Ethio Addis Zena

Ethio Addis Zena Welcome to our page this page is dedicated to providing the latest Ethio news in the Amharic

10/07/2025


#ከየትኛውም

10/07/2025

#ጀምሮ #ከየትኛውም

10/07/2025

የኬንያ ፕሬዚደንት መንግሥትን «ለመገልበጥ» የሚያሴሩ ይጠንቀቁ አለ #ጀምሮ #ከየትኛውም

09/07/2025
ኦሮሞ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባJuly 9, 2025 by ሥዩም ጌቱኦነግ ባለፉት 50 ዓመታት ባከናወናቸው የፖለቲካ ትግሎች በርካታ ድሎች መገኘታቸውን ገልጾ ዛሬም ድረስ ግን ህዝ...
09/07/2025

ኦሮሞ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ
July 9, 2025 by ሥዩም ጌቱ
ኦነግ ባለፉት 50 ዓመታት ባከናወናቸው የፖለቲካ ትግሎች በርካታ ድሎች መገኘታቸውን ገልጾ ዛሬም ድረስ ግን ህዝቡ ሙሉ ነጻነት እንዳልተጎናጸፈ እንደሚያምን አስታውቋል። በፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነት ምክንያት ዛሬም መታሰርና መሳደድ እንዳለ የገለጸው ኦንግ፤ ባለፉት7 ዓመታትም ችግሮችን በንግግር ወደመፍታት መሻገር አለመቻሉን ገምግሜያለሁ ብሏል፡፡
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር(ኦነግ)ለሁለት ቀናት ጉሌሌ በሚገኘው ዋና ቢሮው በማካሄድ ትናንት ባጠናቀቀው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባው የፓርቲውን አሁናዊ ሁኔታን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል እና ኢትዮጵያ ብሎም የቀጣናው ተጨባጭ ይዞታዎችን መገምገሙን አስታውቋል፡፡ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ በዚህ ላይ በሰጡን ተጨማሪ አስተያየት፤ “ፓርቲው ባለፉት አምስት ዓመታት ያለቢሮ መንቀሳቀስን ጫምሮ በርካታ ተግዳሮቶችን አሳልፏል” በማለት በዚህን ወቅት በየጊዜው መገናኘት የነበረበት የፖለቲካ ድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ ሳይገናኝ የቆየበትና የአመራሮች ከፓርቲው መውጣትን ጨምሮ በርካታ ተግዳሮቶች የገጠሙበት በመሆኑ ችግሩን እልባት በመስጠት የወደፊቱን አቅጣጫ ማስቀመጥ የአሁኑ የማዕከላዊ ኮሚተው ዋና ዋናዎቹ ትኩረት ናቸውም ብለዋል፡፡
ፓርቲው በውይይቱ ወቅታዊውን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በተመለከተ ፓርቲው ባሳለፈው አምስት ዓመታት የገጠሙትን ተግዳሮች ገምግሞ የወደፊት አቅጣጫውን አስቀምጧል ተብሏልም፡፡ ከመስከረም 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ አገር ቤት በመመለስ አዲስ አበባ የነበረውን ቢሮውን ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ የከፈተው ኦነግ አገሪቱ ያስቀመጠቻቸው ህጋዊ መሰረቶችን በማሟላት በሰላማዊ መንገድም ለመንቀሳቀስ ፈቃድ ማግኘቱን በመጥቀስ፤ አሁን ላይ የተፈጠሩትን ክፍተቶች ለመድፈን በአጭር ጊዜ ውስጥ 5ኛውን ድርጅታዊ ጉባኤ ለማድረግ ኮሚቴ ማዋቀሩንም አስታውቋል፡፡
ፓርቲው “ያለአግባብ ከፓርቲው የወጡ” ያሏቸውን የፓርቲው አመራር አባላትን በማስመልከት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አመራር አባላቱን ከፓርቲው ያገለለ መሆኑንና ይህንኑን ውሳኔ ለፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ለማቅረብ አቅጣጫ ስለመቀመጡን ነው የተጠቆመው፡፡ ቃል አቀባዩ አቶ ለሚ በነዚህም ጉዳዮች ላይ በሰጡን ተጨማሪ ማብራሪያ፤ “ውሳኔዎቹም አንደኛው የፓርቲው አምስተኛ ጠቅላላ ጉባኤ የጠራበት ሲሆን ከድርጅቱ በራሳቸው ጊዜ የወጡ አመራር አባላቶችን በማገድ ውሳኔውን ነለጠቅላላ ጉባኤው ለማሳለፍ ተወስኗልም” ነው ያሉት፡፡
በክልላዊ፣ አገራዊ እና አህጉራዊ ብሎም ቀጣናዊ አሁናዊ ሁኔታዎች ላይ የሚስተዋሉ እውነታዎችን የኦነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ በስብሰባው መገምገሙንም ያወሱት አቶ ለሚ ፓርቲያቸው በአገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እውን ሊሆኑ የሚችሉበት መንገድ ላይም ምክረሃሳብ ማስቀመጡን አንስተዋል፡፡ እንደፓርቲቸው “ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ህዝባዊ ጽናትና ድርጅታዊ አንድነት አስፈላጊ ነው” በማለት አስተያየት ሰየሰጡት ፖለቲከኛው “ውስብስብ” ካሉት ከወቅታዊው የአገሪቱ ፖለቲካዊ ሁናቴ መውጣትም የሚቻለው ዴሞክራሲን በማስፈን እንደሆነም ነው በአስተያየታቸው ያብራሩት፡፡
ፓርቲው በውይይቱ ወቅታዊውን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በተመለከተ ፓርቲው ባሳለፈው አምስት ዓመታት የገጠሙትን ተግዳሮች ገምግሞ የወደፊት አቅጣጫውን አስቀምጧል ተብሏልም፡፡
ምስል፦ Seyoum
ኦነግ በሰሞነኛው ማዕከላዊ ኮሚቴው ስብሰባ ድርጅቱ ባለፉት 50 ዓመታት ባከናወናቸው የፖለቲካ ትግል በርካታ ድሎች መገኘታቸውን እንደሚያምን ገልጾ፤ ይሁንና ዛሬም ድረስ ህዝቡ ሙሉ የሆነን ነጻነት እንዳልተጎናጸፈ እንደሚምን በመግለጫው አብራርቷል፡፡ በፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነት ምክንያት ዛሬም መታሰርና መሳደድ እንዳለም የገለጸው ኦንግ፤ ባለፉት ሰባት ዓመታትም ችግሮችን በንግግር ወደመፍታት መሻገር አለመቻሉን ገምግሜያለሁ ብሏል፡፡
ኦነግ “በአስመራ ከተገባው ስምምነት በተቃራኒ ባለፉት ሰባት ዓመታት የፓርቲውን አመራሮች እና አባላትን በማሳደድ የፖለቲካ ደባ ተፈጽሞብኛል” ያለ ሲሆን በኦሮሚያ የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ በርካቶች በፓርቲው ስም የምንቀሳቀሱ ያለአግባብ እስር ማቀው ታይተዋል በሚል ገምግሟልም፡፡
ኦነግ የተለመደ ያለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ አካሄድ ላይ ትችት በማቅረብም መንግስት የህዝብን ደህነነት አደጋ ላይ የሚጥል ያለውን የሰላማዊ ፖለቲካ ምህዳር መጥበብን እልባት እንዲሰጥ ሲል ጥሪ አቅርቧልም፡፡
ስዩም ጌቱ
ኂሩት መለሰ

