Aussa Insider

Aussa Insider A modern media hub bridging Afar heritage with today’s world.

የፈንገስ በሽታ ስርጭትና ምርመራ ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ የዕውቀት ሽግግር መድረክ በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደአፋር-ሰመራ፤ የካቲት 21/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከፈረንሳ...
28/02/2026

የፈንገስ በሽታ ስርጭትና ምርመራ ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ የዕውቀት ሽግግር መድረክ በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 21/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከፈረንሳዩ ሬን ዩኒቨርሲቲ (Rennes University) ጋር በመተባበር በፈንገስ በሽታዎች ስርጭት፣ በምርመራ ተግዳሮቶችና በመፍትሔዎቻቸው ዙሪያ ያተኮረ ከፍተኛ የዕውቀት ሽግግር መድረክ አዘጋጀ።

​በመድረኩ ላይ በሕክምና፣ በፓራሳይቶሎጂ እና በማይኮሎጂ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ-ጥር የሆኑት ፕሮፌሰር ዣን-ፒየር ጋንግኔክስ (Jean-Pierre Gangneux) ለተሳታፊዎች ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።

​ፕሮፌሰሩ ባቀረቡት አጠቃላይ ገለጻ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን የፈንገስ ኢንፌክሽኖች ጫና በጥልቀት መርምረዋል።

በገለጻቸውም አጽንኦት ከሰጡባቸው ነጥቦች መካከል፦
• ​የበሽታው ስርጭት (Epidemiology): በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭትና ክሊኒካዊ ተፅዕኖ።
• ​የምርመራ ተግዳሮቶች: በሽታውን ለመለየት የሚገጥሙ እንቅፋቶች።
• ​የላብራቶሪ አቅም ግንባታ: በተለይም ውስን ግብዓት ባለባቸው አካባቢዎች የላብራቶሪ አቅምን የማጠናከር እና ቅድመ መከላከል ሥርዓቶችን የመዘርጋት አስፈላጊነት እና የመሳሰሉት ይገኙበታል።

​በመድረኩ ላይ የሕክምና ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣ የጤና እና ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የላብራቶሪ ረዳቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሙያዎች አዳዲስ የምርመራ ቴክኖሎጂዎችን እና የሕክምና ዘዴዎችን ለመገንዘብ ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሯል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #አፋርክልል #አፋር #ሰመራዩኒቨርስቲ

በአፋር ክልል ባለፉት ሰባት ወራት 4.6 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰበሰበ​አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 20/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)​በአፋር ክልል ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ባለፉት ሰባት ወራት ውስጥ 4...
28/02/2026

በአፋር ክልል ባለፉት ሰባት ወራት 4.6 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰበሰበ

​አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 20/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

​በአፋር ክልል ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ባለፉት ሰባት ወራት ውስጥ 4.6 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

​የተሰበሰበው ገቢ ከዕቅዱ አንጻር 98 በመቶ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ የ51 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተጠቁሟል።

​የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል አብዱ እንደገለጹት፤ የክልሉን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ፣ የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን ለማዘመንና ከህዝቡ የሚጠበቁ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል።

​በመሆኑም በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ውስጥ ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ 4 ቢሊዮን 663 ሚሊዮን 806 ሺህ 506 ብር መሰብሰብ ተችሏል።

​አቶ አወል አብዱ አክለውም፤ የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ1.5 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው አረጋግጠዋል።

​ቢሮው በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ካቀደው 8 ቢሊዮን 261 ሚሊዮን 919 ሺህ ብር ውስጥ ቀሪውን ገቢ በሚቀጥሉት አምስት ወራት ውስጥ ለመሰብሰብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አሳስበዋል።

​በመጨረሻም ግብር መክፈል የሥልጣኔ መገለጫ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ ነጋዴዎችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ዕቅዱ እንዲሳካ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አፋርክልል #አውሳኢንሳይደር #አፋር

የኳታሩ አምባሳደር ሰዓድ ሙባረክ አልኑአይሚ ለአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ሃጂ አወል አርባ የክብር የኢፍጣር ግብዣ አደረጉ​አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 20/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)በኢትዮጵያ የኳታር...
27/02/2026

የኳታሩ አምባሳደር ሰዓድ ሙባረክ አልኑአይሚ ለአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ሃጂ አወል አርባ የክብር የኢፍጣር ግብዣ አደረጉ

አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 20/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

