Ethio Arsenal

Ethio Arsenal The Aim Of This Page Published Sport News, Transfer Playrs, Commentaters Opnion, Fealings And Odd News, Sport Breaking News For Public.

ሞ ሳላህ ከስሎት ጋር ባደረገው ፊት ለፊት ንግግር በኋላ ዛሬ ሜዳ እንደምገባ ታውቋል• ሳላህ በሚቀጥለው ሳምንት ለአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) ከመሄዱ በፊት በአንፊልድ በሚደረገው የብራይተን ጨ...
13/12/2025

ሞ ሳላህ ከስሎት ጋር ባደረገው ፊት ለፊት ንግግር በኋላ ዛሬ ሜዳ እንደምገባ ታውቋል

• ሳላህ በሚቀጥለው ሳምንት ለአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) ከመሄዱ በፊት በአንፊልድ በሚደረገው የብራይተን ጨዋታ የሊቨርፑል ቡድን አካል ይሆናል።

• አርኔ ስሎት ከሞ ሳላህ መመለስ ጋር ተቃውሞ እንደሌለው ጠቁሟል፣ ምክንያቱም ንግግሩ ከሰዓት በኋላ ፊት ለፊት ተካሂዷል።

ዣቢ አሎንሶ እሁድ ነጌ አላቬስን የማያሸንፍ ከሆነ ከሪያል ማድሪድ አሰልጣኝነት ይባረራል
13/12/2025

ዣቢ አሎንሶ እሁድ ነጌ አላቬስን የማያሸንፍ ከሆነ ከሪያል ማድሪድ አሰልጣኝነት ይባረራል

♦️ የአርሰናል ደጋፊ ሊያወቀው የሚገባ የአርሰናል ድንቅ መረጃ¶ ክለብ ፡ አርሰናል♦️¶የተመሰረተበት ዓመት፡- 1886 ዓ.ም¶ የክለቡ መስራች: ዴቪድ ደንስኪን¶የክለቡ ባለቤት፡ ስታን ክሮንኬ...
14/11/2025

♦️ የአርሰናል ደጋፊ ሊያወቀው የሚገባ የአርሰናል ድንቅ መረጃ

¶ ክለብ ፡ አርሰናል♦️

¶የተመሰረተበት ዓመት፡- 1886 ዓ.ም

¶ የክለቡ መስራች: ዴቪድ ደንስኪን

¶የክለቡ ባለቤት፡ ስታን ክሮንኬ

¶የክለቡ ፕሬዝዳንት፡ ሰር ጆን ቺፕስ ኬስዊክ

¶ የክለብ ቅጽል ስም፡ መድፈኛ

¶ ክለብ ስታዲየም ፡ ኤምሬትስ

¶ የክለቡ የምንግዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ፡ ቲዬሪ ሄንሪ 228 ጎሎች

¶ ለክለቡ ብዙ ጨዋታዎችን ያደረገ ተጫዋች፡ ዴቪድ ኦሊሪ 722 ጨዋታዎች

🏆የክለቡ ስኬቶች፡-¶

¶የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፡ 13 ጊዜ

¶የኤፍኤ ዋንጫ፡ 14 ጊዜ

¶የእንግሊዝ ሊግ ዋንጫ፡ 2 ጊዜ

¶የእንግሊዝ ኮሚኒቲሽልድ: 16 ጊዜ

¶የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ: 1 ጊዜ

¶ ሌላም ልጨምር....

¶ፈርጉሰን ሞክረው አልተሳካም።

¶ፔፕ ሞክሮ አልተሳካለትም።

¶ሞሪንሆ ሞክረው አልተሳካላቸውም።

¶ክሎፕ ሞክረው ነበር ጉልበቱ አለቀ አልተሳካም

¶አንቼሎቲ ስለሱ እንኳን ማሰብ አይችልም።

¶Hansi Flick በፍፁም ሊዛመድ አይችልም።

🏆ግን አንድ ሰው አደረገው አርሰን ቬንገር ይባላል

¶የማይበገር ዋንጫ

¶ ይህ ዋንጫ ለእኛ የአርሰናል ደጋፊዎች ከ UCL ይበልጣል🏆

♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
-----------------------

በየጨዋታው የማሸነፍ ሥነ-ልቦና ይዘን እንቀጥላለን:-ቡካዮ ሳካ የአርሰናሉ ወሳኝ ተጫዋች ቡካዮ ሳካ ዛሬ እንግሊዝ ከሰርቢያ ከምታደርገው የዓለም ዋንጫ  ጨዋታ አስቀድሞ ስለ ክለቡ ጉዞ በሰጠው...
13/11/2025

በየጨዋታው የማሸነፍ ሥነ-ልቦና ይዘን እንቀጥላለን:-ቡካዮ ሳካ

የአርሰናሉ ወሳኝ ተጫዋች ቡካዮ ሳካ ዛሬ እንግሊዝ ከሰርቢያ ከምታደርገው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ አስቀድሞ ስለ ክለቡ ጉዞ በሰጠው አስተያየት እኛ ስራችን ላይ ብቻ እናተኩራለን ብሏል።

