አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network

አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network ለአገው ህዝብ ድምጽ ለመሆን የተቋቋመው የሚድያ ስለሆነ አድማጭ ተመልካቾቻችን ኮፒ ሼር ላይክ ኮሜንት በማድረግ ቤተሰብ እንድትሆኑ የአክብሮት ግብጀችን ነው ።

እነዚህ ሁለቱ ዘንደዎች የአገዉ ህዝብን አንድነት እየበተኑ ያሉ ናቸዉ የበአዲስ አበባ የሚኖር አገዉ የሚባል ደግሞ በእነዚህ አገዉን እንዲበትኑ በገንዘብ የተሸጡ የአማራ ታላላኪዎች እየተታለለ ...
01/09/2025

እነዚህ ሁለቱ ዘንደዎች የአገዉ ህዝብን አንድነት እየበተኑ ያሉ ናቸዉ የበአዲስ አበባ የሚኖር አገዉ የሚባል ደግሞ በእነዚህ አገዉን እንዲበትኑ በገንዘብ የተሸጡ የአማራ ታላላኪዎች እየተታለለ ነዉ።

አተክልት ዳኛዉ የሚባለዉ በአማራ ብልጽግና በአማራ ባለሃብቶች የተገዛዉ አገዉን የሚያጭበረብር ከአገዎች የዛሬ አመት ሻዳይን ለማክበረ በተሰበሰበዉና በአገዉ ምሁራን ስም በተሰበሰበዉ ብር ገንዘብ ሚስት አገባ። የዛሬ አመቱን የሻደይ ማክበረያ ገንዘብ ሲሰበስብ የነበረዉ በግሉ አካዉንት ነበር። ዉሸት ነዉ የሚል አገዉ ካለ ደግሞ በስሙ የተላከበትን ማስረጃ እናቀርባለን። በአገዉ ምሁራን ስም ከሰበሰበዉ ብር በተጨማሪ 2016 ነሐሴ ላይ በሻደይ ማክበር ስም ብር ሯገስሙ ሰብስቦ መስከረም ይሁን ጥቅምት ሚስት አገባ።

የአገዉ ህዝብ ግን እዉነቱን መረዳት አይፈልግም። አሁንም በአንታጉ አገዉኘ ፊልም ስም በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ብር ሰብስቦል። የአገዉ ምሁራን ማህበረ ዷአዲስ አበባ ፊልሙን ለማስመረክ ሀላፊነት ከወሰደ በሆላ ህዝቡ ይጠዉን ሃላፊነት ለጥቅመኛዉ ዘንድ አሳልፎ ሰጦ በአገዉ ህዝብ ላይ እየቀለደ ነዉ።

ዘንዶ ደግሞ በለመደዉ ስርቆና ማጭበርበር የአገዉ ምሁራን ማህበረን በግል ስም ገንዘቡን እየሰበሰበ የኪስ ማሞያ ተቆም ሆኖል። ይሄ ዘንዶ የአገዉ ህዝብን ሁለት ጊዜ ከመግደል መቆጠብ አለበት። ለዚህ ተጠያቂ ደግሞ የአገዉ ምሁራን ማህቀር አመራሮች ከፊት በመሆን ማስተባበር ሲገባቸዉ ከሆላ ተደብቆ ህዝብ ላይ ወንጀል እያስፈፀሙ ስለሆነ ተጠያቂ ናቸዉ።

ሁለተኛዉ ዘንዶ ዶ.ር ታምሬ አንዶለም ይባላል የአገዉ ምሁራን ማህበረን ከአተክልት ዳኛዉ ጋር በመሆን የሸጠና የግል ገንዘብ ማፈላለጊያ ያደረገ ያለ እንደፊቱ ጥቁረት በአገዉ ላይ ጥላቻ ያለዉ ሆዳምና ሲረኛ ሰዉ ነዉ።

ይሄ ሰዉየ ከአገዉ ምሁራን ማህበር ሰብሳቢነት እያመመኝ መልቀቅ እፈልጋለሁ ቢልም ሴራዉ ገንዘብ ጋር የተያያዘና አገዉን አማራ ማድረግ ስለሆነ በጉባአ የተመረጠ አመራሮች እያሉ ከአተክልት ጋር በመሆን በማህበሩ አስተባባሪነት በሻዳይና በአገዉ ፈረሰኞች ማህበረ በአዲስ አበባ ማክበር ሰም ገንዘብ እያሰባሰበ ነዉ። የአገዉ ምሁራን ማህበር የተቆቆመ ጊዜ 2600 በላይ አባላት የነበሩት የአገዉ ምሁራን ማህበረ አሁን ላይ 10 አባላት የሉትም።

ባለፈዉ ራስአምባ ሆቴል በተደረገዉ ጠቅላላ ጉባአ በዉስጥ መስመር የጠራቸዉ 50 እንኮ የማይሞሉ ነገር ግን የአገዉ ምሁራን ማህበር አባል ያልሆኑ ሰዎችን ጠርቶ ነዉ ያካሄደዉ። ዶ.ር ታምሬ አንዶለም የሚባለዉ ሌባ በአማራ ባለሀብቶችና መሪዎች ተገዝቶ የአገዉን አንድነት እየበተነ እና እዉነተኛ አገዎች እንዳይሰባሰቡ እየሰራ ነዉ። አብዛኛዉ አዲስ አበባ የሚኖር አገዉ ይሄን አልተረዳም።

አገዉ ምሁራን ማህበረን አመመኝ ብሎ የለቀቀዉ ዶ.ር ታምሬ ዛሬ ከጀርባዉ በመሆን በአገዉ ምሁራን ማህበር ስም ገንዘብ ከአተክልት ዳኛዉ ጋር በመሆን እየሰበሰቡ ወደ ኪሳቸዉ እየከተቱ ነዉ።

