Mhs Media

Mhs Media This Media Is Provides Hot Information and Support humanity Anywhere.
ءالحمد الله ربلعالمين My Main Page

የአፋርና ሶማሌ ሕዝብን አብሮነት ለማጠናከር በትብብር መስራት ይገባል- ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋአዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋርና የሶማሌ ሕዝብን አብሮነት ይበልጥ ለማጠ...
17/03/2025

የአፋርና ሶማሌ ሕዝብን አብሮነት ለማጠናከር በትብብር መስራት ይገባል- ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋርና የሶማሌ ሕዝብን አብሮነት ይበልጥ ለማጠናከር በትብብር መስራት ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ ገለጹ።

የአፋር እና ሶማሌ ወንድም ሕዝብ የጋራ ኢፍጣር መርሐ ግብር በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ተካሂዷል።

ሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ በዚህ ወቅት፥ ረመዳን የአንድነት፣ የመተሳሰብ እና የመተጋገዝ ወር መሆኑን አውስተዋል።

ይሄን ታላቅ የወንድማማቾች የፍቅርና የመተሳሰብ ኢፍጣር ከአመራሮቹ አልፎ በሕዝቦች ዘንድ እርቅና ሠላምን ለማስረጽ ማዋል እንደሚገባ ተናግረዋል ።

በቀጣይም የሁለቱን ህዝቦች ወንድማማችነትና ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክሩ የልማትና የሰላም ግንባታ ሥራዎችን በትኩረት ማከናወን ይገባል ነው ያሉት።

በተያዘው ረመዳን ወር በሕዝቦች መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር እየተጉ ያሉ አካላትን አመስግነዋል።

የሰላም ሚኒስትር መሐመድ ኢድሪሰ በበኩላቸው ÷ ሁለቱ ክልሎች ተቀራርበው ዘላቂ ሰላም ለመገንባት የሚያደርጉት ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።

የሁለቱ ክልል ሕዝቦች በርካታ የሚያስተሳስሯቸው ጉዳዮች እንዳሉ ጠቁመው÷ይህን ትስስር ለማጠናከርና ወንድማማችነትን ለማጉላት የተጀመረው ጥረት መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የሠላም፣ የእርቅ፣ የፍቅር ወር በሆነው የረመዳን ወር ምሽት በተካሄደው የሠመራ የጋራ ኢፍጣር ላይ የሁለቱ ክልል አመራሮች ዳግም ግጭት ውስጥ ላለመግባት ቃል ገብተዋል።

17/03/2024

ሰሞኑን በአየር መንገዳችን እና በንግድ ባንካችን ላይ እየተከሄደ ያለዉ ዘመቻ ሊቆም ይገባል።
===========================
"የማይረባ ብልት ለእናት ይገተራል አሉ" ይህ አባባል ነዉር አዘል ቢሆንም ትክክል ላልሆነ ተግባር ትክክል ያልሆነ አባባል ይመጥናል ብዬ ነዉ።

ሰሞኑን አቅጣጫ የጠፋባቸዉ የአገራችን ነፃ አውጪ ነን ባዮች ጥቃታቸዉን የአገር መከታ በሆኑ እንደ አየር መንገድ እና ንግድ ባንክ ባሉ የአገራችን አንጡራ ሃብት በሆኑ ተቋማት ላይ አናጣጥሯል።

እንዲህ ማድረጋቸው ባንዳነታቸዉን እንጂ ነፃ አዉጪነታቸዉን በፍጹም አያመላክትም። አገሩን የሚወድ እና ለአገሩ የተሻለ እሰራለሁ የሚል ለግል ጥቅሙ ስል አገሩን አሳልፎ አይሰጥም። በአገር ሀብት ላይ አላስፈላጊ ዘመቻ መክፈት ደግሞ አገርን አሳልፎ እንደመስጠት ነዉ።

