Halaba Tv

Halaba Tv This is the official Halaba TV page - where you can get all the latest information's in diff

Halaba TV detail contact information:
https://t.me/halabatelevision

የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የልማት ትሩፋት ስራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑን- የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመዳ ሄለሞ ገለጹ!***********...
03/06/2026

የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የልማት ትሩፋት ስራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑን- የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመዳ ሄለሞ ገለጹ!
*************
(ግንቦት፤26/2018 ዓ.ም)

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ ስርዐት ምግብን ክፍታትን ለማሟላት (በHCO)ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት በቁንጩ የዬና በ2ኛ ጡቃ ቀበሌ በመንደር የዶሮ ስርጭት ተደርገዋል።

በዛሬው ዕለት በወረዳው ከ1200 በላይ የ45 ቀን የዶሮ ጨጩት ስራጭት ለማድረግ መቻሉን ግብርና ጽ/ቤት አስታወቋል።

የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም የሚያስችሉ የልማት ትሩፋት ስራዎች በመንደር መሰራጨት ተጠናክሮ መቀጠሉን ተገልጸዋል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመዳ ሄለሞ እንደገለጹት የልማት ትሩፋት ስራዎችን ማስፋፋት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ እንደሆነ አስረድተዋል።

የልማት ትሩፋት ስራዎች ዝቅተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆናቸው እነዚህን ተሞክሮዎች ለመስፋፋት በልዩ ትኩረት ልሰራ ይገባል ብለዋል።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊና እንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሉሉ ከድር በበኩላቸው የዶሮ እርባታ አነስተኛ ቦታና ቀላል ጉልበትን በመጠቀም ምርታማነትን በማሳደግ የቤት ፍጆታን ማሟላትና የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠር ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

የተሰራጩት ዶሮዎች በጥሩ ጤንነት አድገው ለታለመላቸው ውጤት እንዲበቁ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ተከታታይ የሙያ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ግብርናን በማዘመንና በየቤቱ የልማት ስራዎችን በመተግበር ዜጎች ራሳቸውን እንዲችሉና የአካባቢያቸውን እንዲያነቃቁ የሚሆን ተግባር መሆኑን አመልክቷል።

የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የልማት ዕቅድ ባለሙያ የሆኑት አቶ አ/ቃድር ኑርዬ በበኩላቸው በወረዳው በስርዓተ ምግብ ላይ የሚከሰቱ ተስተውሎትን ለመቅረፍ የHCO ፕሮጀክት ለህዝብ የሚበጅ መፍትሔ ይዞ መምጣቱን ተናገረዋል

በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የዶር ስርጭት በመንደር ማድረጉ ገልጸው፦በዛሬው ዕለት አርሶአደሩ በአንድ ቦታ ሁሉንም ነገር አግኝታው እራስንና ተደግ የሆኑ ልጆች ብቁ ሆኖ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በምግብ እራሳቸውን መገንባት ወሳኝ መሆኑን አመልክቷል።

በፕሮግራሙ ላይ የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሀሰን አብደላ፣እንዲሁ የቀበሌው አመራሮች ተጠቃሚ ማህበረሰብ ክፍል ሌሎችም ተገኝተዋል ሲል የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

የሀላባ ዕድገት ጤና እግር ኳስ ቡድን ለሀላባ ከነማ በ20,000 ብር የገቢ ማሰባሰቢያ ቻሌንጅ ተቀላቀለ።የሀላባ ከነማ ሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ተከትሎ የገቢ መሰብሰቢያ ቻሌንጅ...
03/06/2026

የሀላባ ዕድገት ጤና እግር ኳስ ቡድን ለሀላባ ከነማ በ20,000 ብር የገቢ ማሰባሰቢያ ቻሌንጅ ተቀላቀለ።

የሀላባ ከነማ ሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ተከትሎ የገቢ መሰብሰቢያ ቻሌንጅ ተጀምሮ ገቢ እየተሰበሰበ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን ሁሉም የቡድኑ አባላት ከዚህ ቀደም በግል የገቢ አሰባሰቡን ከተቀላቀሉት በተጨማሪ ዛሬ በጤና እግር ኳስ ቡድን ስም በአንድነት 20,000 ብር ገቢ አድርገዋል።

ከልብ እናመሰግናለን!!!

