Halaba Tv

Halaba Tv This is the official Halaba TV page - where you can get all the latest information's in diff

Halaba TV detail contact information:
https://t.me/halabatelevision

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ለሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ለሁለተኛ ዙር የአንድ ወር ደሞዛቸውን ድጋፍ አደረጉ ‎‎በህዝብ ተሳትፎ እየተገነባ የሚገኘው የሀላባ  ኢንተርናሽናል ስ...
16/10/2025

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ለሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ለሁለተኛ ዙር የአንድ ወር ደሞዛቸውን ድጋፍ አደረጉ

‎በህዝብ ተሳትፎ እየተገነባ የሚገኘው የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ ድጋፍ በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠናክሮ የቀጠለ ስሆን በዛሬው ዕለት የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር አመራሮች የአንድ ወር ደሞዛቸውን ድጋፍ አድርጓል።

‎የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አ/መጅድ ፍጣሞና የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሁሴን አብደላ የዉይይት መድረኩን መርቷል።

‎በመድረኩም ስታዲዬማችን ከምንም በላይ ቅድሚያ የምንሰጠው ታላቅ ፕሮጄክት በመሆኑ ድጋፍ በቀጣይ በፐብሊክ ሰርቫንቲ በአርሶ አደር በነዋሪዎች ና በሌሎች በሁሉም ዘርፎች ተጠናክሮ የምቀጥል እንደሆነም ተገልጿል።

‎አመራሩ ከደሞዙ በተጨማሪ በተለያዩ ቻሌንጆች በመሳተፍ ስታዲየም ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድጋፉን እንደምቀጥሉ ቃል ገብተዋል።

ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የህዝቦች አንድነትን ለማጎልበት የወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነው ፦ አቶ ይሁን አሰፋ****ጥቅምት 6/2018) ''ሚዲያ ለክልላችን ከፍታና ለላቀ እምርታ'' በሚል መሪ...
16/10/2025

ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የህዝቦች አንድነትን ለማጎልበት የወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነው ፦ አቶ ይሁን አሰፋ
****
ጥቅምት 6/2018) ''ሚዲያ ለክልላችን ከፍታና ለላቀ እምርታ'' በሚል መሪ ቃል በክልሉ ሰላምና ልማት ዙሪያ ከወጣቶች ጋር መግባባት ለመፍጠር በወጣት ፌዴሬሽን የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይሁን አሰፋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የህዝቦች አንድነትን ለማጎልበት የወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ክልሉ በስኬት ጎዳና ላይ የሚገኝ መሆኑን የተረዱ አፍራሽ ሀይሎች ክልሉን ወደ ኋላ ለመቀልበስ በርካታ ጥረቶችን ቢያደርጉም እንዳልተሳካላቸው ገልፀዋል።

የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እውን እንዲሆን የህብረተሰቡና የወጣቱ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተጨባጭ ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት።

ክልሉን የሰላም ተምሳሌት በማድረግና የስራ ፈጠራና ህብረ- ብሄራዊነት ማሳያ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ወጣቱ የላቀ ድርሻ እንዳለው በመጠቆም ክልሉን የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ በሚደረገው ሂደት ወጣቶች በስኬትና በትጋት ለመወጣት መረባረብ ያስፈልጋል ሲሉም አቶ ይሁን አጽንኦት ሰጥተዋል።

በክልሉ የሚገኙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ከህዝብና ከመንግስት ጋር ተቀናጅቶ በመስራታቸው በርካታ ፈተናዎችን በድል ለመወጣት ተችሏል ብለዋል።

በሀሰተኛ ሚዲያ በሚለቀቁ መረጃዎች ሳይረበሹ ወጣቱ በአስተሳሰብና በተግባር በሁሉም መስክ በመላቅ ለህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ብልጽግና መረባረብ ያስፈልጋል ብለው ትክክለኛ መረጃዎችን ከትክክለኛ ሚዲያ ምንጭ በመጠቀም ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራም እንዲሰሩ አሳስበዋል።

ወጣቶች ያላቸውን መልካም ፀጋዎችን በመጠቀም ለሀገር ግንባታና ለሰላም ተቀናጅቶ በመስራት ጉልበታቸውን እና የፈጠራ አስተሳሰባቸውን ለልማት ማዋል ይጠበቅባቸዋል።

ሚዲያን ለሰላም፣ ለልማት እና ለታሪክ እጥፋት በመጠቀም በውይይት የሚያምን ወጣቶችን በመፍጠር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞን እውን ለማድረግ በጋራ እንዲተጉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወጣት አብዱ ድንቁ ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት በመሆኑ ወጣቶች ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና መጫወት ያስፈልጋል።

