Ethio Press

Ethio Press for more information and breaking news
(1)

የካራቴ ስፖርት በአማራ ክልል የበላይነት ተጠናቀቀ።  ሰኔ 16/2017 ዓ.ም (Ethio press) በ6ኛው የመላው ኢትዮጰያ ጨዋታዎች የአማራ ክልል በጅማ ከተማ በካራቴ ስፓርት ደምቋል። ሁለ...
23/06/2025

የካራቴ ስፖርት በአማራ ክልል የበላይነት ተጠናቀቀ።

ሰኔ 16/2017 ዓ.ም (Ethio press) በ6ኛው የመላው ኢትዮጰያ ጨዋታዎች የአማራ ክልል በጅማ ከተማ በካራቴ ስፓርት ደምቋል።

ሁለት አሰልጣኝ እና 16 ወንድና 10 ሴት የስፖርቱ ተፋላሚዎችን ይዞ ክልሉ ጅማ ከትሟል።

በአማራ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል መካከል የአጠቃላይ አሸናፊ ለመኾን የነበረው ፍጥጫ በመጨረሻም በአማራ ክልል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

ዛሬ አሸናፊውን የሚለዩ በሁለቱም ጾታ የቡድን ውድድሮች ተደርገዋል። በወንድ የቡድን ፋይት ውድድር ተጠበቂ የነበረ ነው። ሁለቱም ክልሎች አራት አራት የወርቅ እና ተጨማሪ ሜዳልያዎችን ይዘው ለፍጻሜው በቅተዋል።

ይሄንን የፍጻሜ ውድድር አማራ ክልል በብርቱ ልጆቹ በማሸነፍ የበላይ ኾኗል። በሴቶቹ የቡድን ፋይት የነሐስ ሜዳልያ አግኝተዋል። ውጤቱን ተከትሎም የካራቴ ስፖርት ውድድርን የአማራ ክልል አሸንፏል።

አማራ በ5 ወርቅ 4 ብር እና 5 ነሐስ ቀዳሚ ኾኗል። ኦሮሚያ 4 ወርቅ፣ 4 ብር እና 3 ነሐስ ሁለተኛ ሲኾን ድሬደዋ 2 ወርቅ፣ 2 ብር እና 8 ነሐስ በመሰብሰብ ሦስተኛ ኾነው አጠናቅቀዋል። አዲስ አበባ፣ ቤንሻንጉል፣ አፋር፣ ሲዳማ እና ጋምቤላ ከአራተኛ እስከ ስምንተኛ ደረጃ በማግኘት አጠናቅቀዋል።

23/06/2025
ኢራን በእስራኤል ላይ አዲስ የሚሳኤል ጥቃት ፈፀመች+++++++++++++++ኢራን በዛሬው ዕለት በእስራኤል ላይ አዲስ የሚሳኤል ጥቃት ፈፀመች።በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግጭት እየተባባሰ በ...
23/06/2025

ኢራን በእስራኤል ላይ አዲስ የሚሳኤል ጥቃት ፈፀመች
+++++++++++++++

ኢራን በዛሬው ዕለት በእስራኤል ላይ አዲስ የሚሳኤል ጥቃት ፈፀመች።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግጭት እየተባባሰ በመጣበት በዚህ ወቅት ኢራን አዲስ የሚሳኤል ማዕበል በእስራኤል ላይ መክፈቷን የእስራኤል ጦር አስታውቋል።

ወታደራዊ መግለጫው እንዳመለከተው፤ አዲሱ የሚሳኤል ጥቃት በማዕከላዊ እና በሰሜን እስራኤል አከባቢዎች ያነጣጠረ ነው።

የአየር መከላከያዎች የኢራን ሚሳኤሎችን ለማክሸፍ እየሰሩ መሆናቸውን ጦሩ ተናግሯል።

እስራኤል እና ኢራን ቴል አቪቭ ወታደራዊ እና የኒውክሌር መስሪያ ቤቶችን ጨምሮ በተለያዩ የኢራን ጣቢያዎች ላይ ድንገተኛ ጥቃት ከሰነዘረች በኋላ ቴህራን የአጸፋ ጥቃቶችን እንደምትፈፅም በተደጋጋሚ ስትገልፅ ቆይታለች።

የሁለቱ ሀገራት ጦርነት አሜሪካን አሳትፎ የቀጠለ ሲሆን፤ በኢራን የሚሳኤል ጥቃት ቢያንስ 25 ሰዎች መሞታቸውን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መቁሰላቸውን የእስራኤል ባለስልጣናት ገለፀዋል ሲል አናዶሉ ዘግቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢራን ውስጥ በእስራኤል ጥቃት ቢያንስ 430 ሰዎች ሲገደሉ ከሦስት ሺህ 500 በላይ የሚሆኑ ዜጎች መቁሰላቸውን የኢራን ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በክብረአብ በላቸው
+++++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ኢትዮጵያ #እስራኤል #ኢራን