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መላው የክልሉ ሴቶች እና ባለድርሻ አካላት ላደረጉት የነቃ ተሳትፎ የክልሉ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ አመሰገነየቢሮው ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር በስተላለፉ...
03/06/2026

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መላው የክልሉ ሴቶች እና ባለድርሻ አካላት ላደረጉት የነቃ ተሳትፎ የክልሉ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ አመሰገነ

የቢሮው ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር በስተላለፉት የምስጋና መልዕክት በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መላው የክልሉ ሴቶች እና ባለድርሻ አካላት ላደረጉት የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል ብለዋል፡፡

የክልሉ ሴቶች በመመረጥ፣ በመምረጥ፣ በመተዘብና ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡

ኃላፊዋ አክለውም በክልሉ የሚገኙ ሴቶች በሴቶች ልማት ህብረትና በሌሎችም አደረጃጀቶች በተቀናጀ መልኩ በተፈጠረው ግንዛቤ በምርጫው የሚደነቅ ተሳትፎአቸውን አሳይተዋል ብለዋል፡፡

ለስኬቱም በየደረጃው የሚገኙ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ ሁሉም የሴቶች አደረጃጀቶችና መላው አመራር ከፍተኛ አበርክቶ አድርጓል ያሉት ወ/ሮ ዘቢባ ለዚህም በክልሉ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና በራሳቸው ስም አመስግነዋል፡፡

ኢትዮጵያ መርጠለች ያሉት ክብርት የቢሮ ኃላፊዋ መላው አመራርና ፈጻሚው የኢትዮጵያን የቀጣይ መፃዒ እጠፈንታ በሚወስነው ምርጫ ያሳየውን አበረታች እንቅስቃሴ በቀጣይ የሴቶችና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በሚያሳድጉ ስራዎች መድገም ይገባናል ብለዋል ሲል የበገበው የክልሉ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ነው

በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ ዝናብ ያገኛሉበሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባ...
03/06/2026

በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ ዝናብ ያገኛሉ

በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢንስቲትዩቱ እንዳስታወቀው እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን እየተጠናከረ በመምጣት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛው እና በደቡብ ምሥራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ የተሻለ የዝናብ ስርጭት ይኖራቸዋል።

በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገራችን ክፍሎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር አኃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ።

በሌላ በኩል የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜን እና በደቡብ ምዕራብ ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

በመደበኛ ሁኔታ ወቅታዊው የክረምት ዝናብ ቀደም ብሎ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ አጋማሽ የሀገራችን ክፍሎች ላይ የሚጀምር ሲሆን፣ በሂደት እየተጠናከረ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም እንደሚስፋፋ ተጠቁሟል።

በዚህም መሠረት በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛው እና በምሥራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በስርጭት የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ይህ የሚኖረው እርጥበት ለግብርና ሥራ የማሳ ዝግጅት ለማድረግ፣ የመኸር ሰብሎችን ለመዝራት እንዲሁም ለበልግ ሰብል ተጠቃሚ አካባቢዎች መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል።

በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚኖርም ታውቋል።

በዚህም መሠረት በመካከለኛው እና ታችኛው አባይ፣ በላዩኛው እና መካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ በላዩኛው ስምጥ ሸለቆ፣ በኦሞ ጊቤ፣ በአዋሽ እንዲሁም በገናሌ ዳዋ ተፋሰሶች ከመካከለኛ እስከ ከባድ የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚጠበቅ ተጠቅሷል።

በተመሳሳይ በላይኛው አባይ፣ በኦጋዴን፣ በመካከለኛው አዋሽ፣ በስምጥ ሸለቆ እና በኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚኖራቸውም ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ ገልጿል።

በበጀት ዓመቱ በቀሪ ግዜ የገቢ አሰባሰቡን በስኬት ለማጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና ተቋማት እርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ!የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ አሰባሰብ ስራንና የ...
03/06/2026

በበጀት ዓመቱ በቀሪ ግዜ የገቢ አሰባሰቡን በስኬት ለማጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና ተቋማት እርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ!

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት የገቢ አሰባሰብ ስራንና የደረጃ ''ሀ'' እና ''ለ'' ግብር አከፋፈል አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብድልቃድር ኢማም ሎላሶ በመሩት በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ በበጀት ዓመቱ በቀሪ ጊዜያት የገቢ አሰባሰቡን በስኬት ለማጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና ተቋማት ያለምንም መዘናጋት ቀን ከሌት ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በመደበኛና በማዘጋጃ ቤት ዘርፍ እስካሁን የተከናወኑ የገቢ አፈጻጸሞች የተገመገሙ ሲሆን የከተማውን የወጪ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በቀጣይ በቀሪ ቀናት የደረጃ ''ሀ'' እና የደረጃ ''ለ'' ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንዲከፍሉ በማድረግ፣ የኦዲት ውዝፍ ያለባቸውን በልዩ ሁኔታ በመለየት፣ የደረሰኝ ቁጥጥር ስራን በማጠናከርና ወርሃዊ ሪፖርቶችን በትክክለኛው ጊዜና ጥራት በማደራጀት የተሸላ የገቢ አሰባሰብ ስራን ለመስራት እርብርብ ይደረጋል ብለዋል።

