አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network

አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network ለአገው ህዝብ ድምጽ ለመሆን የተቋቋመው የሚድያ ስለሆነ አድማጭ ተመልካቾቻችን ኮፒ ሼር ላይክ ኮሜንት በማድረግ ቤተሰብ እንድትሆኑ የአክብሮት ግብጀችን ነው ።

በበራህሌ የተከሰተውን ሰደድ እሳት ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው፦ የወረዳው አስተዳደር *************************በአፋር ክልል በራህሌ ወረዳ የተከሰተው የሰደድ እሳት ከ86 ሄክታር ...
26/06/2025

በበራህሌ የተከሰተውን ሰደድ እሳት ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው፦ የወረዳው አስተዳደር
*************************

በአፋር ክልል በራህሌ ወረዳ የተከሰተው የሰደድ እሳት ከ86 ሄክታር በላይ ተጠብቆ የነበረ ደን እና ሳር ማውደሙን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አሊ ሁሴን ለኢቲቪ ተናግረዋል።

አሁን ላይ ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር በተደረገው ርብርብ አብዛኛውን ማጥፋት ቢቻልም አካባቢው ተራራማ በመሆኑ ከአናት እሳቱ ሙሉ ለሙሉ እንዳልጠፋ አቶ አሊ ገልፀዋል።

የሰደድ እሳቱ መነሻ ምክንያት እንደማይታወቅ የገተናገሩት አስተዳዳሪው፤ እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በሁሴን መሀመድ

AGEW MEDIA NETWORK

አቶ አገኘው ተሻገር ወደ ውጪ ሀገር ሂደው ሊታከሙ ነውየኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሆኑት አቶ አገኘው ከሁለት ሳምንት በፊት ጎንደር ጎርጎራ ላይ በተከሰተው የጦር ሄሊኮፕተሯ መመ...
26/06/2025

አቶ አገኘው ተሻገር ወደ ውጪ ሀገር ሂደው ሊታከሙ ነው

የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሆኑት አቶ አገኘው ከሁለት ሳምንት በፊት ጎንደር ጎርጎራ ላይ በተከሰተው የጦር ሄሊኮፕተሯ መመታት ተከትሎ ጉዳት እንደደረሰባቸው ታውቋል ፡፡

አቶ አገኘው ሕክምናቸውን በአዲስ አበባ ሳራ ቤት አካባቢ በሚገኘው ሲልክሮድ ሆስፒታል ላለፉት 10 ቀናት እየታከሙ እንዳለውና ለተጨማሪ ሕክምና ወደ ውጪ ሀገር ውጥቶ መታከም እንዳለባቸው የሆስፒታሉ ዶክተሮች መናገራቸው ተሰምቷል፡፡

የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ Yeshambel Alamirw ስለ ድርጅታዊ አላማ ፣ እቅድና እስትራቴጂ ጉዳዮች ላይ እንዲህ ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል👇ለመላው የአገ...
26/06/2025

የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ Yeshambel Alamirw ስለ ድርጅታዊ አላማ ፣ እቅድና እስትራቴጂ ጉዳዮች ላይ እንዲህ ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል👇
ለመላው የአገው ህዝብ ደጋፊዎችና ትግሉን ለተቀላቀላችሁ የህዝባችን ነፃነት ፈላጊዎች በሙሉ!!

🔘 የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (የድርጅታችን) አቋም መሠረት ያደረገው ህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለዉን መዋቅራዊ በደል ሲሆን የምንታገለዉም በሀሳብ, በእወቀትና በመርህ ላይ ተመሰርተን ነዉ!!

🔘 የእኛ ትግል መሠረት ያደረገው ግለሰቦችን አይደለም ፤ በገዥዎች የተደገሰልንን መዋቅራዊ በደል፣ ፖለቲካዊ ጭቆና፣ ኢ-ፍትህዊ የሆነ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዝንፈት በህዝባችን ላይ የሚፈጸመዉን መዋቅር እና በመዋቀር ዉስጥ ያሉ ግለሰቦችንና ቡድኖች ነው። መዋቅር ብቻዉን በደልና ጭቆና አያደርስም ብቻዉንም ግዑዝ ነው። የምንታገለው የዚህ አስፈፃሚዎች የሆኑ አካላት ነው።
አሁንም ቢሆን እኛ ቸቋም መስርተን የምንታገለዉ ሥርዓትንና የሥርዓቱ ፈላጭ ቆራጭ ነን የሚሉትን ግልገል አምባገነኖችን ነው።

