Halaba Tv

Halaba Tv This is the official Halaba TV page - where you can get all the latest information's in diff

Halaba TV detail contact information:
https://t.me/halabatelevision

ቃል በተግባር ከUAEአብዱልቃድር  ከማል   ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አልአይን ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራቸውን ለማኖር ቃል ከገባው አምስት መቶ ሺ ብር ውስጥ 100,000 (...
05/07/2025

ቃል በተግባር ከUAE

አብዱልቃድር ከማል ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አልአይን ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራቸውን ለማኖር ቃል ከገባው አምስት መቶ ሺ ብር ውስጥ 100,000 (አንድ መቶ ሺ) ብሩን ገቢ አድርጓል።

እናመሰግናለን!!

የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና አርሶአደሩ ከአስከፊው ድህንነት እንድወጣ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል -  ክቡር አቶ መሀመድከማል *********ሰኔ 28/2017 የሀላባ ዞን ብልጽግና ...
05/07/2025

የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና አርሶአደሩ ከአስከፊው ድህንነት እንድወጣ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል - ክቡር አቶ መሀመድከማል
*********
ሰኔ 28/2017 የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሀመድከማል ኑሪዬ የሚመራ ልኡክ በዌራ ወረዳ ሙዳመያፋ ቀበሌ ባህርዛፍና ሌሎች የተለያዩ እንጨት የተነሳበት ቦታ የቡና ችግኝ ተከለ ተከናውነዋል።

በዚህ ወቅት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሀመድከማል ኑሪዬ እንደገለጹት የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና አርሶአደሩ ከአስከፊው ድህንነት እንድወጣ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

አርሶአደሮች ተሞክራቸውን በመቀበል ምርት የማይሰጡት በማሳቸው ያሉትን የቡና ችግኝ መትከል የሁልጊዜ ልምድ መኖር ይገባል ብለዋል።

የተጀመረውን ቡና ተከላ ለማስፋት ሁሉም ርብርብ እንዲያደርጉ የመንግስት ተጠሪ አቶ መሀመድከማል ኑሪዬ አሳስበዋል።

ቡና ችግኝ ለመትከል ሁሉም አርሶአደር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲያሳድጉ አስገንዝበዋል።

የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳደርና ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ ባህር ዛፍን በመንቀል ቡናንን በመተካት፣ የቡናን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አርሶአደሩ የቡና ምርትና ምርታማነቱን ለመጨመር የማይባለውን በመንቀል የሚባለውን ነገር በመተካት የምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትና ማረጋገጥ እንደሚገባ አቶ ሀጂ ኑሪዬ አሳስበዋል።

ቡና ምርታማነት በመጨመር የአርሶአደሩን ህይወት ለመቀየር በተወሰደው አቋም በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

ቡና ልማትን ስኬታማ ለማድረግ ለማስፋፋት እየተደረገ በለው ጥረት የዘርፉ አመራሮችና የግብርና ባለሙያዎች የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር የሴ እንደገለጹት
በባህር ዛፍና በተለያዩ እንጨት የተያዘውን ሰፊ መሬት ነጻ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚያስችል መንገድ በቡና ልማት ላይ እንዲውል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ባህር ዛፍ በመንቀል ቡናን፣ እንሰትን፣ ፍራፍሬን እና ሌሎችን የሚበላ ነገሮችን የመተካት ስራ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የሀላባ ዞን ቀይ መስቀል ቅ/ጽ/ቤት የቀይ መስቀል ምስረታ 90ኛ ዓመት ክብረ በዓል በድምቀት አክብረዋል።******ሰኔ 28/2017 ዓ.ም ፦ሀላባ ቲቪየሀላባ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት...
05/07/2025

