28/05/2026
ከ3 ዓመት በኋላ የተለቀቀ👇
የሠላማዊ ሠልፍ ክልከላን ይመለከታል፦
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በዛሬው ዕለት ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ/ም በአገው ምድር በተወሰኑ ከተሞች ሊደረግ የነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ከዞን እስከ ወረዳዎች በአዊ ዞን አመራሮች ዝግጅታችንን ሁሉ ከጨረስን በኋላ ሊከለከል ችሏል። ይህ በእውነቱ ያሳዘነና ያሳፈረ ተግባር ነው።
መላው ህዝባችን ያሳየው ድጋፍና አልኝታነት ለወደፊት ለምናካሄደው አገዋዊ የነፃነት ትግላችን ትልቅ ስንቅ የሰነቅነበት መሆናችንን እየገለፅን ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባልተናነሰ የአዊ ዞን ከዞን እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች በፅንፈኛው የአማራ ፋኖ እየተደረገብን ላለው አገዋዊ ዘር ማፅዳት ዘመቻ ተባባሪ መሆናቸውን ስለተረዳንበት ለመላው የአገው ህዝብ፣ ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እንዲሁም ለሚመለከታችሁ የፌዴራል የመንግስት አካላት ለማሳወቅ እንወዳለን።
አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ) ዝርዝር የውሎ ነጥቦችንና ቀጣይ የትግላችንን አቅጣጫ ከታች በጥልቀት ስላቀረበ በትግስት እንድታነቡና እውነተኛ ፍርድ እንድትሰጡ እንጠይቃለን።
ነፃነትና ፍትህ ለተጨቋኙ የአገው ህዝብ!!!
AGEW TV 🔴 AGEW TV Fans