🔘 የትግል መስመራችን ግልጽ ነዉ ፤ ህዝባችን ማንነትን መሰረት ባደረገ ፍትሃዊ የሆነ የፖለቲካ ዉክልና, ኢኮኖማዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እና እኩልነት እንዲሁም ወንድማማችነት እንዲሰፍንና እንዲረጋገጥ ነዉ።
🔘 ተቋም መስርትን እየታገልንና እያተገልን ያለነው የህዝባችን የረጅም አመታት የመዋቅር፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ጥያቄዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ምላሽ እንዲያገኘ ነዉ:: ትናንትም ስንታገል የነበርነዉ፣ ዛሬም እየታገልን ያለነዉ፤ ነገም የምንታገለዉ ለዚሁ ትልቅ አገዋዊ ዓለማ ነዉ።
ሁላችንም ማትኮር እና መገንዘብ ያለብን ነገር ቢኖር የምንታገለዉ የህዝባችንን ህልዉና ለማስጠበቅና ለማስቀጠል በህገ-መንግስቱ መሠረት የአገው ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ዕውቅና እንዲያገኝ ነዉ።

🔘 በዚህ የትግል መንገዳችን ድርጅታችን ፍትህ ከውስጥም ከውጭም በርካታ ፈተናዎችና በደሎች የደረሱበት ቢሆንም መሰናክሎችን በጥበብ፣ በማስተዋል፣ በምክንያታዊነት እና በበሳል ስትራቴጂ አልፎ ዛሬ ላይ የህዝባችን ድምፅና መከታ መሆኑን እያረጋገጠ ይገኛል። : በጥቂት ካጋጠሙን ፈተናዎችና መሰናክሎች መካከል እስራት፣ እንግልት፣ ድርጅቱን በተደራጀ መልኩ የማጠልሸት እኩይ ተግባር እና ሌሎች ይገኛሉ።

አሁን ላይ ፓርቲያችን ፍትህ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተጽኖ ፈጣሪ ከሚባሉ ጥቂት ተቋማት/ፓርቲዎች ዉስጥ አንዱ በመሆኑ ኩራት እየተሰማን ትናንትም ዛሬም ነገም ለህዝባችን መክፈል የሚገባንን ውድ መስዕዋትነት ከፍለን የህዝባችንን ህልውና የምናስቀጥል መሆናችንን እናረጋግጣለን።

🔘 እኛም ሆን ድርጅታችን ገና ብዙ የሚጠበቅብን ቢሆንም የትናንት ስህተቶቻችንን እንደ ግብዓት በመጠቀም የነገን መልካም እድሎችን ከህዝባችን ጋር በመሆን እየታገልንና እያታገልን የህዝባችንን ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ እንዲመለሱ ለማድረግ ሙሉ ዝግጅት ጨርሰን አሁን ላይ በትግበራ (በትግል) ላይ እንገኛለን።

👉ለአገው ፍትህ ታግሎ የህዝቡን ህልዉና ማስጠበቅና ማስቀጠል ግዴታ እንጅ ቅንጦት አይደለም!!!

በቀጣይ ማስተማር አይችሉምበቀጣይ አመት ማስተማር የማይችሉ ት/ቤቶች    | በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉ የትምህርት ተቋማትን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስል...
26/06/2025

በቀጣይ ማስተማር አይችሉም

በቀጣይ አመት ማስተማር የማይችሉ ት/ቤቶች

| በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉ የትምህርት ተቋማትን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ይፋ አድርጓል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ትምህርት ቤቶችን አሳውቋል።

በ2016 ዓ.ም ማጠቃለያ ላይ በተደረገው የእድሳት ፍቃድ ምዘና ለ2017 የትምህርት ዘመን ካሳዩት ዝቅተኛ ውጤት መሻሻል እንዲያሳዩ እስከ 2017 ዓ.ም ታህሳስ ድረስ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፤ በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም በታህሳስ 2017 በተደረገ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው መሻሻል ባለማሳየቱና ዝቅተኛና ከደረጃ በታች በመሆኑ ምክንያት በ2018 የት/ት ዘመን ማስተማር የማይችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።

በመሆኑም የትምህርት ማህበረሰቡ እና ወላጆች ይህን በማወቅ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እንድታከናውኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር አሳውቋል።

የኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባህር መምጣት ለሁሉም ጥቅም አለው - አቶ ጥላሁን ጣሰው*******************ኢትዮጵያ የባህር በር አግኝታ በንግድና ኢኮኖሚ ተጠቃሚ ብትሆን ሶማሊያውያን፣ ኤርትራ...
26/06/2025

የኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባህር መምጣት ለሁሉም ጥቅም አለው - አቶ ጥላሁን ጣሰው
*******************

ኢትዮጵያ የባህር በር አግኝታ በንግድና ኢኮኖሚ ተጠቃሚ ብትሆን ሶማሊያውያን፣ ኤርትራውያንና ኢትዮጵያዊውያን ተጠቃሚ ይሆናሉ እንጂ አይጎዱም ሲሉ በወታደራዊ ጉዳዮች ፀሐፊና ተመራማሪ የሆኑት አቶ ጥላሁን ጣሰው ገልጸዋል፡፡

አቶ ጥላሁን ጣሰው ከኢቢሲ ዳጉ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ በነበረባት አለመግባባት የባህር በርና የባህር ኃይሏን አጥታለች ብለዋል።

