Fana tv fans

Fana tv fans ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎችን በታማኝነት ያገኛሉ !

" ክልከላው በተለምዶ  #ኩርቱ ፌስታልን ጨምሮ በተለያየ ዲዛይን የተሰሩና በቀላሉ በስብሰው ከአፈር ጋር የማይዋሃዱ ፌስታሎችን ያካትታል " - የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣንለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም...
08/02/2026

" ክልከላው በተለምዶ #ኩርቱ ፌስታልን ጨምሮ በተለያየ ዲዛይን የተሰሩና በቀላሉ በስብሰው ከአፈር ጋር የማይዋሃዱ ፌስታሎችን ያካትታል " - የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን

ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም የሚከለክለው አዋጅ ካሳለፍነው ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

ህብረተሰቡ ጋር ግርታን የፈጠረው አንዱ ጉዳይ በአዋጁ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የተከለከሉ የፕላስቲክ ከረጢቶች የትኞቹ ናቸው ? የሚለው ነው።

በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የከተማ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ክትትል ዴስክ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ዓለሙ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን (ኤፍኤምሲ) በዚህ ጉዳይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

" በአዋጁ የተከለከሉት የፕላስቲክ ከረጢቶች በተለምዶ #ፌስታል ተብለው የሚጠሩት ናቸው፡፡

እነዚህ ፕላስቲኮችም አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ ውለው በቀጥታ የሚወገዱ ሲሆኑ በመልሶ ዑደትም ጥቅም ላይ አይውሉም።

በዚህም መሰረት ክልከላው በተለምዶ ኩርቱ በሚል ስያሜ የሚታወቀውን ፌስታል ጨምሮ በተለያየ ዲዛይን የተሰሩና በቀላሉ በስብሰው ከአፈር ጋር የማይዋሃዱ የፕላስቲክ ከረጢቶች ወይም ፌስታሎችን ያካትታል " ብለዋል።

፦ ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በተለይ በቲክቶክ " ትንሹ ስስ ፌስታል ብቻ ነው የተከለከለው፤ ትልልቆቹ ፌስታሎች (በተለምኮ ኩርቱ የሚባለው) እና ጠንካራ ፌስታሎች አልተከለከሉም " የሚሉ የተሳሳተ መረጃዎች በተለያዩ አካላት ሲሰራጩ ነበር።

NB. በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ 1383/2017 መሰረት የፕላስቲክ ከረጢቶችን የተጠቀመ ወይም ለመጠቀም ይዞ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ ከ2 ሺህ ብር የማያንስ ከ5 ሺህ ብር የማይበልጥ የገንዘብ ቅጣት ይጣልበታል፡፡

#ፌስታል

16/01/2026
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን ለጌታችን ለመዳኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እንዃን አደረሳችሁ።                                            ...
07/01/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን ለጌታችን ለመዳኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እንዃን አደረሳችሁ። መልካም በዓል!

ሰበር‼️ እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ ጨምሮ የአማራ የህሊና እስረኞች ሳያጠፉ መንግስት በይቅርታ ይፈቱ ማለቱ ተሰማምንጮቻችን እንዳሉት ከአማራ ክልሉ ግጭት ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙት ...
30/12/2025

ሰበር‼️ እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ ጨምሮ የአማራ የህሊና እስረኞች ሳያጠፉ መንግስት በይቅርታ ይፈቱ ማለቱ ተሰማ

ምንጮቻችን እንዳሉት ከአማራ ክልሉ ግጭት ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙት እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ በገፍ በማረሚያ ቤት የሚገኙ የአማራ ተወላጆች በይቅርታ ሊፈቱ መሆኑን ተሰምቷል።

ከሁለት ዓመት በፊት በክልሉ በተቀሰቀሰው ግጭት እጃችሁ አለበት በሚል ታፍሰው የታሰሩት ፖለቲከኞችና የማህበረሰብ አንቂዎች ከመጭው ገና በዓል በፊት ከእስር እንደሚፈቱ ይጠበቃል።

በመጀመሪያ ዙር ከእስር ይፈታሉ ተብሎ ከሚጠበቁት መካከል

አቶ ክርስቲያን ታደለ
አቶ ዮሀንስ ቧያለው
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው
ረ/ፕ ሲሳይ አውግቼው
ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃይለማርያም
ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ
መ/ረት መስከረም አበራ
ዶ/ር ጫኔ ከበደ እና ዶ/ር ካሳ ተሻገር እንደሚገኙበት ምንጮች አሳውቀውናል።

አክለውም ከእስር የሚፈቱበት ዋነኛ ምክንያት የተባለው ደግሞ የእነ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ አፋሃድ ከመንግስት ጋር በገባው ስምምነት መሠረት ነው ተብሏል።

ሀሳብዎን ያካፍሉን ?