የአገዉ ምሁራን ማህበርን ይመራሉ የተባሉ በስም የተሰየሙ ምሰለኒዮች የት ጠፉ? ዶ.ር ታምሬ አንዶለምና አተክልት ዳኛዉ በግል አካዉንታቸዉ በምሁራን ማህበር ስም የአገዉ ፈረሰኞች ማህበረንና ሻዳይን እናከብራለን ብለዉ ገንዘብ ወደ ኪሳቸዉ ሲሰበስቡ ምን እየሰሩ ነዉ።

በየት ሀገር እና በየትኛዉ የህግ አሰራር ነዉ የሲቪክ ማህበራት የሚያዉቀዉ የአገዉ ምሁራን ስራ አስፈጻሚ እያለ አማካሪ ነን በሚል ዉሸት ከአገዉ ህዝብ ገንዘብ የሚዘርፉ ዋነኛ ተወናይ የሚሆኑት ።

አገዉ ምሁራን ማህበር አመራሮችና የአገዉ ህዝብ እንኮ በይጠይቃችሁ የአገዉ ህዝብን በዶ.ር ታምሬ አንዶለምና በአተክልት ዳኛዉ ገንዘብ ማፈላለጊያ በማድረጋችሁ ትጠየቃለችሁ። ታምሬና አተክልት የአገዉን አንድነት እየበተኑ በአገዉ ስም ደግሞ ያለ ምንም ዉክልና በግል አካዉንታቸዉ ገንዘብ እየሰበሰቡ መሆኑን ሁሉማ አገዉ ያዉቃል።

ወደፊትም ገመናቸዉን እናጋልጣለን። የአገዉ ምሁራን አመሪሮች በታምሬና በአተክልት የተመለመላችሁ ደግሞ ስሌጣናችሁን አሳልፋችሁ በመስጠት አገዉን እያወራዳችሁ መሆን ወደፊት ተጠያቄ ናችሁ።

የምሁር ሆዳም እና አንድንትን የሚበትን አካል ወደፊት በህግም ጭምር ይጠየቃል። በግል አካዉንት በአተክልት ዳኛዉ ስም በሻደይ እና በአገዉ ፈረሰኞች ማህበር ከበሬታ ስም ከግለሰቦች የገባዉንና ከዉጭ ሀገር የተላከዉን ገንዘብ ከባንክ ስቴትመን አሰርተን በእጃችን ይዘናል። የባንኩን ስቴትመንት በቅርቡ እንለጥፋለን።

አገዉ አገዉ ሆኖ አንድነት እንዳይኖረዉ ከአማራ ባለሃብቶችና መሪዎች ጋር በመሆን አተክልት ዳኛዉና ዶ.ር ታምሬ እየሰሩና በአገዉ ስም ገንዘብ እያሰባሰቡ ነዉ።

ተማሬ አንዶአለምና አተክልተ ዳኛዉ ገንዘብ ከመሰብሰብ በተጨማሪ የአገዉ ህዝብ በአገዉነት መሰብሰብን ለመበተን የሚሰሩትን ደባ ለማወቅ በሚያሳዝን መልኩ ለሁለት አመታት በአገዉ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለዉን ወንጀል አንዲት ቀን በፓርላማ ተወካይ ሆነዉና የመንግስትን ስልጣን ይዘዉ ያለወገዙትንና በአገዉነት የሚያፍሩቱን ስብስቦች አምጥተዉ የአገዉኛ ፊልም ምርቃቱን ሲያጨማልቁት ዋሉ።

በፊልሙ ፕሮግራም ላይ እንደፈለጉ ጉሮሮቸዉ እስኪሰነጠቅ ንግግር ሲያደርጉና ካባ ሲሸልሙ የነበሩት ለአገዉ ህዝብ ሞት ድምፅ ሆነዉ የማያዉቁ የአማራ ፖሊሲ አራማጆች ናቸዉ።

ታምሬ አንዶለምና አተክልት ዳኛዉ በሻዳይ ስም ከ1,200,000 በላይ ብር ከሰበሰቡ በሆላ ሻደይ በአዲስ አበባ ነሐሴ 25 አይከበረም ብለዉ ትናንት ባለቀ ሰአት ነገሩን። በሻደይ ስም የተሰበሰበዉ ብር እንደተለመደዉ ወደ ታምሬ አንዶአለምና አተክልት ዳኛዉ ኪስ ገቢ ሆኖል።

በአገዉ ስም ገንዘብ እየሰበሰቡ የአገዉ ህዝብን እየከፋፈሉና የአገዉን አንድነት እየበተኑ ያሉ ታምሬ አንዶለምና አተክልት ዳኛዉ መሆናቸዉን አገዉ ማወቅ አለበት። ሻደይን መንግስት አልከለከልም ዉሸት ነዉ። ሻዳይ ስም የተሰበሰበዉን ብር ተከፋፍለዉ ነዉ።

የዛሬ አመት አተክልት በሻዳይ ገንዘብ በግል አካዉንት ሰብስቦ ሚስቱን አገባበት። አሁን ደግሞ የሻዳይ ገንዘብ 1,200,000 ብር በመኮንን ተድላ የግል አካዉንት ገቢ ተደርጎ የተከፋፈሉት 1,000,000 ሚሊዮን ታምሬ አንዶለምና አተክልት ዳኛው ናቸዉ።

ዘንዶዎቹ በአማራ በለሃብትና በአማራ ብልጽግና ተገዝተዉ አገዉ እንዳይሰባሰብ እያደረጉ ነዉ። ለተመልካች ሁለቱ ዘንዶዎች የአገዉ ተቆርቆሪ ይመስላሉ። ግን የአገዉ ገደይ ናቸዉ።