09/07/2025

አርዕስተ ዜና፦ ኢትዮጵያ ዉስጥ በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት የክልሉን የጤና አገልግሎት በብርቱ ማወኩን ድንበር የለሽ ሐኪሞች (MSF-በፈረንሳይኛ ምሕጻሩ) የተሰኘዉ ግብረ-ሠናይ ድርጅት ዐሳወቀ ። የኬንያ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ፦ «ኢ-ሕገመንግሥታዊ በሆነ መልኩ» መንግሥትን «ለመገልበጥ» የሚያሴሩ ያሏቸው ሰልፈኞችን እግር ፖሊስ በጥይት እንዲመታ ዛሬ ትእዛዝ አስተላለፉ ። ሩስያ ምሽቱን በ728 ድሮኖች እና 13 ሚሳይሎች ምዕራብ ዩክሬንን ደበደበች ። ይህ የሩስያ ጥቃት በሦስት ዓመታቱ የዩክሬን ጦርነት ከፍተኛው ነው ተብሏል ። የዩክሬን መከላከያ 711 ድሮኖችን እና ሰባት ሚሳይሎችን ዐየር ላይ ማክሸፉን ገልጧል ።
ዜናው በዝርዝር
ናይሮቢ-የአማራ ክልል ግጭት የጤና አገልግሎትን እያወከ ነዉ-MSF
ኢትዮጵያ ዉስጥ በአማራ ክልል የሚደረገዉ ግጭት የክልሉን የጤና አገልግሎት በብርቱ ማወኩን ድንበር የለሽ ሐኪሞች (MSF-በፈረንሳይኛ ምሕጻሩ) የተሰኘዉ ግብረ-ሠናይ ድርጅት ዐሳወቀ ። ዓለም አቀፉ የሕክምና አገልግሎት ድርጅት ዛሬ እንዳሳወቀዉ ግጭቱ ከፍተኛ የመድኃኒት እጥረት አስከትሏል ። የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይላትና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች ግጭት የክልሉን ሕዝብ እንቅስቃሴ በጅጉ ማወኩንም ድርጅቱ አክሎ ዘግቧል ። ድንበር የለሽ ሐኪሞች እንዳለዉ የካላ-አዛር (Leishmaniasis ወይም ቁንጭር) በሽታንና በእባብ መነደፍ የሚደርሰዉን ሕመም ለማከም የሚረዱ መድኃኒቶች ማግኘት ሲበዛ ከባድ ነዉ ። ድርጅቱ እንዳለዉ፦ በክልሉ የሚገኙ የጤና ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት የቀነሰ ሲሆን፤ በቂ መድኃኒትም የላቸዉም ። በግጭቱ ምክንያት ዓለም አቀፉ የሕክምና ግብረ-ሠናይ ድርጅት ለጽኑእ ኅሙማን ይሰጥ የነበረዉን የአምቡላስ ሕክምና አገልግሎት ማቋረጡን አሳውቋል ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል እየጨመረ በመጣው የወባ በሽታ ሥርጭት ሰዎች እየታመሙ እና እየሞቱ መሆኑን ነዋሪዎች ገለጹ ። ነዋሪዎቹ እንዳሉት፦ በበሽታው ብዛት ያላቸው ሰዎች መያዝ የጀመሩት ከባለፈው የየካቲት ወር አንስቶ ነው ። ዶቼ ቬለ በዞኑ ቤንች ሸኮ ፣ ምዕራብ ኦሞ እና ኮንታ ዞኖች ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በበሽታው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች መኖራቸውንም ጠቅሰዋል ።
ናይሮቢ፥ የኬንያ ፕሬዚደንት መንግሥትን «ለመገልበጥ» የሚያሴሩ ይጠንቀቁ አለ
ፖሊስ ላይ የሚቃጣ ማንኛውም ጥቃት እንደ «የጦርነት እወጃ» ይታያል ሲሉምት ፕሬዚደንቱ አስጠንቅቀዋል ። ዊሊያም ሩቶ ነውጡን የሚያስነሱት መንግሥትን በሕገመንግሥታዊ ሒደት ለመቀየር «ትእግስት ያጠራቸው ጥቂቶች ናቸው» ሲሉ ዛሬ በስዋሒሊ ቋንቋ ከናይሮቢ ተናግረዋል ።