የባህር በርና የባህር ኃይል ባለቤትነት ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለፖለቲካዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች መጎልበት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ በተለያዩ ፖለቲካዊ ምክንያቶች ወደብ አልባ በሆነችባቸው ዘመናት ሁሉ መሪዎች ይብዛም ይነስም የባህር በር አስፈላጊነትን እያነሱት መቆየታውን አቶ ጥላሁን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በነገስታት ስትመራ በነበረችባቸው ዘመናት ሁሉ መሪዎች የባህር በር እንዲኖረን ለማድረግ ከውጭ ኃይሎች ጋር ልዩ ልዩ ድርድሮችንና ጥረቶችን ያደርጉ እንደነበረ አንስተዋል።

የባህር ኃይል ከሌለህ የባህር በርን መቆጣጠር እጅግ አዳጋች መሆኑን የሚናገሩት አቶ ጥላሁን፤ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር የነበራት የፌዴሬሽን ጥምረት መፍረሱን ተከትሎ ዳግም ያጣችውን የባህር በርና የባህር ኃይል ባለቤትነት ታሪካዊ ክስተት አስታውሰዋል፡፡

እርስ በራሳችን በፈጠርነው አለመግባባትና መለያየት የባህር በራችንን አጥተናል ያሉት የታሪክ ተመራማሪው፤ የባህር ኃይል እያሰለጠንን ቢሆንም የባህር በር ባለቤት ግን እስካሁን አልሆንም ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ፣ የኤርትራና ሶማሊያ ሕዝቦች ጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ያላቸው ሕዝቦች መሆናቸውን ያነሱት አቶ ጥላሁን፤ ኢትዮጵያ የባህር በር አግኝታ በንግድና ኢኮኖሚ ተጠቃሚ ብትሆን ለሀገራቱና ለቀጠናው ትልቅ ጥቅም እንጂ አንዳችም ጉዳት እንደማይኖረው ተናግረዋል፡፡

በሀገር ውስጥ ያሉ ምሁራንና ልሂቃን ኢትዮጵያ እንድትወድቅ በመስራት የሚያገኙት ጥቅም አለመኖሩንም አውቀው በጋራ ተጠቃሚነት ላይ አትኩረው ቢሰሩ መልካም መሆኑን አቶ ጥላሁን ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ 70 የፌዴራል ተቋማት እና ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶቻቸው መመሪያን ሳይከተሉ ከ404 ሚሊዮን በላይ በሆነ ብር ግዢ መፈፀማቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታወቀ።መመሪያን ሳይከተሉ ግዢ ...
25/06/2025

በኢትዮጵያ 70 የፌዴራል ተቋማት እና ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶቻቸው መመሪያን ሳይከተሉ ከ404 ሚሊዮን በላይ በሆነ ብር ግዢ መፈፀማቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታወቀ።

መመሪያን ሳይከተሉ ግዢ ከፈፀሙ ተቋማት መካከል የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን፣ አርሲ ዩኒቨርሲቲ፣ እና በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር-2 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እንደሚገኙ ተገልጿል።

ይህ የተገለጸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 39ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የፌዴራል ዋና ኦዲተር ባቀረቡት የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የ2016 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ነው።

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ባቀረቡት ሪፖርት፤ በ70 የፌዴራል ተቋማት እና በ7 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶቻቸው ከ404 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ በሆነ ብር የመንግሥትን የግዥ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ግዢ ተፈጽሞ ተገኝቷል ብለዋል።

በተጨማሪም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ያለፍቃድ የቀን ሠራተኞችን ለቋሚ የሥራ ቅጥር መደቦች በመቅጠር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈጸማቸው ተገልጿል፡፡

በዚህም ጅማ ዩኒቨርሲቲ 25,310,211 ብር፣ አምቦ ዩኒቨርሲቲ 10,938,834 ብር፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 7,888,374 ብር፣ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ 5,170,600 ብርና ዲላ ዩኒቨርሲቲ 4,414,974 ብር ክፍያ መፈጸማቸው ተጠቅሷል፡፡

የምክር ቤት አባላት የሀብት ብክነትን መቆጣጠርና ተጠያቂነት ማስፈን ላይ ዋና ኦዲተር በትኩረት እንዲሰራ ያሳሰቡ ሲሆን፤ የኦዲት ክፍተት የተገኘባቸውና ሀብት ያባከኑ ተቋማትና የሥራ ኃላፊዎች ተጠያቂ በማድረግ ረገድ ያሉ ውስንነቶች መቀረፍ እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን ከምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በበኩላቸው በዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት መሰረት የኦዲት ግኝት ክፍተት ባሳዩ ተቋማት ላይ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ምክር ቤቱ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ አመላክተዋል።

‎አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ‎አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ )2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉበኤ ሐምሌ ወር 11/2017 ዓ/ም ለማድረግ ቅድማ ዝግጅቱን ጨርሶ መጠባበቅ ላይ ይገኛል ...
25/06/2025

