wanos ze sina

wanos ze sina God always with me

ብዙወች ከትናንት ጋር ተከማችተዋል ፤ጥቂቶች ከነኀጢአታችንም ተሻግረናል።መርከባችን ሆይ ስላሻገርሽን ስላደረሽንም አመስግነናል።ክበሪልን የወልድ እናቱ
01/12/2023

ብዙወች ከትናንት ጋር ተከማችተዋል ፤ጥቂቶች ከነኀጢአታችንም ተሻግረናል።መርከባችን ሆይ ስላሻገርሽን ስላደረሽንም አመስግነናል።ክበሪልን የወልድ እናቱ

ከጭቃው መሀል.....ንፁህ ዘሬን፡ ስጋ ነፍሴን፡ አጎደፍኩት፣በተሰጠኝ እስትንፋሴ፡ እየቀለድኩ ጠፋሁበት።ፀጋ ክፍሌን፡ ዋሸሁበት አንደበቴን፣ወረወርኳት መዳኛየን፡ ፆም ፀሎቴን።ቀናንሼ ከእስትንፋ...
30/11/2023

ከጭቃው መሀል.....
ንፁህ ዘሬን፡ ስጋ ነፍሴን፡ አጎደፍኩት፣
በተሰጠኝ እስትንፋሴ፡ እየቀለድኩ ጠፋሁበት።
ፀጋ ክፍሌን፡ ዋሸሁበት አንደበቴን፣
ወረወርኳት መዳኛየን፡ ፆም ፀሎቴን።

ቀናንሼ ከእስትንፋሴ፣
ሳላነሳሽ በውዳሴ።
ስንት አመታት መሼ ነጋ፣
ነፍሴ!
ከጋኖች መሀል ጠውልጋ።
ስትሰጭኝ ገፀበረከት፣
እኔ መች አጌጥኩበት።

ልጅሽ እኔን ለማዳን፡ ከዙፋን ሽሽት ገጠመ፣
ጠብቄ ተዘባበትኩት፡ በነፍሱ ነፍሴን ላተመ።
ከሰማይ ዙፋኑ ወርዶ፡ በፍቅር ሊያድን ለመጣ፣
መራራ ሀሞት ጋተችው፡ የነፍሴ ፅሀይ ሳትወጣ።
ጨለማ ውስጥ እያደረ፡ ብርሀንን የሰበረ፣
ማን አለና ከኔ ሌላ፡ ህያው ነፍሱን የቀበረ።
በልጅሽ ፊት ተመዝኜ፡ ፅድቅ የሌለኝ ጎዶሎ ነኝ፣
ደሙን ትቼ አንቀላፋሁ፡ ከንቱነት ተበተበችኝ።

መዳን በአለም ሲሆን፡ መዳኔን አልዳንኩበትም፣
አደርኩ አምላኬን ሽጨ የሴት ገላን ስሳለም።
ከመቅደስ ማልዶ ተነስቶ፡ ፈልጎ በአለም ከጠፋ፣
ከሄደ ይሂድ ግድየለም፡ የልቡን መለከት ይንፋ።
ብለዋል ብዙ አውርተዋል
በሞቴ ስለት ከፍለዋል።
ከእልፍ ልጆችሽ መሀል፡ ለምን ፈለግሽኝ ድንግል፣
ተይ አትጠጊኝ ማርያም፡ ክርፋት ገላየ ይሸታል።
ና! ስትይኝ ስትጠሪኝ፡ አዝኖ ልብሽ በመራቄ፣
እንዳልሰማ እንዳላየ፡ አሳለፍኩሽ ተደብቄ።
ለምን መጣሽ እመብርሀን፡ አትድከሚ አማላጄ፣
ሰው መሆኔ ተሽጧል፡ ኮብልየበት ማልጄ፣
መቅረቢያ ከፊትለፊትሽ፡ ምን አለኝና ከጄ።

እኔን ግርም የሚለኝ፡ የልጅሽ ሀያል ፍቅር ነው፣
ሰክሬ ወድቄ ትቢያ፡ እየጠበቀኝ አድራለው።
ስራው ድንቅ ነው ጌታየ፡ የበጎች ሁሉ እረኛ፣
እናቱን እናቴ አረገ፡ እንዳልሆንበት ብቸኛ።
ኃጢአቴ ሰፍቶ ከሰማይ፡ ሸትቼ ሰው ሲተፋብኝ፣
ስጋየን ለመከላከል፡ ለዝንቦች አቅም አጣሁኝ።
ፍጥረት ሲገባ ከቤቱ፡ ጭቃ ለብሼ አደርኩኝ፣
ነግህ ሲነጋ በአለም፡ ከጭቃው መሀል ፈለግሽኝ።
አፈር መስየም ቢሆን፡ እታወቃለሁ በእናቴ፣
ነፍሴ ማርያም ናት ዘላለም፡ አይቀይራትም ማጣቴ ፣
አየሁኝ አምራ ተውባ፡ በምልጃሽ ደምቃ ህይወቴ።
Alex.com.sisay

13/10/2023
መታሰቢያ ሐምሌ 22-ኢትዮጵያዊው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡ኢትዮጵያዊው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ፡- የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ በ1875 ዓ.ም...
28/07/2023

