አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network

አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network ለአገው ህዝብ ድምጽ ለመሆን የተቋቋመው የሚድያ ስለሆነ አድማጭ ተመልካቾቻችን ኮፒ ሼር ላይክ ኮሜንት በማድረግ ቤተሰብ እንድትሆኑ የአክብሮት ግብጀችን ነው ።

የአማራ ክልል መንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አባላት የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕ...
26/10/2025

የአማራ ክልል መንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አባላት የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ ክቡር ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በብልፅግና ፓርቲ አማራ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፤ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የፓለቲካ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር አቶ መለሰ አለሙን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ከለውጡ ማግስት በሀገሪቱ የነበረውን የማይመች የዲሞክራሲ ሁኔታን በመቀየር ሰፊ የዲሞክራሲ ምህዳር እየፈጠረ ያለ ፓርቲ ሲሆን ባለፉት አመታትም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያስችልና የፖለቲካ ስርአቱን ለማዘመን ቁልፍ ሚና ያላቸው ልዩ ልዩ ተግባራትን እንደፓርቲና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የመሪነት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።

ውይይቱ ጤናማ እና ውጤታማ የፖለቲካ ምህዳር እንዲኖር እና መሬት ላይ ያለው ነባራዊ ሁኔታን ምቹ በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል

የአማራ ክልል መንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አባላት የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕ...
26/10/2025

የአማራ ክልል መንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አባላት የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ ክቡር ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በብልፅግና ፓርቲ አማራ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፤ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የፓለቲካ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር አቶ መለሰ አለሙን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ከለውጡ ማግስት በሀገሪቱ የነበረውን የማይመች የዲሞክራሲ ሁኔታን በመቀየር ሰፊ የዲሞክራሲ ምህዳር እየፈጠረ ያለ ፓርቲ ሲሆን ባለፉት አመታትም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያስችልና የፖለቲካ ስርአቱን ለማዘመን ቁልፍ ሚና ያላቸው ልዩ ልዩ ተግባራትን እንደፓርቲና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የመሪነት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።

ውይይቱ ጤናማ እና ውጤታማ የፖለቲካ ምህዳር እንዲኖር እና መሬት ላይ ያለው ነባራዊ ሁኔታን ምቹ በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
•~•~•
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

https://t.co/GDwswRYC3chttps://t.co/AWdLoSfxHEhttps://t.co/gkYyAyoSWM

 #ሰበር  #ዜና ፨፨፨፨፨፨፨፨፨በምእራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ፅንፈኛ የፋኖ ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት የ22 ንፁሃን ህይወት አለፈ።ሰሞኑን በአማራ ክልል አንድ የፋኖ ታጣቂ በውጊያ መካከል ህይ...
20/10/2025

#ሰበር #ዜና
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በምእራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ፅንፈኛ የፋኖ ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት የ22 ንፁሃን ህይወት አለፈ።

ሰሞኑን በአማራ ክልል አንድ የፋኖ ታጣቂ በውጊያ መካከል ህይወቷ ማለፉን ተከትሎ የፅንፈኛ ታጣቂ ቡድኑ ደጋፊዎች ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት ያሌለውን የኦሮሞ ህዝብ ኢላማ ያደረገ ዘመቻ በማህበራዊ ሚዲያ ስስተጋቡ ነበር። በኦሮሞ ህዝብ ላይ ጥቃት እንዲፈፀምም ስያነሳሱ በስፋት ተስተውሏል።

ይህ ሆኖ ከጥቂት ቀናት በኋላ ትናንት ምሽት በምእራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ሀሎ ድንኪ በተባለች ቀበሌ ፅንፈኛ የፋኖ ታጣቂዎች በንፁሃን ላይ ከባድ ጥቃት አድርሰዋል።