‎አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ
‎አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ )2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉበኤ ሐምሌ ወር 11/2017 ዓ/ም ለማድረግ ቅድማ ዝግጅቱን ጨርሶ መጠባበቅ ላይ ይገኛል ፦
‎**********************
‎የአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በፈርጧና በደገዋ ገነት እንዲሁም በአገዎች መዲና በውቢቷ እንጅባራ ከተማ በእንጅባራ ባህል አዳራሽ በቅርቡ ያካሄዳል፣

‎ወደፊት የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና መቀመጫ በምትሆነው ውቢቱ ከተማ እንጅባራ የአገው ህዝብ ስለህልውናው ቀጣይነት ልብ ለልብ ይመካከራል፤ ይወያያል፤ በአገዋዊ ቃለ-መሃላ ይፈፅማል ይተሳሰራል፤ በአንድነት ተግባብቶና ተናብቦ የነፃነት መንገዱን በተባበረ ክንዱ ይጠርጋል፣

‎አዎ!!! ፤ እንጅባራ ከየአቅጣጫው የሚመጡትን ውድ ልጆቿን አዲናስ!! (እንኳን ደህና መጣችሁ!!!) ለማለት የተባረኩና ነፃነቱን የሚናፍቁ እጆቿን ዘርግታ የጃኖ ምንጠፍ አንጥፋ፤ በጃኖ ምንጣፍ ላይ ራሷን የሚገልፀውን ለምለም ቄጤማ ጎዝጉዛ፤ አብዚ (አነባብሮ) በተለያዩ ዓይነቶች አዘጋጅታ እና የአገው ህዝብ ልዩ መገለጫ የሆነውን የአገው ድንችና ድንች ቀቅላ ብሉልች ለማለት ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ትገኛለች፣

‎የአገው የነፃነት ታጋዮችም 2ኛውን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በውቢቷ መዲናችን እንጅባራ ከተማ ለማካሄድ የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ደግሞ መሰናዶውን በማጠናቀቅ ከውጭ ሀገርና ከሀገር ውስጥ ከየአቅጣጫው የሚመጡ የጉባኤ ተሳታፊ እንግዶችን አቀባበል ለማድረግ በአገዋዊ ስስት የጉባኤው ቀን እየጠበቁ ይገኛሉ፣

‎በደጋማዋ የአገዎች ፍርጥ እንጅባራ ከተማ አገውነት ጃኖ በለበሱ የ2ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ታዳሚዎች ከፀሀይ ብርሃን በላይ ይፈካል፣ ይደምቃል፣ አገውነት በአገው ልጆች ይነግሳል። በውቢቱ መዲናችን ሁሉም ዝግጁ!!! ፤ ደስ አይልም አገዎች!!!

‎በመዲናችን እንጅባራ ከተማ የሚካሄደው 2ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ለ2 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከ1000 በላይ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት ይሆናል፣

‎ለ2 ቀናት በሚቆየው ጉባኤያችን የአገው ህዝብ ዘርፈ ብዙ የሆኑ ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት ይካሄዳል፤ በአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጥያቄ የደረሰበት ደረጃ ለታዳሚው ይገለፃል፤ የአገው ህዝብ እስከ አሁን ምላሽ ያላገኛቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በምን አግባብና በማን መጠየቅ እንዳለባቸው የጋራ ውሳኔ ላይ ይደረሳል፤ በፍትህ እጦትና በዴሞክራሲ ጥያቄዎች ዙሪያ ልባዊ ውይይት ተካሄዶ ለአገው ህዝብ የመፍትሔ አማራጭ ይቀመጣል፣

‎ የ2 ቀናት ጉባኤያችን ለቀጣይ አገዋዊ ነፃነታችን ስለሚያግዙ ስትራቴጂዎች እና የትግላችን ፍኖተ ካርታ የምንመካከርበት፤ አገዋዊ ውሳኔ የምናሳርፍበት እና ቀጣይ የረቀቁ አገዋዊ የትግል አቅጣጫችንን የምናስቀምጥበት እንዲሁም ለቀጣይ 3 ዓመታት በዓላማ ፅንተው፣ በአገዋዊ ፍቅር ተክነው፣ በቆራጥነት፣ በአታጋይነት፣አዳዲስ የትግል ሃሳቦችን በማፍለቅና ወደ ተግባር በመቀየር የአገው ህዝብ ጥያቄዎችን በትንሽ መስዋትነት መፍታት የሚችሉ መሪዎችን በፍፁም ነፃ፣ ታኣማኒነት እና በዴሞክራሲያዊ መንገድ የሚመርጡበት ይሆናል።

‎""አገዋዊ ዓላማችን በፀና ትግላችን እውን ይሆናል"" በማለት የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ(ፍትህ) ፕሬዚዳንት ዶ/ር አዲሱ መኮነን ለአገው ሚድያ ኔትዎርክ ገለፁ ።

ቋራ ወረዳ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ሚፈተኑበት ጎንደር ዩኒቨርስቲ የሽኝት ፕሮግራም ተካሄደ።ቋራ/ገለጉ:- ሰኔ 18/2017 ዓ.ም (ቋራ ኮሙኒኬሽን) በሽኝት ፕሮግራሙ ...
25/06/2025