መታሰቢያ
ሐምሌ 22-ኢትዮጵያዊው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ኢትዮጵያዊው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ፡- የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ በ1875 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰላሌ አውራጃ ፍቼ ከተማ ተወለዱ፡፡ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት እንደሚሞቱ አስቀድመው መምህራቸው በትንቢት ነግረዋቸው ነበር፡፡ ‹‹አለቃ ተጠምቀ›› የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን አቡነ ጴጥሮስን ጠርተው «ኀይለ ማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፣ አደራ›› ብለዋቸው ነበር፡፡ ይኸውም ትንቢት ደርሶ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት ለማረፍ በቅተዋል፡፡ ብፁዕ አባታችን የጵጵስና ስማቸውን ከማግኘታቸው በፊት መመህር ኀይለ ማርያም ይባሉ ነበር፡፡ በልጅነታቸው ወላጆቻቸው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመውሰድ በሃይማኖትና በምግባር ተኮትኩተው እንዲያድጉ አድርገዋቸዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዓተ ትምህርት ከንባብ እስከ ቅኔ ያሉትን ትምህርቶች በሚያስገርም ፍጥነት ከተማሩ በኋላ ወደ ቅኔው አውድማ ጎጃም በመሄድ በዋሸራ የቅኔ ትምህርታቸውን ፈጽመው መምህር ሆነዋል፡፡ የዜማውንም ትምህርት ወደ ጎንደር ሄደው ተምረዋል፡፡ በመቀጠልም ወሎ ቦሩ ሜዳ ላይ ወንበር ዘርግተው የመጻሕፍትን ምሥጢር ይመግቡ ወደነበሩት ወደ ሊቁ አካለ ወልድ ዘንድ በመሄድ ዋና ዋናዎቹን የመጻሕፍት ትርጓሜ ማለትም ብሉያትን፣ ሐዲሳትንና ሊቃውንትን በሚገባ አካሄዱ፡፡ ከዚህ በኋላ በ1900 ዓ.ም ወሎ አምሐራ ሳይንት ሄደው በምስካበ ቅዱሳን ገዳም ገብተው ወንበር ዘርግተው ለ9 ዓመታት ቅኔንና መጻሕፍትን አስተማሩ፡፡ በ1910 ዓ.ም ወደ ደብረ ሊባኖስ መጥተው ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጸሙ፡፡ ከዚያም መምህርነት ተሹመው ደብረ መንክራት ምሁር ኢየሱስ ገዳም ሄደው ለ6 ዓመታት ካስተማሩ በኋላ በ1916 ዓ.ም እንደገና በዝዋይ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም በመምህርነት ተሹመው ለ3 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በ1919 ዓ.ም ወደ አ.አ በመምጣት የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ መምህርና በቤተ መንግሥት የግርማዊ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ የንስሓ አባት ሆኑ፡፡ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በራሷ ተወላጅ ጳጳሳት ልጆቿ እንድትመራ ከ1600 ዓመታት በኋላ ስለተፈቀደላት ከዚህ በኋላ በሃይማኖታቸውና በስነ ምግባራቸው የተመሰከረላቸው አምስት ደጋግ አባቶች ሲመረጡ አንዱ አቡነ ጴጥሮስ ነበሩ፡፡ በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የራሷን ጳጳስ ስትሾም አቡነ ጴጥሮስ ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ.ም ጵጵስና ተሾሙ፡፡ ከዚህም በኋላ ብፁዕ አባታችን ‹‹አቡነ ጴጥሮስ ጳጳስ ዘምሥራቀ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዐ›› ተብለው በያኔው መንዝና ወሎ ሀገረ ስብከት ተሾሙ፡፡
ብፁዕ አባታችንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና ቅድስት ሀገራችን በጸሎታቸው፣ ሕዝቡን በትምህርታቸው እየጠበቁ በተጋድሎ እየኖሩ ሳለ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት በ1928 ዓ.ም በኢትዮጵያ ላይ የግፍ ጦርነትን አውጆ ሕዝቡን በግፍ ይገድል ቤተ ክርስቲያንን ያቃጥል ጀመር፡፡ በየገዳማቱ እጅግ በርካታ ካህናትና መነኮሳት ተገደሉ፣ ብርቅዬ የቤተ ክርስቲያን ቅርሶች ተዘረፉ፡፡ አቡነ ጴጥሮስም ይህንን ግፍ በማየታቸው ከሀገራችን አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎታቸው ሊዋጉት ተነሡ፡፡ አባታችን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ተከትለው ወደ ሰሜን ጦር ግንባር ማይጨው ዘምተዋል፡፡ ፋሺስቱ በማይጨው በመርዝ የተደገፈ ጦርነት ከማድረጉ የተነሣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሲበታተንም ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ወደ አ.አ የተመለሱት አቡነ ጴጥሮስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው ለአገርና ለነፃነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ለሠላሌ አርበኞች በሚገባ አስተምረዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ጫካዎች ውስጥ መሽጎ የነበረው የእነ ደጃዝማች አበራ ካሣ አርበኛ ጦር እና በሸንኮራ በኩል መሽጎ የነበረው የእነ ፍቅረ ማርያም አርበኛ ጦር እንደሁም በምዕራብ ይመራ ከነበረው የእነ ደጃዝማች አባ ነፍሶ ጦር ሦስቱም በአንድ ጊዜ ወደ መሐል አ.አ በመግባት አ.አ ላይ መሽጎ የነበረውን ፋሽስትን ለመውጋት ታቅዶ የነበረው ዕቅድ በመረጃ ክፍተት ምክንያት ውጤታማ ሳይሆን ቀረ፡፡ በተለያየ ጊዜ መሐል አ.አ እየደረሱ ማለትም በመጀመሪያ የእነ ፍቅረ ማርያም አርበኛ ጦር ለብቻው በኮተቤ አድጎ የካ ሚካኤል ላይ ሲድርስ ተመቶ ተመለሰ፤ ይሄኛው እንዳለቀ ቀጥሎ የእነ አባ ነፍሶ ጦር በባቡር ጣቢያ መጣሁ ቢልም በጠላት ጦር ድጋሜ ተመቶ ተመለሰ፤ መጨረሻ ላይ የእነ ደጃዝማች አበራ ካሣ አርበኛ ጦር በእንጦጦ በኩል ቢመጣም እርሱም በጠላት ጦር ተመቶ ተመለሰ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ሦስቱም የአርበኞች ጦር በመረጃ ክፍተት ምክንያት እየተመታ ወደመጣበት ሲመለስ አቡነ ጴጥሮስ አብረው ከአርበኛው ጦር ጋር መመለሱን አልፈለጉትም ይልቁንም ‹‹ብችል ጠላት በኢትዮጵያውያን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ በቅርብ ርቀት ሆኖ የሚመለከተውን ሕዝብ በማትጋት በጠላት ላይ እንዲነሣ አደርገዋለሁ ካልሆነም ደግሞ እዚሁ እሞታለሁ›› በማለት አባታችን ከአርበኞቹ ተነጥለው አ.