አጋልጥ - Expose

አጋልጥ - Expose Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አጋልጥ - Expose, Social Media Agency, Addis Abeba, Addis Ababa.

አጋልጥ - Expose is the first fact-checking page in Ethiopia. አጋልጥ - Expose works it's part to ensure the dissemination of factual information and to limit the influnce of fake news and scammers. አጋልጥ በኢትዮጲያ የመጀመሪያው የእውነታ ማጣሪያ የፌስቡክ ገጽ ነው። ሁሉም ኢትዮጲያዊ እውነተኛ መረጃ የማግኘት መብቱ እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን ጥረት በሚያደርጉ በጎ ፈቃደኞች የተመሰረተ ገጽ ነው። ዋና ዓላማው ኢትዮጲያ ላይ አተኩረው የሚሰሩ ዲጂታል ሜዲያወችን በተለይም በማህበራዊ ሜዲያ የሚወጡ ኢትዮጲያን የሚመለ

ከቱ መረጃወችን በመከታተል ሀሰትን ለይቶ የማጋለጥ፣ እውነትን የማጣራትና ለተደራሾቹ የማንቂያ መረጃ መስጠት ነው። በተጨማሪም ስለ ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት መንገዶች፣ አሉታዊ ተጽእኖው እና ጉዳቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ አገልግሎትም ይሰጣል።

Commercial Bank Of Ethiopia የሠጠው መግለጫ▼ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት በሙሉ=================ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. አዲስ ስታንዳርድ፣ አዲስ...
24/07/2025

Commercial Bank Of Ethiopia የሠጠው መግለጫ▼

ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት በሙሉ
=================
ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. አዲስ ስታንዳርድ፣ አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የተባሉና ሌሎችም የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች በባንካችን ላይ ተቃጥቶ ከነበረው ብር 7.735 ቢሊየን ገንዘብ ከባንኩ የውስጥ ሂሳቦች ያለሕጋዊ ምክንያትና ሥልጣን በባንካችን በሚገኙ 10 የሌሎች ግለሰቦች ሂሳብ በማዛወር ገንዘቡን ለማይገባው ሰው ጥቅም ወይም ለራሳቸው ለተጠርጣሪዎች ለማዋል የማመቻቸት ተግባርን ባንኩ ባለው ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ደርሶበት ምንም አይነት ገንዘብ ወጪ ሳይደረግ ገንዘቦቹን ከተላለፉባቸው ሂሳቦች ወደ ትክክለኛዎቹ የውስጥ ሂሳቦቹ ተመላሽ አድርጓል።

ባንካችንም ለሚመለከተው የሕግ አካል ወዲያውኑ የወንጀል ተግባሩን ጥቆማ በማቅረቡ ምርመራዎች ሲካሄዱና ማስረጃዎች ሲሰባሰቡ ቆይቶ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ ለራስ ወይም ለሌላ ሰው የማይገባ ጥቅም ለማግኘት አስቦ ስልጣንን አላግባብ የመገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል በዋና ወንጀል አድራጊነትና በልዩ ወንጀል ተሳታፊነት በፌደራል ዓቃቢ ሕግ የሙስና ወንጀል ዳይሬክቶሬት በኩል በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ የወንጀል ክስ ተመስርቷል።

በሌላ በኩል ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. “በኢትዮጵያ ንግድ ባንከ የውስጥ አካውንት ውስጥ ተቀምጦ የነበረ ከ7 ቢሊየን ብር በላይ መዘረፉ ተገለፀ” በማለት ባንካችን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደተዘረፈ፣ ዘራፊዎቹ እንዳልተያዙ እና ባንካችንም ጉዳዩን አድበስብሶ እንዳለፈው የሚገልጽ የሐሰት መረጃ መሰራጨቱን ተከትሎ ባንካችን ትክክለኛውን እውነታ በመግለፅ ግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. በይፋዊ የማህበራዊ ሚድያ ገፆቹ ባስተላለፈው መልዕክት:-