ዩናይትድ ስቴትስ ለናይጄሪያ ዜጎች የምትሰጠውን የጉብኝት ጊዜያዊ ቪዛ በሦስት ወራት ገደበች ።ይህንንም ናይጄሪያ አቡጃ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ዛሬ ይፋ ማድረጉን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት (AFP) ዘግቧል ። ቀደም ሲል የናይጄሪያ ዜጎች አሜሪካ እንደሚቆዩበት ቀን ልክ ነበር ቪዛ ያለ ሦስት ወር ገደብ ይሰጣቸው የነበረው ። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ12 አገራት ዜጎች ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት የጉዞ እገዳ ጥለው እንደነበር ይታወሳል ። እገዳ የተጣለባቸው አብዛኛዎቹ አገራት ከአፍሪቃ ሲሆኑ፤ የእገዳው ምክንያትም የብሔራዊ ደህንነት ሥጋት እና በቂ ያልሆኑ የማጣራት ሂደቶች ናቸው ብለው ነበር ። በትእዛዙ መሰረት የሰባት አፍሪቃ አገራት ዜጎች ማለትም ቻድ፣ የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ኤርትራ፣ ሊቢያ፣ ሶማሊያ እና ሱዳን ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳ ተጥሎባቸዋል ። አጸፋውን ለመመለስ ቻድ ለአሜሪካ ዜጎች ቪዛ መስጠት ማቋረጧን ወዲያውኑ ነው ያሳወቀችው ። የናይጄሪያ መንግሥት በዜጎቹ ላይ ስለተጣለው ገደብ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም ።
ኪዬቭ፥ ሩስያ ዩክሬንን እስከዛሬ ታይቶ በማይታወቅ የድሮን ውርጅብኝና ሚሳይል ደበደበች
ሩስያ ምሽቱን በ728 ድሮኖች እና 13 ሚሳይሎች ምዕራብ ዩክሬንን ደበደበች ። ይህ የሩስያ ጥቃት በሦስት ዓመታቱ የዩክሬን ጦርነት ከፍተኛው ነው ተብሏል ። የዩክሬን መከላከያ 711 ድሮኖችን እና ሰባት ሚሳይሎችን ዐየር ላይ ማክሸፉን ገልጧል ። ሩስያ መጠነ ሰፊ ጥቃቱን ያጠናከረችው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ለዩክሬን አልሰጥም ብለው የነበሩትን የዐየር መከላከያ እንዲሰጥ መወሰናቸው ከተሰማ በኋላ ነው ። የሩስያ መከላከያ ዒላማ ያደረገው የዩክሬን የዐየር ማረፊያ ጦር ሰፈሮችን እንደሆነ በመግለጥ፦ «የተመረጡ ዒላማዎች በአጠቃላይ ተመትተዋል» ብሏል ። የዩክሬን ባለሥልጣናት እንዳሉት ግን፦ የሩሲያ ሰዉ አልባ አዉሮፕላኖችና ሚሳዬሎች ከዋና ከተማዪቱ ኪዬቭ እስከ ፖላንድ ጠረፍ ድረስ የሚገኙ አካባቢዎችን ደብድበዋል ። የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ የዩክሬን ጦርነትን ለማብቃት ዲፕሎማሲያዊ መንገዶች መሟጠጣቸውን ገልጠዋል ። ጀርመን ለዩክሬን የረዥም ርቀት ተጓዥ ጦር መሣሪያዎች ለማቀበል ዕቅድ እንዳላትም ዛሬ ቤርሊን ከሚገኘው ምክር ቤት ባሰሙት ንግግር ይፋ አድርገዋል ።
#ከየትኛውም