አ ቀሩ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላዋ ከተማ ያሰማራቸው ባንዳዎች አባታችንን እንዳሰቡት ሊያነቀሳቅሷቸው አልቻሉም ነበር፡፡ በመሆኑም አባታችን ‹‹የሀገሬን ሕዝብ ለጠላት እንዳይገዛ በአደባባይ አውግዤ ጠላትን ረግሜ በሰማዕትነት ባልፍ ይሻለኛል›› ብለው ራሳቸውን ለጠላት አሳልፈው ለመስጠት ወሰኑና የፋሺስት ኢጣሊያ እንደራሴ ለሆነው ለራስ ኀይሉ ሄደው እጃቸውን ሰጡት፡፡ እርሱም ብፁዕ አባታችንን ወስዶ ለግራዚያኒ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም አሳልፎ ሰጧቸው፡፡ ግራዚያኒም ግማሽ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንዲገደሉ ወሰነባቸው፡፡ አቡነ ጴጥሮስ በፈቃዳቸው እጃቸውን አሳልፈው ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ በጠላት የጥይት እሩምታ በሰማዕትነት እስካለፉበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሒደት ኮርየሬ ዴላሴራ የተባለው ጋዜጣ ወኪልና የምሥራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕል አዘጋጅ የነበረው ፖጃሌ የተባለው ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ ሰኔ 15 ቀን 1936 ዓ.ም በአዲስ አበባ በነበረ ጊዜ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ የተሰጠውን ፍርድና የተፈጸመውን የግፍ ግድያ ባየውና በተመለከተው መንገድ እንደሚከተለው ጽፎ ነበር፡-
‹‹ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ፡፡ በዚህ ጊዜ አቡነ ቄርሎስ የተባሉት ግብፃዊ ጳጳስ ቀርበው ‹ለእስክንድርያው መንበረ ፓትርያርክ ምክር ቤት ሳታሰማ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ እንዳች ነገር ማድረግ አይገባህም››› ሲሉ ለግራዚያኒ ነገሩት፡፡ አቡነ ቄርሎስ ይህን ማለታቸው በዲፕሎማቲክ ደረጃ ለዓለም ለማሰማትና የአቡነ ጴጥሮስን ሕይወት ለማትረፍ አስበው ነበር፡፡ ነገር ግን ግራዚያኒ የአቡነ ጴጥሮስ የሞት ፍርድ እንኳንስ እስከ ግብጽ ከአ.አ ውጭ እንኳ ከመሰማቱ በፊት በግማሽ ቀን እንዲፈጸም መመሪያ አስተላለፈ፡፡ ወደ ምሥራቅ አፍሪካው ዜና መዋዕል አዘጋጁ ወደ ፖጃሌ ዘገባ እንመለስና የአቡነ ጴጥሮስን መልካቸውንና ተክለ ቁመናቸውን እንዲህ በማለት ይገልጸዋል፡- ‹‹ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ፣ መልካቸው ጠየም ያለ፣ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ፡፡ ለፍርድ የተሰየሙት ዳኞቸ ሦሰት ሲሆኑ እነዚህም ጣሊያኖችና የጦር ሹማምንቶች ናቸው፤ መካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር፡፡ የቀረበባቸውም ወንጀል ‹ሕዝብ ቀስቅሰዋል፤ ራስዎም አምፀዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምፁ አድርገዋል› የሚል ነበር፡፡ ዳኛውም ‹ካህናቱም ሆኑ የቤተ ክህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የጣሊያንን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን አመፁ? ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስም በቆራጥነት የሚከተለውን መለሱ፡- ‹‹አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተ ክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡ ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም፡፡ ለፈጣሪዬ ብቻ የምናገረውን እናገራለሁ፡፡ እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ ዐውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» አሉ፡፡ ‹‹ይህንንም ብለው በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ እንዲመለከት ተጋብዞ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚከተለውን ሕያው መልእክት አስተላለፉ፡- ‹አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት ቤተ ክርስቲያንን ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው፤ እንጂ በጎ ለመሥራት ስላልመጣ ለዚህ ለግፈኛ አትገዙ፡፡ ስለ ውድ ሀገራችሁ፣ ስለ ቀናች ሃይማኖታችሁ ተከላከሉ፡፡ ነጻነታችሁ ከሚረክስ ሙታችሁ ስማችሁ ቢቀደስ ታላቅ ዋጋ ያለው ክብር ታገኛላችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ ለጠላት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን፡፡ በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተገዘተች ትሁን› ብለው አወገዙ፡፡ ቀጥሎም ብፁዕነታቸው በፍጥነት ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለ እርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ፡፡ ወዲያው የሞታቸው ፍርድ ሲሰማ ሕዝቡ በኢጣሊያ የእጅ ሰላምታ ዓይነት እጁን እንዲያነሳ ታዘዘ፡፡ በዚያን ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ፡፡ በዚህን ጊዜ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር፡፡ የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣሊያዊው ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር፡፡ ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ላይ ይታይ ነበር፡፡ የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኳቸው፡፡
የሀገራቸው በጠላት መወረር፣ የሕዝባቸው መገደልና መታሰር፣ የቤተክርስቲያናቸው መደፈር እስከ ሞት ያደረሳቸው እኒያ እውነተኛ ጳጳስ እንዲገደሉ ሲወሰዱ ጥይት አልፎ ሌላ ሰው እንዳይመታ ግንብ ይፈለግ ጀመር፡፡ ሩቅ ባለመሄድ ከመካነ ፍትሑ ዐሥር ሜትር ርቆ ግንብ ያለው መግደያ ቦታ ተገኘና ወደዚያ ተወሰዱ፡፡ ከገዳዮቹም አንዱ ‹ፊትዎን ለመሸፈን ይፈልጋሉን?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ ‹ይህ ያንተ ሥራ ነው› ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ፡፡ ከመግደያውም ቦታ እንደደረሱ ወንበር ቀረበላቸውና ፊታቸውን ወደ ግንቡ ጀርባቸውን ወደ ሕዝቡ አድርገው እንዲቀመጡ ሆኑ፡፡ ከዚያም በኋላ ስምንት ወታደሮች በስተ ጀመርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተጠንቀቅ ቆሙ፣ ወዲያው አዛዡ ‹ተኩስ!› በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም ተኩሰው መቱዋቸው፡፡ ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ፡፡ መሞታቸውንና አለመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ፡፡ ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ፡፡ ከዚያም በኋላ አንድ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው፡፡ ብፁዕነታቸው የተገደሉበት ቦታ መሐል አዲስ አበባ ላይ ዛሬ መታሰቢያ ሐውልታቸው ቆሞ በሚገኝበት ቦታ ላይ ነው›› በማለት የጋዜጣ ወኪልና የምሥራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕል አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛው ፖጃሌ ስለ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ደራሲና ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ ‹‹አቡነ ጴጥሮስ እንዴት ሞቱ?›› ሲል በወቅቱ አባታችን ሰማዕትነትን ሲቀበሉ በቦታው ላይ በአካል በመገኘት ሁኔታውን ይከታተሉ የነበሩትን ሙሴ ፓይላክን ጠይቋቸው እርሳቸውውም የሚከተለውን ተናግረዋል፡- ‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት፡፡ ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት፡፡ ወዲያው ወታደሮቸ በሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው፡፡ ይህ እንደሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ፡፡ ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት ‹በዚህ ቄስ መገደልኮ ሕዝቡ ተደስቷል› አለኝ፡፡ ‹እንዴት?› ብለው ‹አላየህም ሲያጨበጭብ?› አለኝ፡፡ ‹ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል› አልኩት፡፡ ‹እንዴት?› ቢለኝ እጄን አጨብጭቤ አሳየሁት፡፡ ‹ከዚህ በኋላ የሆነው ቢሆን እኔ ትልቅ ማስታወሻ አግኝቻለሁ› ብሎ አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ ይዘውት የነበረውን መስቀልና መጽሐፍ ቅዱስ የኪስ ሰዓታቸውንም ጭምር አሳየኝ፡፡ መጽሐፍ ቅዱሱ መሐል ለመሐል በጥይት ተበስቷል፡፡ መስቀሉም ልክ በመሐሉ ላይ ጥይት በስቶት ወጥቷል፡፡ የኪስ ሰዓታቸውንም እንዳየሁት እንዲሁ ጥይት በስቶታል›› ብለው በወቅቱ የተመለከቱትን መስክረዋል፡፡
ብፁዕ አባታችን በአደባባይ በሕዝብ ፊት የሰማዕትነት ጽዋቸውን ሲቀበሉ ከሕዝቡ ጋር ሆና ትመለከት የነበረች አንዲት ከድጃ የምትባል እስላም ሴት ማንም ሰው ያላየውን ታላቅ ነገር እርሷ ተመልክታለች፤ ይኸውም አባታችን ሰማዕትነትን ሲቀበሉ የብርሃን አክሊል በራሳቸው ላይ ሲቀዳጁ ተመልክታ በዚያው እርሷም ‹‹የእኚህን አባት ሃይማኖት እከተላለሁ›› ብላ በመጠመቅ ክርስቲያን ሆናለች፡፡ የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል በሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ሰማዕቱን አቡነ ጴጥሮስን ገድሎ አስክሬናቸው አደባባይ ላይ ጥሎ ከዋለ በኋላ ቀብራቸው በምሥጢር መፈጸሙን አንዳንዶች ይናገራሉ፡፡ የእኚህን ታላቅ አባት ቀብር በምሥጢር የተፈጸመበት ቦታ ለማግኘት የተለያዩ ምሁራን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የታሪክ ሰነዶችን ሲመረምሩ ቢቆዩም ‹‹ከአዲስ አበባ በስተደቡብ በምሥጢር ቀበሯቸው›› ከሚል ከመላምት ያለፈ ነገር ምንም ዓይነት የተረጋገጠ ማስረጃ ሳይገኝ ቀርቷል፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከአዲስ አበባ ከተማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ‹‹ፉሪ ለቡ›› ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ የሰፈሩ ምዕመናን በአካባቢው ተወልደው ካደጉ አረጋውያን ጋር ባደረጉት ማኅበራዊ ግንኙነት ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ፋሽስቶች በመኖርያነትና በእስር ቤትነት ይጠቀሙበት በነበረው ‹‹ሙኒሳ ጉብታ›› ላይ መቀበራቸውን ከወላጆቻቸው ሲሰሙ እንዳደጉ እየተነገረ ይገኛል፡፡ እንዲሁም የአቡነ ጴጥሮስን ሥጋ በተመለከተ ማንም እንዳይወስደው በአስቸኳይ ከአ.አ ውጭ ማንም በማያውቀው ቦታ በምሥጢር እንዲቀበር መደረጉ በትንሣኤ መጽሔት ቁ.58 1978 ዓ.ም ላይ የተገለጠ ቢሆንም ነገር ግን አንዳንድ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶች ቅዱሳን መላእክት የጻድቃንን በድን እያመጡ ወደሚያስቀምጡበትና በውስጡ የሚቀመጥ አስክሬን ወደማይፈርስበት አቡነ መልከ ጼዴቅ ዋሻ ገዳም መላእክት ወስደው እንዳስቀመጡትና በዚያም እንደታየ ይናገራሉ፡፡ ሰሜን ሸዋ ሚዳ ወረዳ ውስጥ በሚገኘው በአቡነ መልከ ጼዴቅ ዋሻ ውስጥ የቅዱሳኑ አጽም ሳይፈርስና ሳይበሰብስ የአንገት ክራቸው ራሱ ሳይበጠስ እንደዛው እንደነበሩ ስለሚገኝ ቦታውም እጅግ ትልቅ የቃልኪዳን ቦታ ስለሆነ የዚህ ጽሁፍ አዘጋጅም በዚህ በጨረሻው ሀሳብ ይስማማል፡፡
ሰማያዊ ክብርን የሚያስገኝ አኩሪ ገድል በመፈጸም የቤተክርስቲያን ታላቅ አለኝታ አባትና መሪ የሆኑት የዘመናችንን ታላቅ ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስን ትውልዱ የግድ ሊያስባቸውና ሊዘክራቸው ይገባል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (united nations) አቡነ ዼጥሮስን "የሺህ ዓመቱ ምርጥ ሰማዕት" ወይም በፈረንጅኛው አፍ (MARTYR OF THE MILLENIUM) በሚል መጠሪያ ሰይሟቸዋል፡፡ ላልተነገረላቸውና ላልተዘመረላቸው ለእኚህ ብርቅዬ የቤተ ክርስቲያናችን ድንቅ አባት ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምት 12 ቀን 1998 ዓ.ም እኚህን ሰማዕት ‹‹አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ›› ተብለው እንዲጠሩ ወስኗል፡፡ በስማቸውም መቅደስ እንዲታነጽ ፈቅዶ በመጽሐፍ ቅዱስ ትእዛዝ መሠረት (ኢሳ 56፡4) ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቁ በተወለዱበት ሥፍራ መታሰቢያ አቁማላቸዋለች፡፡ ግንቦት 1 ቀን 2001 ዓ.ም በስማቸው የተሰየመው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንና መታሰቢያ ሐውልታቸው ሲሠራ የፍቼ ከተማ ነዋሪዎች የሆኑ የእስልምና እምነት ተከታዮችም ጭምር ለግንባታ የሚሆን አሸዋ ከመርዳት አንስቶ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ ድንኳን እስከመትከል ተሳትፈዋል፡፡ በገንዘብም በጉልበትም ተባብረዋል፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀች በኋላ የአባታችንን እጅግ አኩሪ ታሪክ ሲያዘክራቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአ.አ መሐል ከተማ ላይ ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ የአባታችን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
(ከገድላት አንደበት)
✞ ✞ ✞

