26/10/2025
የአማራ ክልል መንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አባላት የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ላይ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ ክቡር ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በብልፅግና ፓርቲ አማራ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፤ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የፓለቲካ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር አቶ መለሰ አለሙን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አመራሮች ተገኝተዋል።
ብልጽግና ፓርቲ ከለውጡ ማግስት በሀገሪቱ የነበረውን የማይመች የዲሞክራሲ ሁኔታን በመቀየር ሰፊ የዲሞክራሲ ምህዳር እየፈጠረ ያለ ፓርቲ ሲሆን ባለፉት አመታትም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያስችልና የፖለቲካ ስርአቱን ለማዘመን ቁልፍ ሚና ያላቸው ልዩ ልዩ ተግባራትን እንደፓርቲና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የመሪነት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
ውይይቱ ጤናማ እና ውጤታማ የፖለቲካ ምህዳር እንዲኖር እና መሬት ላይ ያለው ነባራዊ ሁኔታን ምቹ በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል