Dagu Tube - ዳጉ ቲዩብ

Dagu Tube - ዳጉ ቲዩብ Midia / News Company

የእናት ባንክ " እማዬ " ቅርንጫፍ ስራ ጀመረ ።     👉 ይህን ምክንያት በማድረግ ለ10 ቀናት የሚቆይ ውድድር ይፋ አድርጓል ።**************************************...
21/03/2025

የእናት ባንክ " እማዬ " ቅርንጫፍ ስራ ጀመረ ።
👉 ይህን ምክንያት በማድረግ ለ10 ቀናት የሚቆይ ውድድር ይፋ አድርጓል ።
***************************************************
" እናት ባንክ " ከ11 ዓመት በፊት የገንዘብ አቅምን ከማሳደግና የግል ሀብትን ከመጨመር ያለፈ ራዕይ ባላቸው 11 እንስት ባለሀብቶች የተቋቋመ ባንክ መሆኑ ይታወቃል ። ባለ ራዕዮቹ ከዓላማቸው ስያሜያቸውን አወጡ ፤ " እናት ባንክ " ሲሉ ። ልክ እንደ እናት ያሉ ተግባራትን ሲያከናውኑ ቆይተዋል ። እንደ መደበኛ ባንክ ለሁሉም ዜጋ እኩል ፣ በተለይ ደግሞ የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና የአቅም ውስንነት ሊቀርፉ የሚችሉ አማራጮችን በመተግበር ሴቶች ኢኮኖሚው ጉልህ ተሳትፎና ድርሻ እንዲኖራቸው ሲያደርጉ ቆይተዋል ።

እናት ባንክ የድካማቸውን ያህል ያልተነገረላቸውን ብዙሃን ኢትዮጵያውያን እናቶችን የሚወክል "እማዬ" የተሰኘ ቅርንጫፍ በይፋ ከፈተ። በመላ ሃገሪቱ ይሄንን "እማዬ" ቅርንጫፍን ሳይጨምር 206 ቅርንጫፎች ያሉት እናት ባንክ ከአሁን ቀደም በአዲስ አበባ የሚገኙ ቅርንጫፎቹን ለሃገርና ለወገን የጎላ አስተዋጽዖ ያደረጉ ኢትዮጵያውያንና ጥቂትም ኢትዮጵያን ወዳድ የውጭ ሀገር እንስቶች ስም ሲሰይም ቆይቷል። አሁን ደግሞ በአይነቱ እጅግ የተለየና በአገልግሎቱም ከባንክ አገልግሎቶች የተሻገሩ ተግባራት የሚከወንበት ቅርንጫፉን " እማዬ ቅርንጫፍ " በሚል ስያሜ ትናንት በይፋ ከፍቷል። ይህ ቅርንጫፍ ለልጆቻቸው ሕይወታቸውን የሰጡ ፣ በጎ አርአያ የሆኑ ፣ እድሜያቸውን ሁሉ ፣ ሕይወታቸውን ሁሉ ለልጆቻቸው ሰጥተው ታሪክ ላልመዘገባቸው ፣ ስም ላልተሰጣቸው ፣ በመልክና በግብር ተለይተው " እገሊት " ተብለው ስም ላልወጣላቸው ለሁላችንም እናቶች ማስታወሻ እንዲሆን ነው " እማዬ ቅርንጫፍ " የተከፈተውና ትናንት ስራ የጀመረው ።

የቅርንጫፍ ባንኩን ስራ መጀመር ምክንያት በማድረግ ትናንት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተገለጸው በተለይ " እማዬ ቅርንጫፍ " ን ምክንያት በማድረግ ካሁን ቀደም ባንኩ ለመላው ደንበኞቹ አውጥቶት መላው ደንበኞቹን ሲያወዳድርበት የነበረው " ለእናቴ " የጽሑፍ እና " የዓመቱ ድንቅ እናት " የጽሑፍ ወይም የድምጽ ወይም የምስል ውድድር ለ10ቀናት ብቻ ከዛሬ አርብ የካቲት 12/17 እስከ መጪው ቅዳሜ የካቲት 20/17 11:00 ሰዓት ድረስ የሚቆይ ውድድር አዘጋጅቷል ። ለውድድሩ የሚላኩት ጽሑፎች በአዲስ አበባ ፒያሳ አቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ ሐውልት አጠገብ የቀድሞው ኢትዮጵያ ሬዲዮ ወይም ብዙሀን መገናኛ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አዲሱ ( ከአወሊያ ት/ቤት ፊትለፊት ) ህንጻ ምድር ቤት በአካል እንዲሁም ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚገኙ ተወዳዳሪዎች በአቅራቢያቸው የሚገኙ የእናት ባንክ ቅርንጫፎች በአካል ቀርበው ማስረከብ ይችላሉ ።

የውድድሩን መስፈርቶች ከታች ባለው ሊንክ ያገኙታል ።

https://www.facebook.com/share/14yYe9kf1h/

"እንዳለሁ አበራለሁ"የተሰኘ መፅሀፍ በአሜሪካን ሃገር ተመረቀ::************************************************* በደራሲ ማክዳ አርሺ Shining As I am በ...
26/02/2025

