ቆንጆ Ethiopia

ቆንጆ Ethiopia 💚💛❤በቆንጆ Ethiopia ላይ ለሀገሪቷ ከፍታና ብልፅግና የማዕዘን ድንጋይ የሆኑ ሀሳቦች ይነሳሉ !!! ቆንጆ ኢትዮጵያን እናያለን !!

ኢትዮጵያ ውብ ሀገር ነች - የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች*******በርካታ የውጭ ሀገራት ዜጎች በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተከናወኑ የደመራ ሥነ-ሥርዓቶች ላይ ታድመዋል።በሀገር ባህል ልብስ ...
26/09/2025

ኢትዮጵያ ውብ ሀገር ነች - የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች
*******

በርካታ የውጭ ሀገራት ዜጎች በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተከናወኑ የደመራ ሥነ-ሥርዓቶች ላይ ታድመዋል።

በሀገር ባህል ልብስ ተውበው በባህር ዳር በተከበረው የደመራ በዓል ላይ የተገኙት የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች፣ የበዓሉ ትዕይንት ደስታን እንደፈጠረላቸው ለኢቢሲ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያዊያን የብዝሃ ባህሎች ባለቤት መሆናቸውን እንደተገነዘቡ አንስተው፤ ይህንን የቱሪዝም አቅም ይበልጥ መጠቀም እንደሚያስፈልግም ነው ያመላከቱት።

ባህርዳር ምቹ ነች፣ ነዋሪዎቿም እንግዳ ተቀባይ ናቸው ያሉት የውጭ ዜጎቹ ፤ በከተማዋ ጥሩ ጊዜን እያሳለፉ መሆኑን ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ በተከናወነው የደመራ በዓል ላይ የተሳተፉ የውጭ ሀገራት ዜጎች በበኩላቸው፤ የደመራ በዓሉ ደማቅ እና ቀልብን የሚስብ እንደነበርም ነው የገለፁት።

ኢትዮጵያ ውብ ሀገር መሆኗን አንስተው፤ በዩኔስኮ የተመዘገበው የበዓሉ አከባበር ልዩ ስሜት እንደፈጠረባቸውም ነው የተናገሩት።

በበዓሉ የተመለከቱት ልዩ አለባበስ፣ ትውፊት እና ሐይማኖታዊ ስርዓት እንደሳባቸው ገልጸው፤ ይህንን የቱሪዝም ሃብት ይበልጥ መጠቀም እንደሚገባም አመላክተዋል።

አዲስ አበባ እያሳየችው ያለው እድገት የሚያስገርም ነው ያሉት ጎብኚዎቹ፤ ሌሎች ጎብኚዎችም ወደኢትዮጵያ መጥተው ባህል እና ቅርሶችን እንዲጎበኙ ጥረት እናደርጋለን ብለዋል።

በተስፋሁን ደስታ እና በሜሮን ንብረት

26/09/2025
የሕዳሴ ግድብን ኃይል የማመንጨት አቅም ከ1 ሺህ 400 ወደ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት ያሳደገው የኮርቻ ግድብ *******************ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አሁን ካለበት ኃይል የ...
21/09/2025

የሕዳሴ ግድብን ኃይል የማመንጨት አቅም ከ1 ሺህ 400 ወደ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት ያሳደገው የኮርቻ ግድብ
*******************

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አሁን ካለበት ኃይል የማመንጨት አቅም ላይ እንዲደርስ ካስቻሉት መሠረታዊ ክፍሎች መካከል ኮርቻ ግድብ ዋነኛው ነው።

በሁለት ተራሮች መካከል የተገነባው የኮርቻ ግድብ ፊት ለፊቱ በጥቅጥቅ አርማታ፣ ጀርባው በዐለት የተሞላ በጥበብ እና በከፍተኛ ጥንቃቄ የተገነባ ነው።

ኮርቻ ግድብ በ15 ሚሊዮን ሜትር ኪዮብ የድንጋይ ሙሌት የተገነባ ሲሆን፣ ወደ ላይ 50 ሜትር ከፍታ ያለው፣ እንዲሁም ወደ ጎን 5.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ግዙፍ ግድብ በመሆኑ የሕዳሴ ግድቡን አጠቃላይ ከፍታ ከ90 ሜትር ወደ 145 ሜትር ከፍ አድርጎታል።

የሕዳሴ ግድብ ገፀ በረከት የሆነው የኮርቻ ግድብ የግድቡን ኃይል የማመንጨት አቅም ከ 1 ሺህ 400 ሜጋ ዋት ወደ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት አሳድጎታል።

የኮርቻ ግድቡ ሕዳሴ ከሚፈለገው የውኃ ከፍታ ላይ እንዲደርስ እና የግድቡ አጠቃላይ ውኃ የመያዝ አቅም በአምስት እጥፍ ከፍ እንዲልም አድርጓል።

