Mujib Amino

Mujib Amino ስለፍትህ እንጮሀለን፣ ሠላምን እንሰብካለን፣ አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!
(1)

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ክቡር ዶር ሸይኸ ሱልጣን አማን በመላዉ ሀገሪቱ ላበረከቱት የልማት ስራዎች ምስጋናና እዉቅና ተሰጣቸዉ::♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ...
13/07/2025

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ክቡር ዶር ሸይኸ ሱልጣን አማን በመላዉ ሀገሪቱ ላበረከቱት የልማት ስራዎች ምስጋናና እዉቅና ተሰጣቸዉ::
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ክቡር ዶር ሸይኸ ሱልጣን አማን በመላው ሀገሪቱ እያደረጉት ላለው የልማት ስራና በተለይም በቀቤና ልዩ ወረዳ እንዲሁም በወልቂጤና አካባቢዋ እያደረጉት ላለው ዘርፈ ብዙ የልማት ስራ ከማህበረሰቡ የምስጋና እና እውቅና ፕሮግራም በዛሬው ዕለት ተከናውኗል::

በእውቅና መድረኩ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ጨምሮ በማህበረሰቡ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ሰዎች የሚሰጠውን የሰንጋ በሬ በስጦታ መልክ ተበርክቶላቸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ክቡር ዶር ሸይኸ ሱልጣን አማን በአካባቢው ላይ አልቢር ሐሰን ኡንጀሞ የተሰኘ የጤና ማዕከል አስገንብተው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ማዕከሉን ወደ ሆስፒታል ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝን ተጠቅሷል::

“ጥንካሬያችንን በማስቀጥል በሀገር ፍቅር ስሜት መስራት አለብን”- ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️የገቢዎች ሚኒስቴ...
13/07/2025

“ጥንካሬያችንን በማስቀጥል በሀገር ፍቅር ስሜት መስራት አለብን”
- ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️

የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በ2018 በጀት ዓመት የገቢ እቅድ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በእቅድ ወይይቱ ላይ የሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች ተገኝተው የዓመታዊ የእቅድ ክፍፍል አድርገዋል፡፡

የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ የቀደመውን በጀት ዓመት እቅድ በጋራ፣ በትብብር እና በትጋት በመስራት ማሳካት መቻሉን ጠቁመው የ2018 በጀት ዓመት የገቢ እቅድን ለማሳካት በተመሳሳይ መልኩ ጥንካሬያችንን በማስቀጥል በሀገር ፍቅር ስሜት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ሥርዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ መስከረም ደበበ በበኩላቸው የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካት ከግብር ከፋዮች ጋር በቅርበት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ከክልሎች ጋር በትብብር እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እና በጋራ መሰራት ባለባቸውን ጉዳዮችን ለይቶ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አብዱራህማን ኢድ ጣሂር ዕቅዶቹን ለቅርንጫፎች ብቻ በማውረድ የሚተው ሳይሆን በቀጣይ ዕቅዱ እንዲሳካ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡

የእቅድ ክፍፍል የተደረገባቸው መስፈርቶችን በተመለከተ በሚኒስቴር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ታደሰና በስትራቴጂክ ፕላንና ፕሮጀክት ልማት ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ተሰማ በኩል ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በልዩ ልዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል፡፡ በምረቃውስነ ስርዓት ላይ የኢትዮጵያን ህልም፣ክብርና ሉዓላዊነት ለመ...
12/07/2025

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በልዩ ልዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል፡፡

በምረቃውስነ ስርዓት ላይ የኢትዮጵያን ህልም፣ክብርና ሉዓላዊነት ለመሸከም የተዘጋጀ ትውልድ መፈጠሩን የተመለከትንበት ብቻ ሳይሆን በዕውቀት በጥበብና በምርምር የተካነ ዘመናዊ ሰራዊት እየገነባን ለመሆኑም ትልቅ ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡

የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ሀገራዊ ጥቅም በታማኝነት የሚያስጠብቅ ሙያዊ ብቃቱ የተመሰከረለት ፕሮፌሽናል ሰራዊት ለመፍጠር ካስቀመጥነው ግብ አኳያም የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ እያስመዘገበ ያለው አፈፃፀም ትልቅ ተቋማዊና አገራዊ አንደምታዎች ያሉት በመሆኑ ለተመዘገበው ስኬት መላው የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡🇪🇹

የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ወሮAisha Mohammed M***a

"ወጣቱ ትውልድ ለዲኑ፣ ለሐገራዊ ሰላምና ልማት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል" ክቡር ዶ/ር ሼይኽ ሐጅ ኢብራሂም  ቱፋ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ወጣቱ ትው...
12/07/2025

"ወጣቱ ትውልድ ለዲኑ፣ ለሐገራዊ ሰላምና ልማት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል" ክቡር ዶ/ር ሼይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ

♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ወጣቱ ትውልድ ለዲኑ ለሐገራዊ ሰላምና ልማት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንትና የዑለማ ጉባዔ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር ሸይኸ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ።

በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ"ፅኑ ወጣት ለተቋም ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል::