"እንዳለሁ አበራለሁ"የተሰኘ መፅሀፍ በአሜሪካን ሃገር ተመረቀ::
*************************************************
በደራሲ ማክዳ አርሺ Shining As I am በእንግሊዝኛ ግጥም ተፅፎ በታገል ሰይፉወደ አማረኛ የተተረጎመው ይኸው "እንዳለሁ አበራለሁ" የተሰኘው መፅሃፍ February 23,2025 በአሜሪካን ሃገር ሲልቨር ስኘሪንግ ሜሪላንድ ቬተራንስ ፕላዛ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ተመርቋል::

"እንዳለሁ አበራለሁ" ለልጆች ኦቲዝም ምን እንደሆነ በቀላል ቋንቋ የሚያስረዳ ሲሆን ታሪኩ አንድ የኦቲዝም ተጠቂ የሆነ ልጅ ቀኑን ሙሉ የሚገጥመውን ነገር የሚገልፅበት ሲሆን በልዩነት ውስጥ ያለን ውበት አጉልቶ ያሳያል፡፡ ልጆችንም ትዕግስትን ሌሎችን መቀበልን እና ርህራሄን ያስተምራል ተብሏል፡፡

በምርቃቱ ላይ የመፅሃፉ ደራሲ ማክዳ አርሺ ኦቲስቲክ ልጆች አለምን የሚገነዘቡበት መንገድ ልዩ ነው ያሉ ሲሆን: ሆኖም በሃገራችን እንደሚታሰበው ኦቲዝም “ እብደት” ወይም “ እርግማን” ሳይሆን በተፈጥሮ የሚከሰት ሰዎች ከማያስትውሉት አነስተኛ የባህሪ ልዩነት አንስቶ፤ እጅግ በጣም ከፍተኛ እገዛና እርዳታ የሚያስፈልገው የአዕምሮ እድገት ልዩነት መሆኑን ተገንዝቦ ልጆቹ የፈጣሪ ስጦታ መሆናቸውን አምኖ መቀበል ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ፡፡ ይህን ልዩ መሆናቸውን እስከ ዛሬ በቅጡ አልተረዳነውም ነው ያሉት ማክዳ :: ብዙ ወላጆች ከማህበረሰብ የሚደርስባቸው መገለልና እነሱም ስለ ህመሙ በቂ መረጃ ስለ ማይኖራቸው ለከፍተኛ ስቃይና እንግልት ይዳረጋሉ ብለዋል::
ኑሮአቸውን በሃገረ አሜሪካ ያደረጉት ማክዳ አርሺ ከዚህ ቀደም የአለም መብራቶች የተሰኘ የልጆች መፅሃፍ ደራሲ ሲሆኑ በዚሁ መፅሃፍ moms choice award የተሰኘ አሜሪካን ሃገር የሚገኝ ሽልማትን ጨምሮ የአምስት ሽልማቶች አሸናፊ መሆናቸው ይታወሳል::
"እንዳለሁ አበራለሁ" በአሁኑ ወቅት Amazon ላይ እየተሸጠ ሲሆን:: Shining As I am “ Amazon Best seller” መሆኑም የሚታወቅ ነው::

በቅርብ ጊዜ በሃገር ውስጥ ለሚገኙ አንባቢያን እንደ ይደርሳል ተብሏል::

23/02/2025
እናት ባንክ በ2017 ዓ.ም ሁለት የስነ ጽሑፍ ውድድር አዘጋጀ:: ውድድሩ ለአንድ ወር የሚቆይ ነው::*************************************************እናት ባንክ...
20/12/2024

እናት ባንክ በ2017 ዓ.ም ሁለት የስነ ጽሑፍ ውድድር አዘጋጀ:: ውድድሩ ለአንድ ወር የሚቆይ ነው::
*************************************************
እናት ባንክ ለመጀመሪያ ጊዜ “የዓመቱ ድንቅ እናት” በሚል እና ለሁለተኛ ጊዜ “ለእናቴ” በሚል ርዕስ ሀገራዊ የስነ ጽሑፍ ውድድርን በይፋ ማስጀመሩን አሳወቀ።

ለሀገርም ሆነ ለቤተሰብ ምሰሶ ለሆኑት የኢትዮጵያ እናቶች መታሰቢያ ይሆኑ ዘንድ ለአንድ ወር የሚቆዩና ሽልማት ያስገኛሉ የተባሉት ሁለት እናት ተኮር ውድድሮችን በይፋ መጀመሩን አስመልክቶ ዛሬ በስካይላይት ሆቴል ለጋዜጠኞች መግለጫ ተሰጥቷል።

ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው “የዓመቱ የእናት ባንክ ድንቅ እናት” የተሰኘው ውድድር፣ ተወዳዳሪዎች በአካባቢያቸው የሚያውቋቸውን ወይም የራሳቸውን እናቶች፣ በድምጽና በምስል ቀርጸው በቀጥታ በመጠቆም የሚሳተፉበት ውድድር ሲሆን ለሁለተኛ ጊዜ የሚደረገው “ለእናቴ” የተሰኘ የጽሑፍ ውድድር ደግሞ፣ በዋናነት ሁሉም ሰው ለእናቱ ያለውን ፍቅር፣ አክብሮት፣ ውለታና ምስጋና በዝርው ጽሑፍ (ግጥም ያልሆነ፣ በወግ መልክ፣ በደብዳቤ ቅርፅ ወዘተ.) የሚገልፅበትና “ለእናቴ” የሚልበት መልካም አጋጣሚ ነው።