አገዉ ምሁራን ማህበሩን ከስራ አስፈጻሚ ቀምተዉ የገንዘብ ምንጭ አደርገዉታል።

27/08/2025

በአማራ ክልል መንግስት የሚደገፈው ፅንፈኛ ፋኖ አገው ህዝብ ላይ ዘርን መሰረት ያደረገ ጥቃት እየፈጸመ ይገኛል ተባለ ፦

በአማራ ብልፅግና መንግስት አጀንዳ ተሰጥቶት በሀሳብ ፣ በኢኮኖሚ ተደግፎ ፣ የሚቀሰቅሰው ፅንፈኛው ፋኖ አገው ህዝብ ከምድረ ገጽ ለመጥፋት ሴራ እየሰራ ይገኛል ሲል አገው ሚድያ ኔትዎርክ ገለጻ ።

በአማራ መንግስት እና በአማራ ፖለቲካኞች ያልተዋጠላቸው የአገው ህዝብ የማንነት ጥያቄ ህገመንግስታዊ መብት ሁኖ ሰላ ህገመንግስታዊ መብትን በሀይል በመናድ የአገው ህዝብ የማንነት ጥያቄ እንዳይመለስ ፀረ ኢትዮጵያ ፀረ አገው ሃይል ፅንፈኛው ፋኖ በመሰማራት የማንነት ጥያቄ እና የእርስትነት ይገባኛል ጥያቄ እንዳይጠየቅ ተፈናቃይ እና ስደተኛ የማድረግ ሴራ እየተሰራ ይገኛል ብሏል አገው ሚድያ ኔትዎርክ ።

በአማራ ክልል መንግስት እና በአማራ ፖለቲካኞች በተሰጠው አጀንዳ መሰረት እንዲሁም የአዊ ዞን አሰተዳደር አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው ስራ አስፈጻሚነት የአገው ህዝብ መሬት የአማረ የማድረግ ሴራ በጃዊ፣ በአምባላና ሶሪት፣ በሁዲት ፣ በሁሉም ወረዳዎች በሚባል ደረጃ የመሬት ወረራ በአማራ ፋኖ እየተፈጸመ ይገኛል ።

ፅንፈኛው ፋኖ በክልሉ መንግስት በተሰጠው ፍቀድ መሰረት አዊ ዞን በአዮ/ ጓግሣ ወረዳ ጬሌ በሚባል የማሰልጣኛ ቦታ ተሰቶት እየሰለጠነ የሚገኝ ሃይል ስለሆነ ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ ሲገበው የአዊ ዞን አሰተዳደር እና የአዊ ዞን ፀጥታ ቢሮ ዝምታን በመምረጥ የአገው ህዝብ ስካይና መከራ እንዲባባስ ምክንያት ሁንዋል ሲል አገው ሚድያ ኔትዎርክ ወቅሰዋል ።

አገው ህዝብ እራሳችሁን ተደራጅታችሁ ጠብቁ የሚሉ አካላት የሚታሰሩበት ገዳይ እና አስገዳዮች ጀግና የሚበሉበት አገው ምድር ።

በአዲስ-አበባ ከ11 ሺህ በላይ ሰራዊት ይሰማራል‼️በአዲስ አበባ የከተማዋን “ሰላም እና ፀጥታ የሚጠብቁ ከ 11 ሺህ በላይ የሰላም ሠራዊት ይሰማራሉ" ተባለ።በቀጣይ የ 2018 ዓ.ም. የከተማ...
24/08/2025

በአዲስ-አበባ ከ11 ሺህ በላይ ሰራዊት ይሰማራል‼️

በአዲስ አበባ የከተማዋን “ሰላም እና ፀጥታ የሚጠብቁ ከ 11 ሺህ በላይ የሰላም ሠራዊት ይሰማራሉ" ተባለ።

በቀጣይ የ 2018 ዓ.ም. የከተማዋን ሰላም እና ጸጥታ የሚጠብቁ ከ 11 ሺህ በላይ የሰላም ሠራዊት እንደሚሰማሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።

የሰላም ሰራዊቶቹ ለ 15 ተከታታ ቀናት የሚቆይ “ንድፈ ሀሳባዊ” እና “ወታደራዊ” ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በአራት ኮርሶች የተዘጋጀ የሰላም ሠራዊት ሥልጠና ባለፈው ረቡዕ ነሐሴ 14/2017 ዓ.ም. አስጀምሯል።

በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ይከናወናል የተባለው ሥልጠና ላይ ከ 11 ሺህ በላይ አዲስ እጩ የሰላም ሠራዊት እንደሚሳተፉ ኢትዮኒቲዩብ ተገንዝቧል።

የሰላም ሰራዊቶቹ በንድፈ ሀሳብ ከሚሰጣቸው ትምሕርት ባለፈ “የመስክ ወታደራዊ ሥልጠና” እንደሚሰጣቸው የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ ከሆነ ለአባላቱ የሚሰጠው የንድፈ ሀሳብ ሥልጠና በከተማዋ ዓይነት እና ቅርጻቸውን እየለዋወጡ የሚከሰቱ ወንጀል እንቅስቃሴዎች ላይ ያተኮረ ነው።

የጸጥታ መዋቅሩንና ሕዝቡን ባጣመረ ጠንካራ ስምሪት ከተማዋ የሚገጥማትን “የጸረሰላም” እና “የጽንፍ ኃይሎች” እንቅስቃሴ መከላከል እንደተቻም ወ/ሮ ሊዲያ ተናግረዋል።
#አዲስአበባ #ዜና #ኢትዮጵያ

የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት ጥያቄ ፦የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት ጥያቄ መንግስት በአስቸኳይ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል ተባለ ።መንግስት ባለበት ሀገር አገው ህዝብ የብልፅግና መንግስት ትደግፋለህ...
22/08/2025

የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት ጥያቄ ፦

የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት ጥያቄ መንግስት በአስቸኳይ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል ተባለ ።