በመድረኩ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት ክቡር ፕሬዝደንቱ ወጣቱ ለሃይማኖቱና ለሐገር ግንባታ ብቁ እንዲሆን ጠቅላይ ምክር ቤቱ አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ሊጉ ባለፉት ሶስት ዓመታት የሰራቸው በጎ ተግባራት አጠናክሮ እንዲቀጥል ክቡር ዶ/ር ሼይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ አሳስበዋል። ዓሊሞች የነብያት ወራሾች በመሆናቸው ሊጉ ከኢሊሞች ጋር በመተባበርና በመተጋገዝ እንዲሰራ አመላክተዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል በማደራጀት ዲናዊ እና ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጣ ለማስቻል እየሰራ እንደሚገኝ ፕሬዝደንቱ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር ዶር ሼይኽ ሱልጣን አማን ኤባ በበኩላቸው በወጣትነቱ ጊዜ ፈጣሪያችን አሏህ ያዘዘውን ፈፅሞ በከለከለው ታቅቦ ጊዜውን ያሳለፈ ወጣት የጀነት ትሩፋትን እንደሚጎናፀፍ ነቢያዊ ሀዲስን በማጣቀስ ወጣቱ እንዲበረታ አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ሼይኽ ሑሴን በሽር የተራጀ ወጣት ለዲኑና ለሐገሩ አዎንታዊ አስተዋፅኦ የሚያበረክት በመሆኑ ምክር ቤቱ የወጣት ሊግ ከዚህ በላቀ ውጤታማ እንዲሆን ምክር ቤቱ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ሼይኽ ሑሴን በሽር ተናግረዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በሊጉ የተከናወኑ ተግባራት በሊጉ ዋና ፀሐፊ በሆኑት አብዱልዓዚዝ አወል ለጉባዔው ተሳታፊዎች ቀርቧል።

በ2018 በጀት ዓመት የወጣቱን ሁለንተናዊ አቅም የሚያሳድጉ ተግባራትን ይበልጥ በማጠናከር ወጣቱን ተጠቃሚ ለማድረግ ሊጉ እንደሚሰራ ተገልጿል።

በ2017 በጀት አመት ለሊጉ መልካም አፈፃፀም የነበራቸውን ክፍለከተሞችና ግለሰቦችን በሊጉ እውቅና ተበርክቶላቸዋል።

12/07/2025

የአዲስአበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ 3ኛ ዓመት 2ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ከሚሊኒየም አዳራሽ

09/07/2025

የዓሊም መሪነት ፍላጎት የሚመነጨው ከስልጣን ፍቅር ሳይሆን ከተጠያቂነት ስሜት ነው።
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️

•••አንድ ዕድሜውን ሙሉ ውስብስብ የፊቅህ ትንታኔዎችንና የቁርኣን ምስጢሮችን ሲያጠና የኖረ ዓሊም፣ በዘመናዊው አስተዳደር የተቀመጠው መስፈርት ቢያንሰው ፣ይህ የዓሊሙን ድክመት ሳይሆን የስርዓቱን ክፍተትና የእይታ ማነስ ነው የሚያሳየው። ኢስላማዊውን የእውቀት ስርዓት በማኮሰስና ክፍተቶችን በማጉላት፣ መፍትሄውን በአንድ የአሰራር ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ ጠቅልሎ ለማቅረብ መሞከር ፣ ለችግሩ ከልብ ከማሰብ ይልቅ ለቀረበው የመፍትሄ ሀሳብ ድርጅታዊ ገበያ የመፍጠር ዘመቻ ያስመስለዋል።

ችግሩ የዓሊሙ አለማወቅ ሳይሆን ጥበቡን ለመጠቀም የሚያስችል ድልድይና አጋዥ መዋቅር አለመዘርጋቱ ነው። መፍትሄውም ጥበበኛውን ከደጅ ማስቀረት ሳይሆን የፅሑፍና የአስተዳደር ስራዎችን የሚያግዙለት ባለሙያዎችን በማቅረብ ጥበቡ ለህዝብ እንዲደርስ ማድረግ ነው።

ይህንን ተከትሎ የሚመጣው ሌላኛው አደገኛ አካሄድ ዑለሞች በማህበረሰቡ መሪነት ላይ ያላቸውን ድርሻና ፍላጎት እንደ ስልጣን ጥማትና ወንበር ፍቅር አድርጎ መተርጎም ነው። ይህ እጅግ አደገኛና ስር የሰደደ አንድምታ ያለው ስህተት ነው። የዓሊም መሪነት ፍላጎት የሚመነጨው ከስልጣን ፍቅር ሳይሆን ከተጠያቂነት ስሜት ነው።•••

ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም ገፅ የተወሰደ

የነብያት ውርስ በ«ዘመናዊነት» ሚዛን ስም አይዋረድም!ሐምሌ 02 ቀን 2017 ፡ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ  "ዑለማ" የሚለው ቃል በእስልምና ውስጥ ከፍተኛውን የእውቀት ደረጃ የተቆናጠጡ የማህበረ...
09/07/2025

የነብያት ውርስ በ«ዘመናዊነት» ሚዛን ስም አይዋረድም!

ሐምሌ 02 ቀን 2017 ፡ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ

"ዑለማ" የሚለው ቃል በእስልምና ውስጥ ከፍተኛውን የእውቀት ደረጃ የተቆናጠጡ የማህበረሰቡ መንፈሳዊ መምህራንና የአዕምሮ መሪዎች የሆኑትን የነብያት ወራሾች የሚገልፅ የክብር ስያሜ ነው። አንድ ዓሊም ይህንን የክብር ደረጃ ለማግኘት እንደ ቁርኣን ትርጓሜ (ተፍሲር)፣ የሐዲስ እውቀት (ኩቱበ-ሲታን ጨምሮ)፣ እስላማዊ የህግ ስርዓት (ፊቅህ)፣ የህግ መነሻ መርሆች (ኡሱለል-ፊቅህ)፣ ስነ-መለኮት (አቂዳ) እና የዓረብኛ ቋንቋ ሰዋሰው (ነህው እና ሶርፍ) ያሉትን የእውቀት ዘርፎች ጠንቅቆ ማወቅ ይጠበቅበታል። ይህ ሁሉ እውቀት ሲደመር፣ ለመሪነት የሚያበቃ ልዩ "ግርማ" ይሰጣቸዋል፤ ይህም በስልጣን የሚገኝ ጉልበት ሳይሆን ከመንፈሳዊ ብስለት የሚመነጭ ፣በሰዎች ልብ ውስጥ መተማመንንና መረጋጋትን የሚዘራ የተፈጥሮ ስበት ነው።