ቋራ ወረዳ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ሚፈተኑበት ጎንደር ዩኒቨርስቲ የሽኝት ፕሮግራም ተካሄደ።

ቋራ/ገለጉ:- ሰኔ 18/2017 ዓ.ም (ቋራ ኮሙኒኬሽን) በሽኝት ፕሮግራሙ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ፣ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበባው ንጉሴ እና ሌሎች የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

በሽኝት ፕሮግራሙ የተገኙት አቶ አስማረ አንዳርጋቸው ለተማሪዎች መልካም ዕድልን እየተመኙ ተማሪዎች ለ12 ዓመት ያህል የለፋችሁበት ትምህርት በውጤት እንዲታጀብ ፈተናቸውን ተረጋግተው መስራት መቻል እንዳለባቸው ገልፃዋል።

ፈተና መረጋጋትን የሚጠይቅ እንዲሁም የተማሩትን ማስታወስ የሚጠይቅ በመሆኑ ተማሪዎቻችን በፈተናችሁ የተሻለ ውጤት እንድታስመዘግቡ በተረጋጋ ህሊና እና የማስታወስ አቅማችሁን በመጨመር መፈተና መቻል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ በወረዳችን በ12ኛ ክፍል የተሻለ ውጤት እንዲመጣና የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ማስመዝገብ እንድትችሉ ተማሪዎቻችን ፈተናዎችን በጥንቃቄ መስራት መቻል እንዳለባቸው ገልፀው ለተማሪዎች መልካም ዕድልን ተመኝተውላቸዋል።

የቋራ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ
አገው ሚድያ ኔትዎርክ

የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ለዕርቅና ሠላም የሚጫወቱትን ሚና ማጠናከር አለባቸው - ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ዕርቅና ሠላምን በማስፈን ሂደት...
25/06/2025

የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ለዕርቅና ሠላም የሚጫወቱትን ሚና ማጠናከር አለባቸው - ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ

የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ዕርቅና ሠላምን በማስፈን ሂደት የሚጫወቱትን ሚና የበለጠ ማጠናከር እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ።

የሰላም ሚኒስቴር "ማህበራዊ ሀብቶቻችን ለህብረ-ብሔራዊ አንድነታችን" በሚል መሪ ሀሳብ ሀገር አቀፍ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የጎሳ መሪዎች እና የሰላም ተቋማት አመራሮች የምክክር መድረክ መካሄድ ተጀምሯል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፥ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በሀገራዊ የሰላም ግንባታና አንድነት ላይ ያላቸውን ሚና የሚዳስስ የውይይት መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል።

በጽሁፋቸውም ኢትዮጵያ የውብ ባህልና ታሪክ ባለቤት የሆነች ታላቅ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የታሪክ ጉዞም የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች በሀገረ-መንግስትና ሰላም ግንባታ የማይተካ ሚና ማበርከታቸውን አንስተዋል።

በተጨማሪም የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ዕርቅና ሠላምን በማስፈን ሂደት ውስጥ የሚጫወቱትን ሚና የበለጠ ማጠናከር እንዳለባቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም በሀገራዊ ሰላም ግንባታ ሂደት የመንግስት አጋር በመሆን የተሰጣቸውን ዕውቀትና ጥበብ መጠቀም እንደሚኖርባቸው አስረድተዋል።

የፍትሕ ሥርዓትን በማሳለጥም የሚፈጸሙ ወንጀሎች ትክክለኛና ተመጣጣኝ የፍትሕ ምላሽ እንዲያገኙ አይነተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተናግረዋል።

በዚህም ገለልተኛና ተዓማኒነታቸውን በማስጠበቅ ለመደበኛ የመንግስት አስተዳደር ምክርና ድጋፍ በመስጠት የሞራል ኃላፊነታቸውን መወጣት ይኖርባችኋል ብለዋል።

የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ህጋዊነት ከባህላዊ ውርስና ከበሬታ የሚመነጭ መሆኑንም አስረድተዋል።

በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ከዛሬ ሰኔ 18/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው መድረክ የሰላም ሚኒስትር አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ተገኝተዋል ።

#አገው #ሚድያ #ኔትዎርክ #የህዝብ ድምጽ

ኢራን !🤞ሞቱ  የተባሉት 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙበእስራኤል ጥቃት ሞተዋል የተባሉት የኢራን ጄኔራሎች የድል በዓል ላይ ታዩ!እስራኤል በቅርቡ "ገ**ኳቸው" ያለቻቸው 3...
25/06/2025

ኢራን !🤞

ሞቱ የተባሉት 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል
በዓል ላይ ተገኙ

በእስራኤል ጥቃት ሞተዋል የተባሉት የኢራን ጄኔራሎች የድል በዓል ላይ ታዩ!

እስራኤል በቅርቡ "ገ**ኳቸው" ያለቻቸው 3 ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ መሪዎች ትናንት የኢራንን የድል በዓል ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ ታይተዋል!