ነዋሪዎች #አገው #ሚድያ #ኔትዎርክ በሰጡት አስተያየት፣ በጥቃቱ ሀገር ሰላም ብለው በቤታቸው የነበሩ ነዋሪዎች በታጣቂዎቹ ተወረው እልቂት ተፈፅሞባቸዋል።

22 ንፁሃን በአንድ ቀበሌ በአንድ ጀንበር በቤታቸው ህይወታቸውን አጥተዋል።

ህይወታቸውን ካጡት በተጨማሪ 3 ቆስለው በህክምና ተቋም እንደሚገኙ አስረድተዋል።

በፅንፈኛ ታጣቂዎቹ ታፍነው የተወሰዱም እንዳሉ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ህይወታቸው ያለፈ ንፁሃን አስክሬን ከየቦታው ተሰብስቦ ዛሬ ስርአተቀብራቸው እየተፈፀመ መሆኑን አንድ ነዋሪ ከስፍራው #ለአገው #ሚድያ #ኔትዎርክ ተናግሯል።

ፅንፈኛ ታጣቂዎቹ በከጎራባች ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ተደራጅተው እንደሚገኙ የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ቦታው ምእራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳን እና ደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳን እንደሚያዋስን ገልፀዋል።

20/10/2025

ሰበር ዜና
ከአዊ ዞን ጠብቁኝ ነገ ሙሉ መረጃ ለህዝባችን ይፋ አገው ሚድያ ኔትወርክ የድርገል!!

 #ሰበር  #ዜና ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በፓርቲው ዋናው ጽ/ቤት እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ የብልፅግና ...
19/10/2025

#ሰበር #ዜና

ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በፓርቲው ዋናው ጽ/ቤት እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የዘርፍ ኃላፊዎች፣ የሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ስለሆነም ፓርቲው በዚህ ውይይት በአገው አዊ ብሔረሰብ ዞን በገዢው መንግስት(ብልፅግና) አመራሮችና አስተዳደሮች በአገው ህዝብ እየተፈፀመ ያለውን የመልካም አስተዳደር ችግር ብሎም ግልፅ የፅንፈኛው ቡድን ቀኝ እጅ የሆኑ የዞን እና የየወረዳ ባንዳዎች ላይ እርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ካልሆነ ግን ብልፅግና ታጥቦ ጭቃ መሆኑን በግልፅ ያሳያል።

#አገው #ሚድያ #ኔትዎርክ #የህዝብ #ድምጽ #ነው

 :-ከአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትሕ) የተሰጠ መግለጫ፣የአገው ህዝብ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ከሌሎች የኢትዮጳያ ብሔሮች፣ ብሔሮችና ህዝቦች ጋር በመሆን ውድ ህይ...
18/10/2025

:-

ከአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትሕ) የተሰጠ መግለጫ፣

የአገው ህዝብ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ከሌሎች የኢትዮጳያ ብሔሮች፣ ብሔሮችና ህዝቦች ጋር በመሆን ውድ ህይወቱን ሳይሳሳ በመገበር ትናንትም፣ ዛሬም እና ነገም የአንበሳውን ድርሻ የተወጣ፤ እየተወጣ ያለ እና የሚወጣ መሆኑን ሁሉም የሚያውቁት እውነታ ቢሆንም በማንነት ግንባታ ላይ ህገ-መንግስቱ የስጠውን መብት እንዳይጠቀም በክልሉ መንግስት በኢ-መደበኛ አሠራር እና ፀረ-አገው በመሆን በተዘረጋው መንግስታዊ መዋቅርበተፈጠረው ችግር ምክንያት ህዝባችን አሁን ላይ የመኖርና ያለመኖር ህልውናው በከፍተኛ