የኮርቻ ግድቡ ውኃ በማያሳልፍ እና በማያሰርግ መልኩ የተሰራ ቢሆንም የውኃ ስርገትን እና የመሬት ንዝረትን ለመቆጣጠር እንዲሁም ለማጥናት የሚያስችሉ 1 ሺህ 300 ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያላቸው መሳሪያዎች ተገጥመውለታል።

የግድቡን የውኃ ስርገት ለመከታተል እና የተለያዩ ጥገናዎችን ለማከናዎን እንዲቻል ወደ ውስጥ ዘልቆ ለመግባት የሚያስችል 5 ኪሎ ሜትር የሚሆን ሰው ሠራሽ ዋሻ ያለው የውስጥ ለውስጥ መንገድም ተገንብቶለታል።

የግድቡን አጠቃላይ ውኃ የመያዝ አቅም ከ14 ቢሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ወደ 74 ቢሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ከፍ ያደረገው የኮርቻ ግድብ ውስጥ የተገነባው ዋሻ በኢትዮጵያ ካሉ ሰው ሠራሽ ዋሻዎች ግዙፉ ነው።

በሕዳሴ ግድብ የተሠሩ አጠቃላይ ሥራዎች 246 ኪሎ ሜትር ወደ ኋላ የተዘረጋ ሰው ሠራሽ ሐይቅ እንዲፈጠር ያስቻሉ ሲሆን፣ ለቱሪዝም ለዓሣ እርባታ እና ለትራንስፖርት አዳዲስ እድሎችን ይዞ መጥቷል።

በሔለን ተስፋዬ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  በቅርቡ የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ያለውን ትልቅ የቱሪዝም አቅም በማስገንዘብ ከምረቃው በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት እንደሚሆን መግለጻቸው...
20/09/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ያለውን ትልቅ የቱሪዝም አቅም በማስገንዘብ ከምረቃው በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በዚህ መነሻ ግድቡን መጎብኘት የምትፈልጉ ተቋማት፣ የጎብኚ ቡድኖች አልያም ግለሰቦች ከፊታችን ሰኞ መስከረም 12 ጀምሮ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተከታዮቹ አድራሻዎች

[email protected]

+251911516125

ወይም

[email protected]

+2519-04 05 03 22

መመዝገብ እና መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

በተዘጋጀው ልዩ የህዳሴ ጉብኝት ጥቅል የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት ሁለት በረራዎችን ወደ ጉባ በማድረግ በእያንዳንዳቸው 50 ጎብኚዎችን ያስተናግዳል።

19/09/2025

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመስከረም 9 ቀን ጀምሮ ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል።
1ኛ. ዶ/ር እዮብ ተካልኝ - የብሔራዊ ባንክ ገዥ
2ኛ. ወ/ሮ እናታለም መለስ - በሚንስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሃላፊ አድርገው ሾመዋል።

16/09/2025

#ይህ የዘመናዊት ኢትዮጵያ የትግል ታሪክ ነው !

💚💛❤ ቆንጆ Ethiopia

ከንቲባ አዳነች ብሔራዊ ድሉን ላከበረውና ጀግኖቹን ላመሰገነው የከተማዋ ነዋሪ ምስጋና አቀረቡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ብሔራዊ ድሉን ላከበረውና ብሔራዊ ጀግኖቹን ...
14/09/2025

ከንቲባ አዳነች ብሔራዊ ድሉን ላከበረውና ጀግኖቹን ላመሰገነው የከተማዋ ነዋሪ ምስጋና አቀረቡ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ብሔራዊ ድሉን ላከበረውና ብሔራዊ ጀግኖቹን ላመሰገነው የከተማዋ ነዋሪ ምስጋና አቅርበዋል።

ከንቲባዋ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የመቻል ማሳያ፣ የአይቀሬው ብልፅግናችን ማረጋገጫ ብሔራዊ ምልክት ነው ብለዋል።

በከፍተኛ የሀገር ፍቅር ስሜትና ድል አድራጊነት ወደ አደባባይ በመትመም ደስታውን ለገለጸው ብሔራዊ ድሉን ላከበረው እና ብሔራዊ ጀግኖቹን ላመሰገነው የአዲስ አበባ ነዋሪ በሙሉ ምስጋናዬን አቀርባለውም ነው ያሉት።

የመዲናዋ ነዋሪ የሌሊት ቁር እና ከባድ ዶፍ ዝናብ ሳይበግረው የዘመናት የትውልዶች ትግል ዉጤት የሆነውን ድል በጋራ አክብሯል ሲሉም አብራርተዋል።

ለዚህ ድል ከነበራችሁ ደጀንነት አንፃር ይገባቹሃል ያሉት ከንቲባዋ÷ ይህ ድል የኢትዮጵያ የመቻል ማሳያ፣ የአይቀሬው ብልፅግናችን ማረጋገጫ ብሔራዊ ምልክት ነው ማለታቸውን የከተማ አስተዳደሩ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል።