ወጣቱ ትውልድ ከልዩነት ይልቅ አንድነትን፣ ከመበታተን ይልቅ መሰባሰብን በማጉላት የጋራ እሴትን የሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል።

ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የህዝቦች አንድነትና የአብሮነት አስተሳሰብ እንዲጎለብት በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።

በሚዲያ የሚለቀቁ የተዛቡ መረጃዎችን በመመከት ትክክለኛውን መረጃ ለህዝቡ በማድረስ ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡም አሳስበዋል።

ይህ የንቅናቄ መድረክ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ የሚካሄድ መሆኑንም ገልፀዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት የጋራ እሴቶችን የሚሸረሽሩ ጉዳዮችን በማስወገድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማውረስ እንደሚረባረቡ ገልፀዋል።

በመድረኩም የክልልና የታችኛው መዋቅሮች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝቷል።
ዘገባው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ነው

በዌራ ዲጆ ወረዳ በበንዶ ጮሎቅሳ ቀበሌ በክላስተር እየለማ የሚገኘው ቺያ ሲድ(Chia seed) የተባለ ሰብል የመስክ ምልከታና የልምድ ልውውጥ ተደረገ።በወረዳው በበንዶ ጮሎቅሳ ቀበሌ በክላስተ...
16/10/2025

በዌራ ዲጆ ወረዳ በበንዶ ጮሎቅሳ ቀበሌ በክላስተር እየለማ የሚገኘው ቺያ ሲድ(Chia seed) የተባለ ሰብል የመስክ ምልከታና የልምድ ልውውጥ ተደረገ።

በወረዳው በበንዶ ጮሎቅሳ ቀበሌ በክላስተር እየለማ የሚገኘው ቺያ ሲድ(Chia Ceed) የተባለ ሰብል የመስክ ምልከታና የልምድ ልውውጥ ተደርጓል።

የመስክ ምልከታና የልምድ ልውውጥ ፕሮግራሙ ዋና አላማው የቺያ ሲድ(Chia seed) ሰብል ለተለያዩ በሽታዎች መድሃኒትነትና ለውጭ ሀገር የኤክስፖርት ምርት ስለሆነ፣ በቀጣይ አርሶአደሮች ልምድ በመውሰድ በስፋት ማምረት እንዲችሉ እንደሆነ ተገልጿል።

በመስክ ምልከታው የዌራ ዲጆ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ከይራቱ ለራጎ፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎበና ሰማን፣የዌራ ዲጆ ወረዳ የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሱራጅ ጎድሶ፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሪባቶ ቃበታን ጨምሮ የቺያ ሲድ(Chia Ceed) ሰብል አቅራቢዎች፣የወረዳና የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች፣የቀበሌው አመራሮችና አርሶአደሮች ተገኝተዋል።

ዘገባው የዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን ነው

የስራ አጥ ምጣኔን በመቀነስ አምራችና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ የዞኑ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሰመሩ ሀ/ሆራ ገለጹ *****ጥቅምት 5/...
15/10/2025

የስራ አጥ ምጣኔን በመቀነስ አምራችና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ የዞኑ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሰመሩ ሀ/ሆራ ገለጹ
*****
ጥቅምት 5/2018 የሀላባ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ አመት ታችኛው ጽ/ቤት በተገኙበት ተገምግመዋል።

በመድረኩ ላይ የአራቱም መዋቅር ሀላፊዎች የ2018 በጀት ዓመት የሶስት ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን የቀረቡ ስሆን በቀረቡት አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

በዚህ ወቅትም የሀላባ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሰመሩ ሀጂ/ሆራ እንደገለጹት የስራ አጥ ምጣኔን በመቀነስ አምራችና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በአከባቢያችን ያሉ ጸጋዎቻችንን በአግባቡ በመለየት ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ በተጨባጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ዜጎች በሚፈጠሩት የስራ ዕድሎች ከራሳቸው ባለፈ ሌሎችንም ተጠቃሚ በማድረግ የስራ አጥነትን ችግር መቅረፍ እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።

በገጠርና በከተማ ያሉ መሬቶችን በመለየት እንዲሁም መንግስት በርካታ ሀብት አፍስሶ ያስገነባቸውን ሼዶች በመለየት በአግባቡ በመምራት ለስራ ዕድል ፈጠራ ምቹ መፍጠር ይገባል ብለዋል።