የኢትዮጵያ የሀገር አቋራጭ ሾፌሮች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ተካ ደበሌ አሽከርካሪዎች በግዳጅ በተሰማሩባቸው ጦርነቶች ህይወታቸው ካለፈ በኋላ እንኳን ለቤተሰቦቻቸው ለማርዳት ተቸግረናል ይላሉ፡፡...
04/07/2025

የኢትዮጵያ የሀገር አቋራጭ ሾፌሮች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ተካ ደበሌ አሽከርካሪዎች በግዳጅ በተሰማሩባቸው ጦርነቶች ህይወታቸው ካለፈ በኋላ እንኳን ለቤተሰቦቻቸው ለማርዳት ተቸግረናል ይላሉ፡፡ግዳጅ እንሰማራለን የቀሩ ወንድሞቻችንም አሉ መስዋዕት የሆኑ በረዳት፣በገንዘብ ተቀባይ በሾፌር ይህን ያህል ተብሎ የሚነገር አይደለም፡፡
በኢትዮጱያ የሀገር አቋራጭ አዉቶብስ አሽከርካሪዎች ፈተና
አሽከርካሪ እሸቱ በላይ ባለፉት 6 ዓመታት የሐገር አቋራጭ አውቶቡስ ሾፌር ሆኖ በተለያዩ ጦርነቶች ከሰሜኑ ጦርነት ጀምሮ ተሳትፏል፡፡ እሱና ጓደኞቹ በተሳተፉባቸው ግዳጆችም በርካታ ጓደኞቹን በሞት እንዳጣ ይናገራል፡፡ ይሁን እንጂ የእነኝህን በሞት የተለዩ አሽከርካሪዎች ቤተሰቦቻቸው ዛሬ ላይ ኑሮ ቢከብዳቸውም ይህንን ችግር የሚካፈል አካል ቀርቶ ሞታቸውን በአግባቡ የሚነግራቸው የለም ይላሉ፡፡
‹‹ከህልውና ዘመቻ ጀምሮ ያለው የሰላም ሁኔታ አስቸጋሪ ነው፡፡ በዘመቻ በሄድንበት ጊዜ የሞቱ ብዙ ጓደኞች አሉኝ፡፡ የተረዳም የለም፤ እናርዳ ብንል እንኳን ለማንም አልተነገረም፡፡ ቤተሰቦቻቸው ግን አውቀዋል፡፡ ምንም የሚያደርጉት ነገር ግን የለም፡፡››
የሾፌሮቹን መብት ለማስጠበቅ የተቋቋመዉ ማህበር ስራ አለመስራት
ሌላው ለዶቼቬሌ አስተያየቱን ያጋራው አሽከርካሪም የሀገር አቋራጭ ሾፌሮችን ደህንነት ለመከታተል እና ለመተጋገዝ የተቋቋመው የሾፌሮች ማህበር ስራውን በአግባቡ እየሰራ ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ የአሽከርካሪዎችን ዋስትና ማህበሩም ሆነ መንግስት ማስጠበቅ አልቻለም ሲል ነው የሚናገረው፡፡
‹‹ምንም አይነት ዋስትና የለም አደጋው ከደረሰ ደረሰ ነው፡፡ የሾፌሮች ማህበር አለ ምንም አይነት ስራ እየሰራ አይደለም፡፡ ሾፌር ከሞተም ቤተሰቡን በትኖ ነው የሚሞተው በማህበር ደረጃም ሆነ በመንግስት ደረጃ ምንም ዋስትና የለም፡፡››
አሁን ላይ በአማራ ክልልም ሆነ በኦሮሚያ አካባቢ ያለው እገታና ዝርፊያ ሰርተን ለመለወጥም ሆነ ለህይወታችን ዋስትና አለመኖር ስራችንን ትተን እንድንቀመጥ እያደረገን ነው ሲሉም አሽከርካሪዎቹም ይገልፃሉ፡፡ ‹‹እገታው በገብረ ጉራቻ መንግስትም ያውቀዋል፡፡ በአዋሽ በኩልም እንደዚሁ ሁሉም ቦታ እገታ ስለሆነ እኔ አሁን ሾፌር ነኝ ትቼ ቁጭ ብያለሁ ፤ ምንም ዋስትና የለም፤ ከሞመት ይሻላል ብየ መቀመጡን መርጫለሁ፡፡››
በግዳጅ ላይ እያሉ የሞቱ አሽከርካሪዎች ቤተሰቦች መቸገር
በኢትዮጵያ የሀገር አቋራጭ ሾፌሮች ማህበር ዋና ፀሀፊ አቶ መሳይ ኃ/ማርያም እንደሚገልፁት በሰሜኑ ጦርነት ሲያገለግሉ የነበሩ የህዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪዎች በጦርነት ውስጥ ህይወታቸው በማለፉ ዛሬ ላይ ቤተሰቦቻቸው ለከፋ ችግር ተዳርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ በጦርነቱ የሞቱ አሽክርካሪዎችን ቤተሰቦች ለመደጎም የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስተር በባለፈው ዓመት ሰኔ ወር የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ቢያዘጋጅም እስከ ዛሬ ግን ተፈፃሚ አልሆነም፡፡