ከዚህም ባሻገር እነዚህ የእውቀት ዘርፎች ከዘመናዊው አለም የተፋቱ አይደሉም፤ አንድ የፊቅህ ሊቅ የህብረተሰቡን ማህበራዊ አወቃቀር (ሶሺዮሎጂ)፣ የፍትህ መርሆችን (ህግ) እና የንግድ ስርዓቶችን (ኢኮኖሚክስ) ሳይረዳ የህግ ፍርድ ሊሰጥ አይችልም። ለዚህ ደግሞ ታሪክ ራሱ ህያው ምስክር ነው፤ አለም በዘመናዊ ሳይንስ ከመራቀቋ በፊት የበራችው እንደ አል-ሑሰይን ኢብን ዐብደላህ ኢብን ሲና ባሉ በህክምናና በፍልስፍና በተራቀቁና እስካሁን በዘርፉ ማጣቀሻ (Reference) መሆን በቻሉ የኢስላም ልጆች ጥበብ ነበር፤ በሒሳብ ዘርፍ ብንመለከት አል ጀብራ እንደ ሙሐመድ ኢብን ሙሳ አል-ኸዋሪዝሚ ባሉ ሊቃውንት ተፈጥሮ ለአለም ሲበረከት ፣የስነ-ፈለክ (አስትሮኖሚ) እና የጂኦግራፊ ሳይንስ ደግሞ እንደ አቡ ረይሓን አል ቢሩኒ ባሉ ምሁራን የኢስላም ልጆች ሲመራ ነበር።

ይህ የጥበብ አመራር የሩቅ ዘመን ቅርስ ብቻም አይደለም፤ የራሳችን የኢትዮጵያ መጅሊስ እጅግ ፈታኝ በነበረ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሲመሰረት፣ ተቋሙ በፅናት እንዲቆምና ህዝበ ሙስሊሙን በአንድነት እንዲመራ ያደረገው፣ እንደ ክቡር ሸይኽ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ ያሉ አባቶች የነበራቸው የብስለት አመራርና የጥበብ ልህቀት ነው። ስለሆነም የዛሬዎቹን ዑለሞች ከዚህ የበለፀገ ታሪካዊና አዕምሯዊ ውርሳቸው ነጥሎ መመልከት ለራሱ ለእውቀት ታሪክ ጀርባን እንደመስጠት ይቆጠራል።

በማህበረሰባችን ውስጥ የሚነሱ ውይይቶች ወደ እድገት የሚያመሩ መሆናቸው የማይካድ ሀቅ ሲሆን፣ የውይይቱ ሚዛን ሲዛባና የመለኪያ መስፈርቱ ሲሰፋ ግን አቅጣጫውን ስቶ ወደ ማፍረስ ያመራል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነብያት ወራሾች በሆኑት በክቡራን ዑለሞቻችን ላይ እያተኮረ ያለው ዘመቻ ፣የዚህ የተዛባ ሚዛን ህያው ማሳያ ሆኗል። ይህ ጉዳይ የጥበብን ውቅያኖስ በወረቀት ሰርተፊኬት ለመለካት የሚደረግ አደገኛ ሙከራ ነው፤ የመንፈስን ልዕልና በአስተዳደራዊ ችሎታ ለመመዘን የሚደረግ መሰረታዊ ስህተት ነው። ይህ ዘመቻ የአስተሳሰብ ልዕልናን ሳይሆን የአመለካከት ድህነትን ይዞ የቀረበ፣ የነብያትን ውርስ የተሸከሙትን ትከሻዎች በቀላል አስተዳደራዊ መመዘኛዎች ክብደት ዝቅ ለማድረግ የሚሞክር፣ ለራሱ ለውርሱ ክብር የማይሰጥ "የተሃድሶ" ቃና ያዘለ አካሄድ ነው።

የኢትዮጵያዊ ዓሊም የእውቀት ፍለጋ ጉዞ በምቾትና በቅንጦት የተሞላ ሳይሆን በራሱ አንድ ትልቅ የህይወት ተጋድሎ ነው። ከቤተሰብ ተለይቶ ለዓመታት የሚዘልቅ የስደትና የልፋት ህይወት ሲመርጥ፣ የሚመራው የእውነት ጥማት እንጂ የሹመትና የዝና ጥማት አይደለም። በየገጠሩ ከመስጂድ መስጂድ እየተንከራተተ ፣ በዑለሞች ጉልበት ስር ተንበርክኮ፣ ሌሊቱን በብርድ፣ ቀኑን ሀሩር እና በርሃብ አለንጋ ተገርፎ እያሳለፈ የሚገነባው የእውቀት ግንብ በቀላል ንፋስ የሚናድ አይደለም። ይህ በላብና በእንባ የተገነባ የህይወት ልምድ፣ ከገፆች የሚነበብ እውቀት ብቻ ሳይሆን የህይወትን ትርጉም፣ የሰውን ልጅ ስቃይና የማህበረሰብን የልብ ትርታ የሚያስተምር ጥልቅ የህይወት ዩኒቨርሲቲ ነው።