ለነገሩ የተሻለ ሀሳብ አለኝ የሚል መጀመርያዉኑ ሃሳቡን ለዉድድር አቅርቦ በሃሳብ ልእልና ልቆ በመገኘት አሸናፊ ይሆናል እንጂ የአገር ሀብት እና ቅርፅ የሆኑ ተቋማትን ስም በመጉደፍ፣ አገር በማሸበርና በማዋከብ፣ ህዝብን በማጋጨት እና በመግደል ስልጣንን በአቋራጭ ለመቆናጠጥ አይጥርም። ይህ ሆድ እንጂ ጭንቅላት የሌላቸው ባንዳዎች ተግባር በመሆኑ በአስቸኳይ መቆም አለበት ባይ ነኝ።

አቶ  ደመቀ መኮንን የዓለም አቀፉ የጥቁር ሕዝቦች የታሪክ፣ የቅርስና የትምህርት ማዕከል የጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡማዕከሉ የጥቁር ህዝቦችን ታሪክ ቅርስ እና ትምህርት መሰረት ያ...
24/02/2024

አቶ ደመቀ መኮንን የዓለም አቀፉ የጥቁር ሕዝቦች የታሪክ፣ የቅርስና የትምህርት ማዕከል የጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

ማዕከሉ የጥቁር ህዝቦችን ታሪክ ቅርስ እና ትምህርት መሰረት ያደረገ ስራ የሚያከናውን ሲሆን÷ ደረጃውን የጠበቀ የምርምር ማዕከልን የማቋቋም እና የተሻለ የትምህርት ስርዓት በመፍጠር በራሱ መተማመ የሚችል ወጣት እንዲፈጠር የሚሰራ ይሆናል ተብሏል።

EBC

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ወደ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ እንዳይገባ ለመከልከል ተሞክሯል” ብለዋል።የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ በራሳቸው እና በልኡካቸው ላይ ደርሷል ስላሉት መጉላላት ላይ ...
17/02/2024

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ወደ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ እንዳይገባ ለመከልከል ተሞክሯል” ብለዋል።

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ በራሳቸው እና በልኡካቸው ላይ ደርሷል ስላሉት መጉላላት ላይ የኢትዮያ መንግስት ምለሽ ሰጠ።

37ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን፤ የሶማያሊው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃድ ወደ ስብሰባው እንዳይገቡ የመከልከል ሙከራ እንደተደረገባቸው አስተውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ ከስብሰባው መክፈቻ በኋላ በሰጡት መግለጫ፤ በዝግ በሚደረገው ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ በሚሞክሩበት ጊዜ የኢትዮያ የጽታ ኃይሎች ካረፉበት ሆቴል እንዳይወጡ መንገድ ዘግተው እንደከለከሏቸው ገልጸዋል።

“በሌላ ፕሬዝዳንት መኪና ከሆቴል በመውጣት የስብሰባው ስፍራ ብደርስም፤ የፀጥታ አካት እንዳንገባ ክልከላ አድርገውብን ነበር ብለዋል” ፕሬዝዳቱ በመግለጫቸው።

በኋላ ላይ ግን ፕሬዝዳነቱ ወደ ስብሰባው መግታቸው እና በስብሰባው መክፈቻ እንዲሁም የቤተሰብ ፎቶ ላይም ታይተዋል።

የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ከሰዓት ላይ በሰጠው መግለጫውም፤ “የኢትዮጵያ መንግስት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት እና ልኡካቸው ወደ 2024 የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ እንዳይገቡ ያደረገውን ሙከራ የሶማሊያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ መንግስ በጽኑ ያወግዛል” ብሏል።

የኢትዮጵያ መንግስት ድርጊት የዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ደንብን የሚጥቀስ ነው ያለው የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ የአፍሪካ ኅብረትን የቆየ ባህል የሚቃረን በመሆኑ ህብረቱ ጉዳዩን በገለልተኛ ሆኖ እንደሚረምርም ጠይቋል።

#የኢትዮጵያ መንግስት ምን ምላሽ ሰጠʔ

አል ዐይ ኒውስ በጉዳዩ ላይ ከምንግስት ኮሙዩኒኬሽን ባገኘው ምላሽ “የኢትዮጵያ መንግሥት ለአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ለመጡ ሁሉም ሀገራትና መንግስታ መሪዎች ያደረገውን የክብር አቀባበል ለሶማሊያ ፕሬዚዳንት ማድረጉን አስታውቋል።