የሀላባ ዞን ቀይ መስቀል ቅ/ጽ/ቤት የቀይ መስቀል ምስረታ 90ኛ ዓመት ክብረ በዓል በድምቀት አክብረዋል።
******
ሰኔ 28/2017 ዓ.ም ፦ሀላባ ቲቪ
የሀላባ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የማህበሩን የ90ኛ ዓመት ክብረ በዓል የማህበሩ የክልልና የዞን ስራ አመራር ቦርድ አባለት በተገኙበት በተለያዩ መርሃ ግብር አክብረዋል።

የማህበሩ ሰራተኞች፣ በጎ ፈቃደኞች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካለት በተገኙበት በከተማ ጽዳት፣ በእግር ጉዞ እና የፍራፍሬ ችግኝ ተከላ በማከናወን በድምቀት አክብረዋል።

በአከባበሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሃላፊና የክልሉ ቀይመስቀል ቦርድ አባል ወ/ሮ ባይዴ ሙንድኖ ፣የዞኑ ቀይመስቀል ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሰይፈዲን ቱሊሳ ፣የዞኑ የቦርድ ተወካይ አቶ አብዱልቃድር ጌትቻ ፣የማህበሩ ሰራተኞች፣ በጎ ፈቃደኞች ተገኝተዋል።

በተቀናጀ ጤና ዘመቻ በተሰሩ ሥራዎች የሚታይ ለውጥ መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።*** #ቢሮው በበጀት ዓመቱ በተቀናጀ ዘመቻ የተከናወኑ ተግባሮች ግምገማና እውቅና ...
05/07/2025

በተቀናጀ ጤና ዘመቻ በተሰሩ ሥራዎች የሚታይ ለውጥ መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።
*** #
ቢሮው በበጀት ዓመቱ በተቀናጀ ዘመቻ የተከናወኑ ተግባሮች ግምገማና እውቅና የመስጠት መድረክ በሆሳዕና ከተማ አካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንዳሉት፦ በተቀናጀ ጤና ዘመቻ በተሰሩ ሥራዎች የሚታይ ለውጥ ተመዝግቧል።

አቶ አሸናፊ፦ በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ምክንያቶች ያልተከተቡ ህጻናትን በመለየት በቂ የክትባት አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ተደርጓል።

በዚህ ሂደት 2 መቶ 36 ሺህ 3 መቶ 85 የነፍሰ ጡርና አጥቢ እናቶች ልየታ ተደርጎ የምግብ እጥረት ያለባቸውን አገልግሎት እንዲያገኙ አስቻይ ሁኔታዎች መፈጠሩን አክለዋል አቶ አሸናፊ።

ከ5 ዓመት በታች ያሉ 1 ሚሊዮን 1 መቶ 68 ሺህ 6 መቶ 59 ህጻናትን በመለየት የምግብና ህክምና አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ተደርጓል ነው ያሉት ኃላፊው።

በተጨማሪ 1 ሺህ 6 መቶ 51 የታመሙ ህጻናትን በመለየት ከጤና ተቋማት ጋር በማገናኘት ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እድል ተፈጥሯል ሲሉም ተደምጠዋል አቶ አሸናፊ።

አቶ አሸናፊ፦ በበጀት ዓመቱ በተሰሩ የጤና ዘመቻዎች ላይ የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ እውቅናና ምስጋና አቅርበዋል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን በበኩላቸው፦ በድጋፋዊ ክትትል ሥራዎች የተቀናጁ የጤና ዘመቻዎች በጥንካሬ የተሰሩ ናቸው ብለዋል።

በቀጣይ የተመዘገበው ውጤት ተግባራት በማቀናጀት የተገኘ መሆኑን ገልጸው በቀጣይም በክልሉ ወረርሽኞችን አስቀድሞ መከላከል የሚችል የጤና ስርዓት መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡

አቶ ማሙሽ፦ በበጀት ዓመቱ በነበረው ጤና ዘመቻዎች የመገናኛ ሚዲያዎች የጎላ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው እውቅናና ምስጋና አቅርበዋል።

በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጤና መምሪያዎች፣ ጽ/ቤቶች፣ መድኃኒት አቅራቢዎችና አጋር አካላት የእውቅና ሰርትፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ መጠነ ሰፊ የተቀናጀ የጤና ዘመቻ ሲያካሄድ ቆይቷል። የኩፍኝ ክትባት፣ የካችአፕ ክትባት፣ የሥርዓተ ምግብ፣ የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎቶችና የቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ዘመቻዎች ተደርጓል።
ዘገባው የክልሉ ጤና ቢሮ ነው

የሀላባ ዞን ሁለተኛ ዙር የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩንቨርስቲ  ሽኝት ተካሄዷል ።በሁለተኛ ዙር የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ 684 ተማሪዎች በዛሬው እለት ወደ ዋቻሞ ዩንቨርስቲ...
05/07/2025

የሀላባ ዞን ሁለተኛ ዙር የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ዩንቨርስቲ ሽኝት ተካሄዷል ።

በሁለተኛ ዙር የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ 684 ተማሪዎች በዛሬው እለት ወደ ዋቻሞ ዩንቨርስቲ ሽኝት ተካሄዷል።

በተማሪዎቹ ሽኝት ሂደት ላይ የተገኙት የሀላባ ዞን አስተደደር ዋና አማካሪ አቶ ከድር ቆርቾ ለተማሪዎቹ መልካም ፈተና እንድሆንና በሠላም ተፈትነው በሠላም እንድመለሱ በጉዞም ተረጋግተው እንድሄዱ ጭምር አሳስቧል።

በሽኝት ሂደቱ የዞኑ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሙደስር ጉታጎ ፣ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ኮ/ር ኑሪዬ ከድር እንዲሁም የ3 ወረዳ እና የቁሊቶ ከተማ አስተደደር ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊዎች የፖሊስና የዞኑ ትምህርት መምሪያ ማናጅመንት አበላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የከተማዋ የለውጥ ግስጋሴ በይበልጥ ለማሳደግ ከንግዱ ማህበረሰብ የሚሰበሰበው ዓመታዊ የስራ ግብር ወሳኝ ነው፦አቶ ገመዳ መሀመድ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ2017 የግብር...
04/07/2025

የከተማዋ የለውጥ ግስጋሴ በይበልጥ ለማሳደግ ከንግዱ ማህበረሰብ የሚሰበሰበው ዓመታዊ የስራ ግብር ወሳኝ ነው፦አቶ ገመዳ መሀመድ

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ2017 የግብር ዘመን የደረጃ ሐ/ግብር አከፋፈል እና የንግድ ፍቃድ ዕድሳት ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ አካሄዷል።

የንቅናቄ መድረኩን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ገመዳ መሀመድ፣የከተማዋ ምክትል ከንቲባና የገቢ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብድልቃድር ኢማም ሎላሶ እና የከተማ ንግድ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኡስማን ከድር መርተዋል።

አቶ ገመዳ መሃመድ እንደተናገሩት፦ባለድርሻ አካላቱ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት ዓመታዊ የስራ ግብር በአግባቡ እንዲሰባሰብ ከመቼውም ግዜ በላይ በልዩ ትኩረት ልሰራ ይገባል ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን ዕድገት ልያፋጥን የሚችልና ህዝቦቿን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ ወደተግባር የገባ ስሆን ይህ ለተግባራዊነቱ የግብር አሰባሰብ ስራ ወሳኝነት አለው ብለዋል።

የከተማ አስተዳደሩ የልማት ዕቅድ ከግብ እንዲደርስ ባለድርሻ አካላቱ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር በመናበብ ዓመታዊ የስራ ግብሩን በአግባቡ ልሰበስብ ይገባልም ብለዋል።

የግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ዓመታዊ ግብሩን በወቅቱና በአግባቡ በመክፈል በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ከግብ እንዲደርሱ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ ከንቲባው ጥሪ አስተላልፈዋል።