''የኢትዮጵያ ብር በዓለም አቀፍ ደረጃ በዝቅተኛ የዋጋ ደረጃ ካላቸው ገንዘቦች ተርታ ተመደበ''የኢትዮጵያ ብር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር ያለውን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በማጣቱ፣ በዓለም አቀፍ ደረ...
25/12/2025

''የኢትዮጵያ ብር በዓለም አቀፍ ደረጃ በዝቅተኛ የዋጋ ደረጃ ካላቸው ገንዘቦች ተርታ ተመደበ''

የኢትዮጵያ ብር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር ያለውን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በማጣቱ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአርጀንቲና እና ከቱርክ ቀጥሎ ሦስተኛው ደካማ መገበያያ ገንዘብ ሆኗል ተባለ።

እንደ ብሉምበርግ ዘገባ ከሆነ፣ የብር ዋጋ በተያዘው የአውሮፓውያን ዓመት ውስጥ ብቻ በ15 በመቶ ማሽቆልቆል አሳይቷል። ይህ የዋጋ መዳከም ብርን ከአርጀንቲናው 'ፔሶ' እና ከቱርኩ 'ሊሬ' በመቀጠል በዓለም የገንዘብ ገበያ ዝቅተኛ አፈጻጸም ካላቸው መገበያያ ገንዘቦች ተርታ እንዲሰለፍ አድርጎታል።

የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙት፣ የብር ዋጋ ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ኢትዮጵያ ካለባት የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (Debt Restructuring) ጋር በቀጥታ የተቆራኘ ነው።

መንግሥት የ3.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር መልሶ ለማዋቀር ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ላይ መድረሱ የሚታወስ ቢሆንም፣ የሂደቱ መዘግየት በገንዘቡ ላይ ጫና ፈጥሯል።

ባለፉት ጥቂት ወራት የታየው የብር መዳከም በመደበኛውና በትይዩ (ጥቁር) ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት አባብሶታል። በአሁኑ ወቅት በመደበኛው ባንክ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 151 ብር አካባቢ ቢሆንም፣ በጥቁር ገበያ ግን እስከ 180 ብር ድረስ እየተመነዘረ ይገኛል።

ይህ የገንዘብ ዋጋ መዳከም በሸቀጦች ዋጋና በአጠቃላይ የኑሮ ውድነት ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስተዋለ ይገኛል።

ለማስተር አብነት ከበደ አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ ቀረበ[አዲስ አበባ] — ለሀገራችን በበጎ አድራጎት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ በታላቅ አክብሮትና ፍቅር የሚታወቀ...
17/12/2025

ለማስተር አብነት ከበደ አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ ቀረበ

[አዲስ አበባ] — ለሀገራችን በበጎ አድራጎት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ በታላቅ አክብሮትና ፍቅር የሚታወቀው ማስተር አብነት ከበደ፣ በአሁኑ ወቅት ከባድ የጤና እክል ገጥሞት የሁላችንንም እገዛና ጸሎት ይሻል።

ወንድማችን አባይነህ ባስተላለፈው ጥሪ መሰረት፣ ማስተር አብነት የሚገኝበትን የጤና ሁኔታ ለመደገፍና የሚመጡትን የሕክምና ወጪዎች ለመሸፈን የGoFundMe የገቢ ማሰባሰቢያ እንዲከፈት ጥሪ ቀርቧል።

የአብነት ጓደኞች፣ ወዳጆችና በተለይም በደቡብ አፍሪካ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች፣ ይህንን የድጋፍ ስራ እንድታስተባብሩና ከወንድማችን ጎን እንድትቆሙ ጥሪ ቀርቧል።