የከተማችን ነዋሪዎች ከመቀነቱ ፈቶ፣ ካለው ቆርሶ፣ የኑዛዜው አካል አድርጎ፣ በብዙ ዓለም አቀፍ ጫና ውስጥ በደምና አጥንት መስዋትነት በመገንባት ለፍፃሜ እንዲበቃ ያደረጉትን የሕዳሴ ግድብ ድል በታላቅ ድምቀት አክብሯል ሲሉም ነው የገለጹት።

በመርሐ ግብሩ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የዲፕሎማሲው ማህበረሰብ መገኘታቸውንም አውስተዋል።

በዮናስ ጌትነት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)

"ከግድቡ ወደ ወደቡ "
14/09/2025

"ከግድቡ ወደ ወደቡ "

ዮሚፍ ቀጀልቻ በአስደናቂ ተጋድሎ የብር ሜዳሊያውን ለኢትዮጵያ አስገኝቷል።እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ!ሁሉም የቡድን አባሎቻችን በውድድሩ ላይ የነበራቸው መነጋገር እጅግ አስደሳች ...
14/09/2025

ዮሚፍ ቀጀልቻ በአስደናቂ ተጋድሎ የብር ሜዳሊያውን ለኢትዮጵያ አስገኝቷል።

እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ!

ሁሉም የቡድን አባሎቻችን በውድድሩ ላይ የነበራቸው መነጋገር እጅግ አስደሳች ነው፤ ይህን ነው ምንፈልገው!!!

13/09/2025

በግብርና ላይ ትኩረት አድርጉና በኑሮ ውድነት ለሚሰቃየው ህዝቤ ድረሱለት -ሼህ መህሙድ

አንዲት ሴት እንዲህ ትላለች...ቤቴን አጽድቼ ካስተካከልኩ በኋላ ወንድሜ ደወለ...ከባለቤቴ ጋር ልንጠይቅሽ እንመጣለን ኣለኝ። ኩሽና ገባሁ ለእንግዶቸ ያለኝ ላዘጋጅ። ለመስተንግዶ ምንም አላገ...
13/09/2025

አንዲት ሴት እንዲህ ትላለች...
ቤቴን አጽድቼ ካስተካከልኩ በኋላ ወንድሜ ደወለ...ከባለቤቴ ጋር ልንጠይቅሽ እንመጣለን ኣለኝ። ኩሽና ገባሁ ለእንግዶቸ ያለኝ ላዘጋጅ። ለመስተንግዶ ምንም አላገኘሁም! አንድ ነገር ላቀርብላቸው ብፈልግ፡ ምንም ማግኘት ኣልቻልኩም ጥቂት ብርቱካን ብቻ አገኘሁ… እናም ወዲያውኑ ሁለት ብርጭቆ ቀዝቃዛ ጭማቂ አዘጋጀሁ። ወንድሜ እና ሚስቱ ሲገቡ ለመጀመሪያ ጊዜ እየጎበኘችን ያለው የወንድሜ ሚስት እናት ከሳቸው ጋር ነበረች። ሁለት ብርጭቆ ለሚስቱና እናትዋ ኣቀረብኩላቸው። ኣንድ ብርጭቆ ውሃ ደግሞ ለወንድሜ። 7up እንደምትወድ ኣቃለሁ ኣልኩት። ትንሽ ጠጣና ውሃ መሆኑን ኣወቀ። እናትየዋ እኔ 7up ነው የምፈልግ ለሆዴ ይመቸኛል እና ስጡኝ.. ትላለች። ግራ ገባኝ ደነገጥኩ … ወንድሜ እንዲህ ሲል አዳነኝ: - አዲስ ብርጭቆ ከኩሽና ኣመጣለሁ ብሎ ብርጭቆውን ይዞት ሄደ። ከዚያም የጠርሙሱ መሰበር ድምፅ ሰማን፡ እናም ተመልሶ መጥቶ አማቱን እንዲህ አላት... የሚያሳዝነው ከኔ ወድቆ ብርጭቆውን ተሰበረ.. ግን ምንም አይደለም ሌላ ላመጣሽ ወደ ግሮሰሪ እሄዳለሁ... ኣላት። አማቹ አያስፈልግም አለች... ሲወጡ ወንድሜ ሲሰናበተኝ፡ አቅፎ በእጄ ገንዘብ አስጨበጠኝና እና እንዲህ አለኝ: ​​-ከኩሽናው 7up ማጽዳት እንዳትረሺ፡ ጉንዳኖችን እንዳያመጣ! ብሎ በፈገግታ እና በፍቅር ተሰናበተኝ..። ራስሺን ተንከባከቢ ኣለኝ። በዚህ መንገድ... ወንድሜ ጭንቀቴንና ጉድለቴን ሸፈነልኝ.. ስሜቴን ጠበቀልኝ..
ወንድማማችነት እንዲህ መሆን ኣለበት
የደም ትስስር...
#ሼር 💚💚💚

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቆንጆ Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share