12/07/2025
ይቺ ግብፅ የተባለች ሀገር ለኢትዮጵያ እድገት ፀር ነች ምቀኛ ነች አተቅርቧት!!!
የግብፅ መንግሥት 'ስምምነቱ በፅሁፍ ይሁን' ማለቱ በግድቡ ዙሪያ የሚሰሩ ሥራዎች ላይ ገደብ ለማስቀመጥ ነው ሲሉ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ገለጹ
#የግብፅ መንግሥት በብራዚል ሪዮ ዲ ጄኔሮ በተካሄደው የብሪክስ አባል አገራት ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ኢትዮጵያ ግብፅን እንደማትጎዳ ለተናገሩት ንግግር በፅሁፍ እንዲሆን በይፋ ጠይቋል፡፡
ጉዳዩን አስመልክቶም አሐዱ ባለሙያዎችን ያነጋገረ ሲሆን፤ ባለሙያዎቹ "ግብፅ ይህንን ጥያቄ ያቀረበችው በሕዳሴው ግድቡ ዙሪያ የሚሰሩ ሥራዎች ላይ ህጋዊ ሰነድ በመያዝ ጫና ለማድረግ በማሰብ ነው" ሲሉ ገልጸዋል፡፡
አሐዱ ያነጋገራቸው የፓለቲካ ተንታኙ እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያው ጥላሁን ሊበን፤ "ግብጽ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የነበረው ንግግር በፅሁፍ እንዲሆን የጠየቀችው፤ የሕዳሴው ግድብ ሙሌት እንዲቀንስ እና በዙሪያው ከሚገኙ ደሴቶች አገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እንዳታገኝ ለማድረግ ነው" ብለዋል፡፡
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንግሥት ስምምነቱን የሚፈራረም ከሆነ፤ ከስምምነቱ ውጭ ለሚሰሩ ሥራዎች በዓለም አቀፍ ሕግ ተጠያቂ ለማድረግ የታሰበ መሆኑን ባለሙያው ተናግረዋል።
"በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ግድቡን በሚገነባበት ጊዜ የዓለም አቀፍ ህግን ያከበረ በመሆኑ ስምምነቱን መፈረም የለበትም" ብለዋል።
ሌላኛው የዓለም አቀፉ ግንኙነት፣ የፖለቲካ ተንታኝ እና የቀድሞ ዲፕሎማቱ ደያሞ ዳሌ በበኩላቸው፤ "ግብፅ ይህን ስምምነት በወረቀት እንዲሆን ጥያቄ ማቅረቧ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ችግር ቢከሰት የኢትዮጵያ መንግስት ከግድቡ ምንም ውሃ እንዳይጠቀም ለማድረግ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም "ይህን ስምምነት በፊርማ እንዲሆን መጠየቋ ተጨማሪ ግድብ እንዳይገነባ ለማድረግ እና ውሃውን ለመስኖ እንዳንጠቀም ለማድረግ ነው" ብለዋል።
ባለሙያዎቹ ግብፅ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የምትፈጥረውን የዲፕሎማሲ ጫና ለመቋቋም የሀገር ውስጥ አንድነትን ማስጠበቅና ማጠናከርም ያስፈልጋል ሲሉም አሳስበዋል።