በኢትዮጵያ የኳታር ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ክቡር ሰዓድ ሙባረክ አልኑአይሚ ለአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት ክቡር ሃጂ አወል አርባ የክብር የኢፍጣር ግብዣ አደረጉላቸው።

​በታላቅ የክብር ስነ-ስርዓት በተከናወነው በዚህ የኢፍጣር ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ከእነዚህም መካከል፦
• ​በኢትዮጵያ የኦማን ሱልጣኔት አምባሳደር ክቡር አፍካር ቢን ናዚም አልፋሪሲ፤
• ​በኢትዮጵያ የፍልስጤም አምባሳደር ክቡር ፋሪስ አልቃብ፤
• ​የአልጀዚራ ሚዲያ አውታር የአዲስ አበባ ቢሮ ኃላፊ ክቡር መሐመድ ጣሃ ተወከል እንዲሁም ሌሎች የአረብ አገራት ዲፕሎማቶች ይገኙበታል።

​በዚሁ የክብር ግብዣ መድረክ ላይ ፕሬዝዳንት ሃጂ አወል አርባ ከአምባሳደር ሰዓድ ሙባረክ እና ከሌሎች የዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ወዳጃዊ ውይይት አካሂደዋል።

​ክቡር ፕሬዝዳንቱ ለዓለም አቀፍ አምባሳደሮች እና ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ አባላት የሚሰጡት ከፍተኛ ክብር እና ትኩረት፣ የአፋርን ህዝብ ታላቅነትና እንግዳ ተቀባይነት ባህል ከማስተዋወቅ ባለፈ የክልሉን ስም በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አፋር #አፋርክልል #አውሳኢንሳይደር

የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኃፊ አቶ ያሲን ሃቢብ ለ1447ኛው የረመዳን ፆም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ​አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 9/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)​የአፋር ክልል ጤና ቢሮ...
16/02/2026

የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኃፊ አቶ ያሲን ሃቢብ ለ1447ኛው የረመዳን ፆም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

​አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 9/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

​የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ያሲን ሀቢብ፣ 1447ኛውን ዓመተ ሂጅራ የረመዳን ፆም መግቢያን አስመልክተው ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

​ኃላፊው በመልዕክታቸው፤ የረመዳን ወር የእዝነት፣ የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የመንፈሳዊ ከፍታ ወር መሆኑን ገልጸው፤ ህዝበ ሙስሊሙ በፆሙ ወቅት መንፈሳዊ ተግባራትን ከጤና ጥበቃ መመሪያዎች ጋር አቀናጅቶ ሊተገብር እንደሚገባ አሳስበዋል።

​አቶ ያሲን ሀቢብ በፆሙ ወቅት ሊተገበሩ የሚገባቸውን የጤና መመሪያዎች በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች አሳስበዋል፦

• ​በሱሁርና በኢፍጣር ወቅት ለጤና ተስማሚ የሆኑና የተመጣጠኑ የምግብ አይነቶችን በመመገብ የሰውነትን ጉልበት መጠበቅ፤

• የሰውነት ድርቀትን ለመከላከል በቂ ውሃና ሌሎች ፈሳሽ ነገሮችን አዘውትሮ መጠጣት፤

• ለተላላፊ በሽታዎች እንዳይጋለጡ የምግብ አዘገጃጀትና የአያያዝ ጥንቃቄን በልዩ ትኩረት መተግበር፤

• ​ማንኛውም አይነት የህመም ስሜት ወይም የጤና መጓደል ሲያጋጥም ሳይዘገዩ በአቅራቢያ ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ እንዳለብን አሳስበዋል።

​በመጨረሻም ኃላፊው ይህ የተቀደሰ ወር የአንድነትና የሰላም መንፈስ ይበልጥ የሚጠናከርበት እንዲሆን በመመኘት፤ ለሁሉም የእምነቱ ተከታዮች የሰላም፣ የጤና እና የበረከት ወር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

​ረመዳን ሙባረክ!

