03/06/2026
የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የልማት ትሩፋት ስራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑን- የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመዳ ሄለሞ ገለጹ!
*************
(ግንቦት፤26/2018 ዓ.ም)
በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ ስርዐት ምግብን ክፍታትን ለማሟላት (በHCO)ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት በቁንጩ የዬና በ2ኛ ጡቃ ቀበሌ በመንደር የዶሮ ስርጭት ተደርገዋል።
በዛሬው ዕለት በወረዳው ከ1200 በላይ የ45 ቀን የዶሮ ጨጩት ስራጭት ለማድረግ መቻሉን ግብርና ጽ/ቤት አስታወቋል።
የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም የሚያስችሉ የልማት ትሩፋት ስራዎች በመንደር መሰራጨት ተጠናክሮ መቀጠሉን ተገልጸዋል።
የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመዳ ሄለሞ እንደገለጹት የልማት ትሩፋት ስራዎችን ማስፋፋት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ እንደሆነ አስረድተዋል።
የልማት ትሩፋት ስራዎች ዝቅተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆናቸው እነዚህን ተሞክሮዎች ለመስፋፋት በልዩ ትኩረት ልሰራ ይገባል ብለዋል።
የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊና እንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሉሉ ከድር በበኩላቸው የዶሮ እርባታ አነስተኛ ቦታና ቀላል ጉልበትን በመጠቀም ምርታማነትን በማሳደግ የቤት ፍጆታን ማሟላትና የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠር ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
የተሰራጩት ዶሮዎች በጥሩ ጤንነት አድገው ለታለመላቸው ውጤት እንዲበቁ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ተከታታይ የሙያ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ግብርናን በማዘመንና በየቤቱ የልማት ስራዎችን በመተግበር ዜጎች ራሳቸውን እንዲችሉና የአካባቢያቸውን እንዲያነቃቁ የሚሆን ተግባር መሆኑን አመልክቷል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የልማት ዕቅድ ባለሙያ የሆኑት አቶ አ/ቃድር ኑርዬ በበኩላቸው በወረዳው በስርዓተ ምግብ ላይ የሚከሰቱ ተስተውሎትን ለመቅረፍ የHCO ፕሮጀክት ለህዝብ የሚበጅ መፍትሔ ይዞ መምጣቱን ተናገረዋል
በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የዶር ስርጭት በመንደር ማድረጉ ገልጸው፦በዛሬው ዕለት አርሶአደሩ በአንድ ቦታ ሁሉንም ነገር አግኝታው እራስንና ተደግ የሆኑ ልጆች ብቁ ሆኖ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በምግብ እራሳቸውን መገንባት ወሳኝ መሆኑን አመልክቷል።
በፕሮግራሙ ላይ የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሀሰን አብደላ፣እንዲሁ የቀበሌው አመራሮች ተጠቃሚ ማህበረሰብ ክፍል ሌሎችም ተገኝተዋል ሲል የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!