
18/09/2025
የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ንቀት ለማህበረሰብ ለውጥ በጎ አድርጎት ማህበር ጋር በመተባበር ለተቸገሩ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ንቀት ለማህበረሰብ ለውጥ ከበጎ አድርጎት ማህበር ጋር በመተባበር በዌራ ዲጆ ወረዳ የትምህርት ቁሳቁስ የተቸገሩ ለ100 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል።
የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ መድረክ ላይ የተገኙት የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ ይሄንን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለደረጉ ለበጎ አድራጎት ማህባር አስተባበርዎችን በመማስገን አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት ከመማር ወደኋላ መቅረት የለበትም ብሏል።
የትምህርት ቁሳቁሱ በብር ስገመት ከ100,000 ብር በላይ ሲሆን የበጎ አድራጎት ማህባሩ አስተባባሪዎች የተማሪዎች ችግር የኛ ችግር ነው በማለት በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት ከትምህርት ገባታ ውጪ እንዳይሆኑ እየሠሩ እንደሆነ ገልጿል።
የበጎ አድራጎት ማህባሩ በትምህርት ዘርፍ ለተማሪዎች የማያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እና በሌሎች ዘርፎች ጭምር ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።
በድጋፍ መድረኩ የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ ፣የበጎ አድራጎት ማህባሩ አስተባባሪዎች የዌራ ዲጆ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ባለሙያዎች የትምህርት ቤት ር/መ/ራን እና ተማሪዎች ተገኝቷል ሲል ሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ዘግቧል።