ህዝባችን ከሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ራሱን የአማራ ፋኖ ብሎ በሚጠራው ኢ-መደበኛ ኃይል ለ2 ዓመታት ዙሪያውን ተከቦ ከፍተኛ ጭፍጨፋ፣ ዝርፊያ፣ ንብረት ውድመት እና እንደ ህዝብ የህልውና አዳጋው ተጋርጦበት ይገኛል፡፡ ይህ ኢ-መደበኛ አሸባሪ ኃይል አይጥን ከማገርአገውን ከምድር አጠፋለሁ የሚል መሪ ቃል አንግቦ በአገው ህዝብ ላይ ጦርነት ማወጁ የአደባባይ ምስጢር መሆኑን ከተገነዘብን የቆየን ቢሆንም ህዝባችን ተፈጥሯዊ መብቱን በመጠቀም ከአሸባሪው ኃይል ራሱን መከላከል እና መመከት እንዲችል ጠንካራ አደረጃጀት ለመፍጠር እንቅስቃሴ በሚያደርግበት ጊዜም አዊ ዞንን አዞን እስከ ከተማ አስተዳደሮችና ወረዳዎች እንዲመሩ የክልሉ መንግስት በሚያስቀመጣቸው አሻንጉሊቶች ስውር ኔትዎርኪንግ እና በረቀቀ ሴራ ጠንካራ የህዝብ ልጆች በጽንፈኛው ሀዕቡ አደረጃጀት እንዲገደሉ ተደርገዋል! እየተደገደሎም ይገኛሉ፡፡

ድርጅታችን የአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) በአገው ህዝብ ላይየታወጀውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በተለያዩ ጊዜያት ለሚመለከታቸው የመንግት አካላትና ለዓለም አቀፍ ተቋማት በተደጋጋሚ ያላወቀ ቢሆንም በህዝባችን ላይ በአሸባሪው ኃይል የታወጀው የህልውና ማጥፊያ ዘመቻ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጠናክሮ እና ተባብሶ በመቀጠሉ እጅግ ያዝናል።

ይህ አሸባሪና ጽንፈኛ ኃይል ም ወረዳዎች ማንነትን መሠረት ላይ በአዊ ዞን በሁሉም በማድረግ በተደራጀ መልኩ ባወጀው ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ህይወት ጠፍቷል እየጠፋም ይገኛል፤ ከፍተኛ ሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል እየተፈፀመም ይገኛል፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠር የህዝብ ንብረት ተዘርፏል እየተዘረፈም ይገኛል፤ከተሞችን አውድሟል እያወደመም ይገኛል፣ የህዝብ መገልገያ የሆኑ የመንግስት ተቋማትን አውድሟል እያወደመም ይገኛል፡፡ ይህ ሁሉ በህዝባችና ላይ ማንነትን መሠረት በማድረግ እየተፈፀመ ያለው ወንጀል የዘር ማፅዳት ወንጀል በመሆኑ ድርጅታችን ፍትህ አጥብቆ ይቃወማል።

በቅርብ ጊዜ ማለትም ጥቅምት 05 እና 06 ቀን 2018 ዓ/ም በፋግታ ለኮማ ወረዳ በአዲስ ቅዳም ከተማና ዙሪያ ነዋሪ የሆኑ ሠለማዊ የአገው ተወላጆች እና ሠላም ማስፈን (ህግ ማስከበር) ላይበነበሩ ፖሊሶችና ሚኒሻዎች ላይ ማንነትን መሠረት በማድረግ በአሸባሪው ፋኖ ጭፍጨፋ የተፈፀመ ሲሆን ይህንን በሰው ላጆች ላይ የተፈፀመውን ጭፍጨፋ የፌዴራል መንግስትና ሌሎች የሚመለከታቸሁ ተቋማት በጋራ በመተባበር ገለልተኛ አካላትን በማቋቋም እንዲያጣሩልንና ለሟች ቤተሰቦች ተመጣጠሳኝ ካሳ እንዲከፈላቸው የአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) በጥብቅ ይጠይቃል፡፡ በዚህ ልክ አሻባሪው ፋኖ በአገው ህዝብ ላይችግር እንዲፈጥር ያደረጉ ዋነኛ ምክንያቶች