አጠቃላይ የውድድሩ ይዘት፣ የዓመቱን የእናት ባንክ ድንቅ እናት ውድድርን አስመልክቶ ተወዳዳሪዎች፣ በጽሑፍ ማቅረብ ሳያስፈልጋቸው በቃላቸው፣ በድምጽንና በምስል ቀርጸው የሚወዳደሩበትና የዓመቱ ድንቋን እናት የሚያስመርጡበት ሂደት ነው።

“ለእናቴ” በተሰኘው የጽሑፍ ውድድር ላይም፣ ስለእናታቸው የሚያጋሩትን ፍቅርና ስሜት ዳኞች አወዳድረው የሚያበላልጡበት ሳይሆን ይልቁንም ተወዳዳሪዎች ለእናታቸው ያላቸውን ፍቅርና አክብሮት እንዴት እንደገለጹ፣ ስሜታቸውን ወደሌሎች ለማጋባት እንዴት እንደጠሩ የሚዳኙበት ዐውድ ነው።

የማወዳደሪያ መስፈርቶቹም በተመሳሳይ መልኩ የተቃኙ ሲሆኑ የቅርፅ ጉዳዮች 50 ከመቶ፣ የይዘት ጉዳዮች 50 ከመቶ፣ በድምሩ 100 ነጥብ እንዲይዙ ተደርገው ተዘጋጅተዋል፡፡

በተጨማሪም ተወዳዳሪዎች፣ ስለእናታቸው ያላቸውን ፍቅርና አክብሮት በፈለጉት መንገድ የሚገልፁባቸው ሁሉም የ “ለእናቴ” ጽሐፎች ሆኑ የዓመቱ ድንቅ እናትን የማወዳደሪያ ጥቆማዎች የኅብረተሰቡን ሥነ ምግባር፣ ሀገራዊ መልክና የሃይማኖት ልዩነት ወዘተ. ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡፡

የዓመቱን ድንቅ እናት ውድድር

ይሄ ውድድር በሕይወት ያሉ እናቶች የሚመሰገኑበት የውድድር አይነት ሲሆን ከ “ለእናቴ የፅሁፍ ውድድር” የሚለይባቸው የራሱ መመዘኛዎች አሉት፤ መወዳደሪያ መስፈርቶቹም፡-

➢ ለውድድር የሚቀርቡት ባለታሪኮች በሕይወት ያሉ እናቶች መሆን አለባቸው፤
➢ ታሪካቸው የሚነገርላቸው እናቶች ግዴታ ወላጅ እናት (የስጋ እናት) መሆን አይጠበቅባቸውም፤ ለምሳሌ አሳዳጊ ወይም ደግሞ በሰፈር አሊያም በጎረቤት ያሉ እናቶችን ታሪክ ማቅረብ ይቻላል።
➢ በዚህ ውድድር ላይ ስለ ሚያቀርቡት ታሪክ ከፈለጉ በጽሑፍ አሊያም በድምፅ ወይንም ደግሞ በቪዲዮ ሥራዎቻቸውን ቀርፀው ማቅረብ ይችላሉ።

➢ ውድድሩ የሚቆይበት ጊዜ ከታህሣሥ 14/2017 ዓ.ም. እስከ ጥር 14/2017 ዓ.ም. ይሆናል።

➢ መወዳደሪያ ሥራዎቻችሁን አቅራቢያቸሁ በሚገኙ የእናት ባንክ ቅርንጫፎች ማስረከብ የሚቻል ሲሆን በቪዲዮና በድምፅ ቅጂ ለምታስገቡ እና ውጭ ሀገር ለምትኖሩ ደግሞ በኢሜል፤ አሊያም በእናት ባንክ ኦፊሻል የፌስቡክ ገፃችን ላይ መልዕክት ማስቀመጥ ይችላሉ።

ለእናቴ የጽሑፍ ውድድር የውድድር ጽሑፎቹ መወዳደሪያ መስፈርቶች፡-

➢ በሌሎች የኅትመት እና የኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ ብዙኃን ላይ ያልቀረበ ወጥ፣ አዲስና የተለየ መሆን ይኖርበታል፤

➢ ጽሑፉ ግልጽ እና ተነባቢ እንዲሆን በኮምፒውተር ተጽፎ፣ በ12 ፎንት የፊደላት መጠን እና በ1.5 የኅዳግ መስመር መቅረብ አለበት፤

➢ በ ኤ ፎር (A4) የወረቀት ምጣኔ፣ ከሦስት /3/ ገጽ ያልበለጠ መሆን ይኖርበታል፤

➢ ለተመረጡ አሸናፊ ጽሑፎች የገንዘብ ሽልማት እና የምስክር ወረቀት ይበረከትላቸዋል፤

➢ ተወዳዳሪዎች፣ ስማቸውን እና አድራሻቸውን የጽሐፍ ሥራቸውን ባቀረቡበት ወረቀት ላይ መጻፍ የለባቸውም፤ ይልቁንም _ ሥራቸውን በሚያሽጉበት ፖስታ ላይ ብቻ መጻፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡

➢ እናት ባንክ አሸናፊ ጽሐፎችን በተለያዩ መንገዶች ሊጠቀምባቸው ይችላል፡፡

➢ የማስረከቢያ ጊዜ ከዛሬ ከታኅሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ለአንድ ወር የሚቆይ ይሆናል፡፡

➢ ተወዳዳሪዎች ጽሑፋቸውን በአቅራቢያቸው በሚገኙ የእናት ባንክ ቅርንጫፎች በአካል በመገኘት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

የውድድሩ መዝጊያ በተመለከተ የተወሰኑ የውድድሩ ተሳታፊዎች፣ የውድድሩ አሸናፊዎች፣ ጥሪ የሚደረግላቸው እንግዶች ባሉበት በታላቅ ድምቀት የሚደረግ ሲሆን በዕለቱም ለአሸናፊዎቹ ተወዳዳሪዎች የተዘጋጁላቸው ሽልማቶች ይበረከቱላቸዋል፡፡

ከ " ምን ሆኛለሁ ? " መታተም በኋላ የሚወለዱ ልጆች እድለኞች ናቸው ።👉 አንድ ሰው በሕይወት ዘመኑ ቢያንስ አንድ ጊዜ " ምን ሆኛለሁ ? " ን የማንበብ ግዴታ አለበት ። **********...
29/10/2024

ከ " ምን ሆኛለሁ ? " መታተም በኋላ የሚወለዱ ልጆች እድለኞች ናቸው ።
👉 አንድ ሰው በሕይወት ዘመኑ ቢያንስ አንድ ጊዜ " ምን ሆኛለሁ ? " ን የማንበብ ግዴታ አለበት ።
****************************************************
" ምን ሆኛለሁ ? " በቅጡ እንኳን የ3 ወር እድሜ የለውም ። ልጅነትና ልጅ ማሳደግ ደግሞ ከሰው ልጅ መፈጠር ጀምሮ የነበረ ነው ። አሁንም የተፈጠረ ተዐምር የለም ። የተጨመረ ግን አለ ። " ምን ሆኛለሁ ? " ራስን በማወቅ ፣ ሌሎችን በመረዳት ፣ ልጆችን በተሟላ ስነልቦና በማሳደግ ረገድ አንድ ተጨማሪና ጠቃሚ መጽሐፍ ነው ። መጽሐፉን የሚያነቡ እጅግ የሚበዙቱ " ብዙ ቦታ ላይ ልጅነቴንና አስተዳደጌን አገኘሁበት " ሲሉ ይደመጣሉ ። በልጅነታቸው በማወቅም ይሁን ባለማወቅ አስተዳደጋቸው ላይ የተፈጠረው ስህተትና በደል አድገውና ልጅ አፍርተውም እየመጣ እንደሚያስቸግራቸው እንደተረዱ የሚገልጹ ብዙዎች ናቸው ።

መጽሐፉን ያነበቡ ሰዎች ይህን ያገኛሉ ። የራሳቸውን ገደላማ መንገድ ሲያዩ ልጆቻቸውን በዚያ እንዳይሄዱ ያደርጋሉ ። መቸም ለልጆቻችን የተሻለውንና ምርጡን ነው የምንሰጣቸው ። ራሳችን የመጣንበትን መንገድ ተመልሰን ለማየት ፣ ለልጆቻችን ከእኛ የተሻለ ዓለም ለመፍጠር ምርጡ መጽሐፍ " ምን ሆኛለሁ ? " ነው ።እውነት ከልቤ የሚሰማኝ እንደዚህ ነው ። በዚህ ድፍረት የምነግራችሁ ጥቅሙን ከማንም በፊት እኔ ስላየሁትና መጽሐፉን ባነበቡት ሰዎች ዘንድ " ተሳስተሀል " ስለማልባል ነው ። ካነበቡት ብዙዎቹም ( ቢያንስ በሰማሁትና ባነበብኩት ደረጃ ) ይህ እምነት ስላላቸው ነው ። ለራሴ አጣጥሜው የጣፈጠኝን ነው የምጋብዛችሁ ።

" ምን ሆኛለሁ ? " ን በመረዳት አንብበን ልጆቻችንን እንዳፈተተን ልናሳድግ አንችልም ። ልጆቻችንን በቃላት ዱላ ልንቀጣም አንችልም ። አንዳንድ ወዳጆቼ " ' ምን ሆኛለሁ ? ' ን ካነበብኩ በኋላ ልጆቼን እንደ ቀድሞው ፣ ደስ እንዳለኝ መናገር አቃተኝ " ብለውኛል ። እርግጥ ነው " ምን ሆኛለሁ ? " ከአዋቂም ፣ ከልጆቻችንም ጋር ላለን ግንኙነት አዲስ መስመር ያሳያል ። ለእኔ በግል እንደ ቀድሞው ለፍርድ እንዳልቸኩል አድርጎኛል ። ማንም ሰው ምንም ሲያደርግ ውሳኔው የአሁን ይምሰል እንጂ መብላላቱ ግን ከመጣበትና ከተሰራበት ማንነቱ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል አድርጎኛል ። ትዕግሥት ዋልተንጉሥም ትሁን ሌሎቹ የስነልቦና ባለሙያዎች ሁሉም ማንነታችን የአስተዳደጋችን ውጤት ብቻ ነው አይሉም ። ይሁን እንጂ ትልቁ ማንነታችን ምሥጢሩ ልጅነታችን ጋ መሆኑም አይካድም ።