መንግስት ባለበት ሀገር አገው ህዝብ የብልፅግና መንግስት ትደግፋለህ ተብሎ በፅንፈኛ ፋኖ ሃይል እንዲሁም ቀን ቀን ብልፅግና ማታ ማታ ፋኖ በሆነው የዞኑ አመራር የሚደርሰው ግፍና በደል ተባብሶ መከተሉን በጃዊ ፣ በእሁዲት፣ በአምባላ ፣ በአዛና፣ የሚኖሩ ነዋሪዎች ለአገው ሚድያ ኔትዎርክ ገለፁ ።

መንግስት የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት ጥያቄ እና የህዝብ ጥያቄ ጠጭ ወርዶ ሊመልስልን ይገባል ይህ መይሆን ከሆነ በአገው ስም የሚበጄታው በጀት ለሀገር አፍራሽ ሃይል፣ ለገዳይ ቡድን ፣ የኢትዮጵያ ፀረ ሰላም ሃይሎች ፣ ለመስሪያ መግዣ እና ለስልጠና እየዋለ መሆኑ አደባባይ ሀቅ ነው ።

የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች በዝርዝር እንደሚከተለው ነው ፦

#የአገው ህዝብ የዘመናት ጥያቄዎች !!(ከ1986_2017 የተጠየቁ የህዝባችን ጥያቄዎች))!!
#እንጅባራ ኤርፖርት ይሠራልን።
#ከአዮ ጎግሳ ወደ ምዕራብ ጎጃም የተወሰዱ በርካታ ቀበሌዎች ይመለሱ
#እንጅባራ ከተማ የደረጀ እድገት
#አገውኛ ቋንቋ ስራ ይዋልልን
#እንጅባራ ከተማ ኮሪደር ልማት
#እንጅባራ ከተማ ስቴዲየም ግንባታ
#አገው ምድር የግብርና ኢንዱስትሪ
#እንጅባራ የባንክ ዲስትሪክት
#የአገው ጀግና የአገው ፈረሰኞች ማህበር ዩኔስኮ ይመዘገብልን
#እንጅባራን የሚመጥን የአገው ህዝብ አደባባይ!
#የአገው ህዝብ ባህል ማዕከል ሙዚየም፣
#የአገው ምድር ዘንገና ገብታ ለሃገር ፕሮጀክት
#አገው ምድር ሪፈራል ሆስፒታል፣
#የአገው ምድር አዳሪ ት/ት ቤት
#የአገው ሚዲያ ኮርፖሬሽን ስቱዲዮ
#አገው ምድር የመብራት ሰብስቴሽን ስራ ማስጀመር
#የአገው ምድር ኢንዱስተሪ መንደርና ሌሎች ጥያቄቻችን ይመለሱልን ።
#እንጅባራ አዳሪ ትምህርት ቤት
#የአገው ምድር የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች በጊዜና በጥራት ማለቅ አለባቸው ።!1ኛ ከከሳ_አገው ግምጃቤት_አዘነ_አምምበላ
2ኛ ከቻግኒ_ዚገም_አምበላ መንገድ
3ኛ ከቻግኒ_መንታውሃ_መተከል ዞን
4ኛ ከዳንግላ_ጃዊ _ፓዊ_መተከል
5ኛ ከቲሊሊ_ሰከላ መንገድ

ይህ ሁሉ የአገው ህዝብ መሰረተ ልማት መንግስት በየአመቱ በጄት ይመደባል መሰረተ ልማት ተፈጽሞ ለምርቃት የበቃውን ግን አላየንም አልሰማንም ።

የትርፍ ሰዓት ክፍያ ፦*******************የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ በክልሉ የሚገኙ ከተማ እና ወረዳ አስተዳደሮች ለጤና ባለሞያዎች የዲዩቲ ክፍያ በጀት እንዲይዙ መመሪያ ሰጠ። በአ...
22/08/2025

የትርፍ ሰዓት ክፍያ ፦
*******************
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ በክልሉ የሚገኙ ከተማ እና ወረዳ አስተዳደሮች ለጤና ባለሞያዎች የዲዩቲ ክፍያ በጀት እንዲይዙ መመሪያ ሰጠ።

በአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን ተፈርሞ በሁሉም በክልሉ ለሚገኙ ከተማ እና ወረዳ አስተዳደሮች የተላከው ሰርኩላር፣ በየደረጃው የሚገኙ አስተዳደሮች ለጤና ባለሞያዎች የትርፍ ሰአት ስራ (ዲዩቲ) ክፍያ በጀት እንዲይዙ መመሪያ ተሰጥቷል።
ደብዳቤው " የጤና ስራ በየትኛውም ሁኔታ የማይቋረጥ ስራ በመሆኑ ባለሙያዎች የዲዩቲ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞችን በተመለከተ በመንግስት ጤና ተቋማት ለሚያገለግሉ የጤና ሙያተኞች የዲዩቲ እና የኃላፊነት አበል ክፍያ መወሰኛ የአማራ ብሔራዊ ክልል መስተዳድር ም/ቤት መመሪያ ቁጥር 20/2006 ዓ.ም በማጽደቅ ላለፉት 12 ዓመታት ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል " ሲል ያብራራል።

ነገር ግን አንዳንድ ወረዳዎች እና ከተሞች በጀት ሲይዙ እንደ ግዴታ ወጭ አለመያዛቸው እና አቆራርጠው መክፈላቸው ቅሬታ እና የመልካም አስተዳደር ችግር ፈጥሯል ብሏል።

ይህንን ችግር በመግለጽም መፍትሄ እንዲሰጥበት በክልሉ ጤና ቢሮ በደብዳቤ መጠየቁን ሰርኩላሩ ጠቅሷል።

ጥያቄውን የተቀበለው የገንዘብ ቢሮም ሁሉም ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በበጀት ምደባ ወቅት የዲዩቲ በጀት የግዴታ ወጪ መሆኑን በመገንዘብ አስፈላጊውን የበጀት ምደባ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ከአማራ ክልል በተጨማሪ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተመሳሳይ መመሪያ አውጥተዋል።

አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) መላውን የአገው ህዝብ እንኳን ለ2017 ዓ/ም የሻደይ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ ይላል!!!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨አዎ እኛ የታላቁ የአገው ልጆች ...
22/08/2025

አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) መላውን የአገው ህዝብ እንኳን ለ2017 ዓ/ም የሻደይ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ ይላል!!!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አዎ እኛ የታላቁ የአገው ልጆች ተረትን ሳይሆን ታሪክን እየዘከርን፤ አገዋዊ ታሪክን በተጨባጭ ማስረጃ በማስደገፍ እያጣቀስን አገውነትን በአደባባይ ለማያውቁት እናሳውቅ፤ ለመጪው የአገው ትውልድ ደግሞ ዓለማዊውን (ሳይንሳዊውን) ታሪክ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊውን ትውፊትም የማውረስ ታሪካዊ ኃላፊነት አለብን፣

የሻደይ መነሻ ከአገው ማህበረሰብ ነው ስል በምክንያት ነው። እውነቱን ልንገራችሁ ተከተሉኝ የጥፋት ዘመን ያ "40 ሌሊት 40 ቀናት" በምድር ላይ፣ በምድር ውስጥና በሰማይ ኑሯቸውን ያደረጉ ሁሉ ፍጥረታት ህይወታቸውን ያጠፋ ያ የእርግምት ዘመን እነሆ ዛሬ 7,500 ዓመታት አስቆጥሯል፣

የማያልፍ የለምና በመጨረሻም የኖኅ መርከብ በአራራት ተራራ ላይ አረፈች፤ አራራት ተራራ በለምለም ሳር የተሟላ ውብ ነበር። የኖኅ መርከብ በአራራት ተራራ ላይ ማረፏን ደስታ ለማብሰር እርግቧ ለኖኅ ለምለም የዌራ ዝንጣፊ እንኳን አደረሰህ፤ እንኳን ደስ አለህ ብላ በደስታ አበረከተችው፣

የኖኅ ልጅ ካም እርግቧ ለአባቷ ኖኅ ለምለም የዌራ ዝንጣፊ ስትሰጥ በዓይኑ ስላዓየ መርከቧ በአራራት ተራራ ላይ የማረፏን ደስታ ለማብሰር ለአባቱ ኖኅ ካም እንኳን ደስ አለህ በማለት ለምለም የግራምጣ ዝንጣፊ ሰጠ፣

ለዚህ መታሰቢያነት የካም ወራሽ የሆኑት የአገው ልጃ ገረዶች ከዚያ ጊዜ ጀምረው በወገባቸው የግራምጣ ዝንጣፊ አስረው "ሻደይ" የሚል ስያሜ በመስጠት ማክበር ጀመሩ ማለት ነው፣

ከዚያ ጊዜ ጀምረው የአገው ልጃ ገረዶች ሻደይን የማንነት መገለጫ በዓል በማድረግ ሻደይን እያከበሩ ይገኛሉ። ሻደይ በአገው ልጃ ገረዶች በጉጉት የሚጠበቅ አገዋዊ በዓል ነው፣

ይህንን ከዘመን ዘመን እየተላለፈ ዛሬ ላይ የደረሰውን አገዋዊ የማንነት መገለጫ ሻደይ በዓል "ሰለሞናውያን" ለመዝረፍ ሲኳትኑ እኛ የአገው ልጆች እያየን ነው። እውነት ከዚህ በላይ ለእኛ አገዎች መጠቃት ምን ይኖር ይሆን? በእርግጥ መመኘት ይቻላል የራስ ማድረግ ግን አይቻልም። በዚህ ዙሪያ ወደ ፊት በሰፊው እመለስበታለሁ። አገዎች እንኳን አደረሳችሁ!!!፤ እንኳን አደረሰን!!

አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) መላውን የአገው ህዝብ እንኳን ዓመት የሻደይ በዓል አደረሰን!!፤ አደረሳችሁ ሲል በአገዋዊ ደስታና ኩራት እንደ አዳይ አበባ እየፈካ ነው፣ አገዋዊ የነፃነት ትግሉንም ከፀሀይ ብርሃን ፍጥነት በላይ እያምዘገዘገ ነው፣

ፍትህ ፓርቲ የትግል ዓላማ ያደረገው ከዘራፊዎች አገዋዊ የማንነት መገለጫ የሆኑትን በዓላት ላለማስዘረፍ በቁርጠኝነት ለመታገል የተቋቋመ አገዋዊ ፓርቲ መሆኑን ሁሉም የአገው ህዝብ እንዲያውቅ ያስገነዝባል።

በድጋሜ አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) መላውን የአገው ህዝብ እንኳን ለ2017 ዓ/ም የሻደይ በዓል አደረሰህ!!፤ አደረሳችሁ ለማለት ይወዳል።

፨፨፨፨፨፨፨።፨፨ መልካም ሻደይ በዓል!!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የታሪፍ መረጃ ‼️ከሀምሌ 1 ቀን 2017 እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የታሪፍ ዝርዝር እንደሚከተለው ለመረጃ አቅርበናል። እንደሚታወቀው ይህ የታ...
22/08/2025

የታሪፍ መረጃ ‼️
ከሀምሌ 1 ቀን 2017 እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የታሪፍ ዝርዝር እንደሚከተለው ለመረጃ አቅርበናል።

እንደሚታወቀው ይህ የታሪፍ ማሻሻያ የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበትን እንዳያባብስ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ደንበኞችን የመክፈል አቅም ያገናዘበና ድጎማ የሚያደርግ ሲሆን፤ ጫናውን ለመቀነስ ደግሞ በየሩብ ዓመቱ ተከፋፍሎ የሚተገበር መሆኑንም ይታወቃል፡፡ በዚህም ከ0 እስከ 200 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ የመኖሪያ ቤት ደንበኞች የድጎማው ተጠቃሚ ናቸው፡፡