ሰዎች ስለኛ የሚያወሩት ነገር እንደ አየር ሁኔታው ይቀያየራል ያለው ሳካ አሁን ስለ ዋንጫ ለማውራት ጊዜው ገና ነው ብሏል።

እኛ እያንዳንዱን ጨዋታ የማሸነፍ ሥነ-ልቦና ይዘን መቀጠል እና መጨረሻ ላይ የት እንደምንቀመጥ ማየት ነው ሲል ተጫዋቹ ሀሳቡን ሰጥቷል።

ሰዎች ከሚያወሩት ነገር ይልቅ አስፈላጊው ነገር ጥሩ የሆነ የመልበሻ ክፍላችን፣ መሠረታችን እና በራሳችን ላይ ያለን መተማመናችን ነው ሲል ተናግሯል።

የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ከ21 ዓመት በኋላ ለማንሳት ጠንካራ ጅማሮ ያደረገው አርሰናል ሊጉን በ26 ነጥብ እየመራ ይገኛል።

36 'ሰንደርላንድ 1 - 0 አርሰናል ⚽ ባላርድ
08/11/2025

36 '

ሰንደርላንድ 1 - 0 አርሰናል

⚽ ባላርድ

ሚካኤል ሜሪኖ የመድፈኞቹን የፊት መስመር እየመራ በቋሚነት ይጀምራል***************በስታዲየም ኦፍ ላይት የሚደረገው የአርሰናል እና የሰንደርላንድ  ጨዋታ 2 ሰዓት ከ30 ላይ ይጀመራል...
08/11/2025

ሚካኤል ሜሪኖ የመድፈኞቹን የፊት መስመር እየመራ በቋሚነት ይጀምራል
***************

በስታዲየም ኦፍ ላይት የሚደረገው የአርሰናል እና የሰንደርላንድ ጨዋታ 2 ሰዓት ከ30 ላይ ይጀመራል፡፡

የሁለቱም ቡድኖች ቋሚ 11 ይፋ ሲሆን ሚካኤል ሜሪኖ በቋሚነት የሚጀምር ተጫዋች ሆኗል፡፡

 -league Matches
08/11/2025

-league Matches

08/11/2025
የጋርዲዮላ አዲስ ምዕራፍ - ማንቼስተር ሲቲ ከሊቨርፑልአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ከሊቨርፑል፣ ቶተንሃም ከማንቼስተር ዩናይትድ...
08/11/2025

የጋርዲዮላ አዲስ ምዕራፍ - ማንቼስተር ሲቲ ከሊቨርፑል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ከሊቨርፑል፣ ቶተንሃም ከማንቼስተር ዩናይትድ እንዲሁም ሰንደርላንድ ከአርሰናል የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ፡፡

የፕሪሚየር ሊጉ የ11ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ቀን 9 ሰዓት ከ30 ቶተንሃም ሆትስፐር ማንቼስተር ዩናይትድን በሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጀምራል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊጉ ከቶተንሃም ጋር ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች በሦስቱ ተሸንፎ፥ ሁለቱን አቻ የተለያየ ሲሆን ማሸነፍ አልቻለም፡፡

በሌላ የዛሬ ተጠባቂ መርሐ ግብር በሁሉም ውድድሮች ባለፉት ስምንት ጨዋታዎች ምንም ግብ ያልተቆጠረበት የሊጉ መሪ አርሰናል ወደ ስታዲየም ኦፍ ላይት አቅንቶ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 በጥሩ ብቃት ላይ የሚገኘውን ሰንደርላንድ ይገጥማል፡፡

ስዊዘርላንዳዊው የቀድሞ መድፈኛ ግራኒት ዣካ የቀድሞ ክለቡን በተቃራኒ በሚገጥምበት የምሽቱ ጨዋታ የሰሜን ለንደኑ ክለብ መሪነቱን ለማጠናከር ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

ቼልሲ አሰልጣኝ ጋሪ ኦኔልን ያሰናበተውን ዎልቭስን ምሽት 5 ሰዓት ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ ያስተናግዳል፡፡

በሌሎች የዛሬ ጨዋታዎች ኤቨርተን ከፉልሃም እንዲሁም ዌስትሃም ከበርንሌይ በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ይገናኛሉ፡፡

ፕሪሚየር ሊጉ ነገ ሲቀጥል፥ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል።

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ሲቲን እየመሩ ሊቨርፑልን በሚገጥሙበት የነገ ምሽቱ ጨዋታ 1 ሺህ እና ከዚያ በላይ ጨዋታዎችን መምራት ከቻሉ አሰልጣኞች ተርታ ስማቸውን ማስፈር ይችላሉ፡፡

