Al-Huda News

Al-Huda News Al-Huda News

07/10/2025

ኢስቲግፋር

ሸይኽ ያሲር ሐፊዘሁላህ

05/10/2025

በመካነ ሰላም ግድያ ለተፈፀመባቸው ምዕመናን በአዲስ አበባ መስጅዶች ሶላተል ጋኢብ እንዲሰገድ ከፍተኛ ም/ቤቱ ጠየቀ #መካነሰላም #የመስቀልጦረኞች
#ኃይማኖታዊጦርነት
#መካነሰላም
#ሙስሊምጠልነት
#አሐዳዊነት
#ሞዓተዋህዶ
#ፋኖ
#ኢማሙንገደሉት
#መስጂዱንደፈሩት















04/10/2025

አዳምጡት‼ ሼር ይደረግ

በዚህም ዘመን የልባቸውን ከሠሩ በኋላ ማንነታቸውን መደበቅ የሚችሉ መስሏቸው ነበር?

04/10/2025

የፋኖ የዘመቻ ቅስቀሳ እንዲህ ነው! | ሼር አድርጉት

" እኛ የምናጠቃቸው በእምነታችን ነው ፤ እኛ የምናጠቃቸው በሀይማኖታችን ነው። እኛ የምናጠቃቸው መድሀኔያለምን ሀይል አድርገን ነው ስለዚህ መድሀኔያለምን እስከያዝን ድረስ እነርሱ አርብ እሮብን እያረዱ እየበሉ ከእኛ ጋር ሊመጣጠኑ አይችሉም"

በመካነ ሰላም ግድያ ለተፈፀመባቸው ምዕመናን በአዲስ አበባ መስጅዶች ሶላተል ጋኢብ እንዲሰገድ ከፍተኛ ም/ቤቱ ጠየቀ
04/10/2025

በመካነ ሰላም ግድያ ለተፈፀመባቸው ምዕመናን በአዲስ አበባ መስጅዶች ሶላተል ጋኢብ እንዲሰገድ ከፍተኛ ም/ቤቱ ጠየቀ

መንግሥት በመካነ ሰላም የመስጅድ ኢማምን ጨምሮ ግድያ የፈፀሙ ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ጥሪ አቀረበ
04/10/2025

መንግሥት በመካነ ሰላም የመስጅድ ኢማምን ጨምሮ ግድያ የፈፀሙ ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ጥሪ አቀረበ

የፌዴራሉ መጅሊስ መግለጫ አውጥቷል‼==========================✍️ «ኢናሊላሂ ወኢና ኢለሂ ረጂኡን!እኛ የአላህ ነን ወደ እሱም ተመላሾች! ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም...
04/10/2025

የፌዴራሉ መጅሊስ መግለጫ አውጥቷል‼
==========================
✍️ «ኢናሊላሂ ወኢና ኢለሂ ረጂኡን!
እኛ የአላህ ነን ወደ እሱም ተመላሾች!

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23፣2018 ዓ.ል በመስጂድ ኑር በኢሻ ሰላት ወቅት ወደ መስጂድ የታጠቁ ኃይሎች በመግባት ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት ላይ በነበሩ ፦
1 የመስጂድ ዋና ኢማምና የወረዳው መጅሊስ ም/ሰብሳቢ
2 የመስጂድ አመራሮች
3 የመስጂድ ኻዲሞችን አሰቃቂ እና አረመኔያዊ በሆነ ሁኔታ መግደላቸውን የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አረጋግጦልናል።

እነሱም ሸሂድ ሆነዋል አላህ ጀነተል ፍርዶስ ይወፍቃቸው ።

ጠቅላይ ምክርቤቱ የእምነት ተቋማት የተከበሩ ቦታዎች በመሆናቸው ሊጠበቁ እንጅ እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባር የሚፈፀምባቸው መሆን የለባቸውምና ድርጊቱን በፅኑ ያወግዛል።

መላው የሃይማኖት ተቋማትም በእምነት ቦታዎች የሚደረጉ ትንኮሳዎች እና በእምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ መሰል የጅምላ ግድያ
ሊያወግዙና ሊያስቆሙ ይገባል።

ህዝበ ሙስሊሙ ይህንን በሀይማኖት ተቋማት ላይ የተቃጣ አደጋ ለመከላከል መረጃ በመለዋወጥ የሃይማኖት ተቋማትንና አካባቢውን እንዲጠብቅ ጠቅላይ ምክርቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ብዝሃ ሀይማኖት ባለባት ሀገራችን በተለያየ እምነት ውስጥ ያሉ ህዝቦች ለዘመናት ያቆዩተን ሰላማዊ እና መልካም መስተጋብር ሆን ተብሎ ለመናድና ማባሪያ ያጣ ቀውስ ውስጥ እንድንገባ የሚፈልጉ አካላት የፈፀሙት መሆኑን ጠቅላይ ምክርቤቱ ይገነዘባል።

በመጨረሻም ሁሉም ሃይማኖት ተቋማትና መሪዎች ይህ ጉዳይ አብሮ የመኖር እሴት እንዳይሸረሽር ብሎም እንዳያጠፋ ድርጊቱን እንድታወግዙ እንዲሁም በፅኑ እንድትቃወሙ እየጠየቅን መንግስትም ይህንን ተግባር በእምነት ቦታዎችና አባቶች ላይ የፈፀሙት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።»

©: መስከረም 24፣2018 ዓ.ል
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት

የአዲስ አበባ ከተማ መጅሊስ ትናንት ምሽት በመካነሰላም ህይወታቸው ላለፈው የመስጂድ ኢማም፣ የመጅሊስ አባላትና ሙስሊሞች ግድ'  ያ ጉዳይ መግለጫ አውጥቷል።
04/10/2025

የአዲስ አበባ ከተማ መጅሊስ ትናንት ምሽት በመካነሰላም ህይወታቸው ላለፈው የመስጂድ ኢማም፣ የመጅሊስ አባላትና ሙስሊሞች ግድ' ያ ጉዳይ መግለጫ አውጥቷል።

Address

Addis Ababa
1165

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Al-Huda News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share