አቶ አብድልቃድርም በበኩላቸው፦ የ2017 ዓ.ም የደረጃ ሐ የገቢ አሳባሰብ ስራ በታቀደለት ግዜ እንዲጠናቀቅ ተቋማችን ቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቋል ብለዋል።

የንግዱ ማህበረሰብ የታክስ አዋጁ በሚፈቅደው መሰረት የተገመተውን የዕለት ገቢ ግመታን መሰረት በማድረግ ዓመታዊ ግብሩን በወቅቱ መክፈል ይጠበቅበታል ስሉም ጥሪ አስተላልፈዋል።

ሁሉም ግብር ከፋይ ዓመታዊ ግብሩን ለመክፈል በሚመጣበት ወቅት የገቢ ተቋሙ በቅልጥፍና ለማስተናገድ ዝግጅቱን አጠናቋልም ብለዋል።

አቶ ሁስማን ከድርም እንደተናገሩት፦የንግድ ፍቃድ ዕድሳትና ሌሎች ተያያዥ ጎዳያችን ለመፈፀም ተቋማችን ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል ብለዋል።

በውይይት መድረኩ በርካታ ሀሳብ አስተያይቶች ከታዳሚው የተነሱ ስሆን በተነሳው ሃሳብ አስተያየት ዙሪያ ከመድረክ መሪዎች ሰፊ ሚላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ ውይይት ተጠናቋል

🇿🇦 ቃል በተግባር🇿🇦አቡ ሙሰማ ከደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራውን ለማኖር ቃል ከገባው አምስት መቶ ሺ ብር  ውስጥ 100,000 (አንድ መቶ ሺ) ብር ገቢ...
04/07/2025

🇿🇦 ቃል በተግባር🇿🇦

አቡ ሙሰማ ከደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራውን ለማኖር ቃል ከገባው አምስት መቶ ሺ ብር ውስጥ 100,000 (አንድ መቶ ሺ) ብር ገቢ አድርጓል።

እናመሰግናለን!

🇿🇦 ቃል በተግባር 🇿🇦አምሪያ ሙሰማ ከደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራዋን ለማኖር ቃል ከገባችው አምስት መቶ ሺ ብር  ውስጥ 100,000 (አንድ መቶ ሺ) ብ...
04/07/2025

🇿🇦 ቃል በተግባር 🇿🇦

አምሪያ ሙሰማ ከደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራዋን ለማኖር ቃል ከገባችው አምስት መቶ ሺ ብር ውስጥ 100,000 (አንድ መቶ ሺ) ብር ገቢ አድርጋለች።

እናመሰግናለን!!

🇿🇦 ቃል በተግባር ከጆርጅ 🇿🇦1) ሙስጠፋ አኒቶ 100,000 (አንድ መቶ ሺ) 2) ከማል አኒቶ 100,000 (አንድ መቶ ሺ)3) ያሲን ኤርገና 100,000 (አንድ መቶ ሺ) ከደቡብ አፍሪካ ...
04/07/2025

🇿🇦 ቃል በተግባር ከጆርጅ 🇿🇦

1) ሙስጠፋ አኒቶ 100,000 (አንድ መቶ ሺ)
2) ከማል አኒቶ 100,000 (አንድ መቶ ሺ)
3) ያሲን ኤርገና 100,000 (አንድ መቶ ሺ)
ከደቡብ አፍሪካ ጆርጅ ከተማ በሀላባ ስታዲዮም ግንባታ ላይ አሻራቸውን ለማኖር ቃል ከገቡት ውስጥ በድምሩ
300,000(ሶስት መቶ ሺ) ብር ገቢ አድርገዋል።

እናመሰግናለን ጆርጆች

04/07/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ኅብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ የ2017 በጀት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና ግቦች ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

Address

Alaba K'ulito
212

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaba Tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Halaba Tv:

Share