ይህንን እድሜ ልክ የፈጀ የመንፈስና የአዕምሮ ተጋድሎ በዘመናዊው ቢሮክራሲ በተቀመጡ የአማርኛ ፊደል አጣጣልና የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ወረቀት ጋር ማነፃፀሩ የችግሩን ምንጭ መሳት ነው። አንድ ዕድሜውን ሙሉ ውስብስብ የፊቅህ ትንታኔዎችንና የቁርኣን ምስጢሮችን ሲያጠና የኖረ ዓሊም፣ በዘመናዊው አስተዳደር የተቀመጠው መስፈርት ቢያንሰው ፣ይህ የዓሊሙን ድክመት ሳይሆን የስርዓቱን ክፍተትና የእይታ ማነስ ነው የሚያሳየው። ኢስላማዊውን የእውቀት ስርዓት በማኮሰስና ክፍተቶችን በማጉላት፣ መፍትሄውን በአንድ የአሰራር ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ ጠቅልሎ ለማቅረብ መሞከር፣ ለችግሩ ከልብ ከማሰብ ይልቅ ለቀረበው የመፍትሄ ሀሳብ ድርጅታዊ ገበያ የመፍጠር ዘመቻ ያስመስለዋል። ችግሩ የዓሊሙ አለማወቅ ሳይሆን ጥበቡን ለመጠቀም የሚያስችል ድልድይና አጋዥ መዋቅር አለመዘርጋቱ ነው። መፍትሄውም ጥበበኛውን ከደጅ ማስቀረት ሳይሆን የፅሑፍና የአስተዳደር ስራዎችን የሚያግዙለት ባለሙያዎችን በማቅረብ ጥበቡ ለህዝብ እንዲደርስ ማድረግ ነው።

ይህንን ተከትሎ የሚመጣው ሌላኛው አደገኛ አካሄድ ዑለሞች በማህበረሰቡ መሪነት ላይ ያላቸውን ድርሻና ፍላጎት እንደ ስልጣን ጥማትና ወንበር ፍቅር አድርጎ መተርጎም ነው። ይህ እጅግ አደገኛና ስር የሰደደ አንድምታ ያለው ስህተት ነው። የዓሊም መሪነት ፍላጎት የሚመነጨው ከስልጣን ፍቅር ሳይሆን ከተጠያቂነት ስሜት ነው።

በብዙ ተጋድሎና ትግል ለተመሰረተው የኡለማ ምክር ቤትን የህዝብ ቁቡልነትን ለማሳጣት በጊዜያዊ ልዩነት «ለይስሙላ የተቋቋመ» በሚል ማኮሰስ ክፍተቱን አይሞላም።

ዑለማዎቻችን የነብያት ወራሽ እንደመሆናቸው ማህበረሰቡን በመንፈሳዊና በሞራል ጉዳዮች የመምራት አደራ እንዳለባቸው ያምናሉ። ይህንን አደራ ለመወጣት ሲንቀሳቀሱ "ስልጣን ፈላጊ" የሚል ታርጋ መለጠፍ ሚናቸውን ወደ ተራ ፖለቲካዊ ሽኩቻ ማውረድ ነው። ይህ አካሄድ እያንዳንዱን ፈትዋ በፖለቲካዊ ሚዛን እንዲለካ እያንዳንዱን ምክር በስልጣን ሽኩቻ መነፅር እንዲታይ በማድረግ የዲኑን ንፅህና ያደፈርሳል። በመጨረሻም ማህበረሰቡን ከመንፈሳዊ መሪዎቹ በመነጠል፣ ልጓም እንደሌለው ፈረስ ለፈተና ያጋልጠዋል።

በዚህ ዘመቻ ውስጥ እንደ አማራጭ የቀረበው "ዘመናዊ" የተባለው የአደረጃጀት መዋቅር ግቡ በቁጥር የሚለካ ውጤት የሆነውን የኮርፖሬት ፍልስፍና ወደ ኢስላማዊ ተቋም ለማስገባት ይሞክራል። ይህን መሰል ተቋም ዋና ግብ ግን የኡማውን መንፈሳዊ አንድነትና የዲኑን ክብር ማስጠበቅ እንጂ በሪፖርት የሚለካ ቅልጥፍና አይደለም።

መፍትሄው መዋቅር አልባ መሆን ሳይሆን የራሳችንን የበለፀገ የአመራር ጥበብ መጠቀም ነው። ኢስላም በሹራ (ምክክር)፣ በአማና (ታማኝነት)፣ በዐድል (ፍትህ) ና በሒክማ (ጥበብ) ላይ የተመሰረተ የአመራር መርህ አለው። ስለዚህ ዋናው ተግባር፣ አሰራራችንን እስላማዊ ማድረግ እንጂ እስልምናችንን ኮርፖሬቲካዊ ማድረግ የለብንም። ይህ ማለት ግን ዘመናዊ የአሰራር መሳሪያዎችንና ግልፀኝነትን የሚያሰፍኑ ስልቶችን እንቃወማለን ማለት አይደለም። ይልቁንም እነዚህ መሳሪያዎች በሙሉ የኢስላማዊ መርሆቻችን ተገዥና አገልጋይ ሆነው መንፈሳዊ ግባችንን እንዲያሳኩ ማድረግ አለብን ማለት ነው።

የሚገርመውም ይህ የትችትና የመመዘኛ ሚዛን በአንድ በኩል ብቻ ያጋደለ መሆኑ ነው። ዑለሞች ዘመናዊ ትምህርት እንዲማሩ የሚጮኸው ድምፅ፣ የዘመናዊ ትምህርት ምሁራን ደግሞ በዑለማ ጉልበት ስር ተንበርክከው የዲኑን ጥልቅ እውቀት እንዲማሩ የሚጠይቅ ተመሳሳይ ጉልበት ያለው ድምፅ አያሰማም። ይህ የተዛባ አመክንዮ፣ አላማው መተጋገዝና መሞላላት ሳይሆን የዑለሞችን ተፈጥሯዊ የመሪነት ሚና ለመንጠቅ የሚደረግ ስውር ዘመቻ አካል ነው።