አብነት ለሀገሩና ለወገኑ ካበረከተው ውለታ አንጻር፣ አሁን በደረሰበት አስቸጋሪ ወቅት ልንክሰውና ልንደግፈው ይገባል።

ማስተር አብነት ገና አንድ ዓመት እንኳን ያልሞላቸው መንታ ልጆች አባት ሲሆን፣ የእሱ ጤንነት ለልጆቹ፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ ትልቅ ዋጋ አለው። ይህ ታታሪና ደግ ወንድማችን በጤና እንዲቆይልን ና ልጆቹን እንዲያሳድግ የሁላችንም ርብርብ የግድ ይላል።

ይህንን የሰብዓዊነት ጥሪ የምትደግፉና አብነትን መርዳት አለብን የምትሉ ወገኖች በሙሉ፡

1. ይህ መረጃ ለብዙኃኑ ይደርስ ዘንድ በላይክ (Like) እና በሼር (Share) አጋርነታችሁን ግለጹ።

2. በአስተያየት (Comment) መስጫው ላይ ያላችሁን ገንቢ ሐሳብ በማጋራት ቅስቀሳውን ደግፉ።

"ኢትዮጵያዊነት መረዳዳት ነው!
ማስተር አብነትን በጋራ እንታደገው!"

የ GoFundMe ሊንኩ እንደተዘጋጀ ወዲያውኑ የምናሳውቅ ይሆናል። እስከዚያው ግን ይህንን ጥሪ በማጋራት (Sharing) የበኩላችሁን ተወጡ።

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

ወቅታዊ ዜና: የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን ተከትሎ የትራንስፖርት ታሪፍ መጨመር እንደማይቻል ተገለጸ::አዲስ አበባ – የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ታህሳስ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የተደረገውን የነዳጅ...
11/12/2025

ወቅታዊ ዜና:
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን ተከትሎ የትራንስፖርት ታሪፍ መጨመር እንደማይቻል ተገለጸ::

አዲስ አበባ – የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ታህሳስ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የተደረገውን የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያን ተከትሎ ማንም አካል በገዛ ፍቃዱ የትራንስፖርት ዋጋ መጨመር እንደማይችል አስታወቀ።

ጭማሪ የሚያደርጉ አካላት ላይ ከመስመር እስከማስወጣት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድ ቢሮው አስጠንቅቋል።

የቢሮው የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ለመናኸሪያ ሬዲዮ በሰጡት ቃል፣ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በራስ ፈቃድ የዋጋ ማሻሻያ ሲደረግ እንደነበር ገልጸው፣ ቢሮው ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 4 ሰዓት ድረስ ጥብቅ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

ከባድ ቅጣት ይጠብቃል

* የዕለት ቅጣት:
ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ከመስመር እስከማስወጣት የሚደርስ እርምጃ ይወሰዳል።

* የምሽት ቅጣት:
በምሽት የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ዋጋ የሚጨምሩ አሽከርካሪዎች ለየት ያለ ቅጣት የሚጠብቃቸው ሲሆን፣ እስከ አምስት ሺህ ብር (5,000 ብር) በጭማሪው ብቻ እንደሚያስቀጣ ተጠቁሟል።

አቶ ዳኛቸው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪውን ተከትሎ በታሪፍ ላይ የሚደረግ ማሻሻያ ካለ፣ ቢሮው ከትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ጋር በመሆን ጥናት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኅብረተሰቡም በመደበኛው ታሪፍ ብቻ በመክፈል መብቱን እንዲያስከብር ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ጭማሪ ሲደረግ ሲመለከት የተሽከርካሪውን የሰሌዳ ቁጥር፣ ሰዓት እና ቦታ በመጥቀስ በቢሮው ነፃ የስልክ ጥሪ መስመር 9417 ጥቆማ እንዲያቀርብ ጠይቀዋል።

ቢሮው የሕዝብ ትራንስፖርት ሰጪ አካላት ያለምንም ታሪፍ ጭማሪ፣ በመደበኛው ታሪፍ መሰረት እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስቧል።