➢ ባንካችን ሙከራው በተደረገ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በጠንካራው የውስጥ ቁጥጥር ስርዓታችን አጠራጣሪ ግብይት መፈፀሙን ስለደረሰበት ምንም ዓይነት ገንዘብ ወጪ ሳይደረግ (ሳይመዘበር) ሙከራው ወዲያውኑ እንዲከሽፍ መደረጉን

➢ ሙከራው በጥቂት ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ባሰቡ ተጠርጣሪዎች የተፈፀመ እንጂ የባንካችንን ሲስተም ተላልፎ የተፈፀመ ጥቃት አለመሆኑን፣

➢ ባንካችን ሙከራ የተደረገበትን ገንዘብ ባለው ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት አማካኝነት ከጥቃት ከተከላከለ በኋላ ጉዳዩን ለሚመለከተው የሕግ አካል በማሳወቅ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉና የምርመራ ስራውም ተጠናክሮ እየተከናወነ የሚገኝ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በፖሊስ በኩል ተገቢው ምርመራ ተደርጎ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ በፌዴራል ዓቃቤ ህግ በኩል ክስ መመስረቱን ተከትሎም ገንዘቡ “በተጠርጣሪዎቹ ወጪ ተደርጎ እንደተወሰደ” በማስመሰል፤ “ባንካችን አጭበርብረውኛል ባላቸው ግለሰቦች ላይ ክስ እንደመሰረተ” እንዲሁም “ተመዘበረ የተባለው ገንዘብ ባንካችን ከፖሊስ ጋር በመተባበር ማሳገዱን” በመጥቀስ ሀሰተኛ መረጃዎች በጥቂት የማህበራዊ ሚድያዎች መሰራጨቱንና የዚህን መረጃ ትክክለኛነት ሳያጣሩ ሌሎች የተወሰኑ ሚዲያዎችም ይህንኑ ሀሰተኛ መረጃ ደግመው እያሰራጩ የሚገኙ እንዳሉም ተገንዝበናል።

ቀደም ብለንም እንዳሳወቅነው ባንካችን እንደማንኛውም የፋይናንስ ተቋም በተለይም እንደ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋምነቱ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት አስበው ለሚንቀሳቀሱ አካላት ኢላማ መሆኑ እሙን ቢሆንም እንዲህ አይነቱን ሕገ ወጥ ተግባር ለመከላከል የሚያስችል ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓትና የዘመነ ሲስተም ያለው ለመሆኑ ይህ የሙከራ ድርጊት መክሸፉና ተጠርጣሪዎች ላይም ምርመራ ተጣርቶ የወንጀል ክስ መመስረቱ አንዱ ማሳያ ነው፡፡

በመሆኑም የባንካችንን መልካም ስምና ዝና ለማጠልሸትና ሀሰተኛ መረጃ ለማሰራጨት ሆን ብለው የተዛባና ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት ላይ በአፋጣኝ ተገቢውን የእርምት ማስተባበያ ካልሰጡ ባንካችን ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን እያሳወቅን ክቡራን ደንበኞቻችንም ባንካችንን የሚመለከቱ መረጃዎችን ከታአማኒ የመረጃ ምንጮችና ከባንካችን ይፋዊ የመረጃ ምንጮች ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እያሳወቅን የመረጃዎችን ትክክለኛነታቸውን ሳያጣሩ ሀሰተኛ መረጃዎችን እንዳይቀበሉ በአክብሮት እንጠይቃለን።

  ቀድመን ለመከላከል የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት!!ሰሞኑን አንዳንድ ሰዎች ከማይታወቁ ግለሰቦች ስልክ ጥሪ እየደረሳቸው እንደሆነና ስልክ ቁጥሮቹም፣      Tel: +375602605281   ...
20/07/2025

ቀድመን ለመከላከል የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት!!