ይህ ማለት የህግ ባለሙያው፣ የፋይናንስ ምሁሩ፣ የሚዲያና ቴክኖሎጂ የመሳሰሉት ባለሙያዎች ሚና የላቸውም ማለት አይደለም። ልዩነቱ ያለው ስለ ሚና መኖርና አለመኖር ሳይሆን ስለ ስፍራና ቅደም ተከተል ነው። ልብና አዕምሮ በሌለበት እጅና እግር ብቻቸውን ትርጉም እንደሌላቸው ሁሉ የመሪነት ጥበብና መንፈሳዊ አቅጣጫ ከሌለ የባለሙያዎች ክህሎት ብቻውን ማህበረሰቡን ወደ ትክክለኛው መዳረሻ ሊያደርሰው አይችልም። አመራሩ የጥበብና የብስለት ሲሆን ክህሎት ደግሞ የዚያ አመራር አስፈፃሚና አጋዥ ክንፍ ይሆናል።

ስለሆነም እኛ የምንመኘው ትግል አንዱ ሌላውን የሚያሳንስበት ሳይሆን ሁሉም በቦታው የሚከበርበትን ስርዓት መገንባት ነው። የምንመኘው ተቋም የፊቅህ ሊቃውንት የሆኑት ዑለሞች ስለ አንድ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ውል ኢስላማዊ ፍርድ ከሰጡ በኋላ፣ በዘመናዊ የህግና ኢኮኖሚ ትምህርት የቀሰሙ ባለሙያዎች ደግሞ ያንን ፍርድ መሰረት አድርገው ህጋዊ ሰነዶችን የሚያዘጋጁበትን ነው፤ ዑለሞች የመንፈሳዊ ዳዕዋ አቅጣጫን ሲወስኑ፣ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ደግሞ ያንን መልዕክት በዘመኑ ቋንቋና ቴክኖሎጂ ለህዝብ የሚያደርሱበትን ስርዓት ነው። እውነተኛ ዘመናዊነት ማለት ይህ ነው፤ ጥበብን በክህሎት ማገዝና ማገልገል።

ከፊታችን ያለው አማራጭ የአሰራር ዘዴን ስለማሻሻል ሳይሆን የተቋማችንን ነፍስና የህዝባችንን አደራ ስለመጠበቅ ነው። እውነተኛ ዘመናዊነት ማለት ያለፈውን ጥበብ አውርሶ ለዛሬው ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ለነገው ተስፋ የሚሆን ማንነትን መገንባት እንጂ፣ የሌሎችን ልብስ ለብሶ እንደመራመድ አይደለም። ስለዚህ ትክክለኛው መንገድ የማህበረሰቡ ልብና አዕምሮ የሆኑትን ዑለሞች በአመራር ማዕከል ላይ እንደ ፀሀይ ማስቀመጥና የዘመኑን ክህሎት የያዙትን እንደ ብርቱ ክንፎች አድርጎ ለስኬት መብረር ነው። ከዚህ ውጪ ያለው መንገድ ስርን ቆርጦ ቅርጫፍ ላይ የሚደረግ ውይይት ከመሆኑም በላይ የነብያት ወራሾችን ከዙፋናቸው አውርዶ በተራ አስተዳዳሪዎች ለመተካት መሞከር ነው። ይህም ለማህበረሰቡ መንፈሳዊ ህልውና ፍፁም አጥፊ ነው።

በዘመናዊነት ስም የዑለማን ክብር የማኮሰስ ዘመቻ ሊቆም ይገባል!

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም
ሐምሌ 02 ቀን 2017 አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ

የፓን አፍሪካ አጋርነት፤ ለጋራ ተጠቃሚነትባለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባ...
09/07/2025

የፓን አፍሪካ አጋርነት፤ ለጋራ ተጠቃሚነት

ባለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ Prosperity Party - ብልፅግና ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር Ministry of Finance - Ethiopia ሚንስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ፣ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ወሮ ሙፈሪሃት ካሚል በተገኙበት በስኬት ተጠናቋል፡፡

መድረኩ የአፍሪካ የክህሎት ልማት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ስነ-ምህዳርን ለማሻሻል ትርጉም ያለው ምክክርና አጋርነት መፍጠር ያስቻለ እና የታለመለትን ግብ ያሳካ ነው፡፡

በመድረኩ ኢትዮጵያ ፎረሙን ወደ አህጉራዊ ጉባኤ ለማሳደግ ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ይህም ትስስርን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማላቀ እንደ አህጉር የተያዘውን ጠንካራ አቋም የሚያመላክትና የሥራ ዕድል ፈጠራ የአፍሪካ ህብረት ቋሚ የፓን አፍሪካ መድረክ ሆኖ እንዲቀጥል የሚያደርግ ነው፡፡ለሥራው ስኬት አበርክቶ የነበራችሁ አጋር ድርጅቶች፣ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

ገፃችንን ላይክ አድርጉ - Like our pageይሕ የጸና አቋሜ ነው!“ስለፍትህ እንጮሀለን፣ ሠላምን እንሰብካለን፣ አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!” We fight for justiceWe p...
09/07/2025

ገፃችንን ላይክ አድርጉ - Like our page

ይሕ የጸና አቋሜ ነው!

“ስለፍትህ እንጮሀለን፣
ሠላምን እንሰብካለን፣
አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!”