ከእነዚህ ውስጥ:-

* የእስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፕስ (IRGC) ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ኢስማኢል ቃዓኒ፣

* ⁠የመከላከያ ሚኒስትር ብርጋዴር ጄኔራል አዚዝ ናስርዛዴህ እና

* ⁠የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ አማካሪ አድሚራል አሊ ሻምካኒ ይገኙበታል።

ቪዲዮዎች እና የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እነዚህ መሪዎች ሕያው ሆነው በበዓሉ ላይ እንደተገኙ አረጋግጠዋል።

🌍አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድምጽ

" ከኢሶዴፓ 9 የስራ አስፈፃሚ አባላት 6ቱ ተሰብስበው፣ ምክትል ሊቀመንበሯን ዶ/ር ራሔልን እና ነባሩን ማህተም አግደዋል "- የኢሶዴፓ ጊዜያዊ ሊቀመንበር ነኝ ያሉት አቶ አጫሞ ቦቄ የኢትዮጵ...
25/06/2025

" ከኢሶዴፓ 9 የስራ አስፈፃሚ አባላት 6ቱ ተሰብስበው፣ ምክትል ሊቀመንበሯን ዶ/ር ራሔልን እና ነባሩን ማህተም አግደዋል "- የኢሶዴፓ ጊዜያዊ ሊቀመንበር ነኝ ያሉት አቶ አጫሞ ቦቄ

የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ/ሶዴፓ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት ማለትም ሰኔ 8/2017 ዓ.ም የፓርቲውን ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ራሔል ባፌን ማገዱን የሚያትት መግለጫ ተሰራጭቶ ነበር፡፡

የፓርቲው መሪ ዶ/ር ራሔል ባፌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል መግለጫው ቀደም ሲል በማዕከላዊ ኮሚቴ በታገዱ 4 የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የተፃፈና በህገወጥ ማህተም የተዘጋጀ ነው ብለውታል፡፡

የእግድ መግለጫውን አዘጋጅተዋል ከተባሉት ሰዎች መካከል የሆኑትና በዚሁ መግለጫ ላይ በጊዜያዊ ሊቀመንበርነት መሾማቸው የተገለፀ አንድ አባል በበኩላቸው የዶ/ር ራሔል የመታገድ ውሳኔ በፓርቲው ህገደንብ መሰረት በስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ አባላት በአብላጫ ድምፅ መተላለፉን ተናግረዋል፡፡

የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ አጫሞ ቦቄ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ዶ/ር ራሔል ከተሰጣቸው ሐላፊነት ውጭ እየተንቀሳቀሱ በመሆናቸውና ማህተሙንም ላልተገባ ተግባር እየተጠቀሙበት ስለሆነ " ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የእግድ ውሳኔውን አሳልፏል፣ አዲስ ማህተምም አስቀርፆዋል " ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አቶ አጫሞ ቦቄ በዝርዝር ምን አሉ ?

" እኔ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ/ሶዴፓ የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ ነኝ፡፡ ቢያንስ 30 አመታት ለሚሆን ጊዜ ከፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ጋር በፓርቲው ውስጥ ሰርቻለሁ፡፡

ፓርቲውን ከብሔር ፓርቲነት ወደ ሀገርአቀፍ ፓርቲነት በማሸጋገሩ ሒደት ሚናዬን ተወጥቻለሁ፡፡ አንድ ፓርቲ የሚመራው በህገደንቡ መሰረት ነው፡፡ አደረጃጀቱንና ውሳኔ አሰጣጡን የሚወስነው ህገደንቡ ነው፡፡ እኛም የምንመራውና የምንሰራው በዚሁ ህገደንብ መሰረት ነው፡፡

የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት አሁን 9 ብቻ ነን፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከማለፋቸው በፊትም 10 ነው የነበርነው፡፡ የአባላቱ ቁጥር 11 እንዲሆኑ ዶ/ር አወል አለማየሁ የሚባል ሰው ነሐሴ 20/ 2015 በተደረገ ጠቅላላ ጉባኤ ተመርጦ ነበር፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች አልተቀላቀለንም፡፡

ፕሮፌሰር በየነ በሞት ከተለዩንም በኋላ መንግስቱ እና ወንድሙ የሚባሉ ሁለት ሰዎች እንዲቀላቀሉን ተጠቁመው ነበር፡፡ ነገር ግን ሁለቱ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች አልተቀላቀሉንም፡፡ ስለዚህ፣ ፕሮፌሰር እያሉ 10 ነበርን ከዛ በኋላ ግን እስከዛሬ ድረስ በፓርቲው 9 ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ነን ያለነው፡፡

መስከረም 28/2017 ዘጠኛችንም ዶ/ር ራሔል ሊቀመንበር እንድትሆን ተስማምተን ቃለጉባኤ ፈርመን ለምርጫ ቦርድ ልከናል፡፡ ነገር ግን ምርጫ ቦርድ አልተቀበለውም ውሳኔያችንን፡፡ ሽግሽግ አይቻልም አለን፡፡ በማዕከላዊ ምክር ቤት ምርጫ አድርጋችሁ ነው ሊቀመንበር የምትመርጡት አለን፡፡ ከዛ በኋላ በቃ በምክትል ሊቀመንበርነት ፓርቲውን ምሪ ብለን ተስማማን፡፡