✅ የመኖሪያ ቤት ታሪፍ

➡️ 0 - 50 ኪ.ዋ.ሰ. = 0.6764 ብር በ ኪ.ዋ.ሰ. (+0.0807 )
➡️ 51 - 100 ኪ.ዋ.ሰ. = 1.6708 ብር በ ኪ.ዋ.ሰ. (+0.1807)
➡️ 101 - 200 ኪ.ዋ.ሰ. = 2.9320 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.2614)
➡️ 201 - 300 ኪ.ዋ.ሰ. = 4.2983ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4596)
➡️ 301 - 400 ኪ.ዋ.ሰ. = 4.4898 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.458)
➡️ 401 - 500 ኪ.ዋ.ሰ. = 4.6169 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4424)
➡️ 500 ኪ.ዋ.ሰ. በላይ = 4.6627 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4364)

✅ ለንግድ እና ለአጠቃላይ አገልግሎት = 4.5324 (+0.4817)
✅ ለአነስተኛ ኢንዲስትሪ (380v) = 2.8224 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.2635)
✅ ለመካከለኛ ኢንዱስትሪ (15kv) = 2.2714 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.2208)

👉 የዲማንድ ቻርጅ ክፍያ ታሪፍ

➡️ ለአነስተኛ ኢንዲስትሪ = 404.4ብር በኪዋ (+36.88)
➡️ ለመካከለኛ ኢንዱስትሪ = 297.23 ብር በኪዋ (+27.1)

👉 የአገልግሎት ክፍያ የመኖሪያ ቤት

ለድህረ ክፍያ
✅ ከ0 - 50 ኪ.ዋ.ሰ. = 11.19 ብር (+0.24)
✅ ከ 50 ኪ.ዋ.ሰ. በላይ = 46.75 ብር (+0.95)

ለቅድመ ክፍያ
✅ ከ0 - 50 ኪ.ዋ.ሰ.= 4.36 ብር(+0.18)
✅ ከ 50 ኪ.ዋ.ሰ. በላይ = 16.28 ብር (+0.31)

👉 የንግድ አጠቃላይ
✅ ለድህረ ክፍያ = 59.94 ብር(+1.19)
✅ ለቅድመ ክፍያ = 20.94 ብር (+0.41)

👉 ለዝቅተኛ እና ከፍተኛ ኢንዱስትሪ = 59.94 ብር(+1.19) ነው።

ታጣቂዎች በተሳፋሪዎች ላይ ጥቃት‼️አሽከርካሪው በጥይት ተመቶ ህይወቱ ሲልፍ መኪናው ተገልብጧል‼️በኦሮሚያ ክልል በ 14/12/2017 ዓም ከገብረ ጉራቻ እና ፍቸ መሀከል አሊደሮ ተብሎ በሚጠራ...
21/08/2025

ታጣቂዎች በተሳፋሪዎች ላይ ጥቃት‼️
አሽከርካሪው በጥይት ተመቶ ህይወቱ ሲልፍ መኪናው ተገልብጧል‼️

በኦሮሚያ ክልል በ 14/12/2017 ዓም ከገብረ ጉራቻ እና ፍቸ መሀከል አሊደሮ ተብሎ በሚጠራው የመንገድ ክፍል ከአማራ ክልል ከምስራቅ ጎጃም ጉምዶትን ተነስቶ ህዝብ ጭኖ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ትራንስፖርት ግልጋሎት ሰጭ ታታ አውቶብስ በታጠቁ ዘራፊዎች ተኩስ ተከፍቶበት ሹፌሩ ተመቶ ህይወቱ ሲያልፍ መኪናው በመገልበጡ በተሳፋሪዎች ላይ ቀላል እና ከባድ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል።

የመንግስት የፀጥታ ሀይሎች እጀባ አድርገውላቸው ከገብረ ጉራቻ ቢወጡም መንገድ ላይ ያደፈጡ የታጠቁ ዘራፊወች የተሳፈሩበትን ባስ ለማስቆም ሲሞክሩ በማምለጡ 2 ቦታ ላይ ተኩስ ከፍተው ባሱ ቢያልፍም ከኋላ የነበረውን አውቶብስ ሹፌር በጥይት መተውት መኪናው ሲወድቅ እሱም ህይወቱ ማለፉን በስፍራው የነበሩ ሰዎች ተናግረዋል።

የሀገራችን የመጨረሻ ምሽግ የሆነውን የመከላከያ ተቋም ግንባታ የሁሉም ኢትዮጵያን የጋራ ተግባር ነው።አዊ ብሔ/አስ በ2017 ዓ.ም በነበረው ሁለተኛ ዙር የመከላከያ ምልመላ አጠቃላይ አፈፃፀም ...
21/08/2025

የሀገራችን የመጨረሻ ምሽግ የሆነውን የመከላከያ ተቋም ግንባታ የሁሉም ኢትዮጵያን የጋራ ተግባር ነው።

አዊ ብሔ/አስ በ2017 ዓ.ም በነበረው ሁለተኛ ዙር የመከላከያ ምልመላ አጠቃላይ አፈፃፀም ከክልሉ ካሉ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ጋር ተወዳድሮ 3ኛ ደረጃ ስለወጣ የምስክር ወረቀት ከታላቅ ምስጋና ጋር ተሰጦል።

በቀጣይም ህዝባችን ከጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ጎን በመቆም እና ወጣቱ ወደ ተቋም እንዲቀላቀልና አገራዊ ተልዕኮ እንዲወጣ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልፆል።

"ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም"

አገው ሚድያ ኔትወርክ የህዝብ ድምጽ

የአገው ፓርቲዎችን ጨምሮ 11 የፖለቲካ ፓርዎች አንድ ጥምር ሀገር አቀፍ ፓርቲ መሰረቱ!!በምርጫ ቦርድ የተመዘገቡ 11 የተለያዩ የፖለቲካ ፓርዎች አንድ ጥምር ሀገር አቀፍ ፓርቲ መስርተዋል፡፡...
20/08/2025

የአገው ፓርቲዎችን ጨምሮ 11 የፖለቲካ ፓርዎች አንድ ጥምር ሀገር አቀፍ ፓርቲ መሰረቱ!!