አሁን ያለውን ማንነታችንን ለማረቅ ሞክረን ፣ ሞክረን ያቃተን ጊዜ የለም ? " ደጋግሜ ላለማድረግ እሞክራለሁ ፤ ግን ያቅተኛል " የምንለው አጉል ልማድ የለንም ? ልጅነታችን ሲፈተሽ እዚያ ይገኛል ። ወይም የመገኘት እድሉ የሰፋ ነው ። እኔ በራሴም ፣ በሌሎችም አጋጥሞኛል ። ነገሩ ረቂቅም ፣ ድንቅም ነው ። " አልፏል " ያልነው ልጅነት አያልፍም ። አብሮን ይኖራል ። እንዲህ ያሉ መጻሕፍት በእኛ ሀገር ፣ በእኛው ቋንቋ ፣ በራሳችን ሰው ችግራችን የሚፈታበት መጽሐፍ እምብዛም አያጋጥምም ። አሁን " ምን ሆኛለሁ ? " አለ ። ሌሎችም ይኖራሉ ። በማውቀው ደረጃ አንድ ሰው በሕይወት ዘመኑ ቢያንስ አንድ ጊዜ " ምን ሆኛለሁ ? " ን የማንበብ ግዴታ አለበት ። መጽሐፉን ከየትም አግኝቶ ያንብበው ። አሁን እያደጉ ያሉና ነገ የሚመጡ ልጆች ወላጆቻቸው ከፈቀዱ እድለኞች ናቸው ። " ምን ሆኛለሁ ? " ምርጥና ጠቃሚ መጽሐፍ ገበያው ላይ አለላቸው ።

Dereje Haile  " ' ምን ሆኛለሁ ? ' መጽሐፍ ለ ' ምን ሆኛለሁ ? '  ጥያቄዬ መልስ አግኝቼበታለሁ " ይላል ።*******************************************...
15/10/2024

Dereje Haile " ' ምን ሆኛለሁ ? ' መጽሐፍ ለ ' ምን ሆኛለሁ ? ' ጥያቄዬ መልስ አግኝቼበታለሁ " ይላል ።
***************************************************
ትዕግሥት ዋልተንጉሥ መማሯ ብቻ ሳይሆን ፣ በትምህርቷ ያመጣችው ዕውቀት ብቻም ሳይሆን በተፈጥሮ በታደለችው ከቤተሰብ በወረሰችው ግብረገብ ተንተርሳ ለበርካታ ዓመታት የሰዎችን ችግሮች ያለመታከት እና ያለመቦዘን በማዳመጥ የመፍትሔ መስመር በማበጀት እስካሁን ድረስ በመቆየቷ ዕውነትም 'ትዕግሥት ' ያሰኛታል። ይህንን የህይወት ተሞክዋን በዕርቅ ማዕድም በተለያዩ አጋጣሚዎችም ታሪኮቹን አድምጣ ምስጢራዊነቱን ጠብቃ የሰዎች ህይወት ከመበላሸት ወደ ደህና ሁናቴ እንዲለወጥ ላደረገችው አስተዋጽኦ እያመሰገንኩ እነዚህን ታሪኮች በጥሞና አዳምጦ ጊዜ ወስዶ ወረቀት ላይ ከሽኖ ወደ እኛ የሰጠን የቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ትዕግሥት ደግሞ የበለጠ እንዳደንቀው አድርጎኛል ። እነዚህ ሁለት ሰዎች የሰሩት መጽሐፍ ካሁን ቀደም በራሴ አጋጥመውኝ " ምን ሆኛለሁ ? ምን ሆኜ ነው ይህን ያደረኩት ? ለምን ይህን አደረግሁ ? " ለምላቸው የውስጥ ጥያቄዎቼ መልስ አግኝቼበታለሁ ። ስራዬ ኮሜዲ ይሁን እንጂ ሕይወቴ የማንም ሰው ሕይወት ነው ። ስታም ሀዘንም አለበት ። ጥያቄም መልስም አለበት ። " ምን ሆኛለሁ ? " እሱን ሁሉ የዳሰሰልኝ መጽሐፍ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ።

"ምን ሆኛለሁ ?" መፅሐፍ እያንዳንዱ ቤት ሊኖር የሚገባው መፅሐፍ ነው።ይህ ማለት ራሳችን ተምረንበት ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም የምናስተምርበት ፣ ከእንግዲህ ሽማግሌ ፣ ከእንግዲህ የነብስ አባት የማያስፈልግበት ይህን መፅሐፍ አንብቦ ብቻ የህይወትን አቅጣጫ መሠረት የሚያሲዙበት መፅሐፍ ነው። በዚህ መፅሐፍ ውሰጥ የተጠቀሱት ታሪኮች በሙሉ የእያንዳንዳችንን በር ያንኳኩ ሆነው እናገኛቸዋለን ።

