Shalom news =ሻሎም ዜና

Shalom news =ሻሎም ዜና We are advertising and news company.

14/05/2025

ሕወሓት ከፖለቲካ ፓርቲነት ተሠረዘ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ አውጥቷል 06-09-2017

13/05/2025

" እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ እስካሁን የታገስኩት ይበቃኛል " - አቶ ጌታቸው ረዳ

በትግራይ ያለው ህገወጥ የወርቅ ንግድ ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ የጀመረ ሳይሆን በጦርነቱ ጊዜም ሳይቀር ሲሰራ የነበረ እንደሆነ የቀድሞው የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና የአሁኑ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አደረጉ።

አቶ ጌታቸው፤ "ብዙ ሰው የወርቅ ንግድ የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈራረምን በኃላ የጀመር ይመስለዋል" ያሉ ሲሆን ግን ጦርነቱም እየተካሄደ ንግዱ ነበር ብለዋል።

"እኔ የማምንበትን ትግል ነው ያካሄድኩት ብዬ አምናለሁ በዛ በማምንበት ትግል ውስጥ የትግራይን ህዝብ አጀንዳ ይዘው የታገሉ ብዙ የጦር መኮንኖች አሉ ለሰሩት ስራ ያለኝ ክብር በፍጹም አይቀንስም ግን ደግሞ ገና ገና ጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይበላ በነበረበት ወቅት ሳይቀር ምሽግ ለመቆፈር ብለን የወሰድነው ኤክስካቫተር ወርቅ ለመልቀም ይጠቀሙበት የነበሩ አዛዦችም ነበሩ" ሲሉ አጋልጠዋል።

"ሲዋሹ በጣም ነው የሚገርመኝ" ያሉት አቶ ጌታቸው "እኔ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል እስካሁን የታገስኩትም ይበቃኛል" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው "የኤርትራን ሰራዊት እናፍርሰው" በሚል አላማ ዘመቻ የጀመረና ዘመቻውን የሚመራው አመራር ሰዎችን እያፈነ ገንዘብ ሲበስብ እንደነበር ተናግረዋል።

"ሰው ሲሸጡ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፤ ኤርትራዊ መሸጥ ' ንብረት ' ነው የሚባለው ወርዷል ወይ ? ይባላል፤ ታፍንና ይዘህ 27 ወጣት አንድ ቤት ትዘጋና ቤተሰቦች አላቸው ውጭ ሀገር የሚባሉት ሰዎች አካውንት እየተጠየቀ እያንዳንዱ ሰው በትንሹ 4000 ዶላር እንዲያስገባ ተደርጎ (20 ሰው ካፈንክ 80 ሺህ ዶላር ታስገባለህ) በዚህ የውጭ አካውንት ከፍተው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እየሸጡ፣ እያገቱ ገንዘብ እንዲሰበሰብ የሚያደርጉ አመራር የሚሰጡ ከፍተኛ አመራሮች አሉ" ብለዋል።

ይህ ተግባር መጀመሪያ በኤርትራውያን መጀመሩን ከዛም ወደ ትግራይ ተወላጆች መዞሩን ተናግረዋል።

እዚህ ጉዳይ ላይ ጥናት ተደርጎ አመራሮቹ ለህግ እንዲቀርቡ ሙከራ ቢደረግም ማቅረብ እንዳልተቻለና 2 ዓመት እንደሆነው ጠቁመዋል።

አቶ ጌታቸው "ይሄን የሚመራ የመረጃ መምሪያ ኃላፊ እርምጃ እንዲወሰድበት ወይ ከስራ እንዲነሳ ብለን ወስነን ስናበቃ ለማስፈጸም ኃላፊነት የሚሰጣቸው የፀጥታ አመራሮች አላስፈጸሙም" ሲሉ ተናግረዋል።

የፀጥታ አመራሮች በባህሪያቸው ጥፋት ያጠፋውም ያላጠፋውም የመተጋገዝ ባህሪ አላቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው በወርቅ ንግድ ውስጥ ስላሉ አመራሮችም በዝርዝር ተናግረዋል።

"ወርቅ ንግድ ውስጥ የገባ ' ለትግራይ ነጻነት እስከመጨረሻው እሰዋለው ' እያለ የሚፎክር ጀነራል አለ አሁንም፤ እንዲህ አይነቱን የወርቅ ንግድ ውስጥ ነው ያለኸው ሊባል ይገባል" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው እነ ጀነራል ምግበ በወርቅ ንግድ ውስጥ ተሰማርተው እንደሚገኙ በስም ጠቅሰው ይፋ አድርገዋል።