ምንጭ: መናኸሪያ ሬዲዮ

ይህንን መረጃ ለሌሎች በማጋራት ሌሎችም እንዲያውቁት አድርጉ

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

🚨 የዜና ዘገባ፡ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ግምት በዋና ዋና መንገዶች ላይ ሰው ሰራሽ የናፍጣ እጥረት ፈጠረ፤ የጥቁር ገበያው በ200 ብር መሸጥ ጀመረሲዳማ/ኦሮሚያ — በቅርቡ የነዳጅ ዋጋ ይጨምራል ...
08/12/2025

🚨 የዜና ዘገባ፡
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ግምት በዋና ዋና መንገዶች ላይ ሰው ሰራሽ የናፍጣ እጥረት ፈጠረ፤ የጥቁር ገበያው በ200 ብር መሸጥ ጀመረ

ሲዳማ/ኦሮሚያ — በቅርቡ የነዳጅ ዋጋ ይጨምራል በሚል ከሰፊው በተሰራጨው ግምት ሳቢያ፣ በዋና ዋና የመንገድ መሸጋገሪያዎች ላይ ሰው ሰራሽ የናፍጣ እጥረት ተፈጥሯል።

የዚህ ችግር ዋነኛ ተጠቂዎች የሆኑት አሽከርካሪዎች፣ በአዲስ አበባ 121 ብር አካባቢ የሚሸጠው ናፍጣ በህገወጥ ገበያ እስከ 200 ብር ድረስ እየተሸጠ መሆኑን ተመልክተናል።

ከሀገረ ሰላም እስከ ዝዋይ ባቱ፡ ማደያዎች ባዶ ናቸው
ከሲዳማ ክልል ሃገረ ሰላም ጀምሮ እስከ ዝዋይ ባቱ ባለው መንገድ ላይ በርካታ ማደያዎች ቢኖሩም፣ አብዛኞቹ ማደያዎች ለተሽከርካሪዎች ናፍጣ (Diesel) እንደሌላቸው እየገለጹ ነው።

* በሲዳማ ክልል ሀገረ ሰላም እስከ ሃዋሳ ከተማ መግቢያ ድረስ እንዲሁም ከሃዋሳ እስከ ዝዋይ ባቱ ባሉ አካባቢዎች የናፍጣ እጥረት አሳሳቢ ሆኗል።

'የለም' ከሚለው ማደያ ጀርባ ያለው ህገወጥ ገበያ
ማደያዎቹ ነዳጅ የለንም እያሉ ባሉበት ወቅት፣ በአካባቢው የተደረገው ምልከታ ግን ሌላ ነገር ያሳያል።

ማደያዎች አካባቢና ማደያዎች ውስጥ ያሉ አንዳንድ ግለሰቦች ነዳጅ በጀሪካን እንደሚሸጥ በግልጽ ሲናገሩ ታይቷል።

በዝዋይ ባቱ ከተማም ቢሆን ማደያው ናፍጣ እንደሌለው ከገለጸ በኋላ፣ አጠገቡ ባሉ ሱቆች ውስጥ በጀሪካን እየተሸጠ መሆኑን ተመልክተናል።

* ዋጋው ሰማይ ዳር ደርሷል፡ እ.ኤ.አ ህዳር 27 ቀን 2018 በተደረገው ምልከታ መሰረት፣ የህገወጥ ገበያው ዋጋ እጅግ የናረ ነው።

* በአዲስ አበባ ወደ 121 ብር አካባቢ የሚሸጠው አንድ ሊትር ናፍጣ፣ በአንዳንድ አካባቢዎች 165 ብር፣ በዝዋይ ባቱ ደግሞ ከ180 ብር እስከ 200 ብር ድረስ እየተሸጠ መሆኑ ተረጋግጧል።

ይህ ሁሉ የገበያ መዛባትና የህገወጥ ንግድ መስፋፋት ዋነኛው ምክንያት ሰሞኑን የነዳጅ ዋጋ ይጨምራል በሚል የተፈጠረው ሰፊ ግምትና ነጋዴዎች ነዳጅን በመደበቅ ወደ ጥቁር ገበያ በማዞራቸው ነው ተብሏል።

* የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የጸጥታ አካላት በዚህ መንገድ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የነዳጅ ዝርፊያና የዋጋ መናር ለመቆጣጠር ምን ዓይነት አስቸኳይ እርምጃ ወስደዋል?