We fight for justice
We preach peace.
We seek unity and respect.

Mujib Amino

የነብያት ውርስ በ«ዘመናዊነት»  ሚዛን ስም አይዋረድም!የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም
09/07/2025

የነብያት ውርስ በ«ዘመናዊነት» ሚዛን ስም አይዋረድም!
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም

የነብያት ውርስ በ«ዘመናዊነት» ሚዛን ስም አይዋረድም!

ሐምሌ 02 ቀን 2017 ፡ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ

"ዑለማ" የሚለው ቃል በእስልምና ውስጥ ከፍተኛውን የእውቀት ደረጃ የተቆናጠጡ የማህበረሰቡ መንፈሳዊ መምህራንና የአዕምሮ መሪዎች የሆኑትን የነብያት ወራሾች የሚገልፅ የክብር ስያሜ ነው። አንድ ዓሊም ይህንን የክብር ደረጃ ለማግኘት እንደ ቁርኣን ትርጓሜ (ተፍሲር)፣ የሐዲስ እውቀት (ኩቱበ-ሲታን ጨምሮ)፣ እስላማዊ የህግ ስርዓት (ፊቅህ)፣ የህግ መነሻ መርሆች (ኡሱለል-ፊቅህ)፣ ስነ-መለኮት (አቂዳ) እና የዓረብኛ ቋንቋ ሰዋሰው (ነህው እና ሶርፍ) ያሉትን የእውቀት ዘርፎች ጠንቅቆ ማወቅ ይጠበቅበታል። ይህ ሁሉ እውቀት ሲደመር፣ ለመሪነት የሚያበቃ ልዩ "ግርማ" ይሰጣቸዋል፤ ይህም በስልጣን የሚገኝ ጉልበት ሳይሆን ከመንፈሳዊ ብስለት የሚመነጭ ፣በሰዎች ልብ ውስጥ መተማመንንና መረጋጋትን የሚዘራ የተፈጥሮ ስበት ነው።

ከዚህም ባሻገር እነዚህ የእውቀት ዘርፎች ከዘመናዊው አለም የተፋቱ አይደሉም፤ አንድ የፊቅህ ሊቅ የህብረተሰቡን ማህበራዊ አወቃቀር (ሶሺዮሎጂ)፣ የፍትህ መርሆችን (ህግ) እና የንግድ ስርዓቶችን (ኢኮኖሚክስ) ሳይረዳ የህግ ፍርድ ሊሰጥ አይችልም። ለዚህ ደግሞ ታሪክ ራሱ ህያው ምስክር ነው፤ አለም በዘመናዊ ሳይንስ ከመራቀቋ በፊት የበራችው እንደ አል-ሑሰይን ኢብን ዐብደላህ ኢብን ሲና ባሉ በህክምናና በፍልስፍና በተራቀቁና እስካሁን በዘርፉ ማጣቀሻ (Reference) መሆን በቻሉ የኢስላም ልጆች ጥበብ ነበር፤ በሒሳብ ዘርፍ ብንመለከት አል ጀብራ እንደ ሙሐመድ ኢብን ሙሳ አል-ኸዋሪዝሚ ባሉ ሊቃውንት ተፈጥሮ ለአለም ሲበረከት ፣የስነ-ፈለክ (አስትሮኖሚ) እና የጂኦግራፊ ሳይንስ ደግሞ እንደ አቡ ረይሓን አል ቢሩኒ ባሉ ምሁራን የኢስላም ልጆች ሲመራ ነበር።

ይህ የጥበብ አመራር የሩቅ ዘመን ቅርስ ብቻም አይደለም፤ የራሳችን የኢትዮጵያ መጅሊስ እጅግ ፈታኝ በነበረ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሲመሰረት፣ ተቋሙ በፅናት እንዲቆምና ህዝበ ሙስሊሙን በአንድነት እንዲመራ ያደረገው፣ እንደ ክቡር ሸይኽ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ ያሉ አባቶች የነበራቸው የብስለት አመራርና የጥበብ ልህቀት ነው። ስለሆነም የዛሬዎቹን ዑለሞች ከዚህ የበለፀገ ታሪካዊና አዕምሯዊ ውርሳቸው ነጥሎ መመልከት ለራሱ ለእውቀት ታሪክ ጀርባን እንደመስጠት ይቆጠራል።

በማህበረሰባችን ውስጥ የሚነሱ ውይይቶች ወደ እድገት የሚያመሩ መሆናቸው የማይካድ ሀቅ ሲሆን፣ የውይይቱ ሚዛን ሲዛባና የመለኪያ መስፈርቱ ሲሰፋ ግን አቅጣጫውን ስቶ ወደ ማፍረስ ያመራል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነብያት ወራሾች በሆኑት በክቡራን ዑለሞቻችን ላይ እያተኮረ ያለው ዘመቻ ፣የዚህ የተዛባ ሚዛን ህያው ማሳያ ሆኗል። ይህ ጉዳይ የጥበብን ውቅያኖስ በወረቀት ሰርተፊኬት ለመለካት የሚደረግ አደገኛ ሙከራ ነው፤ የመንፈስን ልዕልና በአስተዳደራዊ ችሎታ ለመመዘን የሚደረግ መሰረታዊ ስህተት ነው። ይህ ዘመቻ የአስተሳሰብ ልዕልናን ሳይሆን የአመለካከት ድህነትን ይዞ የቀረበ፣ የነብያትን ውርስ የተሸከሙትን ትከሻዎች በቀላል አስተዳደራዊ መመዘኛዎች ክብደት ዝቅ ለማድረግ የሚሞክር፣ ለራሱ ለውርሱ ክብር የማይሰጥ "የተሃድሶ" ቃና ያዘለ አካሄድ ነው።