"እነ ምግበ የሰሩት ጀግንነት የወጣት መስዕዋት መሰረት ተደርጎ የመጣ ጀግንነት ነው" ያሉት አቶ ጌታቸው "እነዛን ወጣቶች ለስደት በሚዳርግ ደረጃ ወደ ተራ የወርቅ ንግድ ገብተው ሲያበቁ የስርቆት ተግባራቸውን የትግራይ ግዛት አንድነት የማረጋገጥ አርገው እየገለጹ እንደገና ይሄን ወጣት ለሌላ መስዕዋትነት ሊዳርጉ እየተንቀሳቀሱ ነው" ብለዋል።

"እነ ኃይለስላሰም አሁን በትግራይ ህዝብ አንድነት ስም የትግራይን ወጣት ከኤርትራም ጋር ቢሆን አብሬ ለማገዶነት እንዳርገዋለው በሚል በጀግንነት ስም እየፎከረ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

እነ ምግበ ፣ እነ ኃይለስለሰ ፣ ኮሎኔል ተወልደን "በወንጀል የተነከሩ ሰዎች ናቸው" ብለዋቸዋል።

ድንገት ሰላም ቢፈጠር "ተጠያቂ እሆናለሁ፤ አደጋ ውስጥ እገባለሁ" ብለው ስለሚያስቡም ግርግር እንዲያልቅ አይፈልጉም ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

የትግራይን ህዝብ ለሌላ ጦርነት ለማስገባት እያሰቡ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ጌታቸው " የፌዴራል መንግሥት ድንገት ውጊያ ይገጥመናል " በሚል ስጋት ውጊያው ትግራይ ውስጥ እንዲካሄድ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀይሶ እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል።

" ሰላም መፈጠር አለበት፤ በኢትዮጵያም በኤርትራም መካከል ጦርነት መፈጠር የለበትም፣ የኤርትራ ህዝብ ለአደጋ መዳረግ የለበትም እምነቴ ነው። ግን መምረጥ ካለብኝ የትግራይ ህዝብ ድጋሚ የጦር አውድማ የሚሆንበት ሁኔታ እስከመጨረሻው ድረስ እንዳይሆን እታገላለሁ " ብለዋል።

በዚህ ትግል እንቅፋት የሆኑት የወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩት ዘራፊዎች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።

" ' ግንባር አዛዥ ነኝ ' ይላል ወርቅ ሲዘርፍ ነው የሚውለው " ብለዋል።

"በ2014 ወጣቶች በየግንባሩ ሲተናነቁ በርቀት ዳባት፣ደባርቅ ፣ሊማሊሞ ሆኖ ውጊያ ይመራ የነበረ ሰው በተመሳሳይ ሰዓት በኤክስካቫተር ወርቅ እየቆፈረ ይሸጥ ነበር" ሲሉ ተደምጠዋል።

በዚህ የዝርፊያ ኔትዎርክ ፖለቲከኛውም እንዳለ ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈ አቶ ጌታቸው በመቶ ሚሊዮን ዘርፏል ስላሉት ኃለስላሰም ተናግረዋል።

" ኮምቦልቻ issue account ነበር፤ በዛ ሰዓት ጦርነት ላይ ገንዘብ ስለሚያስፈልገን ትክክለኛ ውሳኔ ነው የወሰነው የግል ባንኮች ሳንነካ የመንግሥት እንውሰድ ብለን ፓለቲካሊ ወሰንን እኔ እንደማውቀው 4 ቢሊዮን ብር ነበረው issue account ላይ ይሄን ከብሔራዊ ባንክ ማረጋገጥ ይቻላል ጊዜያዊ አስተዳደር ከሆንኩም በኃላ ወረቀት መጥቶልኛል ምን እንደተፈጠረ ባንኮች ውስጥ ግለጹልን የሚል እና issue account ውስጥ ያለውን ገንዘብ እንዲሰበስቡ ከተመደቡት ሰዎች መሃል አንዱ የግንባር አዛዥ የሚባለው ኃይለስላሰ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ነው የወሰደው ወደ አንድ ቢሊዮን አካባቢ ገንዘብ ነው የወሰደው እሱ ስር ተፍ ተፍ የሚሉ የሱ አገልጋዮች የተወሰነ ድርሻቸውን የወሰዱ አሉ " ብለዋል።

አብዛኛው ሰው ትግሉን ለትግራይ ህዝብ ካለው የህልውና ጥቅም አንጻር እንጂ "ገንዘብ አገኝበታለሁ" ብሎ አይደለም የተሳተፈው ሲሉ ተናግረዋል።