* መንግስት የነዳጅ አቅርቦት መደበኛ መሆኑን በማረጋገጥ የህገወጥ ንግዱን ማስቆም የሚችለው እንዴት ነው?

Via Sheger FM 102.1 Radio

🌴🌴🌴

ዜና የዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤልን) ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾች ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ተሰጠ!አዲስ አበባ — የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ከኢትዮጵያ አየር ...
03/12/2025

ዜና
የዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤልን) ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾች ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ተሰጠ!

አዲስ አበባ — የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር በተያያዘ ወንጀል የተከሰሱትን ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል) እና ሌሎች ተከሳሾች በእስር ላይ የቆዩበት ጊዜ በቂ በመሆኑ፣ ከእስር እንዲፈቱ ውሳኔ አሳለፈ።

የፍትህ ሚኒስቴር ዐቃቤ ሕግ በነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. በዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ እና ይዲድያ ነጻነት ላይ ክስ መስርቶባቸው ነበር።

* ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ የሚደረገው በረራ በአየር ሁኔታ ምክንያት ሲሰረዝ፣ ተከሳሾቹ ከአውሮፕላኑ ለመውረድ ፍቃደኛ ባለመሆን ቀሪ ተሳፋሪዎችም እንዳይወርዱ በመከልከል የአየር መንገድ ደህንነትን አደጋ ላይ አሳድመዋል የሚል ነበር።

1ኛ ተከሳሽ ጆን ዳንኤል ክስተቱን በቲክቶክ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በተንቀሳቃሽ ምስል ቀርጾ በቀጥታ ስርጭት በማስተላለፍ የኮምፒዩተር ወንጀል ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 958/2008 አንቀጽ 13 ንዑስ ቁጥር 3ን ተላልፈዋል የሚል ክስም ተመስርቶባቸው ነበር።

ችሎቱ ተከሳሾቹ በተከሰሱበት የህግ አንቀፅ ጥፋተኛ ናቸው ብሎ የዐቃቤ ሕግ የቅጣት ማክበጃና የተከሳሾችን የቅጣት ማቅለያ መርምሮ የሚከተለውን ቀላል እስራት የሚጥል ውሳኔ አስተላልፏል፡

* 1ኛ ተከሳሽ (ዮሃንስ ዳንኤል) 1 ዓመት ከ 4 ወር
* 4ኛ ተከሳሽ 10 ወር
* 2ኛ፣ 3ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች 8 ወር

የመጨረሻ ውሳኔ: ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በእስር ላይ የቆዩበትን ጊዜ በመቁጠር፣ የተፈረደባቸውን ጊዜ በቂ በመሆኑ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

Via ኤፍ ኤም ሲ

🌴🌴🌴

ቴዲ አፍሮ: ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ሩሩህ እና ትሁት የጥሩ ሃይማኖት አባት ምሳሌ ነበሩ:: ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን በሞት ማጣት የተሰማው ሀዘን፤ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ...
20/10/2025

ቴዲ አፍሮ: ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ሩሩህ እና ትሁት የጥሩ ሃይማኖት አባት ምሳሌ ነበሩ::

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን በሞት ማጣት የተሰማው ሀዘን፤ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን ገለጸ!

አዲስ አበባ – በዛሬው ዕለት በተሰማው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የቀድሞ ፕሬዚዳንትና ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈተ ህይወት ምክንያት በሃይማኖት አባቱ የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ገልጿል።

ታዋቂው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ባስተላለፈው የሀዘን መግለጫ መልዕክት፣ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ አልፎ በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ እጅግ ተወዳጅ፣ ሩሩህ እና ትሁት የጥሩ ሃይማኖት አባት ምሳሌ እንደነበሩ ገልጿል።

ቴዲ አፍሮ ባጋጠመው በዚህ ከባድ ኀዘን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን ተመኝቷል።

በተጨማሪም “ፈጣሪ ነፍሳቸውን እንዲምርልን” የሚል ልባዊ ምኞቱን ጨምሮ “ነፍስ ይማር!” በማለት ሀዘኑን አጠናቅቋል።

የሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈተ ህይወት የሀገሪቱን ሰላም፣ መቻቻልና አንድነት ሲሰብክ ለኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ኪሣራ መሆኑ ተገልጿል።