9ኙ የስራ አስፈፃሚ አባላት ከፕሮፌሰር ህልፈት በኋላ አንዴ ብቻ ነው የተሰበሰብነው፡፡ ከዛ በኋላ ዶ/ር ራሔል ልትሰበስበን አልፈለገችም፡፡ ነገር ግን ስራ አስፈፃሚውን ሳትሰበስብ የተናጠል ውሳኔ ማሳለፍ ጀመረች፡፡ ለምሳሌ የስራ አስፈፃሚው ሳይነጋገር ፣ በጀት ሳያፀድቅ አጀንዳ ሳይዝ፣ የስብሰባ ቦታም ሳይመርጥ፣ በራሷ ውሳኔ ወላይታ ሶዶ ከተማ ላይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ጠራች፡፡

በህገደንቡ መሰረት ግን ስራ አስፈፃሚው ስለስብሰባው ተወያይቶ መወሰን ነበረበት፡፡ ህገደንቡ ተጥሶ ስብሰባ ተጠርቷል ብለን አቤቱታ አቀረብን ለምርጫ ቦርድ፡፡

ከዘጠኝ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ስድስታችን ነን አቤቱታ ያቀረብነው፡፡ ሁለቱ አባላት በሀሳቡ ያልተስማሙ ናቸው የተባለው ትክክል አይደለም፡፡ ሁለቱ ሰዎች ራሳቸው መፈረማቸውን ለምርጫ ቦርድ አረጋግጠዋል፡፡ በህይወት ያሉ ናቸው ሊጠየቁ ይችላሉ፡፡ ከራሳቸው አንደበትም መስማት ይቻላል፡፡ ከሀሰት ፊርማ ጋር ተያይዞ በፖሊስ ሲፈለግ የነበረም ሆነ የተደበቀ ሰው የለም፡፡ እኔንም ያሳደደኝ ፖሊስ የለም፡፡

ምርጫ ቦርድ በበኩሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ማገድ አልችልም በማለቱ ስብሰባው ተጠራ፡፡ እኛም ወደ ስብሰባው ገብተን፣ ህገወጥ እንደሆነ ገልፀን ፖሊስ ጠርተን አስበተነው፡፡ ከተበተነ በኋላ ስድስት ሽማግሌዎች ተመርጠው አነጋገሩን፣ ስብሰባው ሌላ ቀን ይሁን ብለን ተስማምተን ወደቤታችን ገባን፡፡

ከዛ ዶ/ር ራሔል የተወሰኑትን አባላት አግባብታ በመሰብሰብ ማታ ላይ ቃለጉባኤ እንዲዘጋጅ አደረገች፡፡ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በአራቱ ሰዎች ላይ እግድ አስተላልፏል ብላ የእገዳ ደብዳቤ ሰጠችን፡፡ ይህ ትክክል አልነበረም፡፡ማዕከላዊ ኮሚቴ የስራ አስፈፃሚ አባላትን የሚያግድባቸው በህገደንቡ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎች አሉ፡፡ እነሱን ያሟላ አይደለም እግዱ፡፡ እኛ የሰራነው ስህተት የለም፣ የአካሔድ ክፍተት ተፈጥሯል፣ የህገደንብ ጥሰት ተፈፅሟል ነው ያልነው፡፡

ከታገድን በኋላ ደግሞ አሁንም ስድስታችን ለሁለተኛ ጊዜ ለምርጫ ቦርድ አመለከትን፣ የተጣለብን እግድ ህገወጥ ነው ብለን ማለት ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 6/2017 ዓ.ም ውሳኔ ሰጠ፡፡

ወላይታ ሶዶ ላይ የተደረገው ስብሰባ ህገደንቡን የተከተለ አይደለም፣ የአባላት እግዱም ህገወጥ ነው ብሎ አነሳው፡፡ በፓርቲው አሰራር መሰረት ሁሉም ነገር ወደነበረበት ይመለስ አለ፡፡ ችግራችሁን በስራ አስፈፃሚ ውይይት ፍቱ አለን፡፡ እኛ ደግሞ ሰብስቢን ብለን ጠየቅን ዶ/ር ራሔልን፡፡ አሁንም ፈቃደኛ አልሆችም፡፡

ዶ/ር ራሔል ባፌ ከፓርቲው ህገደንብ በላይ ስላልሆነች ሰኔ 8/2017 ዓ.ም ከዘጠኙ ስራ አስፈፃሚ አባላት ስድስቱ ተሰብስበን የእግድ ውሳኔውን አሳልፈናል፡፡ ወደፊት ማዕከላዊ ኮሚቴው ተሰብስቦ በህገደንቡ መሰረት ሊቀመንበሩን እስኪመርጥ ድረስ እኔን ጊዜያዊ ሊቀመንበር አድርጎ መርጦኛል ስራ አስፈፃሚው፡፡ በስድስቱም ስራ አስስፃሚ አባላት ተመርጫለሁ፡፡