2% የመኖር እድል!😥አለም በመገረም ሚያስታውሰው ፈገግታ________________________________________________ጄን ማርክዚውስኪ (Night bird) American got ...
28/07/2023

2% የመኖር እድል!😥
አለም በመገረም ሚያስታውሰው ፈገግታ
________________________________________________
ጄን ማርክዚውስኪ (Night bird) American got talent በተባለው በዓለም ታዋቂ ውድድር የቀረበችበት ቪድዮ ለስርጭት ከበቃበት August 21/2021 ጀምሮ ባየሁት ቁጥር እምባ ይቀደመኛል፤ የመደመምና የመደነቅ ነው የማለቅሰው፤ በእርግጥ አዝኜላትም አለቅሳለሁ። በዋነኝነት ግን ጽናቷ፣ የእምነት ጥንካሬዋ፣ ተስፋዋ . . . ይደንቀኝና ሳላስበው እምባዬ ይወርዳል።

የሰው ልጅ እንዴት ይህን ያህል ይጸናል? "ከእንግዲህ የመኖር እድልህ 2% ነው" ሲባል ሁለት በመቶማ ዜሮ ማለት አይደለም - It is OK? ለማለት ምን ያህል የውስጥ ጥንካሬ ይጠይቃል?

የሆነው ሆኖ ከትናንት በስቲያ የከፋኝ ጊዜ ያቺን የመጀመሪያ የመድረክ ቪድዮዋ ዳግም YouTube ከፍቼ አየኋት - እንባዬ እየወረደ። እናም ያቺን ቅጽበት ላስቃኛችሁ ወደድኩት - እንደሚከተለው . . . ጄን ማርክዚውስኪ (Night bird)
~ የጽናት ተምሳሌት ~

(ዳኞች ተሰይመው አይኖቻቸው ወደመግቢያ በር እያማተሩ ተረኛ ተወዳዳሪ ይጠብቃሉ።

አንዲት ቀጠን ያለች መልከ መልካም ወጣት ወደመወዳደሪያ መድረኩ አመራች። ሉጫ ፀጉሯ ግንባሯ ላይ ተደፍቷል፤ ጂንስ ሱሪ በጥቁር ቲሸርት ለብሳለች። ፊቷ ላይ በሚያበራው ፈገግታ ደስተኛ ትመስላለች። )

💃 እንደቆመች - Hi, አለቻቸው

🕴ከዳኞቹ መካከል ሃዊ ማንደል/Howie Mandel 'Hi, How are you? ' አላት።

💃 I am awesome, I am happy to be here ብላ መለሰች

🕴 'ደስተኛ በመሆንሽ እኛም ደስተኛ ነን። ስምሽ ማነው? ' የሚል ጥያቄ አስከተለላት።

💃 "ጄን ማርክዚውስኪ እባላለሁ። ስዘፍን ግን የሌሊት ወፍ (Night bird) ልትሉኝ ትችላላችሁ" ብላ መለሰች።

🚶ሲሞን ጣልቃ ገብቶ 'በጣም ጥሩ፣ የሌሊት ወፍ?' ከማለቱ
🕴 ዳኛ ማንደል "ለመኖር ነው የምትዘፍኚው?" በማለት አከለ።

😁 ፈገግታዋ እየፈካ "አይ አሁን እንኳን አይደለም" ብላ ስትመልስ ሁሉም ዳኞች ስለማንነቷ ለማወቅ እንደጓጉ ቢያስታውቅባቸውም ለዓለም ህዝብ የጽናት፣ የስነ ልቦናና የአካል አሸናፊነት ተምሳሌትና ሀውልት ሆኖ ለዘላለም የምትኖር ወጣት ከፊታቸው መቆሟን ግን አላወቁም ነበር።