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

የአፋር ክልል ጤና ቢሮ የረመዳንን ወር በማስመልከት፤ በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ለሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ።አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 9/2018 (አውሳ ...
16/02/2026

የአፋር ክልል ጤና ቢሮ የረመዳንን ወር በማስመልከት፤ በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ለሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ።

አፋር-ሰመራ፤ የካቲት 9/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

የአፋር ክልል ጤና ቢሮ የረመዳን ወርን ምክንያት በማድረግ በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ለሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰራተኞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ።

​መስሪያ ቤቱ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ ለሚያገለግሉ 110 ሰራተኞች ያበረከተው ይህ ድጋፍ፣ በጠቅላላው ከ800 ሺህ ብር በላይ ወጪ የተደረገበት መሆኑ ተገልጿል። ይህም ሰራተኞቹ የረመዳን ወርን ያለ ኢኮኖሚያዊ ጫና እንዲያሳልፉ ለማገዝ የታለመ ነው።

​በዕለቱ በተካሄደው የድጋፍ ርክክብ መርሃ ግብር ላይ የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዊቲካ ኖሬ እና የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ አባሂና መሐመድ አክሌ ተገኝተው ድጋፉን ለሰራተኞች አስረክበዋል።

​ኃላፊዎቹ እንደገለጹት፤ ቢሮው ከጤናው ዘርፍ ስራዎች ጎን ለጎን በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙና ድጋፍ የሚሹ ሰራተኞቹን ማህበራዊ ደህንነት መጠበቅ እና የኑሮ ጫናን የሚያቃልሉ መሰል ተግባራትን ማከናወን እንደ አንዱ ተግባሩ አድርጎ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #አፋር #አፋርክልል

03/10/2025

የአፋር ክልል የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የአመራር ለውጥ አደረገ።

አፋር-ሰመራ፤ መስከረም 23/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #አፋር #አፋርክልል

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሃጂ አወል አርባ የህዳሴ ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎችም የለውጥ አርአያ እንደሚሆን ገለጹአፋር-ሰመራ፤ መስከረም 11/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)​የአፋር ...
21/09/2025

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሃጂ አወል አርባ የህዳሴ ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎችም የለውጥ አርአያ እንደሚሆን ገለጹ

አፋር-ሰመራ፤ መስከረም 11/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

​የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሃጂ አወል አርባ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቅን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ በሌሎች የልማት ዘርፎችም ተመሳሳይ የትብብርና የመፈጸም አቅም እንደምታሳይ ገለጹ። ይህንንም የገለጹት በሰመራ ከተማ በተዘጋጀውና የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ በተካሄደው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ነው።

​በሠመራ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ ሰልፍ ላይ አቶ ሃጂ አወል አርባ፣ ግድቡ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ተሳትፎ የታየበት እና "ኢትዮጵያ የጀመረችውን የመጨረስ አቅም" ያረጋገጠበት ታሪካዊ ክስተት መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱን "ዳግማዊ አድዋ" ሲሉም የገለጹ ሲሆን፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ የብርሃንና የተስፋ ምልክት እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል። አቶ ሃጂ አወል አርባ አክለውም፣ ግድቡ የቀጠናውን ትስስር በማጠናከር የጋራ ማንነትን የገነባ ህያው ምስክር ነው።
​በሰልፉ ላይ የተገኙት የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ ሙሳ፣ የህዳሴ ግድብ የትጋትና በራስ የመተማመን መንፈስን ያሳየ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።

​በመድረኩ ላይ የተለያዩ የባህል ትርዒቶችና መልእክቶች የቀረቡ ሲሆን፣ ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ በርካታ ሰዎች ተሳትፈዋል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #አፋር #አፋርክልል #የአፋርባህል

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ፣ የክብር መኮንኖች ሹመት አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክትአፋር-ሰመራ፤ መስከረም 11/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)​የኢፌዴሪ መከላከ...
21/09/2025

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ፣ የክብር መኮንኖች ሹመት አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት

አፋር-ሰመራ፤ መስከረም 11/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

​የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሐመድ ሙሳ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አቅራቢነት እና በፕሬዚዳንት ታዬ አፀስላሴ ለተሾሙት የጦር መኮንኖች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

​ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው፣ ሹመቱ መኮንኖቹ ለሀገራቸው ላሳዩት የማይናወጥ ቁርጠኝነትና ለከፈሉት መስዋዕትነት የተሰጠ የሀገር ፍቅር ምሳሌ መሆኑን አብራርተዋል። አክለውም፣ ይህ ሹመት ያለፉትን ስኬቶች ዕውቅና ከመስጠት ባለፈ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና አንድነት ለማስጠበቅ የተጣለ ታላቅ ኃላፊነት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

​በመጨረሻም፣ ይህ ስኬት የመኮንኖቹ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቷ ኢትዮጵያ ተተኪ ለሆኑ ወጣቶች ሁሉ ኩራት እንደሆነ ሚኒስትሯ በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #አፋርክልል #አፋር #የአፋርባህል