የከተማችን የልማት ፍላጎት እንዲሟላ ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብሩን በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ግዴታውን መወጣት እንዳለበት ጠቁመው በዚህም መሰረት የደረጃ "ሀ" ሁለተኛ ዙር (1/4) ግብር ከፋዮችና የደረጃ "ለ" ሶስተኛ ዙር (1/4) ግብር ከፋዮች እስከ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም ድረስ ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በኋላ ለሚመጡ ግብር ከፋዮች ወለድና አስተዳደራዊ ቅጣት የሚሰላ መሆኑን አውቀው ህጋዊ ግዴታቸውን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲወጡ አሳስበዋል ሲል የዘገበው የከተማው ኮሚኒኬሽን ነው

የህዝብን አደራ ለመወጣት የጀመርነውን የመንገድ ልማት ስራ አጠናክረን እንቀጥላለን:-ዶ/ር መሐመድ ኑርዬ****የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላ...
03/06/2026

የህዝብን አደራ ለመወጣት የጀመርነውን የመንገድ ልማት ስራ አጠናክረን እንቀጥላለን:-ዶ/ር መሐመድ ኑርዬ
****
የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑርዬ በዛሬው ዕለት በከምባታ ዞን ቃጫ ቢራ ወረዳ በሪካፕ በመሰራት ላይ የሚገኙ ተስፋ ሰጪ የመንገድ ፕሮጀክቶችን በቦታው በመገኘት በአካል ተመልክተዋል።

በዚህም ወቅት የመንገድ መሰረተ-ልማት የህዝባችንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር እንዲሁም የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ የክልሉ መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

​ኃላፊው በምልከታቸው ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ አዲስ የእድገትና የዴሞክራሲ ምዕራፍ በመረጠችበት ማግስት፣ ህዝባችን በሰጠን ታላቅ አደራ መሰረት የምናከናውነው የልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ይህ ምርጫ ህዝቡ በልማት ላይ ያለውን እምነት ያሳየበት በመሆኑ፣ የተጣለብንን አደራ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ለመወጣት ሌት ተቀን እየተሰራ ይገኛል።

​መንገድ የህዝብን የእርስ በርስ ግንኙነት ከማሳለጥ ባለፈ፣ ምርትና ምርታማነትን በፍጥነት ወደ ገበያ ለማቅረብና የነዋሪውን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ዋነኛ የልማት ደም ስር ነው።

በመሆኑም ክልሉ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ በመመስረት ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተናግረዋል።

​በአሁኑ ወቅት በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች እየተገነቡ ያሉ መንገዶች ጥራታቸውን የጠበቁና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ይህ የአካል ምልከታ መደረጉ ተገልጿል።

በጉብኝቱም የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና የተስተዋሉ ጉድለቶችንም በአስቸኳይ እንዲስተካከሉ አቅጣጫ ተቀምጧል።

​"የህዝባችንን የመንገድ ጥያቄ በአንድ ጀምበር መፍታት ባይቻልም፣ በህዝብ የተጣለብንን አደራ ለመወጣት በቅደም ተከተልና በታቀደ መልኩ እያንዳንዱን አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን።"

በምልከታው ወቅትም የከምባታ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳዊት ሀንዲኖ እና የቃጫ ቢራ ወረዳ የሳይት ማህንዲስ እና ባለድርሻ አካላቶች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወራቤ ከተማ የወንዝ ዳርቻ ልማት ተመለከቱ *** ግንቦት 26/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በወራቤ...
03/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወራቤ ከተማ
የወንዝ ዳርቻ ልማት ተመለከቱ
***
ግንቦት 26/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በወራቤ ከተማ
ሜላያን የወንዝ ዳርቻ ልማት ተመለከቱ

ሜላያን የወንዝ ዳርቻ ልማት 9ሄ/ር መሬት የሚሸፍን ሲሆን ለአካባቢው ህብረተሰብ ተጨማሪ የመዝናኛ ስፍራ በመሆን እያገለገለ ነው።

የወንዝ ዳርቻ ልማቱ የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ስለመሆኑም ተመላክቷል።

በልማት ስራ ምልከታው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣
የክልል እና የስልጤ ዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ የአሾካ ጤና ጣቢያ ከአንድ ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአልትራሳውንድ ማሽን እና የማይክሮስኮፕ ግዢ በመፈጸም ርክክብ ተደረገ፡፡ግንቦት 26/2018 በዌራ ወረ...
03/06/2026

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ የአሾካ ጤና ጣቢያ ከአንድ ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአልትራሳውንድ ማሽን እና የማይክሮስኮፕ ግዢ በመፈጸም ርክክብ ተደረገ፡፡

ግንቦት 26/2018 በዌራ ወረዳ ከአንድ ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአልትራሳውንድ ማሽን እና ማይክሮስኮፕ ግዢ በመፈጸም ለአሾካ ጤና ጣቢያ ርክክብ ተደርጓል ።

ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚረጋገጠው ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብ መፍጠር ሲቻል ነው ያሉት የዌራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ከዲር የሴ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ማህበረሰቡ አገልግሎቱን በቅርበት እንዲያገኝ ቋማቱ ከ PBF ፕሮጄክት ካገኙት ገቢ ግዢ መፈጸሙን ገልጸዋል።

የማሽኖቹ መገዛት የጤና ተቋማት የአገልግሎት ጥራት አንድ እርጃ ከፍ የሚያደርግ መሆኑን እና አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ሀላባ አጠቃላይ ሆስፒታል ይሄዱ የነበሩ እናቶችን እንግልት የሚቀንስ መሆኑን በማንሳት በቀጣይም በሌሎች ጤና ጣቢያዎች የውስጥ ቁሳቁስ የማሟላቱ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ የጤና ተቋማትን የተሟላ አገልግሎት ላይ እንድገኙ ከማድረግ አንጻር ወሳኝ መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ እንድቀጥል ጥሪ አስተላልፏል።

አያይዘውም PBF ፕሮጄክት በCORDOID ETHIOPIA አጋርነት ጤና ተቋማት የዉስጥ ገቢያቸው እጅግ በጣም እንድሻሻል ከማድረጉም በላይ መሰረታዊ የአገልግሎት መስጫ የህክምና መሣርያዎችን በራሳቸው እንድያሟሉ በማድረግ የተቋማትን ደረጃ ከፍ እያደረገ ያለውን የPBF ፕሮጄክትን እና CORDOID ETHIOPIAN አመስግኗል።

የዌራ ወረዳ ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ያዲሶ ዱበላ በበኩላቸው ማሽኑን የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየ መሆኑን ጠቅሷል ።

አቶ ያዲሶ አያይዘው ድጋፍ የተደረገውን ማሽን ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ ባለሙያዎች በአግባቡ መገልገል አለባቸው ያሉ ሲሆን የPBF ፕሮጄክት ለዚህ ሁሉ ዉጤት ድርሻው ከፍተኛ በመሆኑ የፕሮጄክቱ ዉጤታማነት ይበልጥ እንድሰፋ ሁሉም ባለድርሻ ሀላፊነቱን በአግባቡ እንድወጣ አሳስበዋል።

በመጨረሻም የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ እና የአገልግሎት ቦታዎችን ተዟዙረው ምልከታ አድርገዋል።

በርክክቡ ወቅት የዌራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመቹ ኤዳሳ፣ የጤና ተቋማ ሀላፊዎች እና ከዞን፣ ከወረዳና ከጤና ጣቢያዎቹ የሚመለከታቸው ባለሞያዎች ተገኝተዋል ሲል የወረዳው ኮሚኒኬሽን ዘግቧል!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ የሌጋሞ ድልድይ ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት እንድጀምር ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ*******...
03/06/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ የሌጋሞ ድልድይ ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት እንድጀምር ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
*******
ግንቦት፣26/2018 በዌራ ዲጆ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት አማካኝነት በጮባሬ ሜዕኖ ቀበሌ በቀድሞ ደቡብ ክልል ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ያልጀመረውን ድልድይ ቀሪ የጋብዮን ስራዎችን ለማጠናቀቅ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን በዱራሜ ዲስተሪክት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም በዛሬው ዕለት የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የዱራሜ ድስትሪክት ስራ አስከያጅ ኢ/ር ሀይሌ አበራ፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሸምሱ አቡቴን ጨምሮ የዱራሜ ድስትሪክትና የወረዳ ትራንስፖርት የሳይት ባለሙያዎች በተገኙበት ቀሪ ስራው ምልከታ ተደርጓል።

በዚህም ወቅት የሌጋሞ ድልድይ ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ የተገለፀ ስሆን፣የጋብዮን ቀሪ ስራ ለማስጀመር ለሁለተኛ ዙር ጋብዮን የማስገባት ስራውም ተከናውኗል። ስል የዘገበው የወረዳው መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ነው።

የም/ቤቱ 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል******ግንቦት፣26፣2018 ዓ.ም፤ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን፣...
03/06/2026

የም/ቤቱ 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል
******
ግንቦት፣26፣2018 ዓ.ም፤ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።

ም/ቤቱ በነገ ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ ፤ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለምዓቀፍ የልማት ማህበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶች ለማፅደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥትና እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ መንግሥታት፤ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በአንጎላ ሪፐብሊክ መንግሥታት፤ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ረፐብሊክ መንግሥታት፤ እንዲሁም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት
መካከል የተፈረመውን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና ውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን የሚያፀድቅ ይሆናል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና ውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

በተያያዘም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመ ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና ውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያፀድቃል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅን፣ የምግብ ስርዓትና ስርዓተ ምግብ ረቂቅ አዋጅን ፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅን እና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል።ከኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Address

Alaba K'ulito
212

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaba Tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Halaba Tv:

Share