የወጣቶችና ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ተግባራትን አጠናክረን የመቀጠል፣ የወጣቱን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት እንዲሁም የተለዩ ተግባራትን መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በቀጣይ በተደራጀ መንገድ ስራዎችን በመስራትና ድጋፍ በማድረግ የተሰሩ ስራዎችን ክትትል በማድረግ በየጊዜው መረጃዎችን በመለዋወጥ የተጠናከረ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ነጥቦችን በተመለከተ በ 3 ወራት ወስጥ ውጭ ያሉ የብድር ገንዘብ ተመላሽ ማድረግ፣ ወጣቶችን በመደራጀት ስራ ስምሪት እንዲያገኙ ማስቻል ይገባል ብለዋል።

በከተማና የወረዳዎች ስራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት ተግራቸውን እንድወጡ መከታተልና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለዘርፉ አፈጻጸም ማነቆ የሆኑና የተለዩ ተግባራትን መከወንና ድጋፍና ክትትል ስራዎችን መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።

ከተቋሙ የስራ ተልዕኮ ባለፈ ሁሉም ተቋማት የስራው ባለቤት በመሆን በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አቶ ሰመሩ ሀጂ ሆራ አሳስበዋል።

ቀጣይ ዕቅዱም ውጤታማ እንዲሆን ከስራ አጥ ልየታ ጀምሮ እየገመገሙ መምራትና የተግባሩን ክብደት በመገንዘብ በርብርብ መስራት ይገባልም ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በሚቀጥለው ወራት የስራ ፈላጊ ቁጥርን በመቀነስ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራን በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በግምገማው መድረኩ ላይ የዞኑ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ መምሪያ የየዘርፉ ሀላፊዎችና የማኔጅመንት አበላት፣ የከተማ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የሶስቱም ወረዳ ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

በዞኑ እየተመዘገቡ ያሉት የልማት፣የሰላም፣ የመልካም አስተደደር፣የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተግባራትን ይበልጥ ለማጠናከር አበክረው እንደሚሠሩ በሀላባ ዞን የሚገኙ ብልጽግና ፓርቲ አባላት ገለፁ...
15/10/2025

በዞኑ እየተመዘገቡ ያሉት የልማት፣የሰላም፣ የመልካም አስተደደር፣የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተግባራትን ይበልጥ ለማጠናከር አበክረው እንደሚሠሩ በሀላባ ዞን የሚገኙ
ብልጽግና ፓርቲ አባላት ገለፁ

በዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፐብሊክ ሰርቭስ ግንባር የማህበራዊ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት የ2018 የ1ኛ ሩብ ዓመት አባላት ኮንፍራንስ ተከናውኗል።

ኮንፈረንሱ በአቶ ታገል ጌታቸው የሀላባ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊና የማህበራዊ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት ሰብሳቢ እና በአቶ መሀመድ ከድር በሀላባ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊና የማህበራዊ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት ምክትል ሰብሳቢ ተመርቷል።

የማህበራዊ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ የፖለቲካ፤የአደረጃጀት እና ፋይናንስ ዘርፎች ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት፣የህብረቷ የእንስፔክሺን እና ስነ-ምግባር ኮሞሽን የ2018 1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2017/2018 የክረምት በጎ ተግባር አፈጻጸም በኮንፈረንሱ ለውይይት የቀረቡ አጀንዳዎች ናቸዉ።

በተጨማሪም በኮንፍረንሱ ላይ በህብረቷ በ90 ቀን የተከናወኑ የፓርቲ እንሼቲቪ ስራዎች ያሉበት ደረጃ ዉይይት ተደርጓል፡፡
በዚህ ወቅት በፓርቲያችን ብልጽግና መሪነት በዞኑ እየተመዘገቡ ያሉት የልማት፣የሰላም፣ የመልካም አስተደደር፣የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተግባራትን ይበልጥ ለማጠናከር አበክረው እንደሚሠሩ አባላት ገልጸዋል።

በኮንፍረንሱ ተሳታፊ የፓርቲ አባላት በሰጡት አስተያየት ብልጽግና ፓርቲ በኢኮኖሚ እቅዱ ያስቀመጣቸውን ግቦች ለማሳካት በአሁን ሰዓት ህዝቡን እየተፈታተነ ያለዉን የኑሮ ዉድነት ችግር ለመቀነስ ሁሉንም በማሳተፍ እየተተገበሩ የሚገኙ የሌማት ቱሩፋትና ምግቤን ከጓሮዬ ተግባራት ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል።