🕴 አሁንም ሲሞን ከየት ነው የመጣሽው? ሲል ጠየቃት፤ ከኦህዮ መምጣቷን ስትናገር ይበልጥ ትኩረቱን የሳበችው ማንደል "እሺ እድሜሽስ ስንት ነው?" በማለት ጠየቃት።
💃 ማርክዚውስኪ እድሜዬዬ 30 ነው" አለች።

🕴(ማንደል ቀጠለ) "እናም በ30 ዓመትሽ ህልምሽ ዘፋኝ መሆን ነው? እሺ ዛሬ ምንድነው የምትዘፍኝልን" በማለት ጥያቄ አስከተለ።

💃 "የምዘፍነው የራሴን ዘፈን ነው። ርዕሱ Its_ok_its_alright ይላል" አለች።

🕴(እንደመደንገጥ ብሎ) 'Its_ok?
💃 አዎ 'Its_ok'

🕴 አሁንም ማንደል ቀጠለ 'Its_ok ምንድነው መልእክቱ?" ሲል ጠየቃት።

😁 ጄን ማርክዚውስኪ ፈገግታዋና በራስ መተማመንዋ እየጨመረ "Its ok ያለፈው አንድ ዓመት የራሴ ታሪክ የሚገልጽ ነው" ከማለቷ
🕴(በዚህች ልጅ ጀርባ ያለው አስደናቂ የታሪክ ቋጠሮ ተሎ እንዲፈታለት የጓጓው ማንደል) " It is ok. እዚህ ከፊታችን የቆምሽው አንቺ ማነሽ?" በማለት ጥያቄ አቀረበላት።

💃 'እኔ በራሴ እዚህ የቆምኩ ነኝ/I am her by myself.'

🕴 ማንደል It is OK የሚለው ርዕስ በጣም መስጦታል። አሁንም 'It is OK, በምን ሥራ ነው ምትተዳደሪው?' በማለት ጠየቃት።

💃 ማርክዚውስኪ ምላሿን ቀጠለች "ላለፉት ጥቂት ዓመታት ምንም ሥራ አልሰራም፤ በካንሰር ተይዤ ለመኖር እየታገልኩኝ ነው"

🕴ማንደል ባነሳው ጥያቄ ተፀፀተ፤ በካንሰር ተይዛ ለመኖር የምትታገልን ወጣት ስለመተዳደሪያ ሥራ በመጠየቁ ራሱን ለመውቀስ አንገቱን ደፍቶ "ኦው በጣም አዝናለሁ" አለ።

😁 ማርክዚውስኪ ግን እሱን ለማጽናናት ይበልጥ ደስተኛ መስላ እየሳቀች 'ምንም ችግር የለም፣ It is OK፣ እኔ በጣም ደህና ነኝ' አለችው።

🚶ሲሞን አሁንም "እኔ ልጠይቅሽ እችላለሁ? አሁን እንዴት ነሽ?" ሲል ጠየቃት።

💃 በቅርቡ ታይቼ ነበር፣ ሳምባዬና የጀርባ አጥንቴ በካንሰር እንደተጎዳ ተነግሮኛል፤ በአጠቃላይ የመኖር እድሌ ከ2% እንደማይበልጥ ሀኪሞች አረጋግጠውልኛል።"

🚶 ሲሞን በሰማው ነገር በጣም ደንግጦና አዝኖ "ስለዚህ ደህና አይደለሽም ማለት ነው?"

💃 አይ በጣም ደህና ነኝ፣ በየትኛውም መንገድ ደህና ነኝ" ብላ ስትመልስ

🕴"የውብ ፈገግታሽ፣ የሚያበራ ፊትሽና የደስታሽ ምንጭ አሁን ማንም ማወቅ አይችልም" አለ ማንደል።

💃 ማንም ቢሆን እኔ የደረሰብኝን ያህል ተደራራቢ ከባድ ችግር ሊደርስበት አይችልም። ነገር ግን ምንም ቢደርስበት የውስጥ ጥንካሬና ጽናት አስፈላጊ ነው"

🙉 ከረጅም ቃለ ምልልስ በኋላ ሁሉም ደኞች በተቀላቀለ አድናቆትና ሀዘኔታ ተመስጠው ይታያሉ።

🕴 ማንደል "በጣም ጥሩ፣ እሺ አሁን ያዘጋጀሽውን ሙዚቃ አቅርቢልን" በማለት ጋበዛት።

በሚስረቀረቅ መረዋ ድምጽ:-

"I moved to California in the summer time
I changed my name thinking that it would change my mind
I thought that all my problems they would stay behind
I was a stick of dynamite and it was just a matter of time, yeah
Oh dang, oh my, now I can't hide
Said I knew myself but I guess I lied
It's okay, it's okay, it's okay, it's okay
If you're lost, we're all a little lost and it's alright
It's okay, . . . " አስተጋባች። ዳኞችና አዳራሹን የሞላው ህዝብ በጸጥታ፣ በአግራሞት፣ በመደነቅ፣ በመመሰጥ ስሜት ፀጥታን ቢያነግስም ብዙዎች እንባቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር። . . .
ስትጭርስ በጸጥታ ድባብ ሰው አልባ መሰሎ የነበረው አዳራሽ በጭብጭባ ተናጋ። ታዳሚውና ዳኞች ለክብሯ ከመቀመጫቸው ተነስተው ረጅም ጭብጨባ . . . ።

እጅግ የላቀ ተሰጥኦ ላላቸው ተወዳዳሪዎች የሚሰጠው የgolden buzzer ደወል የውድድሩ ባለቤትና ዳኛ ሲሞን ኮውል ተጫነ። አዳራሹ በእልልታና ፌሽታ ተናወጠ። . . .