እንደ አስተናጋጅ ሀገር ኢትዮጵያ የሁሉንም ሀገራትና መንግስታት መሪዎችን በቆይታው ደህንነታችቸውን የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበትም አስታውቋል።

ነገር ግን የሶማሊያ ፕሬዝዳት ልኡካን በመንግሥት የተመደበላቸውን የፀጥታ አካላት አንቀበልም ማለታቸውን ነው አል ዐይን ኒውስ ከኢትዮጵያ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ያገኘው መግለጫ ያመለክታል።

ከዚህ በላይ ግን የሶማሊያ ልዑክ የደህንነት አባላት የጦር መሳሪያ ታጥቀው ወደ አፍሪካ ኅብረት ለመግባት ሲሞክሩ በኅብረቱ የፀጥታ አካላት መከልከላቸውን ገልጿል።

በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት የሶማያው ፕሬዝዳንት እና የልኡካቸውን ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር በስብሰባው ላይ እንዳይገኙ እንዳላደናቀፈ እንዲሁም ወደ ኅብረቱ ቅጥር ጊዜ እንዳይገቡ እንዳልከለከለ አሳውቋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር መልካም ግንኙነት ለመፍጠር ቁርጠኛ አቋም እንዳላትም ነው የእኢትዮጵያ መንስት ኮሙዩኒኬሽን መግለጫ የሚያመላክተው።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ባለው የፈረንጆቹ ጥር አንድ ቀን በፈረሙት የመግባቢያ ሰነድ ምክንያት ቁጣቸውን ያሰሙት የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሀሰን ሸክ መሀመድ ትናንት አዲስ አበባ መግታቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና የሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ የፈረሙት የመግባቢያ ሰነድ፣ ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና ሰጥታ በምላሹ 20 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው የባህር ጠረፍ በ50 አመት የሊዝ ኪራይ እንድታገኝ የሚያስችል መሆኑ በወቅቱ ተገልጾ ነበር።

ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አካል አድርጋ የምታያት ሶማሊያ በስምምነቱ ከፍተኛ ቁጣ በማሰማት ከአምባሳደሯን ከኢትዮጵያ መጥራቷም ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በቀረቡበት ወቅት ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር ግጭት ውስጥ የመግባት ፍላጎት የላትም ብለዋል።

ምንጭ:- Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

በአዲስ አበባ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በዛሬው እለት በይፋ ተመርቋል።በ5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ሙዚየም የኢትዮጵያውያን ጀግኖች ለመላው ጥቁር ህዝብ ኩራት የሆነ ተጋድሏቸ...
11/02/2024

በአዲስ አበባ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በዛሬው እለት በይፋ ተመርቋል።

በ5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ሙዚየም የኢትዮጵያውያን ጀግኖች ለመላው ጥቁር ህዝብ ኩራት የሆነ ተጋድሏቸውን የሚዘክሩ ስራዎችን ይዟል።

የአድዋ ድል መሃንዲሶች አፄ ምኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል እንዲሁም የ12ቱ የጦር መሪዎች ሀውልትም በሙዚየሙ ውስጥ ይገኛሉ።

የዓድዋ ድል የክተት አዋጅ የታወጀበት ነጋሪት በነሐስ ተሰርቶ ለእይታ ቀርቧል።

በ4ቱም አቅጣጫዎች የተለያዩ ስያሜ የተሰጣቸው የሙዚየሙ በሮችም በዓድዋ ድል ከአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያውያን በጋራ የተሳተፉበት መሆኑን ያመለክታል ብሏል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር።

ሙዚየሙ ከምድር በታች ያለውን ሁለት ደረጃዎችን ጨምሮ 5 ወለሎች ያሉት ሲሆን፥ ከ1 ሺህ በላይ የመኪና ማቆሚያዎችን ጨምሮ በርካታ አዳራሾችና መዝናኛ ስፍራዎችንም አካቷል።

የሩሲያ ስትራቴጂክ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በአሜሪካ ድንበር መብረራቸው ተገለጸ።አውሮፕላኖቹ ዓለም አቀፍ የዐየር ክልሎችን ተከትለው እንደበረሩ ተገልጿል።የሩሲያ ስትራቴጂክ ቦምብ ጣይ አውሮፕላ...
10/02/2024