ሰሞኑን አንዳንድ ሰዎች ከማይታወቁ ግለሰቦች ስልክ ጥሪ እየደረሳቸው እንደሆነና ስልክ ቁጥሮቹም፣
Tel: +375602605281
Tel: +37127913091
Tel: +37178565072
Tel: +56322553736
Tel: +37052529259
Tel: +255901130460
ወይም ማንኛውም ቁጥር በ+371,+375,+381 የሚጀምሩ እንደሆነ ለመንግስት አካላት አሳውቀዋል።
እነዚህን ስልክ ቁጥሮች የሚጠቀሙት ግለሰቦች ሲደውሉ አንዴ ብቻ ከጠራ በኋላ ይዘጉታል።

እርስዎ መልሰው ሲደውሉ የርስዎን Contact List በ 3sec ውስጥ ወደ ራሳቸው ኮፒ በማድረግ እንዲሁም ሞባዬልዎ ላይ ስለ እርስዎ ባንክ ወይም ክሬዲት ካርድ መረጃ በአንዴ በመጥለፍ የማጭበርበር ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ከላይ በተጠቀሱት ስልክ ቁጥር ከተደወለሎት አይመልሱ ፡ወይም መልሰው አይደውሉ።እንዲሁም በማንኛውም ደዋይ #90 or #09 በመስመር እንዲነኩ ከተጠየቁ አይንኩ።

ምክንያቱም በቀላሉ ሲማችሁን አክሰስ በማድረግ በናንተ ስም የፈለጉት ወንጀል በመስራት እራሳቸውን ስለሚሸሽጉ ነው።

ይህንን መልዕክት ለቻላችሁ ሰው በማጋራት ህዝባችንን ከዚህ መሰል ማጭበርበሮች እንታደግ።

ደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

 #ፋይዳ ተጨማሪ የመረጃ ማስተካከያ ጣቢያዎች የመረጃ ስህተት ሲገጥም  እንዲሁም መረጃ መቀየር ቢያስፈልግዎ በአቅራቢያዎ የሚገኝ የመረጃ እድሳት አገልግሎት ሰጪ ጣቢያ መሄድ እንደሚችሉ ያውቃሉ...
16/07/2025

#ፋይዳ ተጨማሪ የመረጃ ማስተካከያ ጣቢያዎች

የመረጃ ስህተት ሲገጥም እንዲሁም መረጃ መቀየር ቢያስፈልግዎ በአቅራቢያዎ የሚገኝ የመረጃ እድሳት አገልግሎት ሰጪ ጣቢያ መሄድ እንደሚችሉ ያውቃሉ?

እነዚህን እና ተጨማሪ የምዝገባ ጣቢያዎች ለማግኘት id.gov.et/updatecenters ይመልከቱ። ነገር ግን በምዝገባ ቅጽ ላይ የሞሉት መረጃ በመዝጋቢ ባለሙያ በስህተት ከተመዘገበ መረጃዎን ለማስተካከል በአካል መሔድ ሳይጠበቅብዎ id.gov.et/update ላይ ወይም "Fayda ID" የሞባይል መተግበሪያን በመጠቀም በቤትዎ ሆነው የተሳሳተ መረጃዎን እንዲስተካከል መጠየቅ ይችላሉ።

"Fayda ID" ሞባይል መተግበሪያን: ከፕሌይ ስቶር
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.fayda.nidfaydaApp እንዲሁም ከአፕ ስቶር
https://apps.apple.com/app/fayda-id/id6740314990 ያገኙታል።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #መታወቅ #አካታች

በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ**********በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ ...
14/07/2025

በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ
**********

በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደመሰረተ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተገልጿል።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ2016/2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከተለያዩ የዘርፉ ተጠሪዎች ጋር እየገመገመ ባለበት መድረክ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሰረተባቸውገልጸዋል።

ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ሥርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ መግለፁን አንስተዋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።

በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ እና የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።

ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች እንደተያዙ ተገልጿል፡፡

ጉዳዩን ለማጣራትም ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።

በሀምራዊት ብርሀኑ

13/07/2025

እውነቱ የት ነው? ማንን እንመን😁😁😁

ፋክቱር (ማረጋገጫ) ያልጠየቅንባቸው ዜናዎች !1. ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚገኘውን የዳግማዊ ሚኒሊክ ሀውልት እንዲፈርስ አዛዋል። ( የሰበሩ ባለቤት አቶ መሳይ መኮንን ) 2. ...
10/07/2025

ፋክቱር (ማረጋገጫ) ያልጠየቅንባቸው ዜናዎች !

1. ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚገኘውን የዳግማዊ ሚኒሊክ ሀውልት እንዲፈርስ አዛዋል።

( የሰበሩ ባለቤት አቶ መሳይ መኮንን )

2. ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በ UAE እገዛ ወደ ጠፈር ሊመጥቁ ነው ።

( የዜናው ምንጭ : አቶ አልያስ መሰረት )

3. ፌዴራል መንግስት በመጪው ሐምሌ ከ ሀያ ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞችን ሊየባርር ነው ።

( የዜናው ምንጭ : አቶ ኤልያስ መሰረት )

4. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን የያዘ ሄሊኮፕተር ጎርጎራ አካባቢ በፋኖ ተመትቶ እንደጋየ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የሰበሩ ባለቤት : አቶ መሳይ መኮንን።

* * *
ወዳጆቹ ከየዋሆቹ ጋዜጠኞች ደረጄ ሀብተወልድ እና ስታሊን ገብረስላሴ ውጪ ያሉ የተቃዋሚ ጋዜጠኞች የዕብለት ዜናዎች ኮሜንት ሴክሽኑ ላይ ጣፉልኝማ።

አክባሪያችሁ መምሬ Samson Michailovich

የየትኛውን የአሀዝ ሪፖርት እንመን? በቃ ለሚወጡ የተዛቡ መረጃዎች ተጠያቂነት የለም አይደል? እስኪ ሕዝቡ የትኛውን አሀዝ አምኖ ይቀበል?
03/07/2025

የየትኛውን የአሀዝ ሪፖርት እንመን? በቃ ለሚወጡ የተዛቡ መረጃዎች ተጠያቂነት የለም አይደል? እስኪ ሕዝቡ የትኛውን አሀዝ አምኖ ይቀበል?

03/07/2025

ፌደራል ፖሊስ ከ80 በላይ ዲጂታል አጭበርባሪዎችን ይዣለሁ እያለ ነው

የንገድ እና ቀጠናዊ ሚናስትር አደጋ እንዳልደረሠባቸው የተዘገበው ነገር ስህተት ነው። ሚኒስትሩ አደጋው እንደደረሰባቸው የተረጋገጠ ሲሆን፤ ከሰባት (7) ግዜ/ቦታ በላይም የቀዶ ህክምና ተደርጎ...
28/06/2025

የንገድ እና ቀጠናዊ ሚናስትር አደጋ እንዳልደረሠባቸው የተዘገበው ነገር ስህተት ነው። ሚኒስትሩ አደጋው እንደደረሰባቸው የተረጋገጠ ሲሆን፤ ከሰባት (7) ግዜ/ቦታ በላይም የቀዶ ህክምና ተደርጎላቸው ህክምናቸውን በከፍተኛ ክትትል እያደረጉ ለመሆናቸው ታውቋል።

EBC የአማተሮችና የደካማ ጋዜጠኞች፣ ኤዲተሮች እንዲሁም የሚዲያ አመራሮች መሠባሠቢያ ማዕከል ነው። የአንድ አገር ብሄራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ በዚህ ልክ መዝቀጥ እና ንዝህላልነት፤ ተቋሙን በቁሙ ...
24/06/2025

EBC የአማተሮችና የደካማ ጋዜጠኞች፣ ኤዲተሮች እንዲሁም የሚዲያ አመራሮች መሠባሠቢያ ማዕከል ነው። የአንድ አገር ብሄራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ በዚህ ልክ መዝቀጥ እና ንዝህላልነት፤ ተቋሙን በቁሙ መሞቱን ከማሣየቱ በላይ መኖሩም የግብር ከፋዩን ገንዘብ ከማባከኑ በቀር ፋይዳ እንደሌለው ያስረዳል።

ትናንትና የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት ተናገረ ተብሎ የተለቀቀው ዜና ፍጹም ሃሰተኛ ዘገባ Fake news ነው። ጊኒ ቢሳዎ በቻይና መንግስት ትብብር የተሰራ ፈጣን መንገድ ተመርቋል ሁኖም ግን በፈጣ...
19/06/2025

ትናንትና የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት ተናገረ ተብሎ የተለቀቀው ዜና ፍጹም ሃሰተኛ ዘገባ Fake news ነው። ጊኒ ቢሳዎ በቻይና መንግስት ትብብር የተሰራ ፈጣን መንገድ ተመርቋል ሁኖም ግን በፈጣን መንገድ ምርቃቱ ወቅት ስለእስራኤል vs ኢራን ጦርነት የተናገሩት ንግግር የለም። አንድ ውሸታም website የፈጠረው ዜና ነው።

ፕሬዚዳንቱ ያደረገው ሙሉ ንግግር በፈረንሳይኛ ሰምቻለሁ፤ ቻይና መንግሥት ማመስገን እና ስለልማት አስፈላጊነት ከመናገር ያለፈ ስለጦርነት የተናገሩት ሃሳብ አልነበረም። የመረጃ ምንጮች ከፌስቡክ እና ከቲውተር ላይ እየወሰዳችሁ ዜና የምትሰሩ ልጆች ጥንቃቄ ብታደርጉ ይሻላል። ልክ እንደ እግር ኳስ ጨዋታ ግጥሚያ የእስራኤል እና ኢራን ጦርነት ዜና እየዘገበ ያለው ፋና እና ETV በጣም ያሳዝናል። በጎዶሎ መረጃ ፌስቡክ ላይ ጎራ ለይቶ የሚፋተገው ጥቁር የሃገሬ ህዝብ ያሳዝነኛል።

የተመረቀው መንገድ ለማየት ከስር ያለውን ፎቶ ይመልከቱ።

Ashagre Getachew

የገለቴ ቡርቃ የቀድሞ ባለቤት በፓሊስ ቁጥጥር ሥር አይደለም ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።ከትላንት ምሽት ጀምሮ “ የአትሌት ገለቴ ቡርቃ ባለቤት አቶ ታደለ ገብረመድህን በአዲስ አበባ ፓ...
11/06/2025

የገለቴ ቡርቃ የቀድሞ ባለቤት በፓሊስ ቁጥጥር ሥር አይደለም ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

ከትላንት ምሽት ጀምሮ “ የአትሌት ገለቴ ቡርቃ ባለቤት አቶ ታደለ ገብረመድህን በአዲስ አበባ ፓሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ ” የሚሉ መረጃዎች በማኀበራዊ ሚዲያው በሰፊው ተሰራጭተዋል።

የአትሌት ገለቴ ቡርቃ ባለቤት በፓሊስ ቁጥጥር ሥር ውሏል መባሉ እውነት ነው ? ሲል ቲክቫህ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ ብዙ ሰው ያወራል። የለምኮ ፤ ፓሊስ ጋ የለም። እኛ ጋ የለም ” የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

ግለሰቡ እንዳልተያዘና “ የሀሰት መረጃ ” እንደሆነ የገለጹት ኮማንደር ማርቆስ፣ “ አልተያዘም። በፓሊስ ቁጥጥር ሥር አይደለም ” ሲሉም ተናግረዋል።

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
NOTYET

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አጋልጥ - Expose posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አጋልጥ - Expose:

Share