1. አዊ ዞንን የሚመሩ የዞን አመራሮች 'የከተማ አስተዳደር አመራሮችና የወረዳ አመራሮች ህዝባቸውን አስተባብረውና አደራጅተው አሸባሪውን ኃይል መመከትና ዞኑን መጠበቅ ሲገባቸው መንግስትና ህዝብ የሰጣቸውን ስልጣን ያለ አግባብ በመጠቀም በሙስና፣ በኔትዎርኪንግ፤ በሌብነትና በብልሹ አሠራር የተዘፈቁ በመሆናቸውና ከዚህ ፀረ-ህዝብ ተግባር ራሳቸውን ለመታደግ ሲሉ ከአሽባሪ ኃይል ጋር ኢ-መደበኛ እና መዋቅራዊ ባልሆነ መንግድ ግንኙነት በመፍጠር መረጃ በማቃበልና በመቀበል ህዝባችንን በፅንፈኘውና በወንበዴው ኃይል እንዲጠቃ ምቹ ሁኔታዎች ኢንዲፈጠሩ ማድረጋቸው

2. ለፌዴራል መንግስት በተለያዩ ጊዜያት በአካል በመሄድ፣ በአገው ህዝብ ላይ የደረሰውን ወንጀል የሚገልፅ ሠነድ በመስጠትና በየመድራኮቻችን በአዊ ዞን የዞን አመራሮችን ፣የከተማ አስተዳደር አመራሮችንና የወረዳ አመራሮችን በተመለከተ አስፈላጊ ምርመራ፣ ግምገማ እና ተጠያቂነት እንዲኖር ያመለከትንና የጠየቅን ቢሆንም ለህዝባዊ ጥያቄና ጉዳይ ትኩረት ባለመስጠቱ እና ህዝባችንም በመንግስት ላይ ከፍተኛ ተስፋ በማድረግ የአመራሮቹ ችግር እንዲፈታለት የፌዴራል መንግስትን ውሳኔ በትዕግስት ቢጠብቅም ሊደርስለት ያለመቻሉ፣

3. ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር በሌሎች የኢትዮጵያ ሀገሪቱ ክፍሎች በመዟዟር ህዝቡን ሲያወያዩና ህዝቡ የሚያነሳቸውን የመብት ጥሰቶችንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ሲያደረጉ እያየን ቢሆንም ወደ አማራ ክልል በማቅናት ወደ ተለያዩ የአማራ ዞኖችም እንደሚሄዱ ብናውቅም ህልውናው በፈተና ውስጥ የወደቀውን የጎጃም (የአዊ) አገው ህዝብ እንደ ህዝብ አክብረውና ቀርበው እንዲያወያዩ በጠቅላይ ሚኒስቴርጽ/ቤት በተደጋጋሚ በተሳተፍነበት ጊዜ እሳቸው በሚመሩት መድረክ ሃደው እንዲያወያው ጥያቄ ብናቀርብም የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሚስጡት በተሳሳተ መረጃ እና እነሱን ላለማስቀየም ሲሉ ወደ አዊ ዞን ሃደው ህዝባችንን ያለማወያየታቸው ሌላኛው የህዝባችንን ተስፋ ያጨለመ መሆኑ፣

4. አንዳንድ የአገው ተወላጆች በማወቅም ይሁን በጥቅም በመደለል የአገው ህዝብ ተደራጅቶ ማንነትን መሠረት በማድረግ ከመጣው ፀረ-አገው ኃይል ራሱን እንዳይከላከል የአገው ታጋዮች ላይ የጠላትን አጀንዳ በማስተጋባት የውሸት ስም ማጥፋትና ታርጋ መለጠፍ እንዲሁም ያልተጋቡ መረጃዎችን በመንዛት ህዝባችን አንድነት እንዳይኖረው ማድረግ ላይ የተጠመዱትን ህዝባችን የሚያውቃቸው ቢሆንም እነዚህን አካላት እንዲያርፉ አለመደረጉ አሁን በህዝባችን ላይ እየደረሰ ላለው ሌላኛው ችግር መሆኑ ናቸው፡፡