የእጩነት ጊዜአቸው የተጠናቀቁ አባላትም ወደሙሉ አባልነት በመሸጋገር ጸድቋል።የህብረቷ የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ዙር ኮንፍራንስ ከፓርቲዉ በተሰጠዉ አቅጣጫ መሰረት በወቅቱ መደረጉ በጥንካሬነት ተነስቷል።

በ1ኛ ሩብ ዓመት ህብረቷ በእቅዷ የተቀመጡ ግቦችን በሚያሳካ መልኩ የተከናወኑ ተግባራት ከሌሎች ጊዜ የተሻሉ በመሆናቸው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባት አባላት ገልጸዋል።

የውስጠ ፓርቲ ጥንካሬን ለማጎልበት የህብረቷ አመራርና አባል በሀሳብና በተግባር አንድነቱን ከመቼዉም ጊዜ በላይ አጠናክሮ ያከናወነው ተግባር ይበል የሚያሠኝ በመሆኑም ተጠናክሮ እንዲቀጥል በኮንፍረንሱ ወቅት አባላት አስተያየታቸውን ሰጥቷል።

የፓርቲውን አሰራርና መመሪያ ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር በሁሉም ዘርፎች ወቅቱን የጠበቀ ዉይይት፣ሪፖርትና የግንኙነት አግባብ እየተሻሻለ መምጣቱ በቀጣይም መጠናከር እንዳለበት በጥንካሬ ተነስቷል።

የህብረቷ አመራሮች ወርሃዊ የቤተሰብ ዉይይት ክትትል ከማድረግና ከመደገፍ አንጻር ጅምሩ ጥሩ በመሆኑ ቀጣይ ከዚህ በበለጠ ልሰፋ ይገበል የእንስፔክሽን አባላትን መረጃ በየጊዜ ከማደራጀት ፋይሎችን እና አስፈላጊ መረጃዎችን ወቅታዊ የማድረግ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች መኖራቸዉ በጥንካሬ ተነስቷል።

አባላት መብትና ጌታቸዉን አዉቀዉ የፓርቲ መዋጮ በወቅቱ እየከፈሉ መሆኑ እና በየወቅቱ ጠንካራ አባል ለፓርቲ ጥንካሬ እየተዘጋጀ ያለበት ሁኔታ በህብረቷ እያደገ መምጣቱ ተነስቷል።

የንኡሳን ኮሚቴ ተግባር እና የዉይይትና የግንኙነት ሁኔታቸዉ ጅምሩ ጥሩ መሆኑ ቤተሰቦች ወቅቱን የጠበቀ ምዘና ስርኣት እያደረጉ ሪፖርት እየላኩ ያሉበት ሁኔታ ቀጣይም መጠናከር አለበት ተብሏል።

በተለይም በፓርቲ ኢኒሼቲቭ በሰዉ ተኮር ተግባር ለማሳካት የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ በመከናወን በዞኑ የሚገኙ በ4ቱም መዋቅሮች ላይ ህብረቷ የሰራችው ተግባር አበረታች መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተለይም በህብረቷ በክረምት በጎ ስራዎች በዋናነት የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ፤የማዕድ መጋራት ስራ ፤የአልባሳትና የቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገበት፤በጣም የተሸለ መሆኑ ተነስቷል።

ሁሉም ቤተሰቦች የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ስራ ከአመራር እስከ አባል በማስተባበር ገንዘብ ተሰባስቦ መደገፍ የተቻለበት፤የህብረቷ አመራሮች ተግባሩን ለመከታተል ልዩ ትኩረት ሰጥተዉ በመከታተል የፈጸሙት የተሻለ ተግባር
በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።

ከጤና አንጻር በክረምት በጎ ስራ ከ380 በላይ ዩኒቲ ደም መለገስ የተቻለበት፤ከ60 በላይ የሚሆኑ ችግርተኞች ልዩ ልዩ ድጋፍ የተደረገበት፤ከ4600 በላይ ተማሪዎች ደብተርና ሌሎች ቁሳቁሶችን መደገፍ የተቻለበት በጥንካሬ ተነስቷል።

በአጠቃላይ በዞኑ በሁሉም የፓርቲው ቤተሰቦች እና አባላትና አመራሮች እና በሌሎችም በጎ አድራጊዎች ንቁ ተሳትፎ በክረምት ወራት በተከናወኑት አጠቃላይ የበጎ ስራዎች በሁሉም መስኮች 117 ሚሊዮን ብር ለማዳን ታቅዶ 93 ሚሊዬን ብር ከመንግስት ከዝና ማዳን መቻሉ ተገልጿል።