በዘመናዊ እግር ኳስ በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ አሰልጣኞች አንዱ የሆኑት ስፓኒያርዱ አሰልጣኝ በባርሴሎና ዋናውና 2ኛው ቡድን እንዲሁም በባየርን ሙኒክ እና ማንቼስተር ሲቲ በአሰልጣኝነት በመሯቸው 999 ጨዋታዎች 715 ያህሉን በድል ተወጥተዋል።

አሰልጣኝነትን ሲጀምሩ አንድም ቀን 1 ሺህ ጨዋታዎችን እመራለሁ የሚል ግምት ያልነበራቸው ፔፕ፥ ይህ ስኬት የተለየ ትርጉም አለው ብለዋል።

ማንቼስተር ሲቲዎች ካለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች አራቱን አሸንፈው በአንዱ ሽንፈት ያስተናገዱ ሲሆን፥ ሊቨርፑል በአንጻሩ ባለፈው ሳምንት አስቶን ቪላን በመርታት በሊጉ ከአራት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ተመልሷል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በፕሪሚየር ሊጉ እርስ በርስ ባደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል ሁለቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው፡፡

ማንቼስተር ሲቲ በአንዱ ጨዋታ ድል ሲቀናው በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል፡፡

በሌሎች የነገ ጨዋታዎች ብሬንትፎርድ ከኒውካስል፣ አስቶን ቪላ ከቦርንማውዝ፣ ክሪስታል ፓላስ ከብራይተን እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከሊድስ ዩናይትድ በተመሳሳይ 11 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ በስድስት ነጥብ ርቆ በ25 ነጥብ እየመራ ይገኛል፡፡

08/11/2025
አርቴታ ሃቨርትዝ፣ማርቲኔሊ፣ኦዴጋርድ እና ማዱዌኬ ከነገው አሰላለፍ ውጭ ስለመሆናቸው🗣ያንን አስረግጬ መናገር አልችልም ነገር ግን ከእውነታው አልራቃችሁም።ከሃገራት ጨዋታ በኋላ የተጎዱት ተጫዋቾ...
07/11/2025

አርቴታ ሃቨርትዝ፣ማርቲኔሊ፣ኦዴጋርድ እና ማዱዌኬ ከነገው አሰላለፍ ውጭ ስለመሆናቸው

🗣ያንን አስረግጬ መናገር አልችልም ነገር ግን ከእውነታው አልራቃችሁም።

ከሃገራት ጨዋታ በኋላ የተጎዱት ተጫዋቾች ስለመመለሳቸው

🗣አንዳንዶቹ አዎ። ሁሉም ይመለሱ እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም።

ያ እንዲሆን በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት ብዙ ነገሮች በትክክል መሄድ አለባቸው።

አብዛኞቹን መልሰን ለማግኘት በጣም እንቃረባለን ብዬ አስባለሁ።

ፔፕ ጋርዲዮላ በአሠልጣኝነት 1000ኛ ጨዋታውን ያደርጋል በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየርሊግ እሁድ ማንቸስተር ሲቲ ሊቨርፑልን የሚገጥምበት ጨዋታ ለጋርዲዮላ በአሠልጣኝነት 1000ኛው ሆኖ ...
07/11/2025

ፔፕ ጋርዲዮላ በአሠልጣኝነት 1000ኛ ጨዋታውን ያደርጋል

በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየርሊግ እሁድ ማንቸስተር ሲቲ ሊቨርፑልን የሚገጥምበት ጨዋታ ለጋርዲዮላ በአሠልጣኝነት 1000ኛው ሆኖ ይመዘገባል።

በዘመናዊ እግር ኳስ ከታዩና አይነ ግቡ እግር ኳስን ካስመለከቱ ውጤታማ አሠልጣኞች አንዱ የሆነው ፔፕ ጋርዲዮላ፤ ከ999 ጨዋታዎቹ 715ቱን በድል ተወጥቷል።

"የአሠልጣኝነት መንገዴ በባርሴሎና ቢ ቡድን ሲጀምር አንድ ሺህ ጨዋታዎች ላይ ስለመድረስ ለአፍታ እንኳን አስቤ አላውቅም።" ያለው ጋርዲዮላ ይህ የሆነው በጠንካራ ስራና እግር ኳስን በትክክለኛው መንገድ በመጫወት መሆኑን አንስቷል።

"እነርሱን በማሠልጠኔ እድለኝነት ይሰማኛል።" ካላቸው ባርሴሎና፣ ባየር ሙኒክ እና ማንቸስተር ሲቲ ጋር ባሳለፋቸው አስራ ስምንት ዓመታት 40 ዋንጫዎችን አንስቷል፤ ይህ ደግሞ በአማካይ በያንዳንዱ 25 ጨዋታ ዋንጫ ነበር እንደ ማለት ይሆናል።

እናም በግል፣ በሀገር፣ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሳካኋቸው ክብሮች ለብቻ የሚሆኑ አልነበሩምና፤ በእያንዳንዷ እርምጃዬ ድጋፋቸው አልተለየኝም ያላቸውን አካላት በሙሉ "አመሠግናለሁ!" ብሏል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Arsenal posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share