29/05/2026
ይሄ ነው መሪነት🙌
የዩጋንዳ ፕሬዝዳንት አርሰናል ዋንጫ በላ ብሎ የሚጨፍር ባለስልጣን አባርራለሁ ሲሉ አስጠነቀቁ
የዩጋንዳ ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ አርሰናል ዋንጫ በላ ብለው የጨፈሩ የመንግስት ባለስልጣናትን አባርራለሁ ሲሉ አስጠንቅቀዋል
የህዝብን ችግር ይቀርፋል ከድህነት ያወጣል ብዬ የሾሞኩት ሚኒስትር እንዴት ለአርሰናል ሲዘል ይውላል በማለት የተናገሩት ሙሴቬኒ የተሰጠውን ሀላፊነት ሳይወጣ የቀረው ሚኒስትር ተባራሪ ነው ብለዋል::
አንዱማ ጭራሽ አርሰናል ዋንጫ ስለበላ ለህዝቡ የደስታ መልዕክት አስተላልፍ ብሎ መልዕክት ላከልኝ እኔ ብዬ ነው የመለስኩለት ሲሉ ተናግረዋል።
ህዝቡ የሚበላው አጥቶ እኛ እንዴት ስለ አውሮፓ ክለብ መጨፈር ቻልንበት አርሰናልን መደገፍ ትችላለህ ነገርግን ባለስልጣን ከሆንክ መጀመሪያ የህዝቡን ድህነት አሸንፍ ይሄን አልታገስም ብለዋል።