"እኔ በማውቀው ባረጋገጥኩት በሰነድ ጭምር እነ ኃይለ የወርቅ ማሽኖችን ሲያስገቡ ነው የሚውሉት" ብለዋል።

የፖለቲካ አመራሩም አብሮ የወርቅ ንግድ ውስጥ መሰማራቱን ጠቁመዋል።

ሰዎቹ ማሽን ሲያዝባቸው የፌዴራል ሰዎች ጋር እየተደዋወሉ "እናተን የመሰለ ሰው የለም" እያሉ እየተለማመጡ ማሽን ለማስለቀቅ እንደሚሞክሩ ገልጸዋል።

በጥናት " እገለ እግሌ 300 ሚሊዮን ወስዷል በቁጥጥር ስር ይዋል፣ እገሌ ይሄን ያህል ማሽነሪ ወስዷል በቁጥጥር ስር ይዋል እርምጃ ይወሰድ " ከተባለ 2 ዓመት እንደሆነው አመልክተዋል።

የቀረበውን የጥናት ዶክመት እነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) እንደሚያውቁት ጠቁመዋል።

ትግሉ ውስጥ ትልልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች ስም ሌሎችን ይዞ እንዳይጠፋና የውሸት አንድነት ለማስቀጠል ሲባል እምርጃ መውሰድ አልተቻለም ብለዋል።

"የመረረኝ ሰዓት እርምጃ እንዲወሰድ ዶክመንት አቅርቤም ተግባራዊ አልተደረግም" ብለዋል።

እነ ምግበን፣ እነ ኃይለስላሰን በስም ጠቅሰን መጠየቅ ስላልቻልን "ሁሉም የሰራዊት አመራሮች ዘርፈዋል" የሚል የጅምላ መልዕክት እያስተላለፍን ነው የመጣነው ይህ ውሸት ነው ብለዋል።

ተጠያቂነት እንዳይሰፍን የፖለቲካ መሪዎቹ እንቅፋት እንደሆኑ ይህን የሚያደርጉትም እነሱም ተጠያቂ ስለሆኑ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል።

አብዛኛው የሰራዊት አመራር ግን ሰላም ፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።

02/07/2024

A young man asked his grandfather,
"Grandpa, how did you live in the past without technology . . .
without computers
without drones
without bitcoins
without Internet connection
without TVs
without air conditioners
without cars
without mobile phones?"

Grandpa answered:
"Just as your generation lives today . . .
no prayers,
no compassion,
no respect,
no GMRC,
no real education,
poor personality,
there is no human kindness,
there is no shame,
there is no modesty,
there is no honesty.

We, the people born between the years 1930-1980, were the blessed ones. Our lives are a living proof."

¶ While playing and riding a bike, we have never worn a helmet.
¶ after school we did our homework ourselves and we always played in meadows until sunset
¶ We played with real friends, not virtual friends.
¶ If we were thirsty, we would drink frim the fountain, from the waterfalls, faucet water, not mineral water.
¶ We never worried and get sick even as we shared the same cup or plate with our friends.
¶ We never gained weight by eating bread and pasta every day.
¶ Nothing happened to our feet despite walking barefoot.
¶ We never used food supplements to stay healthy.
¶ We used to make our own toys and play with them.
¶ Our parents were not rich. They gave us love, not material gifts.
¶ We never had a cell phone, DVD, PSP, game console, Xbox, video games, PC, laptop, internet chat . . . but we had true friends.
¶ We visited our friends without being invited and shared and enjoyed the food with their family.
Parents lived nearby to take advantage of family time.
¶ We may have had black and white photos, but you can find colorful memories in these photos.
¶ We are a unique and the most understanding generation, because we are the last generation that listened to their parents.