« ፎረሙ ከተሞች ያላቸውን የኢንቨስትመንት፣ የንግድና የቱሪዝም አቅም የሚያንጸባርቁበት ነው » ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ አፋር-ሰመራ፤ መስከረም 9/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)የኢትዮጵያ ከተሞች ፎ...
19/09/2025

« ፎረሙ ከተሞች ያላቸውን የኢንቨስትመንት፣ የንግድና የቱሪዝም አቅም የሚያንጸባርቁበት ነው » ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ

አፋር-ሰመራ፤ መስከረም 9/2018 (አውሳ ኢንሳይደር)

የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ከተሞች ያላቸውን የኢንቨስትመንት፣ የንግድና የቱሪዝም አቅም የሚያንጸባርቁበት መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ከአፋር ክልል መንግስት ጋር በመተባበር በሰመራ ሎግያ ከተማ "የከተሞች እድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ሃሳብ ከህዳር 6 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው ከለውጡ ወዲህ ለከተሞች በተሰጠው ትኩረት ከተሞች በከፍተኛ ደረጃ እያደጉና እየተለወጡ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በተለይም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ እየተገነቡ ያሉ መሰረተ ልማቶች እና አጠቃላይ የልማት ስራዎች ለዜጎች ምቹ የመኖርያ አካባቢ መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።

የዚሁ አካል የሆነው የከተሞች ፎረም በኢትዮጵያ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ በየሁለት ዓመቱ ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው ዓላማውም በከተሞች መካከል የትብብር መንፈስን ማጠናከር መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ወንድማማችነትን በማጎልበት ፉክክርን ማዕከል ያደረገ የስራ ባህልን እንደሚያሳድግ ነው በመግለጫቸው ያመላከቱት።

ፎረሙ ከተሞች ያላቸውን የኢንቨስትመንት፣ የንግድና የቱሪዝም አቅም የሚያንጸባርቁበት እንደሆነም ጨምረው ገልጸዋል።

እንዲሁም ከተሞች በመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በምግብ ዋስትና እና ሌሎች መሰል ዘርፎች ልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበት እንደሆነም ጠቅሰዋል።

በመርሃ ግብሩ 150 ከተሞች ተመዝግበው የሚወክሏቸውን አካላት እንደለዩና ከ10 በላይ የንግድ ድርጅቶች እንደሚሳተፉ ሚኒስትሯ አስታውቀዋል።

በፎረሙ ኤግዚቢሽንና በተለያዩ መስኮች የተከናወኑ ጥናታዊ ፅሁፎች የሚቀርቡ ሲሆን በከተማ ልማት ፖሊሲ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግም ጠቁመዋል፡፡

በፎረሙ ከተሞች ራሳቸውን ለማሳደግ የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድ በመንደፍ ያከናወኑትን ተግባር በማወዳደር የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ ከተሞች ሽልማት እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

የከተሞችን ውበትና ፅዳት ለማስጠበቅ ከተሞች እያበረከቱት ያለው አስተዋፅኦ እንደሚፈተሽም ጠቅሰዋል።

ሚኒስትሯ አክለውም በመርሃ ግብሩ መሳተፍ የሚፈልጉ ከተሞች እና የንግድ ድርጅቶች ምዝገባቸውን እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማጠናቀቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

(መረጃው የኢዜኣ ነው)

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #ኢትዮጵያ #አፋርክልል #አፋር #የአፋርባህል

በኢትዮጵያ ሰሜን-ምስራቅ፣ ከባህር ወለል በታች በሚገኘው የአፋር ምድረ በዳ፣ የሙቀት መጠኑ እስከ 65 ዲግሪ ሴልሺየስ የሚደርስባት ይህች ምድር፣ ለሺህ ዘመናት የዘለቀውን የኢትዮጵያ የጨው ን...
14/09/2025