ስለዚህ ይህን መፅሐፍ በማንበብ ምንም እንኳን በቤታችን ውስጥ ችግር ያልተፈጠረ ሰዎች ካለን እንዳይፈጠር ይሄ አጋዥ ይሆነናል። የተፈጠረም ከሆነ ደግሞ ሦስተኛ ወገን ሳይገባ ራሳችን ተነጋግረን የምንፈታበትን መንገድ ያስቀምጣል ። የልጆችን አስተዳደግ በቅጡ ያሳውቃል ።ልጆችን ያለተፅዕኖ ፣ ያለ ተቆጭነት ምንም የህይወት ጫና ሳይኖርባቸው እንዲያድጉ ይመክራል ። ይህ መጽሐፍ ልጆቻችንን በእንክብካቤ የሚያሳድግልን መልካም ሞግዚት ነው ።

ይህ መፅሐፍ አንዴ ብቻ አይነበብም። በወር አንዴ ሊከለስ ይገባዋል ።በዓመት አንዴ ጊዜ ለስንተኛ ጊዜም ቢሆን በጥሞና ሊነበብና ቆም ተብል ስለ ራሳችን ሊያሳስበን ይገባል ። ስለዚህ በምንም አይነት ማንም ቢመጣ የማናውሰው አንድ መጽሐፍ በቤታችን ሊኖር ግድ ነው ማለት ነው ። ብቻ ግን ፈፅሞ ከማንበብ መታቀብ የሌለብን መፅሐፍ ነው " ምን ሆኛለሁ ? " ። ይህ ህይወት እስካለ ድረስ የሚቀጥል ነው። ቤተሰብ ባይኖረን እንኳን ቢያንስ እኛ አለን ። ወዳጆቻችን አሉ ።

የመንጃ ፈቃድ ለማውጣት የምናነበው መፅሐፍ በተግባር መኪና ይዘን ስናሽከረክር እንደሚጠቅመን ሁሉ ይሄም በህይወት ባለን ጊዜ ፣ ትዳር ለመመስረት ለሚያስቡ ማስተማሪያ ፣ በትዳር ውስጥ ላሉ ችግሮች እንዳይፈጠሩ ቀድሞ ማንቂያ ፣ ችግር ውስጥ ላሉ ደግሞ እንዴት መፍታት እንዳለባቸው መንገድ መሳያ ሲሆን በዕውነት በዕውነት ሊነበብ እያንዳንዱ ሰው እጅ ሊገኝ የሚገባው መፅሐፍ ነው። "ምን ሆኛለሁ ?"

በዕውነትም ተምሬበታለሁ ።አውቄበታለሁ።አይደለም ለራሴ ለሌላውም ትምህርት እንደሚሰጥ ተረድቼበታለሁ።
ትዕግሥትም ቴዎድሮስም ልትመሰገኑ ይገባል ።
ስንት ቤት እንዳከማችሁ ቤት ይቁጠረው ።
እንደነዚህ ዓይነት ሰዎችን ያብዛልን ።
አበቃሁ።

ደረጀ ሀይሌ(ኮሜዲያን )
26/1/2017

" የ ' ምን ሆኛለሁ ? ' ፕሮሞሽን በዛ ለሚሉ መልሴ " ኮካኮላ ለምን ይተዋወቃል ? " የሚል ነው ።*****************************************************  ...
14/10/2024

" የ ' ምን ሆኛለሁ ? ' ፕሮሞሽን በዛ ለሚሉ መልሴ " ኮካኮላ ለምን ይተዋወቃል ? " የሚል ነው ።
*****************************************************
የወቅቱ አነጋጋሪ መጽሐፍ የሆነው " ምን ሆኛለሁ ? " መጽሐፍ ገና በህትመት ላይ ያለውንና ታትሞም ተሸጦ ያላለቀውን ጨምሮ 19,000 ኮፒ ነው የታተመው ። ለ120 ሚሊዮን ሕዝብ ፣ ሌላው ቀርቶ ከ10 ሚሊዮን ለማያንሰው የአዲስ አበባ / ሸገር ነዋሪ 19,000 ነው የታተመው ። ምንም እዚህ ግባ የማይባል ቁጥር ነው ። 100,000 ኮፒ እንኳን ለዚህ ሕዝብ መጣኝ ቁጥር አይደለም ። በእኛ በአዘጋጆቹ እምነት ሽያጩ ገና መጀመሩ እንጂ የሚበቃው አይደለም ። በተለይ መጽሐፉ ካለው ማህበረሰባዊ ፋይዳ አንጻር ገና ብዙ ጩኸትና ፕሮሞሽን ያስፈልገዋል ። ፕሮሞሽኑ የበዛ ለሚመስላቸው የምላቸው " እስከዛሬ ኮካኮላን ያልጠጣውና ጣዕሙን የማያውቅ የለም ። ለዓመታት ግን እየተዋወቀ ይገኛል ። ኮካኮላ የሚተዋወቀው ለጠጣውና ጣዕሙን ለማያውቀው ነው ። የእኛ ' ኮካኮላ ' ግን ገና ጣዕሙ ያልተቀመሰ ነው ። ለምን ፈሳሹ ኮካኮላ እየተዋወቀ የሚነበበው በዛባችሁ ? " ነው ።