በአማራ ክልልም ሆነ በኦሮሚያ አካባቢ ያለው እገታና ዝርፊያ ሰርተን ለመለወጥም ሆነ ለህይወታችን ዋስትና አለመኖር ስራችንን ትተን እንድንቀመጥ እያደረገን ነው ሲሉም አሽከርካሪዎቹም ይገልፃሉ፡፡
ምስል፦ Isayas Gelaw/DW
‹‹ከህልውና ዘመቻ ጀምሮ ችግሮች አሉ፤ በህልውና ዘመቻ እስከ ግንባር ድረስ ነው አሽከርካሪዎች የሚገቡት የተሰውም አሉ የእነሱን ቤተሰቦች አሁን የከፋ ችግር ላይ የሚገኙት ልጆች ትምህርት ቤት አቁመዋል፣ የቤት ኪራይ የሚከፍል የለም፣ ብዙ ነገር የለመዱ ናቸው፡፡ ያን ሁሉ አጥተዋል፡፡ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስተርም ቴሌቶን አዘጋጅቷል ግን እስካሁን አልተጠናቀቀም፡፡››
በግዳጅ ላይ እያሉ የሞቱ አሽከርካሪዎችን ሞት ለቤተሰቦቻቸዉ በተገቢዉ መንገድ አለማርዳት
የኢትዮጵያ የሀገር አቋራጭ ሾፌሮች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ተካ ደበሌ አሽከርካሪዎች በግዳጅ በተሰማሩባቸው ጦርነቶች ህይወታቸው ካለፈ በኋላ እንኳን ለቤተሰቦቻቸው ለማርዳት የተቸገርንበት ሁኔታ ነው ያለው ይላሉ፡፡ ‹‹በህልውና ዘመቻው አሁንም በሚደረገው የመንግስት እንቅስቃሴ የእኛ አገር አቋራጭ አገልጋይ ነው፡፡ ግዳጅ እንሰማራለን የቀሩ ወንድሞቻችንም አሉ መስዋዕት የሆኑ በረዳት፣በገንዘብ ተቀባይ በሾፌር ይህን ያህል ተብሎ የሚነገር አይደለም፡፡ ለዚህ ሁሉ ቤተሰቦች እንኳን ለማርዳት ጥያቄዎችን ብንጠይቅ እናንተን አይመለከታችሁም እኛው በወረዳና ቀበሌ ደረጃ እናረዳለን እናንተ ምን አገባችሁ ተብለናል፡፡››
እንደ አቶ ተካ ደበሌ ገለፃም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በአሽከርካሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው እገታም የማህበሩን አቅም ፈትኗል ሲሉ ይናገራሉ፡፡
‹‹አብዝሃኛው እገታ የሚፈፀመው በእኛ በህዝብ ማመላለሻ መኪኖች ላይ ነው፡፡ በጎጃም በር በርካታ ጊዜ ታግተዋል፡፡ በጥይት ተመተው ያመለጡም አሉ፤ የሚሞቱም አሉ፤ ምንም አቅም የለንም፤ ማህበሩ እራሱ እየተንገዳገደ ቢሮውን መምራት አልቻለም፡፡››
በትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር አማካኝነት የተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብርም በተለያዩ የግዳጅ አጋጣሚዎች ህይወታቸውን ያጡ አሽከርካሪዎችን ቤተሰቦችን ለመደገፍ የታሰበ በመሆኑ ቃል የተገቡ ልገሳዎች ተሰብስበው ሲጠናቀቁ ለቤተሰቦቻቸው ለማድረስ እንደሚሰራ አቶ መሳይ ኃ/ማርያም የማህበሩ ፀሀፊ ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ የአሽከርካሪዎች ደህንነት ከእኛ በላይ በመሆኑ መንግስት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ባይ ናቸው፡፡
‹‹የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ቴሌቶን ገቢ በከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማህበር አካውን የገባ በመሆኑ የእኛ ድርሻ ሲደርሰን የተመዘገቡ አሉ በአካል ለእነሱ ለማድረስ እንሰራለን፡፡ አገር አቋራጭ አውቶቡስ ሾፌር የግል ተቀጣሪ ነው ያው ክስተት ስለሆነ አሁን የመጣብን በሽታ ይታገታል ይሄዳል በእኛ በኩል ከመንግስት በላይ ምንም የምናደርገው ነገር የለም መንግስትም ይህንን ነገር ስሚያውቅ እኛም የሚደርሱትን ነገር ሪፖርት እናደርጋለን፡፡ መንግስትም ጉዳዩን ማቅለል እና ማርገብ ነው የሚገባው፤ እኛ ምንም አቅም ስለሌለን እያዘንን ብቻ ነው ዝም የምንለው፡፡››
ኢሳያስ ገላው
ኂሩት መለ
ነጋሽ መሐመድ