ይህ ትዕይንት የተቀረጸበት ቪዲዮ በYouTube ከተጫነ ወደአንድ ዓመት ሆነው። እስከአሁን ከ60 ሚሊዮን በላይ የዓለም ህዝብ ተመልክቶታል።

ከዛች ቅጽበት ወዲህ CNN, CNBC እና BBCን ጨምሮ ይህቺ የዘመኑ አብሪ ኮኮብ የሆነች ወጣት የሚዲያዎች አጀንዳ ለመሆን በቅታ ነበር። ከዚህ መደረክ በኋላ በተለያዩ ሚዲያዎች እንደገለጸችውም ሀኪሞች "ከዚህ በኋላ የመኖር እድልሽ ከ2% አይበልጥም" ካሏት ወዲህ በውስጣዊ ጽናትና ጥንካሬዋ ጥቂት ዓመታትን ኖራለች። ሁልጊዜ ስለ መኖር እንጂ ስለበሽታዋና ስለመሞት አታስብም። በዚህ ላይ የካንሰር ህመምተኛ በመሆኗ ባለቤቷም ጥሏት ሄዶ ነበር።

በየአጋጣሚው "2% ማለት ዜሮ ፐርሰንት ማለት አይደለም ትላለች፤ የያዘኝ በሽታ ከእኔ አይበልጥም። በፍፁም ነገን አጨልሜ መመልከት አልፈልግም። ተስፋ ሳልቆርጥ ህይወትን መኖር ነው የምፈልገው። ተስፋ ተቆርጦ መኖር ህይወትም አይደለም። የአቅምን እየሞከሩ ችግሮች ቢኖሩም It's ok, it's alright እያሉ መኖር ይገባል" ትል ነበር።

ጄን ማርክዚውስኪ (Nightbird) ለአጭር ጊዜ ብቅ ብላ February 19, 2022 ከዚህ ዓለም ከመለየቷ ቀደም ብሎ ለፈረንጆች 2022 ዘመን መለወጫ CNN ላይ ቀርባ ነበር። ጋዜጠኛው በመደነቅ እስኪደመም ድረስ የደስታና የመኖር ተስፋ፣ የጽናትና በራስ የመተማመን ጣራ ላይ ሆና ማንም ሰው የመኖር እድሉ ተጠናቅቋል ቢባል እንኳን ያቺን ቅጽበት ከውስጥ በሚፈነቅል ፈገግታ ሊያሳልፋት እንደሚገባ ገልጻለች። ይህም በመጪው ዘመንም በዓለም ዙሪያ ሚሊዮኖችን ሲቀሰቅስ ብሎም ጽናትና ጥንካሬን ሲያላብስ ይኖራል።💩
ሃና ፌዴራሊትሶል ኤንጅል
©Hassen M.

በአዲስ አበባ የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነአዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕ...
28/07/2023

በአዲስ አበባ የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸውም በዘንድሮዉ የ 2015 የትመህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን አጠቃላይ 73 ሺህ 385 ተማሪዎች መፈተናቸውን አንስተዋል፡፡

ከነዚህ ውስጥም 70 ነጥብ 6 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን ነው የተናገሩት፡፡

ከ50 በመቶ እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡ መደበኛ ተማሪዎችም ወደ ቀጣዩ ክፍል እንደሚዘዋወሩ ጠቁመዋል፡፡

ተማሪዎች ውጤታቸውን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚለቀቁ ሊንኮች መመልከት እንደሚችሉም አስታውቀዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

 #አርጋኖን ዘአርብ📕                           ♨በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጽሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ፡፡ በየጊዜው በየሰዓቱ ምስጋናና ቅዳሴን ከማያቋርጹ ከትጉ...
28/07/2023