ፕሮሞሽኑን የተጋነነ አድርገው የሚወስዱም እንደዚሁ አሉ ። ከእነዚህ እጅግ የሚበዙቱ መጽሐፉን ያላነበቡ ናቸው ። እንዲህ ያለ ትግል ነው የገጠመን ። ያላየኸውንና ያላወቅከውን " ተጋነነ " ለማለት መነሻው ምን ይሆን ? በአጋጣሚ ሳላየው ቀርቼ ካልሆነ አንድም ሰው " ምን ሆኛለሁ ? " ን አንብቦ " ራሴን ብዙ ቦታ ላይ አገኘሁት " ያላለ የለም ። እንደውም የሚበዙቱ " እንዴት ነው ይህ መጽሐፍ በየመ/ቤቱና ት/ቤቱ የሚከፋፈለው ? " የሚል ጥያቄ የሚያቀርቡ ናቸው ። በየቀኑ በትንሹ ከ3 - 5 የሚሆኑ አንባቢያን በእጅ ስልኬ እየደወሉ ፣ መጽሐፉን ያነበቡና በግል የማውቃቸው ብዙዎቹ " ቲጂን እንዴት ማግኘት እችላለሁ ? ' ቴራፒ ' ማግኘት እፈልጋለሁ ። " የሚሉ ናቸው ። በቀጥታ በ 0921333331 የሚደውሉና አገልግሎቱን ለማግኘት ይጠይቃሉ ። መጽሐፉ ከሰው ልጅ ሕይወት የላቀ ዓላማ የለውም ። አንባቢያን በተለያዩ መጻሕፍት ላይ የተለያዩ አስተያየቶች ይኖራቸዋል ። " ምን ሆኛለሁ ? " ላይ ግን ከመገረም የወረደ አስተያየት አልገጠመኝም ።

ከበደል በረከትን መቁጠር ስለሚሻል እንጂ መጽሐፉን ያነበቡና ተሰሚነት ያላቸው ሰዎች ለምን ምስክርነታቸውን እንዳልሰጡ ይገርመኛል ። ዝም የሚባል ጉዳይ አይደለም " ምን ሆኛለሁ ? " ውስጥ ያለው ። ተዐምር አይደለም ፤ በውስጣችን ያለውን ተዐምር ግን ያሳየናል ። በቀናነት ለተነሳ ይህን መጽሐፍ አንብቦ " አንብቤው ጠቅሞኛል ። እናንተም አንብቡት " አለማለት አይቻልም ፤ ከአዘጋጆቹ ከአንዱ/ዷ ወይም ከሁለቱ ጋር ጠብ ቢኖራችሁም እንኳ ። ስራው " እኔን የጠቀመኝን ያህል ሌሎችንም ይጥቀም " የሚያስብል ነው ። ጉዳዩ ከ Tigist Waltenigus እና Tewodros Teklearegay ውጭ ነው ። የራስ ጉዳይ ነው ። የህብረተሰብ ጉዳይ ነው ። ስለ " ምን ሆኛለሁ ? " ደጋግሜ ስነግራችሁ ብዙ ቢሸጥ አዘጋጆቹ ከምናገኘው የገንዘብ ጥቅም አንጻር ብቻ አይደለም ። ካሁን ቀደም 6 መጻሕፍት ሳሳትም መች ይህን አልኩ ? በእርግጥ " ምን ሆኛለሁ ? " በይዘቱ የተለየና እያንዳንዳችን ቤት መግባት ያለበት መጽሐፍ ነው ። ይህን ያስባለኝ / " ያነበቡስ እንዴት ሳይመሰክሩ ቀሩ ? " ያስባለኝ እኔ ለራሴ ያገኘሁበት ጥቅም ነው ።

" ምን ሆኛለሁ ? " ካነበብኩ በኋላ ( ብጽፈውም ደጋግሞ ማንበብ አለውና ) ካመጣልኝ ለውጥ ጥቂቶቹ ፦
********************************************************

👉 ስለ ራሴ እንድመረምርና እንድረዳ ረዳኝ ።

👉 በዙሪያዬ ስላሉ ወዳጆቼን በጥልቀት እንድገነዘብ አገዘኝ ። ወዳጆቼ የሚያደርጉትን ሁሉ የሚያደርጉት ወደውና ፈቅደው ብቻ እንዳልሆነ እንዳስብ ረዳኝ ። አሁን በሰው ባህሪ ጉዳይ ለውሳኔ አልቸኩልም ። ብችል መረዳት እሞክራለሁ ።

👉 የሆነውና የምናደርገው ሁሉ ድንገተኛና በዚያው ቅጽበት የወሰነው ብቻ እንዳልሆነ ፣ የመጨረሻው ውሳኔያችን የሂደት ውጤት እንደሆነ ፣ ሂደቱ ደግሞ ምንጩ ከልጅነታችን እንደሚቀዳ እንዳስብ ጠቅሞኛል ።

👉 የሰው ልጅ ከራሱ ይልቅ የአስተዳደጉ ውጤት እንደሆነ ፣ ሰውን አሁን ባለውና ባደረገው ብቻ መመዘን እንደማይቻል እንድነቃ አድርጎኛል ።