በኢትዮጵያ ሰሜን-ምስራቅ፣ ከባህር ወለል በታች በሚገኘው የአፋር ምድረ በዳ፣ የሙቀት መጠኑ እስከ 65 ዲግሪ ሴልሺየስ የሚደርስባት ይህች ምድር፣ ለሺህ ዘመናት የዘለቀውን የኢትዮጵያ የጨው ንግድ ማዕከል ናት። እዚህ፣ በጠራራ ፀሐይ ስር፣ የአፋር ጨው ቆራጮች በባህላዊ መሣሪያዎቻቸው ጠንካራውን የጨው ንጣፍ በመቁረጥ "አሞሌ" በመባል የሚታወቁትን (አራት ማዕዘን ቅርጽ ያላቸው ጥንታዊ የጨው ገንዘቦች) ያዘጋጃሉ። እያንዳንዱ ወደ 3 ኪሎ ግራም የሚመዝነው "አሞሌ"፣ ለዘመናት እንደ ገንዘብ ሲያገለግል ቆይቷል። ይህ የጨው ንግድ ተራ የሸቀጥ ልውውጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተሟላ የኢኮኖሚ ሥርዓት ነው። የአፋር ማህበረሰብ በላባቸው ያመረቱትን ይህን የተፈጥሮ ሀብት፣ "አርሆ" በመባል የሚታወቁት (የካራቫን ነጋዴዎች) በግመሎቻቸው ላይ በመጫን ለዘመናት የቆየውን የንግድ መስመር ይዘው ወደ ደጋማ አካባቢዎች ያደርሳሉ። ይህ የጨው ንግድ፣ የወንዶችን የጉልበት ሥራ ብቻ ሳይሆን የሴቶችንም ጉልህ ሚና ያሳያል፤ ሴቶች በመጋዘን ባለቤትነት እና በንግዱ አስተዳደር ውስጥ በመሳተፍ የዚህን ጥንታዊ የንግድ ሥርዓት ህልውና አስጠብቀዋል።

​የጨው ንግድ፣ የአፋርን ምድረ በዳ ከጥንታዊቷ የአክሱም ሥልጣኔ ጋር የሚያገናኝ ወሳኝ የደም ሥር ነበር። ኃያሉ የአክሱም መንግሥት፣ እንደ ሮምና ፋርስ ካሉ የዓለም ታላላቅ መንግሥታት ጋር የንግድ ግንኙነት ሲመሰርት፣ የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚው ዋነኛ መሰረት የነበረው ይህ የጨው ንግድ ነው። አክሱም በቀይ ባህር በኩል በምትገኘው የአዱሊስ ወደብ (የጥንቷ አክሱም ዋና የንግድ በር) አማካኝነት የዝሆን ጥርስ፣ ወርቅና እጣን የመሳሰሉ የቅንጦት ዕቃዎችን ወደ ውጭ ስትልክ፣ ለህዝቧ የዕለት ተዕለት ፍጆታ የሚውለውን ጨው ታገኝ የነበረው ከአፋር ምድር ነበር። ይህ የሚያሳየው፣ የአፋር ማህበረሰብ ለአክሱም መንግሥት የንግድ አጋር እና የኢኮኖሚው ዋልታ እንደነበር ነው።

​ዛሬም ቢሆን፣ የግመሎች ረድፍ ከአድማስ ማዶ እየታየ፣ ጥንታዊው የጨው ንግድ ህያው ሆኖ ቀጥሏል። ነገር ግን፣ ይህ ለዘመናት የቆየ ባህል በዘመናዊነት እየተፈተነ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የጭነት መኪናዎች መስፋፋትና አዳዲስ መንገዶች መገንባት፣ የካራቫን (በበረሃ አብረው የሚጓዙ የነጋዴዎችና የግመሎች ስብስብ) ንግድን እያዳከመው ይገኛል። የጭነት መኪናዎች ይህን ጉዞ ሲያቃልሉት፣ በሌላ በኩል ለዘመናት በዚህ ንግድ ላይ ጥገኛ የነበረውን የአካባቢውን ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ህይወት እየቀየሩት ነው።

​ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በአጠቃላይ የአፋር የጨው ንግድ፣ የኢትዮጵያን የጥንት ታሪክ፣ የህዝቦቿን ጥንካሬ እና የባህሏን ጥልቀት የሚናገር ህያው ሙዚየም ነው። ሆኖም፣ ይህ በዋጋ የማይተመን ታሪካዊ ውርስ በዘመናዊነትና በልማት ግፊት እንዳይጠፋ ስጋት አለ። የዚህን ጥንታዊ የንግድ ሥርዓት ባህላዊና ታሪካዊ ዋጋ በመጠበቅ ከዘመናዊው ዓለም ጋር ማጣጣም፣ የዛሬው ትውልድ ትልቅ ኃላፊነት ነው።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~

#አውሳኢንሳይደር #የአፋርባህል #አፋርክልል #አፋር #ኢትዮጵያ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aussa Insider posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share