ማህተሙንም ዶ/ር ራሔል ለህገወጥ ተግባር ስትጠቀምበት ስለነበረ ቀይረነዋል፡፡ ነባሩን ማህተም በመጠቀም የተላለፉ ውሳኔዎች አሉ ወደፊት በህግ የሚያስጠይቁ ናቸው፡፡ ዶ/ር ራሔል ከታገደች በኋላ የፓርቲው ህልውና መቀጠል ስላለበት ስራ አስፈፃሚው አዲስ ማህተም እንዲቀረፅ አድርጓል፡፡

ይህን የእግድ ውሳኔ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳውቀናል፡፡ ለሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም አሳውቀናል፡፡ ምርጫ ቦርድ፣ የመተዳደሪያ ደንባችንን መርምሮና ፈትሾ ውሳኔያችንን ይቀበላል ብለን እንጠብቃለን፡፡ ቦርዱ የሚሰጠን ውሳኔ የማያረካ ከሆነ የመተዳደሪያ ደንባችንንና ሰነዶቻችንን ሰብስበን ወደ ፍርድ ቤት እንሔዳለን፡፡

ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሐላፊዎችን የማገድ፣ የመሾምና የመሻር ስልጣን አልተሰጠውም የሚለው ትክክል አይደለም፡፡ በህገደንቡ አንቀፅ 14/6 ላይ ይህ ስልጣን በግልፅ ተቀምጧል። በዚህ አንቀፅ መሰረት ስራ አስፈፃሚው ሐላፊዎችን ማገድ ይችላል፡፡

ከዚህ በፊት የውስጥ ችግራችንን በውይይት ለመፍታት ሞክረናል በዶ/ር ራሔል እምቢተኝነት ሁሉም ጥረቶች አልተሳኩም፡፡ አሁንም ጉዳዩን በውይይት ለመፍታት ጥረት ማድረጋችንን እንቀጥላለን፣ ግን ደግሞ የሚሳኩ አይመስለኝም፡፡ ወደ ውይይት የምንመጣ ከሆነ ግን መጀመሪያ እኛንም፣ ሽማግሌዎችንም ይቅርታ መጠየቅ ይኖርባታል፣ ዶ/ር ራሔል ባፌ "

አገው ሚድያ ኔትዎርክ የህዝብ ድምጽ

የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልን ጎበኙ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ.ም የጦር ሃይሎች ...
24/06/2025

የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልን ጎበኙ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና አሠጣጥ ሂደቱን ተመልክተዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የሪፈራል ሆስፒታሉን የእንግዳ ማረፊያም መርቀዋል። የእንግዳ ማረፊያው ሁሉንም ዓይነት የእንግዳ መቀበያ መሥፈርት ያሟላ 26 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ነው።

የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና አሠጣጥ ሂደቱን የተመለከቱት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ሆስፒታሉ በህክምና መሣሪያዎች ቴክኖሎጅና በሙያተኛ ዘመናዊነትን በተከተለ አግባብ ዘምኖ የሪፈራል ሆስፒታል መሆን እንዲችል መከላከያ ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ ማድረጉን ገልፀዋል።

በአለማችን በጦር መሣሪያ፣ በህክምና መገልገያ መሣሪያ፣ በኢንዱስትሪ እና በሌሎች የቴክኖሎጅ ዘርፎች ሞዴል የሚሆኑ ሙያተኞች የሚፈልቁት ከውትድርናው ቤት ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ኢትዮጵያ በየጊዜው ሲገጥማት በነበረው ጦርነት ምክንያት ሞዴል ሳንሆን መቆየታችንን ገልፀው አሁን ላይ ግን በሁሉም ዘርፍ ዘመናዊነትን በተከተለ አግባብ ከቴክኖሎጅው ጋር መላመድና አብሮ ማደግ ይኖርብናል ብለዋል።

ሪፈራል ሆስፒታሉን በማዘመን ወደ ውጪ የሚሄዱ ታካሚዎች እዚሁ እንዲታከሙ የማድረጉ ጥረት ትልቅ ተስፋ ሰጪ በሆነ መንግድ ስኬታማ ሆኗል ለዚህም የ87 የሠራዊት አባላት የዳሌ አጥንት ቅየራ ሥራ በውጤት መሣካት ዋናው ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።

የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የሆስፒታሉ ፅዳትና ውበት እጅግ በተለዬ መንገድ ሳቢ ለሥራ ምቹነት የሚፈጥር ሞዴል በሆነ አግባብ መሠራቱን አድንቀው የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊን ጨምሮ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አመራሮች ላደረጉት ያልተቆጠበ የሥራ ተነሳሽነት ምስጋና አቅርበዋል።

በጉብኝቱ ላይ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላን ጨምሮ ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና ጄኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ ውብሸት ቸኮል
ፎቶግራፍ ተሠማ ኡርጌሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share