Mujib Amino

Mujib Amino ስለፍትህ እንጮሀለን፣ ሠላምን እንሰብካለን፣ አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!
(1)

የሁል ጊዜም አጋራችንና ምርጫችን AMIN General Hospital አሚን አጠቃላይ ሆስፒታል-ጤናን እናስቀድማለን! 📲8080እ ና መ ሰ ግ ና ለ ን
06/06/2025

የሁል ጊዜም አጋራችንና ምርጫችን AMIN General Hospital አሚን አጠቃላይ ሆስፒታል-ጤናን እናስቀድማለን! 📲8080
እ ና መ ሰ ግ ና ለ ን

1446ኛው የኢድ  አል አድሃ(አረፋ )በዓል አከባበር በስልጤ ወራቤ ከተማ
06/06/2025

1446ኛው የኢድ አል አድሃ(አረፋ )በዓል አከባበር በስልጤ ወራቤ ከተማ

ሀበይ አጄጄሙ አጄጄነሀበይ ለ1446ለኜይ የኢድ አል አድሀ ሙሊ ቦገሬት አጄጄነ
06/06/2025

ሀበይ አጄጄሙ አጄጄነ

ሀበይ ለ1446ለኜይ የኢድ አል አድሀ ሙሊ ቦገሬት አጄጄነ

ዒድኩም ሰዒድዒዱኩም ሙባረክ ||አብሮነት : አንድነት : አክብሮት :  ||ወ ጣ ቶ ቻ ች ን
06/06/2025

ዒድኩም ሰዒድ
ዒዱኩም ሙባረክ
||
አብሮነት : አንድነት : አክብሮት :
||
ወ ጣ ቶ ቻ ች ን

05/06/2025
05/06/2025

ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ለዓረፋ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
****************

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ለ1446ኛው የዓረፋ (ዒድ አል አድሃ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዚዳንቱ በመልካም ምኞት መልዕክታቸው፣ “ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው የዓረፋ (ዒድ አል አድሃ) በዓል አደረሳችሁ” ብለዋል።

በዓሉ የሰላም፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት እንዲሆንም ልባዊ ምኞታቸውን መግለጻቸውንም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት አስታውቋል።

05/06/2025

የኢፌዴሪ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር
ለመላው ሕዝቤ ሙስሊም እንኳን ለ1ሺህ 446ኛው የአረፋ ( ዒድ አል አድሃ ) በዓል አደረሣችሁ! አደረሠን ሲል በዓሉ የሠላም ፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል !

05/06/2025
05/06/2025

በነገው ዕለት የሚከበረው 1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ነገ ግንቦት 29 ቀን 2017 ዓ/ም በእስልምና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው 1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሚከናወነው የኢድ ሶላት ስነ ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

በመሆኑም የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁት መንገዶች ዝግ መሆናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡
በዚህም መሰረት፡-
• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ
• ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
• ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ
• ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ ለገሃር መብራት የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛ ላይ
• ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል አካባቢ
• ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ አፍሪካ ህብረት ትራክ መብራቱ መስቀለኛ ላይ
• ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ከፍተኛ ፍ/ቤትአደባባይ አካባቢ
• ከኑር ህንፃ ወደ ባልቻ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ኑር ህንፃ መስቀለኛላይ
• ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ የሚወስደው መንገድ ጨፌ ሜዳ ትራፊክ መብራት አጠገብ
• ከበርበሬ በረንዳ ወደ አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚወስደው መንገድ በርበሬ በረንዳ አካባቢ
• ከተ/ሃይማኖት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ
• ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንደሚኒየም ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሰንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ አካባቢ
• ከጌጃ ሰፈር በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ አካባቢ
• ከተ/ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ተ/ሃይማኖት አደባባይ አካባቢ
• ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ድሮ EBC የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መታጠፊያ
• ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን መስቀለኛ አካባቢ
• ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ
• ከ ንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
• ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ ፓርላማ መብራት ላይ
• ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ኮንሰን መታጠፊያ አካባቢ
• ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ ላየ የሚዘጋ ሲሆን በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዓለም ባንክ መስቀለኛ አካባቢ ከሚከበረው በዓል ጋር ተያይዞ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይደረጋሉ፡፡ በዚህም መሰረት፡-
• ከዩኒሳ አደባባይ ወደ በላይ አብ መኪና መገጣጠሚያ የሚወስደው መንገድ
• ከቱሉዲምቱ - ወደ ጨፌ ይርጋ አደባባይ እስከ ዓለም ባንክ መስቀለኛ የሚወስደው መንገድ
እንዲሁም ከፌሮ ድልድይ እስከ ዩኒሳ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከሌሊቱ 10፡00 ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ በበዓሉ ዋዜማ ከምሽት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሠዓት ማቆም የተከለከለ ሲሆን ህብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን እያስተላለፈ ለእምነቱ ተከታዮች በሙሉ በዓሉ የፍቅርና የሠላም እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”

05/06/2025

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና የአንድነት እንዲሆንላችሁ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ
ድረገጽ፦http://www.hofethiopia.gov.et/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/hofethiopian/
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/channel/
ትዊተር፦ https://twitter.com/hofethiopia
ፍሊከሪ፡-https://www.flickr.com/photos/house of the Federation of Ethiopia
አዲስ አበባ

05/06/2025

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን አስተላልፋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲያከብር በመላው ሀገራችን ከሚገኙ የፀጥታ እና ደኅንነት ኃይሎች ጋር በመተባበር ከወዲሁ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር በመግባት ተልዕኮውን በተገቢው እየተወጣ ይገኛል፡፡

ሰላም ወዳዱ የሀገራችን ሕዝብም ለሰላምና ደኅንነት እንቅፋት የሆኑ ሁኔታዎችን ለማስወገድ በሚካሄደው የፀጥታ ማስከበር ሥራ ውስጥ በባለቤትነት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ የበለጠ አጠናክሮ በመቀጠል የአካባቢያውን ሰላምና ደኅንነት የሚያደፈርሱ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት በዜጎች መተግበሪያ EFPApp እና በነፃ የስልክ መስመር 991 ጥቆማ በመስጠት፤ ለፀጥታና ደህንነት ጥምር ኃይሉ አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጥሪውን ያቀርባል።

የሀገርን እና የህዝብን ጥቅም አስቀድማችሁ በሀገራችን ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ በመወጣት ሌት ተቀን እየሠራችሁ ላላችሁ በግዳጅ ላይ ለምትገኙ የፀጥታ አካላት ላቅ ያለ ምስጋና ያቀርባል።

ለእምነቱ ተከታዮች በድጋሚ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር እና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ ከልብ ይመኛል።

ዒድ ሙባረክ!
በጀግንነት መጠበቅ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ
ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

Address

Addis Ababa

Telephone

+251912776721

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mujib Amino posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share