በመጨረሻ የአገው ህዝብን ማህበራዊ እረፍት በማንሳት እና ጨፍላቂና ፀረ-አገው የሆኑ ዓላማዎችን ለመተግበር ሲል አሸባሪው ኃይል በተለይም ሰሞኑን በፋግታ ለኮማ ወረዳ በአዲስ ቅዳም ከተማና ዙሪያ ከ30 በላይ የሚሆኑ አገዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ ከመጨፍጨፉ በተጨማሪ አሁን ላይ በአዊ ዞን ሁሉንም ወረዳዎች ዙሪያውን ከቦ ህዝባችን ላይ ከፍተኛ ሽብር እየፈፀመ ስለሚገኝ የፌዴራል መንግስት እና የፌዴራል ፀጥታ አካላት ጊዜ ሳይሰጡ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ወደ እዊ ዞን በመላክ ህዝባችንን እንዲታደጉልን የአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) ጥሪውን ያቀርባል፡፡

አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲፓርቲ (ፍትህ)

ጥቅምት 08 ቀን 2018 ዓ/ም

አዲስ አበባ፤ኢትዮጵያ

ከአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) ማንነትን መሠረት በማድረግ በአሸባሪው ፋኖ በአገው ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ጭፍጨፋ በመቃወም የወጣ መግለጫ፦አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድም...
18/10/2025

ከአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) ማንነትን መሠረት በማድረግ በአሸባሪው ፋኖ በአገው ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ጭፍጨፋ በመቃወም የወጣ መግለጫ፦

አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድምጽ

‎ ‎     ‎በአገዉ ምድር/ደቡባዊ አገዉ (አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር) ፋግታ ለኮማና በሌሎች ወረዳዎች አሸባሪ ፋኖ ጄኖሳይድ እየፈፀመ ነው።‎‎አገዉ ምድር ፀጥታ አካላት  እና ህዝባችን የዞን...
17/10/2025



‎በአገዉ ምድር/ደቡባዊ አገዉ (አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር) ፋግታ ለኮማና በሌሎች ወረዳዎች አሸባሪ ፋኖ ጄኖሳይድ እየፈፀመ ነው።

‎አገዉ ምድር ፀጥታ አካላት እና ህዝባችን የዞን፣ክልልና ፌዴራል መንግስት ትኩረት ተነፍጓል አለ ምክንያት አጉል መስዋዕትነት እየከፈለ ይገኛል።

‎የጎጃም ፋኖ ያለ የሌለ ሃይሉንና ዘመናዊ መሳሪያውን ሰብስቦ አገዉ ምድር ፊቱን አዙሯል የፅንፈኛ ፋኖ ዓላማ መንግስት በወሎ፣ሸዋና ምስራቅ ጎጃም ትኩረት ስላደረገ ሙሉ ጉልበቱን አገዉ ምድር/አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር አድርጓል ለአሸባሪ ፋኖ አገው ምድር መተከል ዞንና ወለጋን ለመቆጣጠር መሸጋገሪያ ነው።

‎አገዉ ምድር ላይ የተቀናጀና የተደራጀ መብረቃዊ ጥቃት በማድረስ ወረራ በመፈፀም መተከልና ወለጋን በአጭር ጊዜ የመውረር ዓላማ አለው።መተከልና ወለጋን ከተቆጣጠረ ከሸዋ ፋኖ ጋር ጥምረት ፈጥረን አዲስ አበባን ከበባ ውስጥ እናስገባለን በሚል ከልብ እየሰሩ ይገኛል።