#ገቢ #የህዝብ

ኢትዮጵያ ዉስጥ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ዉስጥ ለሚሰሩ በቂ ትኩረት አልተሰጠም»July 4, 2025 by Azeb Tadesse Hahnበኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ያሉ ሰራተኞች ከመንግስት እና ከክልል ...
04/07/2025

ኢትዮጵያ ዉስጥ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ዉስጥ ለሚሰሩ በቂ ትኩረት አልተሰጠም»
July 4, 2025 by Azeb Tadesse Hahn
በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ያሉ ሰራተኞች ከመንግስት እና ከክልል ባለስልጣናት በቂ ትኩረት እያገኙ እንዳልሆነ አቶ ግፋወሰን ተናግረዋል። በእነዚህ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ያሉ ሠራተኞች በወር ከ26 እስከ 30 ዶላር ያገኛሉ። ሰባት ወይም ስምንት ሠራተኞች በትናንሽ ክፍሎች ተከራይተዉ በጋራ ይኖራሉ። አብዛኛዎቹ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይደርስባቸዋል።
«ኢትዮጵያ ዉስጥ ለሰራተኞች በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ዉስጥ ለሚሰሩ በቂ ትኩረት አልተሰጠም»
«ኢትዮጵያ ዉስጥ ለመንግሥት ሰራተኞች ዝቅተኛ የደሞወዝ ወለል አለ። ግን ለግል ባለሃብቶች የንግድ ተቋም ዝቅተኛ የደሞወዝ ወለል የለም። በሕግ ደረጃ ይፋ እንደተነገረዉ፤ 2019 ዓ.ም. በወጣዉ አዲሱ የሥራ አዋጅ መሰረት ዝቅተኛ የደምወዝ ወለል ቦርድ ተዋቅሮ ይወሰናል የሚል ነገር ነበር። ሆኖም ግን ላለፉት ስድስት ዓመታት እስካሁን፤ ቦርድ አልተቋቋመም ዝቅተኛ የደሞዝ ወለልም አልተሰራም። ስለዚህ ያ በሌለበት ሁኔታ ባለሃብቱ በፈለገበት የወለል መጠን ሰራተኛን መቅጠር ይችላል ማለት ነዉ። » አቶ ግፋወሰን ማርቆስ
በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ከመንግስት እና ከክልል ባለስልጣናት በቂ ትኩረት እያገኙ እንዳልሆነ አቶ ግፋወሰን ተናግረዋል። በእነዚህ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ያሉ ሠራተኞች በወር ከ26 እስከ 30 ዶላር ያገኛሉ። ሰባት ወይም ስምንት ሠራተኞች በትናንሽ ክፍሎች ተከራይተዉ ገባራ ይኖራሉ። አብዛኛዎቹ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይደርስባቸዋል። ሠራተኞቹ ከሚያገኙት ዝቅተኛ ደመወዝ በተጨማሪ፣ በሀገሪቱ ባለው የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ምክንያት ተቸግረዋል።
ግፋወሰን ማርቆስ በጀርመን የዶቼ ቬሌ የራድዮ ጣብያ ዋና መሥርያ ቤት በሚገኝበት በቦን ከተማ ዩንቨርስቲ ዉስጥ በልማት ምርምር ጥናት ማዕከል Center for developenet research ዉስጥ ለዶክትሪት ዲግሪ በምርምር ሥራ ላይ ይገኛሉ። ግፋወሰን ማርቆስ በተቋሙ ዉስጥ የሚያካሂደዉ ጥናት በፖለቲካ ኤኮኖሚ፤ ልማት ብሎም በኅብረተሰብ ጥናት ላይ የተኮረ ነዉ። በተለይም በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዉስጥ የሚገኙ ሠራተኞችን የኑሮ ሁኔታ ከዛም ባለፈ፤ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ ባሉት የሰራተኛ ማህበራት ላይ ጥናቱ እንደሚያተኩር አቶ ግፋወሰን ማርቆስ ተናግረዋል።
ሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ
ምስል፦ Gifawosen Markos
በወላይታ ተወልደው ወላይታ ዉስጥ ባለች ቦዲቲ በተባለች ከተማ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት ግፋወሰን ማርቆስ ፤ የመጀመርያ ዲግሪያቸው በጅማ ዩንቨርስቲ ፤ በልማት ጥናት ዘርፍ ፤ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን መጀመርያ በጀርመን ሃገር በዓለም አቀፍ ፖለቲካል ኢኮኖሚ /Global Political Economy/በመቀጠል በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጀምረውት የነበረዉን በክልል እና የአካባቢ ልማት ጥናት Regional and local development studies የማስትሪት ዲግሪ ትምህርታቸውን አጠናቀው ሁለተኛ የማስትሪት ዲግሪ ባለቤት ናቸው። በወልቂቴ ዩንቨርስቲ መምህርም ነበሩ።
አቶ ግፋወሰን ማርቆስ ለሰጡን ቃለምልልስ በዶቼ ቬለ ስም በማመስገን ፤ ሙሉዉን ጥንቅር እንዲያደምጡ እንጋብዛለን።
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ

የታላቁ የህዳሴ ግድብ  ምረቃ እና የግብፅ የተቃውሞ መግለጫየኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በህዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የሱዳን፣ የግብፅና የሌሎች የዓባይ ተፋሰስ ሐገራት መሪዎች እንዲ...
04/07/2025

የታላቁ የህዳሴ ግድብ ምረቃ እና የግብፅ የተቃውሞ መግለጫ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በህዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የሱዳን፣ የግብፅና የሌሎች የዓባይ ተፋሰስ ሐገራት መሪዎች እንዲገኙ ያቀረቡትን ግብዣ ግብፅ ዉድቅ አደረገችዉ።ጠቅላይ ሚንስትሩ ትናንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሳ ጥያቄ በሰጡት መልስና ማብራሪያ ከአስር አመታት በላይ ግንባታ ላይ የቆየው ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በመጭው መስከረም ወር እንደሚመረቅ አስታዉቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ የግብፅ፣ የሱዳን እና የሌሎች የአባይ ተፋሰስ ሀገራት መሪዎችን ጋብዘዋልም።
«በመስከረም ወር መጨረሻ ዝናቡ እየቀነሰ ሲሄድ ግድቡን የምንከፍተው ሲሆን ለግብፅ እና ሱዳን እንዲሁም ለሌሎች የአባይ ተፋሰስ ሀገራት ጥሪውን በፓርላማ ፊት ማድረስ እፈልጋለሁ» ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ።
ግብፅ ግን ኢትዮጵያ የምትወስደውን «የአንድ-ወገን» ብላ የጠራችውን ተግባር ውድቅ አድርጋለች።
የግብፅ የውሃ ሀብት ሚኒስትር ሃኒ ሰዊላም ከዲፕሎማቶች ጋር ባደረጉት ስብሰባ፤ በታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ኪሳራ ፤ በኢትዮጵያ ልማትን ለማምጣት የሚደረገውን ማንኛውንም ሙከራ ግብፅ በፍፁም አትቀበልም ብለዋል።
ሰዊላም፤ ኢትዮጵያ ከእውነተኛ ድርድር ይልቅ፤ የአንድ ወገን ፍላጎትን ለመጫን እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።
https://www.facebook.com/share/p/1DuRZ6qmBS/

ሩሲያ ለታሊባን አገዛዝ እውቅና የሰጠች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆነችአፍጋኒስታንን የሚመራው  የታሊባን መንግስት እንደገለፀው ሩሲያ አገዛዙን የተቀበለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች ።የታሊባን መንግ...
04/07/2025

ሩሲያ ለታሊባን አገዛዝ እውቅና የሰጠች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆነች
አፍጋኒስታንን የሚመራው የታሊባን መንግስት እንደገለፀው ሩሲያ አገዛዙን የተቀበለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች ።የታሊባን መንግስት ሩሲያ “ብልህ ውሳኔ” በማድረግ ለሌሎች አርአያ ሆናለች ብሏል።
ታሊባን መንግስት ይህንን የገለፀው የአፍጋኒስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር ካን ሙታኪ እና በአፍጋኒስታን የሩሲያ አምባሳደር ዲሚትሪ ዚርኖቭን ትናንት ሐሙስ በካቡል ተገናኝተው ከመከሩ በኋላ ነው።
የአፍጋኒስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር ካን ሙታኪ ሩሲያ ከሁሉም ሀገሮች ቀድማ ለታሊባን መንግስት የሰጠችውን እውቅና «ደፋር ውሳኔ» እና ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ሲሉ በኤክስ ገፃቸው በተለጠፉት ቪዲዮ ተናግረዋል።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩላቸው «የአፍጋኒስታን እስላማዊ ኢሚሬትስ ይፋዊ እውቅና የመስጠቱ ተግባር በአገሮቻችን መካከል በተለያዩ መስኮች ውጤታማ የሁለትዮሽ ትብብር እንደሚያሳድግ እናምናለን»በማለት በቴሌግራም ገፃቸው ፅፈዋል ።
ሞስኮ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማሳደግ እና ካቡል የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውርን እና ሽብርተኝነትን ለመግታት የምታደርገውን ጥረት ማገዝ እንደምትፈልግም ገልፃለች።
https://www.facebook.com/share/p/19R3n1HeCt/

