብዙ ጥፋት ማስከተሉን ገልጸዋል።

ጀኔራል ታደሠ የክልሉን ኢንቨስትመንትና መሬት ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ የተሠጣቸውን ሃላፊነት ራሳቸውንና በዙሪያቸው ያሉ አካላትን ለማበልጸግ ተጠቅመውበታል ያሉት ጌታቸው፣ ጀኔራል ታደሠን ለፈጸሙት ሴራ እና ጥፋት ሁሉ አለመቅጣታቸው ስህተት እንደነበርም አውስተዋል።

ኢትዮጵያ ዝግጅቷን ጨርሳ እንግዶቿን በጉጉት እየጠበቀች ነው!
10/02/2026

ኢትዮጵያ ዝግጅቷን ጨርሳ እንግዶቿን በጉጉት እየጠበቀች ነው!

ኢትዮጵያ ልትመርጥ ነው!አዎ ኢትዮጵያ ምርጫ ልታካሂድ ጥቂት ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል። ኢትዮጵያዊያን ለሃገሬንና ህዝቤን ይምራለኝ የሚሉትን ፓርቲ ይመርጣሉ።ምረጫ የትልቅ ሰው መንገድ ነው።ኢትዮ...
10/02/2026

ኢትዮጵያ ልትመርጥ ነው!

አዎ ኢትዮጵያ ምርጫ ልታካሂድ ጥቂት ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል። ኢትዮጵያዊያን ለሃገሬንና ህዝቤን ይምራለኝ የሚሉትን ፓርቲ ይመርጣሉ።

ምረጫ የትልቅ ሰው መንገድ ነው።
ኢትዮጵያዊያን በሃይል ሳይሆን በመርጫ ያምናሉ።

እኔም ዝግጁ ነኝ!

የተናበበ የህወሓት እና የሻዕቢያ መግለጫ!ከሰሞኑ የኢትዮጵያ መንግሥት ኤርትራ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ለቅቃ እንድትወጣት መግለጫ ያወጣ ሲሆን መግለጫውንም የሻዕቢያ መንግስት ማጣጣሉ ይታወቃ...
10/02/2026

የተናበበ የህወሓት እና የሻዕቢያ መግለጫ!

ከሰሞኑ የኢትዮጵያ መንግሥት ኤርትራ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ለቅቃ እንድትወጣት መግለጫ ያወጣ ሲሆን መግለጫውንም የሻዕቢያ መንግስት ማጣጣሉ ይታወቃል። በሰአታት ልዩነትም ህወሓት የፌደራል መንግሥትን የሚቃወም መግለጫ አውጥቷል። ይህ የሚያሳየው ሁለቱም ለጦርነት ዝግጁ መሆናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

መንግሥት ለህወሓት ተደጋጋሚ የውይይት መድረክ የከፈተ ሲሆን ህወሓት አልቀበልም በማለት ክልሉን በጦርነት እያመሰ ይገኛል። የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዳይከበር እንቅፋት ሲሆንም ቆይቷል። አሁን ደግሞ በቀጥታ ወደ ጦርነት ገብቷል። ታዲያ ኢትዮጵያ ለሰላም ያላትን ፍላጎት የሻዕቢያ መንግስት በውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ በኩል ደብዳቤ የላከች ሲሆን የሻዕቢያ መንግስት ሰላም እንደማይፈልግ በመግለጫው በትላንትናው እለት አስታውቋል። ህወሓትም ሻዕቢያ መግለጫ ካወጣ በሰአታት መግለጫ አውጥቷል። ይህም የሚያሳየው ሁለቱም በጋራ ለጦርነት መዘጋጀታቸውን ነው።

ኢትዮጵያ ሁሌም ቢሆን ሰላም ፈላጊ ሀገር ናት። ሻዕቢያ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ተዳፍራ እንኳን ኢትዮጵያ ለሰላም ካላት ቁርጠኝነት ሁሉንም በትዕግስት ስታልፍ ቆይታለች። እንዲሁም ለውስጥ ኃይሎች የጦር መሳሪያ ስትሰጥ በትዕግስት አልፋለች። ኢትዮጵያ በዚህ ሁሉ ውስጥ ሆና ሻዕቢያን ችግሮቻችንን በሰላማዊ መንገድ እንፍታ ብላለች። የሻዕቢያ መንግሥት ግን አሻፈረኝ በማለት ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል። ህወሓትም ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን በሰአታት ልዩነት በመግለጫው አሳውቋል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio-Mereja posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share