‎በጎጃም አገው ምድር ፋኖ ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን በሰው ሃይል፣በዘመናዊ መሳሪያና በፕሮፖጋንዳ የበላይነት አለው።በተቃራኒው በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር አመራር ውስጥ ደግሞ የፋኖ ክንፍ ሁነው ለፅንፈኛ ፋኖ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያደርጉ አሉ።የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር አብዛኛዉ መንግስታዊ መዋቅር የፋኖ አጋዥ ነዉ።በዚህ መሃል በሴራ ብዙ ንፁሃን ሰላም አስከባሪ ሃይል እያለቀ ነዉ።

‎አሸባሪው ፋኖ በጥቅምት ወር ከፍተኛ ትኩረት ካደረገባቸው የአገው ምድር ክፍሎች አንዱ ፋግታ ለኮማ ወረዳ እና አጂስ/አዲስ ቅዳም ከተማ አስተዳደር ነዉ።
‎ አዲስ ቅዳም ከተማ ውስጥ የነበረው የኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ማን አስወጣዉ? ለምንስ ወጣ? አጂስ/አዲስ ቅዳም ፅንፈኛ ፋኖ እስከ ሰከላ ቋሪት፣ደጋ ዳሞት፣አቸፈር፣ መራዊ ተናቦ የሚሰራበት ለፅንፈኛ ወረራ ተጋላጭ ቦታ ነዉ።

‎ መንግስት በቀን ምድር ይህን ያህል ፅንፈኛ ተሰባስቦ ወረራ ሲፈፅም በከባድ መሳሪያ እርምጃ የማይወስደዉ ለምንድነው? አገዉ ምድር ለምንድነው ድ*ሮን የማይጠቀም? ምስኪን ህዝብ ለምን በመሃል ያልቃል??

‎ የአማራ ክልል መንግስት በሌሎች የክልሉ
‎ አከባቢዎች ፅንፈኛን ክፉኛ እየደመሰሰ አገዉ ምድርን ለምን ተወው? አገዉ ምድር የክልሉ አካል አይደለም ወይ???

‎ፌዴራል መንግስት አገዉ ምድርን/አዊ ብሔረሰብ አስተዳደርን ስለምን ተወው???
‎በአገዉ ምድር እየደረሰ ያለዉን ጄኖሳይድ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሊያወግዙ ይገባል።
‎ለማንኛውም ለህዝብና ሀገር ህልዉና ስትሉ ቅዱስ መስዋዕትነት የከፈላችሁ ጀግኖች አርበኞች ሚሊሻዎች፣ፖሊሶች፣የጥምር ሃይል አባላት ነፍስ ደጋጎች ቅዱሳን ጎን ይሰለፍልን።ለህዝብና ሀገር ህልዉና ሲሉ መስዋዕትነት የከፈሉ ዘላለማዊ ጀግኖቻችን በአካል ቢሞቱም በነፍስ ህያዉ ናቸው።ለኢትዮጵያውያን እና ለኢትዮጵያ ህልዉና ተሰውታችሁልናልና ለዘላለም እናመሰግናለን🙏🙏??

‎አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድምጽ ነው

 #‎እንኳን ለ18ኛው የብሄራዊ ሰንደቅ አላማ ቀን በሰላም አደረሳችሁ።‎🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ...
13/10/2025

#‎እንኳን ለ18ኛው የብሄራዊ ሰንደቅ አላማ ቀን በሰላም አደረሳችሁ።
‎🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ!” በሚል በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

‎የ18ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ በዓል

‎ መልዕክቶች፣

‎🇪🇹ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ማንሰራራት አዲስ ዘመን ድል ብሥራት!

‎🇪🇹ሰንደቅ ዓላማችን የኀብረብሔራዊነታችን እና የአብሮነታችን የታሪክ ማብሰሪ ዓርማ ነው!

‎🇪🇹ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ሕዳሴ!

‎🇪🇹ሠንደቅ ዓለማችን የጀግንነታችንና የአይበገሬነታችን መገለጫ፤ የነፃነታችን ማማ!

‎🇪🇹ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ አዲስ ዘመን ከፍታ!”