And we are also the first ones who were forced to listen to their children.~

25/06/2024

የአዕምሮ ህመምተኛ በመምሰል እና ሌሎች ዘዴዎችን በመፈፀም የመኪና ዕቃ ሰርቀዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች እጅ ከፍንጅ ተያዙ፡፡ አንደኛው ግለሰብ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥሮ በፍርድ ቤት በዋስትና የተለቀቀ መሆኑ ታውቋል፡፡
***
የመኪና ዕቃ ስርቆትና ሌሎች ወንጀሎችን ለመከላከል ፖሊስ እያከናወነው ያለው ተግባር ምቹ ሁኔታ ያሳጣቸው አንዳንድ ወንጀል ፈፃሚዎች ከፖሊስ ጥርጣሬ ውጪ ለመሆን በማሰብ የተለያዩ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ ወንጀል ለመፈፀም እንደሚንቀሳቀሱ ታውቋል፡፡ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 02 ነዋሪ መሆኑን በኪሱ ውስጥ የተገኘው የነዋሪነት መታወቂያ የሚያስረዳው አንደኛው ተጠርጣሪ ፈፅሟል የተባለው ወንጀል የዚህ ማሳያ ነው፡፡
ግለሰቡ የአዕምሮ ህመምተኛ መስሎ እየተንቀሳቀሰ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ፊጋ አካባቢ መሲ ህንፃ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ቆሞ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2- C34174 አ.አ ከሆነ ተሽከርካሪ ላይ የግራ ስፖኪዮ መስታወት ነቅሎ ለማምለጥ ሲሞክር እጅ ከፍንጅ እንደተያዘ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር አባይ ወርቁ ገልፀዋል፡፡
እራሱን የአዕምሮ ህመምተኛ በማስመሰል ከተጠያቂነት ለማምለጥ ጥረት አድርጎ ያልተሳካለት ይኸው ግለሰብ ሚያዚያ 3 ቀን 2016 ዓ/ም በዚሁ ክፍለ ወረዳ 8 ሰሚት ሳፋሪ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የዋጋ ግምቱ 60 ሺ ብር የሚያወጣ የተሽከርካሪ ስፖኪዮ ሰርቆ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በፍርድ ቤት በመዋስትና መለቀቁን እና የተለያዩ ስሞችን እንደሚጠቀም ኢንስፔክተር አባይ አስረድተዋል፡፡ በተጠርጣው ላይ የምርመራ መዝገብ ተደራጅቶ ጉዳዩ በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
በተመሳሳይ ዜና አንዲት ግለሰብ ቤተ ክርስቲያን የመጣች በመምሰል ነጠላ ለብሳ የመኪና ዕቃ ስርቆት ስትፈፅም እጅ ከፍንጅ ተይዛለች፡፡
ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ፈፅማለች የተባለው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ነው፡፡
በክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ከቤተል አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው እሌኒ ታደሰ የተባለችው ግለሰብ ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ 8 ሰዓት ገደማ ቤተክርስቲያን የመጣች በመምሰል ነጠላ ለብሳ እየተንቀሳቀሰች በአካባቢው ቆሞ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2- C49561 አ.አ ከሆነ ተሽከርካሪ ላይ 16 ሺህ ብር የዋጋ ግምት ያለው ስፖኪዮ ነቅላ ለመሰወር ስትሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፍንጅ ተይዛለች፡፡
ወንጀል ፈፃሚዎች በየጊዜው ልዩ ልዩ ስልቶችን በመቀያየር ወንጀል እንደሚፈፅሙ ተገንዝቦ ተገቢውን የመከላከል ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህብረተሰቡም ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገበት በግሉ ለሚወስደው የጥንቃቄ እርምጃ ትኩረት መስጠት እንዳለበት መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
ዘገባ ፦ ሣጅን አዳነ ደስታ እና ዋና ሳጅን ዘላለም አበበ

07/01/2024
አለምን ንቆና ክዶ ጌታን ከልብ ወዶና አገልግሎ ጥንቅቅ ብሎ በምሳሌነት ማለፍ ትልቅ እድል ነው !እናትችን ሂሩት በአደባባይ በብዙ ዋጋ መክፈል የታመንሽለት ሁሉን ትተሽ የተከተልሽው ጌታ በክብ...
12/05/2023

አለምን ንቆና ክዶ ጌታን ከልብ ወዶና አገልግሎ ጥንቅቅ ብሎ በምሳሌነት ማለፍ ትልቅ እድል ነው !
እናትችን ሂሩት በአደባባይ በብዙ ዋጋ መክፈል የታመንሽለት ሁሉን ትተሽ የተከተልሽው ጌታ በክብር እንደሚቀበልሽ የታመነ ነው!
በስጋ በመለየትሽ ላዘኑ ሁሉ በዚህ መፅናናት ይሁን!!

ዘማሪት ሒሩት በቀለ(ከ1935-2015)

ሆኖም ብዙ ሚድያዎች ድምፃዊት ብለው ዜና ይሠራሉ ይህ ትክክል አይደለም።
ድምፃዊትን ንቃ ዘማሪትን መርጣለችና።

11/05/2023

Jesus Is Lord!!

07/04/2023
04/03/2023

🍁 ቤ/ክ ውስጥ ለ‐ #ምኒልክ ሲሸበሸብ ያየ ወጣት "ምኒልክ ዛሬም ንጉሥ ነው" ቢል ይፈረድበታል? #ዓድዋ #ድብቅብሄርተኝነት #ኦርቶዶክስ #ኢትዮጵያ #ቶክኢትዮጵያ

27/02/2023

የእምነት ተቋማት ለቦረና ህዝብ የገንዘብ ድጋፍ ቢያደርጉ

Address

Addis Abeba

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shalom news =ሻሎም ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share