የኢትዮጵያዊ ዓሊም የእውቀት ፍለጋ ጉዞ በምቾትና በቅንጦት የተሞላ ሳይሆን በራሱ አንድ ትልቅ የህይወት ተጋድሎ ነው። ከቤተሰብ ተለይቶ ለዓመታት የሚዘልቅ የስደትና የልፋት ህይወት ሲመርጥ፣ የሚመራው የእውነት ጥማት እንጂ የሹመትና የዝና ጥማት አይደለም። በየገጠሩ ከመስጂድ መስጂድ እየተንከራተተ ፣ በዑለሞች ጉልበት ስር ተንበርክኮ፣ ሌሊቱን በብርድ፣ ቀኑን ሀሩር እና በርሃብ አለንጋ ተገርፎ እያሳለፈ የሚገነባው የእውቀት ግንብ በቀላል ንፋስ የሚናድ አይደለም። ይህ በላብና በእንባ የተገነባ የህይወት ልምድ፣ ከገፆች የሚነበብ እውቀት ብቻ ሳይሆን የህይወትን ትርጉም፣ የሰውን ልጅ ስቃይና የማህበረሰብን የልብ ትርታ የሚያስተምር ጥልቅ የህይወት ዩኒቨርሲቲ ነው።

ይህንን እድሜ ልክ የፈጀ የመንፈስና የአዕምሮ ተጋድሎ በዘመናዊው ቢሮክራሲ በተቀመጡ የአማርኛ ፊደል አጣጣልና የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ወረቀት ጋር ማነፃፀሩ የችግሩን ምንጭ መሳት ነው። አንድ ዕድሜውን ሙሉ ውስብስብ የፊቅህ ትንታኔዎችንና የቁርኣን ምስጢሮችን ሲያጠና የኖረ ዓሊም፣ በዘመናዊው አስተዳደር የተቀመጠው መስፈርት ቢያንሰው ፣ይህ የዓሊሙን ድክመት ሳይሆን የስርዓቱን ክፍተትና የእይታ ማነስ ነው የሚያሳየው። ኢስላማዊውን የእውቀት ስርዓት በማኮሰስና ክፍተቶችን በማጉላት፣ መፍትሄውን በአንድ የአሰራር ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ ጠቅልሎ ለማቅረብ መሞከር፣ ለችግሩ ከልብ ከማሰብ ይልቅ ለቀረበው የመፍትሄ ሀሳብ ድርጅታዊ ገበያ የመፍጠር ዘመቻ ያስመስለዋል። ችግሩ የዓሊሙ አለማወቅ ሳይሆን ጥበቡን ለመጠቀም የሚያስችል ድልድይና አጋዥ መዋቅር አለመዘርጋቱ ነው። መፍትሄውም ጥበበኛውን ከደጅ ማስቀረት ሳይሆን የፅሑፍና የአስተዳደር ስራዎችን የሚያግዙለት ባለሙያዎችን በማቅረብ ጥበቡ ለህዝብ እንዲደርስ ማድረግ ነው።

ይህንን ተከትሎ የሚመጣው ሌላኛው አደገኛ አካሄድ ዑለሞች በማህበረሰቡ መሪነት ላይ ያላቸውን ድርሻና ፍላጎት እንደ ስልጣን ጥማትና ወንበር ፍቅር አድርጎ መተርጎም ነው። ይህ እጅግ አደገኛና ስር የሰደደ አንድምታ ያለው ስህተት ነው። የዓሊም መሪነት ፍላጎት የሚመነጨው ከስልጣን ፍቅር ሳይሆን ከተጠያቂነት ስሜት ነው።

በብዙ ተጋድሎና ትግል ለተመሰረተው የኡለማ ምክር ቤትን የህዝብ ቁቡልነትን ለማሳጣት በጊዜያዊ ልዩነት «ለይስሙላ የተቋቋመ» በሚል ማኮሰስ ክፍተቱን አይሞላም።

ዑለማዎቻችን የነብያት ወራሽ እንደመሆናቸው ማህበረሰቡን በመንፈሳዊና በሞራል ጉዳዮች የመምራት አደራ እንዳለባቸው ያምናሉ። ይህንን አደራ ለመወጣት ሲንቀሳቀሱ "ስልጣን ፈላጊ" የሚል ታርጋ መለጠፍ ሚናቸውን ወደ ተራ ፖለቲካዊ ሽኩቻ ማውረድ ነው። ይህ አካሄድ እያንዳንዱን ፈትዋ በፖለቲካዊ ሚዛን እንዲለካ እያንዳንዱን ምክር በስልጣን ሽኩቻ መነፅር እንዲታይ በማድረግ የዲኑን ንፅህና ያደፈርሳል። በመጨረሻም ማህበረሰቡን ከመንፈሳዊ መሪዎቹ በመነጠል፣ ልጓም እንደሌለው ፈረስ ለፈተና ያጋልጠዋል።

በዚህ ዘመቻ ውስጥ እንደ አማራጭ የቀረበው "ዘመናዊ" የተባለው የአደረጃጀት መዋቅር ግቡ በቁጥር የሚለካ ውጤት የሆነውን የኮርፖሬት ፍልስፍና ወደ ኢስላማዊ ተቋም ለማስገባት ይሞክራል። ይህን መሰል ተቋም ዋና ግብ ግን የኡማውን መንፈሳዊ አንድነትና የዲኑን ክብር ማስጠበቅ እንጂ በሪፖርት የሚለካ ቅልጥፍና አይደለም።