የሩሲያ ስትራቴጂክ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በአሜሪካ ድንበር መብረራቸው ተገለጸ።

አውሮፕላኖቹ ዓለም አቀፍ የዐየር ክልሎችን ተከትለው እንደበረሩ ተገልጿል።

የሩሲያ ስትራቴጂክ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በአሜሪካ ድንበር መብረራቸው ተገለጸ፡፡
ቱ-95ኤምሲ የተሰኙ ስትራቴጂክ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በአሜሪካ ድንበር አቅራቢያ መብረራቸው የብዙዎችን ትኩረት ስቧል፡፡

ያለማቋረጥ ለዘጠኝ ሰዓታት መብረር ይችላሉ የሚባሉት እነዚህ ዘመናዊ የጦር አውሮፕላኖች አላስካ በምትሰኘው የአሜሪካ እና ካናዳ ድንበር አቅራቢያ በረዋል ተብሏል፡፡

የሰሜን አሜሪካ አየር መቆጣጠሪያ እዝ አራት የሩሲያ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች የአላስካ አየር ክልልን ጥሰው ገብተዋል ያለ ሲሆን የአውሮፕላኖቹን በረራ ሲከታተላቸው እንደቆየ አስታውቋል፡፡

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖቹ በአሜሪካዋ አላስካ የበረሩት ዓለም አቀፍ የበረራ መስመርን ተከትለው እንጂ የማንኛውንም ሀገር ሉዓላዊነት አልጣሱም ብሏል፡፡

ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዓመታ በፊት በሰጡት ቃለ መጠይቅ ስትራቴጂክ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖቻችንን ወደ ቀድሞ ሶቪየት ህብረት ግዛት ወደ ሆኑ ቦታዎች እንልካለን ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

በ26 ዓመቷ የ22 ልጆች እናት የሆነችው ሩሲያዊት
ቱ-95 የተሰኘው የሩሲያ ሰራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን አራት ሞተር የተገጠመለት ዘመናዊ የውጊያ አውሮፕላን ሲሆን አሜሪካ ቢ-52 የተሰኘውን ተመሳሳይ የውጊያ አውሮፕላን አላት፡፡

የበረዶ ግግር የማይጠፋባት አላስካ ግዛት ከ65 ዓመት በፊት ወደ አሜሪካ የተካለለች ሲሆን አሜሪካን ከካናዳ እና ሩሲያ ጋር ታዋስናለች፡፡

ከአንድ ሚሊዮን በታች ህዝብ የሚኖርባት አላስካ ግዛት በደሴቶች እና ውሃማ አካላት የተሞላች ቁልፍ አካባቢ ስትሆን አሜሪካ ወደ አውሮፓ እና እስያ በቀላሉ እንድትገናኝ ለማድረግ አመቺም ናት፡፡

ምንጭ:- Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

በጣልያን ተወስዳ የነበረችው የመጀሪያ የኢትዮጵያ አውሮፕላን "ፀሐይ" አዲስ አበባ ገባች።"ፀሐይ" አውሮፕላን በ"አድዋ ድል መታሰቢያ" ሙዚየም እንደትቀመጥ ተደርጓል።በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ...
10/02/2024

በጣልያን ተወስዳ የነበረችው የመጀሪያ የኢትዮጵያ አውሮፕላን "ፀሐይ" አዲስ አበባ ገባች።

"ፀሐይ" አውሮፕላን በ"አድዋ ድል መታሰቢያ" ሙዚየም እንደትቀመጥ ተደርጓል።
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰራችው "ፀሐይ" የሚል መጠሪያ የተሰጣት አውሮፕላን ትናንት ምሽት ላይ አዲስ አበባ መድረሷ ተነግሯል።
በጣሊያን ተወስዳ የነበችረው አውሮፕላን ባሳለፍነው ሳምንት ለኢትዮጵያ ተመልሳ መሰጠቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ማስታወቁ ይታወሳል።

በፈረንጆቹ በ1935 በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ ተገጣጥማ በረራ ያደረገችው ፀሐይ አውሮፕላን ከበርካታ ዓመታት በኋላ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ደርሳለች።