#አርጋኖን ዘአርብ📕

♨በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጽሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ፡፡ በየጊዜው በየሰዓቱ ምስጋናና ቅዳሴን ከማያቋርጹ ከትጉሃን መላእክት ማኅበር ጋራ ወደኔ ነዪ፡፡ ድንግል ሆይ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ማኅበር ከምዕመናን ሁሉ ጋራ ወደኔ ነዪ፡፡
💙ድንግል ሆይ ከቅዱሳን ሁሉ ማኀበር ጋራ ወደኔ ልትመጭ እወዳለሁ፤ ይልቁንም ከዚህ ከማኅሌታዊው አባትሽ ከዳዊት ጋራ ብትመጭ እፈቅዳለሁ፡፡ በተቃጠለ ፍቅር ስላንቺ ይጮሀልና እንዲህ ሲል፡፡
💙በጽዮን ለሚያድር እግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው ዳግመኛም ዳዊት እንዲህ አለ፤ ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ፡፡ እንዳትታወክም እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፡፡ (መዝ ፱፣ ፲፩) (፵፮፣ ፬፣ ፭)
💙ዳግመኛም ዳዊት እንዲህ አለ፡፡ ጽዮንን ክበቡ፡፡ በዙሪያዋም ተመላለሱ፡፡ በቤቷም ተናገሩ፡፡ በብርታቷም ልባችሁን አኑሩ፡፡ ታላላቁንም ቤቶቿን ለሚመጣው ትነግሩ ዘንድ አስቡ፡፡ (መዝ ፵፰፣ ፲፪፣ ፲፫)
💙 በቅድስት ድንግል ምን ያህል የከበደ ሥርዓት ሸክም ተሠራ፡፡ በቅድስት ኦሪት ላይ ቅዱስ ወንጌል፡፡ በቅዱሳን ነቢያት ላይ ቅዱሳን ሐዋርያት፤ በብሉይ ኪዳን ላይ ሐዲስ ኪዳን፤ ለእስራኤልም በተሰጠው የፍርድ መጽሐፍ ላይ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት የቀኖና መጽሐፍ ስለዚህም እንዲህ አለ፡፡
💙ሸክሟንም ትካፈላላችሁ፤ ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ ባለጊዜ ደግሞ ስለ ጥምቀት ልጆች በሥጋ ስለማይመኩ የእግዚአብሔር ልጆች ሊሆኑ ሥልጣን ስለ ሰጣቸው ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከሰው ፈቃድ ከሥጋዊ ፍትወት ከሥጋዊ ከደማዊ ስላይደሉ ይናገራሉ፡፡ (ዮሐ ፩፣ ፲፪፣ ፲፫)
💙 በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጽሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ፡፡ አምላክን በሥጋ የወለድሽ ከትንሽነቴ ጀምሮ ተስፋዬ አለኝታዬ አምባዬ መጸጊያዬ ጉልበቴ የመድኃኒቴ ሽቱ ብልቃጥ የመመከያየ አክሊል ክብሬ ገናንነቴ የራሴ ከፍ ከፍ ማያ ሆይ፡፡ በክርስቲያን ሥርዓት ጠብቂኝ፡፡
💙 በክርስቲያን ሃይማኖት አጽኝኝ፤ ክርስቲያን አድርጊኝ፡፡ ክርስቲያን ልባል በክርስቲያንነት ልኑር፡፡ ልጅሽም ባባቱ ምስጋና በክበበ ትስብእት በመንፈስ ቅዱስ በመጣ ጊዜ ክርስቲያን ሁኜ ልገኝ፡፡
💙 የኃጢአቴን ሥሯን ከኔ ላይ ንቀይልኝ፡፡ ጫፎቿ በሥጋዬ ላይ እንዳይረዝሙ፡፡ ከልቡናዬም የሥጋዊን ፈቃድ ግንድ ቁረጭ፤ እሾክ አሜከላ በላዬ እንዳይበቅል፡፡ ነፍሴንም የምታስጨንቃትን ወደ ጥፋትም የምታደርሸኝን የዚህን ዓለም ማማር ፈቃድከልቡናዬ አጥፊልኝ፤ እንድጎዳም አትተይኝ፡፡

👏አሜን ቅድስት ሆይ ለምኝልን👏

DOOR - is much smaller compared to the house,LOCK - is much smaller compared to the door.KEY -is the smallest to all, bu...
28/07/2023

DOOR - is much smaller compared to the house,

LOCK - is much smaller compared to the door.

KEY -is the smallest to all, but a key can open entire HOUSE..!!

Thus a small, thoughtful solution can solve major PROBLEMS.

የትዳር አጋሩን የገደለው ግለሰብ በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጣ***በሌላ ወንድ እጠረጥርሻለሁ በሚል ምክንያት ሚስቱን በመጥረቢያ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ተከሳሽ የእድሜ ልክ ፅኑ እ...
24/07/2023

የትዳር አጋሩን የገደለው ግለሰብ በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጣ
***
በሌላ ወንድ እጠረጥርሻለሁ በሚል ምክንያት ሚስቱን በመጥረቢያ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ተከሳሽ የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ውሳኔ ተላልፎበታል፡፡

ፍቃዱ ሽፈራው የተባለው ተከሳሹ ወንጀሉን የፈፀመው ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ/ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ቦታው አርሴማ አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ከሌላ ወንድ ጋር እጠረጥርሻለሁ በሚል ምክንያት ከጠዋቱ 3፡30 ሰአት ገደማ የ2 ልጆቹ እናት የሆነችውን የትዳር አጋሩን የተለያየ የሰውነት ክፍሏን በመጥረቢያ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል፡፡

ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሰሞኑን በዋለው ችሎት ተከሳሽ ፍቃዱ ሽፈራው ላይ ከእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጣት በተጨማሪ ከህዝባዊ መብቶቹ ለዘወትር እንዲሻር ውሳኔ አስተላልፎበታል ።

በትዳር አጋሮች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በመነጋገር መፍታት እና በዚህም የማይቻል ከሆነ ወደ ወንጀል ከመግባት ይልቅ ሌሎች ህጋዊ እና ሰላማዊ አማራጮችን መከተል ይገባል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን ያስተላልፋል፡፡

ዘገባ፡ ኢንስፔክተር እመቤት ሀብታሙ

የቆጡን አውርድ ብላ የብብቷን ጣለች ለቲክ ቶክ ጊፍት ብሎ አለቀሰ  ፤ አይኖቹ ማየት አቃታቸው። ናይጄሪያዊው ቲክ ቶከር Tembu ebere  100 ስአት አለቅሳለሁ ብሎ በቲክ ቶክ live በ...
24/07/2023

የቆጡን አውርድ ብላ የብብቷን ጣለች

ለቲክ ቶክ ጊፍት ብሎ አለቀሰ ፤ አይኖቹ ማየት አቃታቸው።

ናይጄሪያዊው ቲክ ቶከር Tembu ebere 100 ስአት አለቅሳለሁ ብሎ በቲክ ቶክ live በመግባት ማለቅስ ጀመረ ።
ጊፍት የሚወርድለት ይህ ግለሰብ ማለቀሱን ለሳምንት ቀጥሎ
በመጨረሻ ጊፍትም በጊፍት የሚላክለት ገነዘብ ሰበሰበ ።
የጊኒስ ሪኮርድ ባለቤትም ሆነ ። ነገር ግን 100 ስእት ካለቀሰ በኃላ አሁን ላይ አይኖቹ በጣም ስላለቀሱ አብጠው ማየት ተሰኗቸዋል::

ጭራሽ እንዳይጠፉ በከፍተኛ የህክምና ክትትል ላይ ይገኛል!

Address

Adis

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when wanos ze sina posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share