ጠቅላይ ሚንስትሩ ለሐይማኖት አባቶች ያደጉት ጥሪየትግራይ ክልል ወደ ጦርነት እንዳይገባ የሃይማኖት አባቶች ሚናቸውን እንዲወጡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐብይ አህመድ  ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ...
04/07/2025

ጠቅላይ ሚንስትሩ ለሐይማኖት አባቶች ያደጉት ጥሪ
የትግራይ ክልል ወደ ጦርነት እንዳይገባ የሃይማኖት አባቶች ሚናቸውን እንዲወጡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐብይ አህመድ ጠይቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት፣ የመንግሥትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ትናንት ሐሙስ፣ ሰኔ 26/2017 ዓ.ም. ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ እና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።
«የትግራይ ሕዝብ በፍጹም ጦርነት አይፈልግም» ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ ነገር ግን በተሳሳተ ስሌት ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ አሉ ሲሉ ተደምጠዋል።
እነዚህ በስም ያልጠቀሷቸው አካላት ጦርነት መክፈት የሚፈልጉት የዓለምን ሁኔታ እና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ ፣ መንግሥት በተለያዩ ኃይሎች ተወጥሯል በሚል እንዲሁም አጋዥ ሀገራት አሉ ብለው በማሰብ መሆኑን ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልፀዋል።
ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህ አካሄድ የተሳሳተ መሆኑን ገልፀው፤ ችግሮችን በውይይት እና በንግግር መፍታት እንደሚገባ ገልፀዋል።ለዚህም የሐይማኖት አባቶች ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

29/06/2025

የሰኔ 22 ቀን2017 የዓለም ዜና

· በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች በሺሕዎች የሚቆጠሩ
ነዋሪዎች የተሳተፉባቸው መንግሥትን የሚደግፉ ሰልፎች ሲካሔዱ ዋሉ። ዛሬ እሁድ የተካሔዱት ሰልፎች ሰላምን ለመደገፍ እና ጽንፈኝነትንለማውገዝ ያለሙ እንደሆኑ የክልሉ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
·
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ “ቁልፍ የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ አለመሆን” እና “በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚደርሰውን ጫና” አወገዘ። አራት ፓርቲዎችን በአባልነት ያቀፈው መድረክ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምኅዳር “በከፍተኛ ሁኔታ መጥበብ” የዴሞክራሲን ጉዞ ከሚያደናቅፉ ተግዳሮቶች አንዱ እንደሆነ አስታውቋል።
· የዩጋንዳ ፕሬዝደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በሚቀጥለው
ዓመት በሚካሔደው ምርጫ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ። ፕሬዝደንቱ በድጋሚ መወዳደር የሚፈልጉት ዩጋንዳን ወደ 500 ቢሊዮን ዶላር ኢኮኖሚ ለማሳደደግ እንደሆነ ገልጸዋል።
· እስራኤል ለ12 ቀናት የዘለቀውን ውጊያ የገታውን የተኩስ አቁም ታከብራለች የሚል ዕምነት እንደሌላት ኢራን ሥጋቷን ገለጸች። የተባበሩት መንግሥታት የኑክሌር ተቆጣጣሪ ድርጅት ኃላፊ በበኩላቸው ኢራን በጥቂት ወራት ውስጥ ቦምብ መሥራት የሚያስችላት ዩራኒየም የማብላላት አቅም እንዳላት አስጠንቅቀዋል።
·
ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ መሬት ውስጥ የሚቀበሩ ጸረ-ሰው ፈንጂዎች መጠቀምን ከሚከለክል ዓለም አቀፍ ሥምምነት ዩክሬንን የሚያስወጣ አዋጅ በፊርማቸው አጸደቁ። አዋጁ ሥራ ላይ እንዲውል በዩክሬን ምክር ቤት መጽደቅ ይኖርበታል።
· የኢየሩሳሌም ፍርድ ቤት በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ላይ የቀረበውን የሙስና ክስ ለመመልከት ይዞት የነበረውን ቀጠሮ ሰረዘ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጠሮው ባይሰረዝ ኖሮ በመጪው ሰኞ ለመስቀለኛ ጥያቄ ፍርድ ቤት መቅረብ ነበረባቸው።
ዜናውን ለማድመጥ
የድምጽ ማዕፉን ይጫኑ፦ https://p.dw.com/p/4weuw?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ

Address

Addis Ababa
00100

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Addis Zena posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share