መፍትሄው መዋቅር አልባ መሆን ሳይሆን የራሳችንን የበለፀገ የአመራር ጥበብ መጠቀም ነው። ኢስላም በሹራ (ምክክር)፣ በአማና (ታማኝነት)፣ በዐድል (ፍትህ) ና በሒክማ (ጥበብ) ላይ የተመሰረተ የአመራር መርህ አለው። ስለዚህ ዋናው ተግባር፣ አሰራራችንን እስላማዊ ማድረግ እንጂ እስልምናችንን ኮርፖሬቲካዊ ማድረግ የለብንም። ይህ ማለት ግን ዘመናዊ የአሰራር መሳሪያዎችንና ግልፀኝነትን የሚያሰፍኑ ስልቶችን እንቃወማለን ማለት አይደለም። ይልቁንም እነዚህ መሳሪያዎች በሙሉ የኢስላማዊ መርሆቻችን ተገዥና አገልጋይ ሆነው መንፈሳዊ ግባችንን እንዲያሳኩ ማድረግ አለብን ማለት ነው።

የሚገርመውም ይህ የትችትና የመመዘኛ ሚዛን በአንድ በኩል ብቻ ያጋደለ መሆኑ ነው። ዑለሞች ዘመናዊ ትምህርት እንዲማሩ የሚጮኸው ድምፅ፣ የዘመናዊ ትምህርት ምሁራን ደግሞ በዑለማ ጉልበት ስር ተንበርክከው የዲኑን ጥልቅ እውቀት እንዲማሩ የሚጠይቅ ተመሳሳይ ጉልበት ያለው ድምፅ አያሰማም። ይህ የተዛባ አመክንዮ፣ አላማው መተጋገዝና መሞላላት ሳይሆን የዑለሞችን ተፈጥሯዊ የመሪነት ሚና ለመንጠቅ የሚደረግ ስውር ዘመቻ አካል ነው።

ይህ ማለት የህግ ባለሙያው፣ የፋይናንስ ምሁሩ፣ የሚዲያና ቴክኖሎጂ የመሳሰሉት ባለሙያዎች ሚና የላቸውም ማለት አይደለም። ልዩነቱ ያለው ስለ ሚና መኖርና አለመኖር ሳይሆን ስለ ስፍራና ቅደም ተከተል ነው። ልብና አዕምሮ በሌለበት እጅና እግር ብቻቸውን ትርጉም እንደሌላቸው ሁሉ የመሪነት ጥበብና መንፈሳዊ አቅጣጫ ከሌለ የባለሙያዎች ክህሎት ብቻውን ማህበረሰቡን ወደ ትክክለኛው መዳረሻ ሊያደርሰው አይችልም። አመራሩ የጥበብና የብስለት ሲሆን ክህሎት ደግሞ የዚያ አመራር አስፈፃሚና አጋዥ ክንፍ ይሆናል።

ስለሆነም እኛ የምንመኘው ትግል አንዱ ሌላውን የሚያሳንስበት ሳይሆን ሁሉም በቦታው የሚከበርበትን ስርዓት መገንባት ነው። የምንመኘው ተቋም የፊቅህ ሊቃውንት የሆኑት ዑለሞች ስለ አንድ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ውል ኢስላማዊ ፍርድ ከሰጡ በኋላ፣ በዘመናዊ የህግና ኢኮኖሚ ትምህርት የቀሰሙ ባለሙያዎች ደግሞ ያንን ፍርድ መሰረት አድርገው ህጋዊ ሰነዶችን የሚያዘጋጁበትን ነው፤ ዑለሞች የመንፈሳዊ ዳዕዋ አቅጣጫን ሲወስኑ፣ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ደግሞ ያንን መልዕክት በዘመኑ ቋንቋና ቴክኖሎጂ ለህዝብ የሚያደርሱበትን ስርዓት ነው። እውነተኛ ዘመናዊነት ማለት ይህ ነው፤ ጥበብን በክህሎት ማገዝና ማገልገል።

ከፊታችን ያለው አማራጭ የአሰራር ዘዴን ስለማሻሻል ሳይሆን የተቋማችንን ነፍስና የህዝባችንን አደራ ስለመጠበቅ ነው። እውነተኛ ዘመናዊነት ማለት ያለፈውን ጥበብ አውርሶ ለዛሬው ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ለነገው ተስፋ የሚሆን ማንነትን መገንባት እንጂ፣ የሌሎችን ልብስ ለብሶ እንደመራመድ አይደለም። ስለዚህ ትክክለኛው መንገድ የማህበረሰቡ ልብና አዕምሮ የሆኑትን ዑለሞች በአመራር ማዕከል ላይ እንደ ፀሀይ ማስቀመጥና የዘመኑን ክህሎት የያዙትን እንደ ብርቱ ክንፎች አድርጎ ለስኬት መብረር ነው። ከዚህ ውጪ ያለው መንገድ ስርን ቆርጦ ቅርጫፍ ላይ የሚደረግ ውይይት ከመሆኑም በላይ የነብያት ወራሾችን ከዙፋናቸው አውርዶ በተራ አስተዳዳሪዎች ለመተካት መሞከር ነው። ይህም ለማህበረሰቡ መንፈሳዊ ህልውና ፍፁም አጥፊ ነው።

በዘመናዊነት ስም የዑለማን ክብር የማኮሰስ ዘመቻ ሊቆም ይገባል!

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም
ሐምሌ 02 ቀን 2017 አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ

07/07/2025

ሁሉም የኀይማኖት ተቋማት በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ በአፋጣኝ የበኩላቸዉን ሚና እንዲወጡ እንገልጻለን።

Address


Telephone

+251912776721

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mujib Amino posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share