በምርጫ ቦርድ የተመዘገቡ 11 የተለያዩ የፖለቲካ ፓርዎች አንድ ጥምር ሀገር አቀፍ ፓርቲ መስርተዋል፡፡

ጥምር ፓርቲ የመሰረቱት አገው ለፍትሕና ዴሞክራሲ ፓርቲ ፣ አገው ብሔራዊ ሸንጎ፣ ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ አርጎባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ አፋር ነፃ አውጭ ግንባር ፓርቲ፣ ከጋሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የካፋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ እና የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ናቸው፡፡

ፓርቲዎቹ በዛሬው ዕለት የምስረታ ጉባዔን እያካሄዱ ነው።

ፓርቲዎቹ ለመጣመር የሚያስችላቸውን መስፈርት ለማሟላት እና አስቻይ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ባለፈው አንድ ዓመት ዝግጅቶች ሲያደርጉ ቆይተዋል።

የፓርቲዎቹ ጥምረት ለሀገር ሰላም፣ ዕድገትና ክብር የሚሰራ ፓርቲ ለመፍጠር ያስችላል ተብሏል።

በመስራች ጉባዔው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ÷ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ልዩነታቸውን በማጥበብ እርስ በርስ በመከባበር መርህ አንድ መሆናቸው የሚያስመሰግን ነው ብለዋል።

ጥምረታቸው የተስፋ፣ የሰላም፣ የዴሞክራሲ መጎልበት ምሳሌ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቦርዱ ተገቢውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድምጽ

ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ያልተዘጋ አማራጭ ነው አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ)- የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች****************ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ያልተዘጋ አማራጭ መሆኑን አገ...
20/08/2025

ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ያልተዘጋ አማራጭ ነው አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ)- የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች
****************

ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ያልተዘጋ አማራጭ
መሆኑን አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ም/ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ዘለቀ ወንድሜ ገለፁ ።

አቶ ዘለቀ ወንድሜ አገው ሚድያ ኔትዎርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ባለፉት አመታት የታዩት ጦርነቶች አውዳሚ እንደነበሩ ገልጸው፤ ዘላቂ የሆነ ሰላም በአፈ-ሙዝ እና በጉልበት መጥቶ አያውቅም ብለዋል፡፡

ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በየትኛውም ስሌት ብቸኛው ዴሞክራሲን የማስገኛ መንገድ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል፡፡

በሚደረጉ ግጭቶች ተጎጂ የሆነው እኛ ብቻ ሳንሆን መጪውም ትውልድ ነው ያሉት አቶ ዘለቀ ወንድሜ ታሪካችን የሰላማዊ ትግል ጥሪት ያላት ሀገር አንዳናስረክብ አድርጎናል ሲሉም አመላክተዋል፡፡

የተካረሩ እና ጽንፍ የሆኑ የፖለቲካ ፍላጎቶች እንዳሉ እገነዘባለው የሚሉት ም/ስብሳቢው አቶ ዘለቀ ወንድሜ፤ "በአፈ-ሙዝ የመጣ አሸናፊነት ጠባሳን ብቻ ጥሎ የሚያልፍ ነው" ብለዋል፡፡

የልዩነት ሃሳቦችንና ጉዳዮችን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍታት ብቸኛው አማራጭ ስለመሆኑም ነው ያነሱት፡፡

ሰላማዊ ትግል ሀገር ስለሚያድን መንግስት በዚህ ዙሪያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

አገው ለፍትህና ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ፍትህ) አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ እጩ ዶክተር ገድፋው አምሳል በበኩላቸው፤ ከሰላማዊ ትግል ውጪ የሚደረግ የፖለቲካ እንቅስቃሴ መጨረሻው አያምርም ብለዋል፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊ ትግልን በማበረታታት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሀገሪቱ እንዲመጣ እና መድብለ ፓርቲ እንዲጎለብት ማድረግ ይገባናል ሲልም አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) የፖለቲካ ዘርፍ ጉዳይ ኃለፊ እጩ ዶክተር ገደፋው አምሳል ለአገው ሚድያ ኔትዎርክ ገልፀዋል፡፡

"ሰላማዊ ትግሎችን አድርገናል ወይ? ሞክረናል ወይ? የሚለውን ጥያቄ መመለስ አለብን" የሚሉት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊው እጩ ዶክተር ገድፋው አምሳል ፤ የሰላም አማራጭ በመንግሥት በኩል ዝግ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡

መገዳደል ሀገርን ከማጥፋት አልታደገም፤ በመሆኑም ሰብአዊነት በተሞላ መልኩ ችግሮችን መነጋገር ይቻላል ነው ያሉት እጩ ዶክተር ገድፋው አምሳል ።

#አገው #ሚድያ #ኔትዎርክ #የህዝብ #ድምጽ

 #ሰበር  #መረጃ  #አገው  #ምድር ምናልባት ሰሚ  #መንግስት ካለ! አገዉ ምድር የዉነትም አደገኛ  #የፀጥታ  #ስጋት ላይ ትገኛለች!የአገዉ ብሄረተኛ ሀይል በስትራቲጂክ አላማዉ እና በህብ...
18/08/2025

#ሰበር #መረጃ #አገው #ምድር

ምናልባት ሰሚ #መንግስት ካለ!