👉 የሰውን ማንነት ከአንድ አቅጣጫ ( ከዛሬ ማንነቱ ) አንጻር ብቻ እንዳላይ ረድቶኛል ። አንድ ሰው አንድ ብቻ እንዳልሆነ ፣ የብዙ ሰዎች ውቅር እንደሆነ እንዳስብ አግዞኛል ።

👉 በግሌ ማድረግ እየፈለግሁ የማላደርጋቸው ፣ ማድረግ ሳልፈልግ ደግሞ የማደርጋቸውና ለውስጤ ጥያቄ የሚሆኑብኝን ብዙ ግራ አጋቢ ጠባያትን የሆኑት ለምን እንደሆኑ ፣ ያልሆኑትም ለምን እንዳልሆኑ እንዳውቅ ፣ ባላውቅ እንኳ አጨንቁሬ እንዳስብ እድል ሰጥቶኛል ።

🔴 እናንተስ " ምን ሆኛለሁ ? " ን በማንበባችሁ ምን አግኝታችኋል⁉️

ልቀት ኮሌጅ ለክቡር ዶክተር ተስፋዬ አበበ እና ለአርቲስት ግሩም ኤርሚያስ የክብር ዕውቅና ሽልማት አበረከተ።***************************************************ኮ...
12/10/2024

ልቀት ኮሌጅ ለክቡር ዶክተር ተስፋዬ አበበ እና ለአርቲስት ግሩም ኤርሚያስ የክብር ዕውቅና ሽልማት አበረከተ።
***************************************************
ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 500 ተማሪዎች አስመርቋል።

ልቀት ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪና በደረጃ አራት ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ጥቅምት 02 ቀን 2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።

ኮሌጁ በቢዝነስ እና ኪነ ጥበብ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለት በቢዝነስ ዘርፍ ማለትም በአካውንቲንግ፣በማኔጅመንት፣ ማርኬቲንግ እና ሂዩማን ሪሶርስ ማይኔጅመንት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል።
እንዲሁም በኪነጥበብ የሙያ ዘርፍ የፊልም አሰራርና አመራር ጥበብ፣ ፊልም ፕሮዳክሽን፣ ሲኒማቶግራፊ እና ትያትር ጥበባት የትምህርት መስኮች በብቃት ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዕለቱ አስመርቋል።
ልቀት ኮሌጅ በዘንድሮው አመት በጥቅሉ 500 ተማሪዎችን አሰልጥኖ በሶስተኛ ዙር አስመርቋል።

በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይም በኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ዘርፍ ውስጥ የላቀ አሻራቸውን በጉልህ ላሳረፉት ወጣቱ ተዋናይ አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ እና የክቡር ዶክተር ተስፋዬ አበበ የክብር ዕውቅና ሽልማት አበርክቷል።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተከተል ዮሃንስን ጨምሮ ታዋቂ የኪነጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።

ልቀት ኮሌጅ በኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን በተለያዩ የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ አግኝቶ በማስተማር ላይ የሚገኝ ተቋም ሲሆን ለባህል እና ኪነጥበብ ሙያዎች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በሀገራችን የፊልም ጥበብ ትምህርት ከዲፕሎማ ጀምሮ እስከ መጀመሪያ ዲግሪ የሚያሰለጥን የመጀመሪያው እና ብቸኛው ኮሌጅ ነው።

ልቀት ኮሌጅ ለ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ጀምረናል።ይምጡ የረጅም ዓመት የስራና የማስተማር ልምድ ባላቸው መምህራን ይማሩ!!
22/09/2024

ልቀት ኮሌጅ ለ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ጀምረናል።

ይምጡ የረጅም ዓመት የስራና የማስተማር ልምድ ባላቸው መምህራን ይማሩ!!

Seife Kibebetsehay Ketema ስለ " ምን ሆኛለሁ ? " የገለጸው******************************************************        ይህ መፅሐፍ እን...
11/09/2024

Seife Kibebetsehay Ketema ስለ " ምን ሆኛለሁ ? " የገለጸው
******************************************************
ይህ መፅሐፍ እንደማህበረሠብ ሊተኩርበት ይገባል መምህራን የሀይማኖት አባቶች በማንኛውም መንገድ ቢያንሰ ትንሸ ትኩረት ሊሠጡት ይገባል ። ቀደም ሲል የተፈጠረብኝ ሕክምና ወሰጄ ከእንደገና መፅሐፋን ካየሁ በሆላ ችግሩችን ሙሉ በሙሉ ለውጦኛል አመሠግናለሁ ።

ማሳሰቢያ ከጎፋ ዞን****************በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በጎርፍ አደጋ ለተፈናቀሉና ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የድጋፍ ማሰባሰቢያ በዞኑ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ...
24/07/2024

ማሳሰቢያ ከጎፋ ዞን
****************
በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በጎርፍ አደጋ ለተፈናቀሉና ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የድጋፍ ማሰባሰቢያ በዞኑ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት ይፋ የተደረገው መሆኑን ይታወቃል ሆኖም አንዳንድ ግለሰቦች አካውንት ከፍተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተደርሶበታል ከዞኑ እውቅና ውጪ እንደሆኑ ህብረተሰቡ እንዲያውቅ ተብሏል።

በዞኑ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት ማቋቋሚያ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000511561276

Address

Addis Ababa
30261ADDISABABA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dagu Tube - ዳጉ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share