በመዲናዋ በትራፊክ አደጋ የሦስት ዓመት ሕጻንን ጨምሮ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ(Ethio Press ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደ...
23/06/2025

በመዲናዋ በትራፊክ አደጋ የሦስት ዓመት ሕጻንን ጨምሮ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ

(Ethio Press ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም)

በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሦስት ዓመት ሕጻንን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ አደጋው በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 3 በተለምዶ አባሳሙኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው የተከሰተው፡፡

ከኃይሌ ጋርመንት ወደ ዩኒሳ አደባባይ ይጓዝ የነበረ የፐብሊክ ሰርቪስ አውቶቡስ ከከባድ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ መንገድ ስቶ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ መግባቱን አብራርተዋል፡፡

ይህን ተከትሎም አውቶቡሱ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ ከገባ በኋላ ከዩኒሳ አደባባይ ወደ ኃይሌ ጋርመንት ሲጓዝ ከነበረ ዶልፊን ተሽከርካሪ ጋር መጋጨቱን ነው የገለጹት፡፡

በዚህም በዶልፊኑ ውስጥ ከነበሩት ተሳፋሪዎች መካከል አሽከርካሪውን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተናግረዋል፡፡

ከሟቶቹ መካከል የ3 ዓመት ሕጻን እንደሚገኝ ጠቁመው÷ በአደጋው 8 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን አመልክተዋል፡(ኤፍ ቢ ሲ)

ኢትዮጵያ በመጪው መስከረም የጋዝ ምርቷን ለገበያ ታቀርባለች" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ይፋ ማድረጋቸውን የሩሲያው ስፑትኒክ ዘግቦ ተመልክተናል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ  ይህን የተናገሩት ...
23/06/2025

ኢትዮጵያ በመጪው መስከረም የጋዝ ምርቷን ለገበያ ታቀርባለች" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ይፋ ማድረጋቸውን የሩሲያው ስፑትኒክ ዘግቦ ተመልክተናል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ ከሚዲያ አመራሮች እና የኮሚኒኬሽን ባለሙያዎች ጋር በነበራቸው ውይይት ላይ ነው ያለው ዘገባው፣ "ሀገሪቱ የራሷን ጋዝ ለማምረት ጥረት ስታደርግ መቆየቷን ገልፀዋል" ብሏል።

ምርቱ ከሀገሪቱ የትኛው ክፍል እንደሚወጣ በግልፅ አለማሳወቃቸውን ስፑትኒክ ጨምሮ ገልጿል።

ኢንተርኔት ለመጠቀም ከሁለቱም የማን ነው አሪፍና ተመራጭ ለናንተ?
23/06/2025

ኢንተርኔት ለመጠቀም ከሁለቱም የማን ነው አሪፍና ተመራጭ ለናንተ?

23/06/2025

Iran 🇮🇷 Vs Israel 🇮🇱

ረሱል ﷺ ከሶሃቦቻቸው ጋር ቁጭ ብለው በዱኒያ ላይ በጣም ስለሚዎዷቸው ነገሮች እየተጨዋወቱ እያሉ ነብዩ ﷺ አቡበክርንረ.ዐ "ያ አቡበከር አንተ በዱኒያ ላይ በጣም የምትወደው ነገር ምንድነው?"...
29/05/2025