ከጣሊያን ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰችው "ፀሐይ" አውሮፕላን በ"አድዋ ድል መታሰቢያ" እንደትቀመጥ መደረጉም ተነግሯል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ "ፀሐይ" አውሮፕላንን በዛሬው ዕለት ተረክበው በዓድዋ ድል መታሰቢያ ለጎብኝዎች ምቹ በሆነ ስፍራ ማኖራቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው አስታውቀዋል።

"ፀሐይ" በኢትዮጵያ የተሰራችው የመጀመሪያ አውሮፕላን አውነታዎች!
"ፀሐይ" በ1935 ዓ.ም ሄር ሉድዊግ ዌበር የተባለው ጀርመናዊ ኢንጂነር እና የንጉሱ ፓይለት በወቅቱ ከነበሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የተሰራች የመጀመሪያው አውሮፕላን ነች።

አውሮፕላኗ "ፀሐይ" የሚለውን ስያሜውም የቀዳማዊ ኃይለስላሴን ልጅ ልዕልት ፀሐይን ለማሰብ የተሰጠ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ፀሐይ ባለሁለት መቀመጫ እና ሁለትዮሻዊ መቆጣጠሪያ ያላት ብሎም የባለከፍተኛ ኃይል ሞተር ባለቤት ተደርጋ የተሰራች አውሮፕላን ነች።

"ፀሐይ" ኮምፓስ፣ የአብራሪ መቆጣጠሪያዎች፣ ሁለት ያለ ፍሬን ማቆሚያ የተገጠሙ የማረፊያ ሽክርክሪቶች እንደነበራም ተመላክቷል።

የ"ፀሐይ" አውሮፕላን ሞተር ባለሰባት ሲሊንደር ዋልተር ቪነስ ሲሆን የውሃ ማቀዝቀዣ ስርዓት የነበረው የ115 የፈረስ ጉልበት ባለቤትም ነበር።
"ፀሐይ" ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በፊት በኢትዮጵያ የተሰራች ብቸኛ አውሮፕላን ነበረች።

ፀሐይ በውስን ሃብት እና ስፍራ በጊዜው የነበሩትን አናፂዎች እውቀት እና የእጅ ጥበብ በመጠቀም የተሰራች አውሮፕላን ሲትሆን ፤ የ1930ዎቹ የአቪየሽን ጥረት ማሳያ ሆና የተረፈች አውሮፕላን ነች።

ምንጭ:- Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

"ከሶማልያ ቶሎ ካልወጣችሁ መጥተን እናጠፋችኋለን ብለው እየዛቱብን ነው፣ ስለዚህ መንግስት በአስቸኳይ ወደ ሀገራችን ይመልሰን"--- በሶማልያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ካደረሱኝ መረጃ የተወሰደ ከ...
07/02/2024

"ከሶማልያ ቶሎ ካልወጣችሁ መጥተን እናጠፋችኋለን ብለው እየዛቱብን ነው፣ ስለዚህ መንግስት በአስቸኳይ ወደ ሀገራችን ይመልሰን"--- በሶማልያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ካደረሱኝ መረጃ የተወሰደ

ከአራት ቀን በፊት የአልሸባብ አባላት እንደሆኑ የተገመቱ ታጣቂዎች ስድስት ኢትዮጵያውያንን እና አንድ የሶማልያ ዜጋን በለሊት ቤታቸው ድረስ በሞተር ሳይክል በመሄድ ከገደሉ በኋላ ተጨማሪ ዛቻ እና ማስፈራርያ እየደረሳቸው እንደሆነ እነዚህ ዜጎቻችን በቴሌግራም አሳውቀውኛል።

በደቡብ-ምዕራብ ሶማሊያ በለድ ሀዎ ከተማ በተፈፀመው በዚህ ጥቃት የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር የታወቀ ሲሆን ይህ ጥቃት እንዲፈፀም በሶማልያ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች እና በአንዳንድ የሀገሪቱ ፖለቲከኞች ጭምር ጥሪ ሲደረግ እንደነበር ይታወሳል።