‎🇪🇹ሠንደቅ ዓላማችን የዘመናት የነጻነታችንና የሥልጣኔያችን አብሪ ኮከብ!

‎🇪🇹ሠንደቅ ዓላማችን የሕዳሴያችን ሕያው ምስክር ነው!

  📌ስለጉዳዩ ከአገው ማህበረሰብ ምሁራን፣ከፖለቲከኞች ፣ከሀገር ሹማግሌዎች ከሀይማኖት አባቶች፣ከተፅኖ ፈጣሪዎች...  በአስቸኳይ አጣሪ ኮሚቴ ተዋቅሮ ስራ ሊጀምር ይገባል‼📌በአዊ ዞን እንጅባራ...
13/10/2025



📌ስለጉዳዩ ከአገው ማህበረሰብ ምሁራን፣ከፖለቲከኞች ፣ከሀገር ሹማግሌዎች ከሀይማኖት አባቶች፣ከተፅኖ ፈጣሪዎች... በአስቸኳይ አጣሪ ኮሚቴ ተዋቅሮ ስራ ሊጀምር ይገባል‼

📌በአዊ ዞን እንጅባራ ከተማ የአየር ማረፊያ እንዲሰራ ከብዙ አመታት ጀምሮ የህዝብ ፍላጎትና ጥያቄ ቀርቦበት የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን የቦታ መረጣ እንዲደረግ ደብዳቤ ተፅፎ፣ የቦታ መረጣውን ተጠናቆ ማረጋገጫ ደብዳቤ መምጣቱ ይታወቃል።

📌ከቦታ መረጣ ማረጋገጫ በኋላ አቬሽኑ ቦታውን መቀበሉን አረጋግጦ ደብዳቤ ከላከ በኋላ ስራ እንዲጀመር ዞኑ ለፌዴራል ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የማረጋገጫ ደብዳቤ እንዲፅፍ ጠይቋል።

📌ነገር ግን የአዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው ደብዳቤውን ለፌዴራል ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አልፅፍም ብሎ አስቀምጦታል። ምክንያት ሲጠየቅ ''እያንዳንዱን አካሄድ የአማራ ክልል መንግስት ማወቅ አለበት፣ ስለዚህ በክልል ፕሬዝዳንቱ የመሠረተ-ልማት አማካሪ ተገምግሞና አልፎ ነው መሄድ ያለበት ብሏል።

አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድምጽ

የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ-አዴን የመጀመርያ ዙር ልዩ ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱ ኮማንዶዎችን አስመርቋል።የጀመርነውን ትግል ዳር ሳናደረስ ንቅንቅ የለም የአገው ህዝብ ላይ ሊቃጣ የሚችል ማንኛ...
07/10/2025

የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ-አዴን የመጀመርያ ዙር ልዩ ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱ ኮማንዶዎችን አስመርቋል።የጀመርነውን ትግል ዳር ሳናደረስ ንቅንቅ የለም የአገው ህዝብ ላይ ሊቃጣ የሚችል ማንኛውንም አይነት ትንኮሳ መመከት የሚችልና የሃገሪቱን አሁናዊ ሁኔታ መሰረት በማድረግ ለአገው ህዝብ ዘብ መሆን የሚችል ሃይል መገንባት እንደሚያስፈልግም ተረድተናል።።

የአገዉ ነፃነት ሰራዊት ፀረአገዉ እና ፀረኢትዮጵያ ጠላቶችን ለመመከት እንዲሁም የአገዉ ህዝብ ሁለንተናዊ አዎንታዊ ለውጥ ጥያቄዎች እንዲመለሱ የሚሰራ ሰራዊት ነው።የአገዉ መከላከያ ሃይል/Agaw Defense Force(ADF) እንደ ሌሎች ሌሎችን ለመውረር ሳይሆን አገው ምድርንና ኢትዮጵያን ለመጠበቅ ነው።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ጄኔራል አገው ኢትዮጵያዊ ጄኔራል ሃይሉ ከበደ ልጆች፣የአድዋው ነብር የአይበገሬው ዋግሹም ጓንጉል ልጆች፣ የጄኔራል አበባዉ ልጆች፣የዛጉዌ ልጆች፣የዋግሹም ልጆች የአገዉ ህዝብንና የኢትዮጵያን ቦታ ወደ ቀደመ ከፍታ ለመመለስ ታሪክ እየደገሙ ይገኛሉ!!!