ረሱል ﷺ ከሶሃቦቻቸው ጋር ቁጭ ብለው በዱኒያ ላይ በጣም ስለሚዎዷቸው ነገሮች እየተጨዋወቱ እያሉ ነብዩ ﷺ አቡበክርንረ.ዐ "ያ አቡበከር አንተ በዱኒያ ላይ በጣም የምትወደው ነገር ምንድነው?" ብለው ጠየቁት።
አቡበክርም ረ.ዐ "3 ነገሮችን እወዳለሁ:-
1.ከአንቱን ጋር መቀመጥ፣
2.አንቱን ማየት፣
3.አንቱ ባዘዙዋቸው ነገሮች ላይ በሙሉ ገንዘቤን መለገስ" ብሎ መለሰ።
°
ዑመርን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያዑመር ?"
"በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ
1.በድብቅ እንኳን ቢሆን በመልካም ነገር ማዘዝ፣
2.በግልጽ እንኳን ቢሆን ከመጥፎ ነገር መከልከል፣
3 መራራ እንኳን ቢሆን እውነትን መናገር።" ብሎ መለሰ።
°
ዑስማንን ረ.ዐ ጠየቁት "አንተስ ያዑስማን?
በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:-
1.ሰዎችን ማብላት፣
2.ሰላምታን ማብዛት፣
3.ሰዎች በተኙ ጊዜ ሶላትን ማብዛት፣
°
አልይን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአልይ ?"
"በዱኒያ ላይ 3ነገሮችን እወዳለሁ:-
1.እንግዳን ማክበር፣
2.በሙቀት ወቅት ፆምን መፆም፣
3.ጠላቴን በሰይፍ መቅላት፣
°
አባ ዘርን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአባ ዘር?"
"በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ :-
1.እርሃብን እወዳለሁ፣
2.በሽታን እወዳለሁ፣
3.ሞትን እወዳለሁ፣
ነብዩም ﷺ "ያ አባ ዘር ለምን እነዚህን ወደድክ?"
አቡዘር መለሰ "ረሃብን ወደድኩት ቀልቤን ፈሪ ሊያደርግልኝ ዘንድ፣
በሽታን ወደድኩት ወንጀሌን ሊያቀልልኝ ዘንድ፣
ሞትን ወደድኩት ከጌታየ ጋር ሊያገናኜኝ ዘንድ።" ብሎ መለሰ።
°
ነብዩ ﷺ " እኔም በዱኒያ ላይ
3 ነገሮችን እወዳለሁ:-
1.ሽቶን እወዳለሁ፣
2.ሚስቶቼን እወዳለሁ፣
3.የአይኔ ማረፊያ ሶላቴን እወዳለሁ፣
በዚህ መካከል ድንገት ጅብሪል አ.ሰ.ወ ዱብ አለ ሰላምታ ካወረደ በኋላ እንዲህ አለ
"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በዱኒያ ላይ እኔም 3 ነገሮችን እወዳለሁ
ነብዩም ﷺ "ምንድናቸው ያ ጀብሪል?" ብለው ጠየቁት።
1.መልዕክትን ማድረስ፣
2. አማናን አደራን መጠበቅ፣
3.ሚስኪኖችን መውደድ፣
ጅብሪል አ.ሰ.ወ ተመልሶ ወደ ከሄደ በኋላ ረሱልና ﷺ ሱሃቦቻቸው ረዲየሏሁ አጅመኢን ከመቀመጫቸው ሳይነሱ
ተመልሶ መጣና አሁንም ሰላምታውን አቅርቦ:-
"አላህም ሱ.ወ. ሰላም ብሏችኋል ካለ በኋላ አላህም ሱ.ወ እንዲህ ብሏል:-
በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:-
1.አላህን አውሺ የሆነችን ምላስ፣
2.አላህን ፈሪ የሆነችን ቀልብ፣
3.መከራ የበዛበት ታጋሽ የሆነችን ጀሰድ።
አላህ ሱ.ወ ታጋሾች አድርጎ ነብዩና ﷺ ሱሃቦች ረ.ዐ.አ የወደዱትን ያስወድደን!
°
ይህን ጣፋጭ ሐዲስ በማንበባችሁ ከፍ ያለ አጅር ታገኛላችሁ -ኢንሻ አሏህ።
ሼር በማድረግ ለሌሎች ብታካፍሉ ግን እነሱ ባነበቡት ልክ ለናንተም ሀሰናት ይፃፍላችኋል!
ኢንሻ አሏህ!!
አላህ አንብበው ከመጠቀሙት ያድርገን!!!

29/05/2025
ጊዜያዊ አስተዳደሩ ማብራሪያ እፈልጋለሁ ብሏልበአዲስ አበባ በአፋር በከል ወደ ትግራይ ሸቀጥ የሚጭኑ መኪኖች ከ18/09/2017 ዓ.ም መከልከላቸው ታውቋል‼️የትግራይ ንግድና ላኪ ኤጀንሲ ማብራ...
29/05/2025

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ማብራሪያ እፈልጋለሁ ብሏል
በአዲስ አበባ በአፋር በከል ወደ ትግራይ ሸቀጥ የሚጭኑ መኪኖች ከ18/09/2017 ዓ.ም መከልከላቸው ታውቋል‼️
የትግራይ ንግድና ላኪ ኤጀንሲ ማብራሪያ እንዲሰጠው ለሚመለከተው የፌዴራል ተቋም ደብዳቤ ጽፏል።
ከሰሞኑ ሸቀጥ የጫኑ በርካታ መኪኖች ምሽት ላይ ከትግራይ ክልል ወደ ኤርትራ እየተጓጓዙ መሆኑን የሚታወስ ነው።

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share