Via ቴዲ አፍሮ

💔

🌴🌴🌴

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ከተጻፈባቸው ቀናት አንዱ ጥቅምት 4……አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ከተጻፈባቸው ቀናት መካከል ጥቅምት 4 ቀን ተ...
14/10/2025

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ከተጻፈባቸው ቀናት አንዱ ጥቅምት 4……

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ከተጻፈባቸው ቀናት መካከል ጥቅምት 4 ቀን ተጠቃሽ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ31 ዓመታት ጥበቃ በኃላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የተመለሰበት ዕለት ጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም መሆኑ ይታወሳል፡፡

ኢትዮጵያ በመሰረተችው መድረክ የበይ ተመልካች ሆና ወደ መድረኩ ለመመለስ 31 ዓመታትን መጠበቅ ግድ ብሏት ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማይዘነጉ ድሎች መካከልም በዚህ ቀን የተጻፈው ታሪክ አንዱ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኦምዱርማን ላይ በሱዳን 5 ለ 3 ተሸንፎ ቢመጣም አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በድምር ውጤት 5 አቻ በመሆን ከሜዳ ውጪ ባገባ በሚለው ሕግ ውጤቱን ቀልብሶ ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለሱ አይዘነጋል፡፡

አዳነ ግርማ እና ሳላዲን ሰይድ በወቅቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

ውጤቱን ተከትሎም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ31 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ደቡብ አፍሪካ ላዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻው እየተመራ ይህንን ታላቅ ታሪክ ከጻፈ 13 ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡

በወቅቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ጨዋታ ለመመልከት ለእሑድ ጨዋታ ከቅዳሜ ጀምሮ አብዛኛው ተመልካች ስታዲየም ዙሪያ ተገኝቶ ነበር፡፡

አዲስ አበባ ስታዲየም በዕለቱ የነበሩ ተመልካቾች አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ በመልበስ ከዛም አልፎ በመቀባት ድጋፋቸውን ለብሄራዊ ቡድኑ ያለስስት ሰጥተዋል፡፡

ይህም የኢትዮጵያዊያን ጥልቅ የእግር ኳስ ፍቅር የታየበት እና የወቅቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾችም ታሪክ የሰሩበት መድረክ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

ዕለቱ ከስታዲየም ውጪ የነበረው መላው ኢትዮጵያ ሕዝብ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በመያዝ ሀገሩ ወደ አፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ በጉጉት ሲጠብቅ የነበረበት እንዲሁም አዲስ ታሪክ በአዲስ ትውልድ የተሰራበትና እግር ኳስ በአንድ ቋንቋ ሁሉንም ያግባበት ነበር።

ስፖርት በአግባቡ ከተሰራበት ምን ያህል ሕዝብን ሊያቀራርብ እንደሚችል የታየበት ታሪካዊ ቀን ሲሆን÷ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኃላም የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ደስታ ልዩ ነበር፡፡

ይህ ደማቅ ታሪክ በወቅቱ ጀግኖች መጻፉን ተከትሎ በርከት ያሉ ዘፈኖች ለብሔራዊ ቡድኑ ተሰርተው እንደነበር ይታወሳል፡፡

በወንድማገኝ ፀጋዬ

"በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ  | ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።ይ...
11/10/2025

"በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል "
- ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

| ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።

ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው።

በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለፁት፤ በሚቀጥሉት ዓመታት የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ምደባ እንደሚያቆምና የማለፊያ ነጥብ የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች በሚፈልጓቸው ዩኒቨርሲቲዎችና የትምህርት መስኮች እንዲያመለክቱ ይደረጋል፡፡

" የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደከዚህ ቀደሙ በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ ሳይሆን በተማሪዎቹ ምርጫ ይሆናል " ብለዋል።

" ተማሪዎች የሚማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ሲመርጡም ምክንያታዊ በመሆን በዬትኛው ዩኒቨርሲቲ የተሻለ የትምህርት መስክ፣ እውቀትና የስራ እድል ላገኝ እችላለሁ በማለት ይመርጣሉ " ሲሉ ገልጸዋል።

#ኢፕድ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fana tv fans posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share