ማዕከላዊ አገዉ (ዋግ ላስታ አገው ምድር) ህዝብ 🙏

በደቡባዊ አገዉ (ጎጃም አገዉ ምድርና መተከል)፣ በምዕራባዊ አገዉ (ጎንደር ዞኖችም) ተመሳሳይ ዜና ይጠበቃል።

 #ፋኖ⁉️ በቅድሚያ አሁን ጫካ ለገባው ሃይል "ዘነገደ ይሁዳ ፋኖ"  ፋኖ የሚለውን ስያሜ ባልሰጠው ደስ ይለኛል፤ የ "ፋኖነትን" ትርጓሜ ሁሉም ያውቀዋልና።  0️⃣. የአማራ ህዝብ ነፃ አውጭ...
04/10/2025

#ፋኖ⁉️
በቅድሚያ አሁን ጫካ ለገባው ሃይል "ዘነገደ ይሁዳ ፋኖ" ፋኖ የሚለውን ስያሜ ባልሰጠው ደስ ይለኛል፤ የ "ፋኖነትን" ትርጓሜ ሁሉም ያውቀዋልና።

0️⃣. የአማራ ህዝብ ነፃ አውጭ ነኝ ባዩ አሁን ጫካ ያለው ሃይል ምን ምን ጥያቄዎች ይዞ ነፍጥ አነሳ? አማራ ለበርካታ ዓመታት በትህነግ (ህወሓት) በደል ስለደረሰበት አይደለምን?

1️⃣.ከወያኔ (ህወሓት) ጋር፣ ከአማራ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተሰልፎ የአማራን ጥያቄ እንዴት ማስመለስ ይቻላል ?

2️⃣.የአማራ ህዝብ ጥያቄ ከሆኑት አንዱ የማንነት እና የወሰን ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል። ታዲያ ከህወሓት ጋር ተሰልፎ ነው የወልቃይትን፣ የራያን፣ የዛታንና የኮረምን የወሰን ጥያቄ የሚያስመልሰው?

4️⃣. የልማት ፍትሐዊነት ጥያቄ ሌላኛው የአማራ ህዝብ ጥያቄ ነበር። ታዲያ በትግል ስም በብልጽግና መንግስት ምላሽ ማግኘት የጀመሩ የአስፋልት መንገድ ግንባታዎችን፣ የአየር ማረፊያ ግንባታ ስራዎችን፣ የመስኖ ግድብ ግንባታዎችን፣ ልዩ ልዩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በማስተጓጎል፣ በማውደም፣ በመዝረፍ ነው የአማራን ህዝብ ጥያቄ የሚያስመልሰው ?

5️⃣. ከ4.5 ሚሊዮን በላይ የክልሉ ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ውጭ አድርገህ፣ ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው ተመርቀው ከአገር አቀፍ ምንዳ የሚያገኙትን ክልላዊ ኮታ ነጥቀህ፣ ጠመኔ የታጠቁ መምህራንን፣ የሐይማኖት አባት፣ የሐገር ሽማግሌ፣ አዛውንት፣ እያዋረድክ፣ ከማህበራዊ እሴቱ ባፈነገጠ መልኩ እያሰቃየህው ፤ ጥያቄ ልታስመልስ አትችልም ‼

ከዚህ በመነሳት አስረግጨ ልናገር ይህ ትግል (የህወሓት፣ የኤርትራና የግብጽ) የውክልና ጦርነት ነው ።

#አገው #ሚድያ #ኔትዎርክ #የህዝብ #ድምጽ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share