አገዉ ምድር የዉነትም አደገኛ #የፀጥታ #ስጋት ላይ ትገኛለች!

የአገዉ ብሄረተኛ ሀይል በስትራቲጂክ አላማዉ እና በህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ህገመንግስታዊ ስርአቱ ሙሉ መተማመን ስላለዉ አሰላለፉ ከፌደራል መንግስቱ ጋራ መሆኑ እሙን ነዉ።

በዚህ መርህ መሰረት ሰሚ ካለ ዛሬም ለመንግስት መረጃ መሰጠት እና የድጋፍ ጥሪ ማሰተላለፍ እንፈልጋለን!

የፋኖን አገዉ ምድርን ልንመታ ነዉ የቅኔ መልዕክት ተንትነን ለህዝባችን የጥንቃቄ ጥሪ ካሰተላለፍን በኋላ በመላ አገዉ ምድር ስምሪት ሰጥተን አዲስ ነገር ካለ መረጃ እንዲሰጡን መልእክት ሰደን ነበረ!

የደረሰን መረጃ ያሰደነግጣል!

#ዚገም!

1.የፋኖ ሀይል በእሁዱት እና ሶሪት በከፍተኛ ደረጃ እየሰለጠነ! ተጨማሪ ሀይልም እያሰፈረ ይገኛል!
2. የፋኖ ሀይል ወደ መተከል ለመወርወር እንቅፋት ነዉ ብሎ ጠምዶ የያዘዉ የአገዉን ህዝብ በተለይም የዚገም ቀጠናን ነዉ። ከዚገምም አርጃ ቀበሌን በልዩ ትኩረት ይዘዉ ለመምታት ጥርሰ ነክሰዉ ቀን እየጠበቁ ነዉ!

3.የአዊ ዞን የወንበሩ የፋኖ አመራር አቶ ቴዎድሮሰ ደግሞ የአርጃ ህዝብ በገንዘብ አዋጦ የገዛዉ ብሬን ወደ ወረዳ ገቢ እንዲደረግ አዟል! የህዝቡን እጅ አስሮ የማሰመታት ሴራ!

4. #አርጃ ራሷን እንዳትከላከል ጀግኖች እንዲሰደዱ ትጥቅ አሰረክቡ የሚል መመሪያ ወርዶ አገር እየታመሰ ነዉ።የታሰሩ አሉ፣ መሳሪያ ላለማሰረከብ ብለዉ ከቀያቸዉ ሸሽተዉ የጠፉም አሉ። አርጃ የመከላከል ቁመናዋን እንድታጣ እየተሰራ ይገኛል። ለዚህ የዚገም ወረዳ አሰተዳዳሪ መልካሙ (ብር አምጣ) ተባባሪ ነዉ!

#አርጃ አደጋ ዉስጥ ናት!

#አገዉ ግምጃ ቤት!

በ አገዉ ግምጃ ቤት ከተማ አሰተዳደር የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ የሆነ በፋኖነት የሚጠረጠር አመራር ሁለት ወንድሞች/ የከተማ አሰተዳደሩ ሚሊሺያ የነበሩ ከነመሳሪያቸዉ ከድተዉ ፋኖን ተቀላቅለዋል!

የቡያ ጓጉሳ ፋኖን ተቀላቅለዉ አገዉ ግምጃ ቤትን #ለማሰወረር ዛቻ እያሰተላለፉ አገር እያመሱ ይገኛሉ! ወንድሞቹ ጫካ የገቡት ሰዉየ ዛሬም ፀጥታውን እየመራ ይገኛል! ትልቅ ስላቅ!

እብሪተኞቹን እነ ካሳን የጣለችዉ አገዉ ግምጃ ቤት አደጋ ላይ ናት!

#ጃዊ!

የሰነበተዉ የወረራ ዉጥረት እንደቀጠለ ነዉ። ወደ መተከል የማስፋፋት ፍላጎት ይታያል!

#እንጅባራ!

ለሁለት አመት በሰላም አስከባሪነት ያገለገሉ ጀግና ተዋጊዎች ተራ ሰበብ ተፈልጎ ወደ ደረቅ ጣቢያ ገብተዉ እንዲታሰሩ ተደርጓል! በዚህም ሰራዊቱ አኩርፏል! የመዋጋት ሞራሉ እንዲደክም የተሰራ የዉስጥ አደገኛ ሴራ መሆኑ ግልፅ ነዉ!

#ሲደመደም!

የአገዉ ምድር ደህንነቷ እዉነትም #ሰጋት ላይ ነዉ! አገዉ ምድር ሰትወድቅ ግን መተከልም አትተርፍም! ቀጠናዉ የባሰ ቀዉስ ይገጥመዋል! ለመንግስት በፍጥነት ነገሮችን መቆጣጠሩ ነዉ የሚመከረዉ!

በህዝባችን ላይ ከዉስጥ በባንዳዉ ቴዎድሮሰ፣ ከዉጭ በጫካዉ ፋኖ የተባበረ ጥቃት ተከፍቷል!

ከመንግስት ምን ይጠበቃል!
1.የፈዴራል መንግሰቱ በቀጥታ እጁን በማሰገባት የተበላሸዉን የዞን የአመራር ምደባ በፍጥነት ማሰተከካል። የዞኑ አመራር ከፋኖ ዘመምነት ነፃ በሆኑ እና ሀቅም ባላቸዉ መሪዎች መያዝ አለበት። ፍጥነት!.
2. ቀጠናዉ በጣም Senstive ሰለሆነ ልዩ ወታደራዊ ድጋፍ እና ስምሪት ሰለሚሻ የፌደራል መንግሰት ለቀጠናዉ ሰላም ልዩ ትኩረት ያድርግ!

#አገው #ምድር #የስጋት #ቀጣና

አገው ሚድያ ኔትዎርክ ህዝብ ድምጽ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share