እነዚህ በመዲናዋ ሞቃዲሾ እና ሌሎች በርካታ ስፍራዎች የሚኖሩ ዜጎች "በቅርቡ ተመሳሳይ ጥቃት ይፈፀምብናል ብለን ስጋት አለን፣ ስለዚህ መንግስት በአስቸኳይ ወደ ሀገራችን ይመልሰን" ብለዋል።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ የወደብ አጠቃቀምን በተመለከተ ከአንድ ወር በፊት የተፈራረሙትን የመግባብያ ሰነድ ተከትሎ ሶማሊላንድ የሉአላዊ ግዛቴ አካል ነች በምትለው ሶማልያ እና ኢትዮጵያ መሀል በቅርብ አመታት ታይቶ የማይታወቅ ውጥረት እና ውዝግብ እንደተነሳ ይታወቃል።

ምንጭ:- Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

የሀውቲ ታጣቂዎች በአሜሪካ እና በዩኬ መርከቦች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን አስታወቁ።የሀውቲ ቃል አቀባዩ በአሜሪካ እና ዩኬ መርከቦች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቀጥላል ሲል ተናግሯል።የሀውቲ ታጣቂዎ...
06/02/2024

የሀውቲ ታጣቂዎች በአሜሪካ እና በዩኬ መርከቦች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን አስታወቁ።

የሀውቲ ቃል አቀባዩ በአሜሪካ እና ዩኬ መርከቦች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቀጥላል ሲል ተናግሯል።

የሀውቲ ታጣቂዎች በሁለት የአሜሪካ እና የዩናይትድ ኪንግደም(ዩኬ) መርከቦች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን የሀውቲ ጦር ቃል አቀባይ ማስታወቁን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

ቃል አቀባዩ ያህያ ሳሪአ "በቀይ ባህር ላይ ሁለት ወታደራዊ ጥቃቶችን ፈጽመናል፤ አንደኛው ጥቃት 'ስታር ናሲያ' በተባለችው የአሜሪካ መርከብ ላይ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ 'ሞርኒንግ ታይድ' በተባለች የዩኬ መርከብ ላይ ነው" ብሏል።

እንደቃል አቀባዩ ከሆነ ሁለቱም መርከቦች በናቫል ሚሳይል ቀጥትኛ እና ትክክለኛ ጥቃት ደርሶባቸዋል።
ጥቃቱን የፈጸሙት ለፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን ሀማሰ አጋርነት ለማሳየት መሆኑን የገለጸው ቃል አቀባዩ በአሜሪካ እና ዩኬ መርከቦች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቀጥላል ብሏል።

ከሰአታት በፊት የዩኬ የማሪታይም ትሬድ ኦርጋናይዜሽን የዩኬ መርከብ በሀውቲ ቁጥጥር ስር ካለው ሆዲህ ወደብ አቅራቢያ በሚሳይል መመታቷን የሚያሳይ ሪፖርት መቀበሉን ገልጾ ነበር።
ድርጁቱ መርከቧ መካከለኛ የሚባል ጉዳት እንደደረሰባት እና አሁንም እየተጓዘች መሆኑን ጠቅሷል።

የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ በትናንትናው እለት አሜሪካ በወሰደችው ራስን የመከላከል እርምጃ ሁለት የሀውቲ ድሮኖችን መትቻለሁ ብሏል። አሜሪካ እንደገለጸችው እነዚህን ሁለት ድሮኖች በሀውቲ ቁጥጥር ስር ባሉ ቦታዎች በመለየት ጥቃት ሳያደርሱ አስቀድማ እርምጃ ወስዳባቸዋለች።

በቀይ ባህር ያለውን የመርከቦች እንቅስቃሴ ሰላማዊ አደርጋለሁ የምትለው አሜሪካ፣ በሀውቲ ታጣቂዎች ይዞታ ላይ አጋሮቿን በማሳተፍ ጥቃት እያደረሰች ትገኛለች።

ምንጭ:- Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

ግብጽ በቀይ ባህር ቀውስ ምክንያት በየወሩ ከ370 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እያጣሁ ነው አለች።የእስራኤል-ሐማስ ጦርነት የዓለም ባህር ትራንስፖርት ዋጋ እንዲያሻቅብ አድርጓል። አራት ወራት ሊ...
04/02/2024

ግብጽ በቀይ ባህር ቀውስ ምክንያት በየወሩ ከ370 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እያጣሁ ነው አለች።

የእስራኤል-ሐማስ ጦርነት የዓለም ባህር ትራንስፖርት ዋጋ እንዲያሻቅብ አድርጓል።

አራት ወራት ሊሆኑት ሶስት ቀናት ብቻ የቀረው የእስራኤል-ሐማስ ጦርነት መቋጫ ያላገኘ ሲሆን የዓለምን ኢኮኖሚ በመጉዳት ላይ ይገኛል፡፡
በዚህ ጦርነት አሜሪካ ለእስራኤል የቀጥታ ድጋፍ ማሳየቷን ተከትሎ የየመን ሂቲ አማጺያን ከእስራኤል እና አሜሪካ ጋር ግንኙነት ያላቸውን መርከቦች በመምታት ላይ ናቸው፡፡
ይህንን ተከትሎም የቀይ ባህር ትራንስፖርት በስጋት እንዲሞላ በማድረጉ የዓለም ሎጅስቲክስ ኩባንያዎች ይህን የንግድ መስመር ከመጠቀም እየተቆጠቡ ይገኛሉ፡፡
የግብጹ ስዊዝ ካናል ዋነኛ የመርከቦች መተላለፊያ ሲሆን በቀይ ባህር ቀውስ ምክንያት ያስተናግዳቸው የነበሩ መርከቦች መቀነሳቸው ተገልጿል፡፡
አዲሱ የፈረንጆቹ 2024 ከገባ ወዲህ ባሉት ቀናት ያስተናገዳቸው መርከቦች ቁጥር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ46 በመቶ ቅናሽ ማሳየታቸውን አልአረቢያ ዘግቧል፡፡
እንደዘገባው ከሆነ ስዊዝ ካናል የሚያስተናግዳቸው መርከቦች ቁጥር በ30 በመቶ እንደቀነሰ የስዊዝ ካናል ባለስልጣን ሀላፊ ኦሳማ ራቢ ተናግረዋል፡፡
ግብጽ ባሳለፍነው ጥር ወር ላይ 804 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታ የነበረ ሲሆን ይህ ገቢ ወደ 428 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል፡፡
በቀይ ባህር ትራንስፖርት ቀውስ ምክንያት ግብጽ ከስዊዝ ካናል የምታገኘው ገቢ በ46 በመቶ ሲቀንስ የመርከቦች ቁጥር ደግሞ የ36 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል፡፡
የእስራኤል-ሐማስ ጦርነት በቶሎ እልባት ካልተበጀለት የዓለምን ንግድ የበለጠ ሊጎዳው እንደሚችልም ተሰግቷል፡፡
ስዊዝ ካናል የግብጽ ዋነኛ የገቢ ምንጭ ሲሆን በየዓመቱ የምታገኘው ገቢ በየጊዜው እየጨመረ በመምጣት ላይ እንደነበርም ተገልጿል፡፡
ግብጽ ከስዊዝ ካናል ባሳለፍነው 2023 ዓመት 9 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ስታገኝ በ2022 ደግሞ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታበት ነበር፡፡
የዓለምን ንግድ በማሳለጥ የሚታወቀው የስዊዝ ካናል በዓመት 25 ሺህ መርከቦች የሚመላለሱበት ሲሆን ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ቶን በላይ እቃም ይጓጓዝበታል፡፡
በቀይ ባህር ባጋጠመው ቀውስ ምክንያት የዓለም የመርከብ እቃ ማጓጓዣ እና የመድህን ዋጋ በሶስት እጥፍ አሻቅቧል የተባለ ሲሆን ቀውሱ እልባት ካልተበጀለት የዓለም ምግብ እና ነዳጅ ዋጋ የበለጠ እንዲጨምር ያደርጋልም ተብሏል፡፡

ምንጭ:- Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

Address

Semera Afar
Afar
7240/254

Telephone

+251912632449

Website

https://t.me/realmhsmedia

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mhs Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mhs Media:

Share

Category