ህብረቷ በሩብ ዓመቱ በፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራትን የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኝ አብዛኛዉ አባላችን በራሱና በፓርቲ ፔጅ ላይክ ሼር ከማድረግ አንጻር የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባቸው
በአጽንኦት ተነስቷል ፡፡

በተማሪ መጠነ-መቋረጥ ላይ ተቀናጅቶ ከመስራት አንጻር ጅምሩ ጥሩ ቢሆንም በተለይ ትምህርታቸዉን አቋርጦ ስደት የሚሄዱ ሴት ተማሪዎችን ወደ ትምህርታ ለመመለስ ቅንጅታዊ ስራዎች ትኩረት መሰጠት እንደሚገባና ከወላጅ ጋር ተቀራርቦ መሥራት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

ከአገልግሎት አሰጣጥን ከማሻሻል አንጻር አብዛኛዉ ቤተሰብ ጥሩ ቢሆንም በተወሰኑ ተቋማት በተለይም የሰዓት አወጣጥና አገባብ መንጠባጠብ መኖሩ በቀጣይ መሻሸል እንደሚገባ ተነስተዋል።

በኮንፍረንሱ ከአባላት ለተነሱት ዝርዝር ጉዳዮች ከሚመለከታቸዉ የቤተሰብ አመራሮችና ከመድረክ ከመድረክ በቂ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዉ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
ሲል የሀላባ ዞን የብልጽግና ፓሪት ቅ/ ጽ/ቤት ዘግቧል።

በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ በላይኛው በደኔ ቀበሌ በአርሶ አደር ማህበራዊ መሰረት በላይ አራዶ ብልፅግና ህብረት አባላት አማካኝነት በክላስተር እየለማ የሚገኝ የበርበሬ ሰብል ከፊል አሁናዊ ገፅታ...
15/10/2025

በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ በላይኛው በደኔ ቀበሌ በአርሶ አደር ማህበራዊ መሰረት በላይ አራዶ ብልፅግና ህብረት አባላት አማካኝነት በክላስተር እየለማ የሚገኝ የበርበሬ ሰብል ከፊል አሁናዊ ገፅታ - በምስል

TIN (ግብር ከፋይ) ቁጥር ላላችሁ በሙሉከዚህ ቀደም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሳይኖራችሁ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላችሁ ግብር ከፋዮች ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥራችሁን ከፋይዳ...
15/10/2025

TIN (ግብር ከፋይ) ቁጥር ላላችሁ በሙሉ

ከዚህ ቀደም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሳይኖራችሁ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላችሁ ግብር ከፋዮች ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥራችሁን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር በአካል መሔድ ሳይጠበቅብዎ ይህን ሊንክ https://mor-migration.fayda.et በመጠቀም ማያያዝ ይችላሉ።

ይህን በማስተሳሰርዎ ፡
- ግብር በሚከፍሉበት ወቅት ጊዜዎን መቆጠብ ይችላሉ ፤
- በኦንላይን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ቀላል እንዲሆን እና እንዳይጭበረበር ይረዳል።

ያስተውሉ፦
የግል መረጃዎ ደህንነት በእርስዎ እጅ ስለሆነ ፤ ፋይዳ ልዩ ቁጥር (FIN) በገቢዎች ለሚሰጡ አገልግሎቶች ያለምንም ችግር ማጋራት ይችላሉ።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #ዲጂታልኢኮኖሚ

በሀላባ ዞን በዌራ ድጆ ወረዳ በሰው ተኮር ተግባር ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተገነቡ ቤቶች የቁልፍ ርክክብ እየተደረገ ነው፣በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መርህ ቃል በክረምት ወጣቶች...
15/10/2025

በሀላባ ዞን በዌራ ድጆ ወረዳ በሰው ተኮር ተግባር ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተገነቡ ቤቶች የቁልፍ ርክክብ እየተደረገ ነው፣

በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መርህ ቃል በክረምት ወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት በበሸኖ ከተማ ነዋሪ ግንባር ብልጽግና ህብረት ቁ.2 ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ የተገነባ ቤት ተጠናቆ የቁልፍ ርክክብ ተደረገ።

በመርሃ-ግብሩም ለአቅመ ደካማ ቤተሰቡ ከቁልፍ ርክክቡ በተጨማሪ የአልባሳትና የቤት ፍራሽናጠትራሶች፣የንብ ቀፎ፣የማሞከት በግ ድጋፍ ለማድረግ ተችሏል።

በዚህም ወቅት የሰው ተኮር ተግባራት የአቅመ ደካሞችን ችግሮች ከመቅረፍ ባሻገር የአብሮነት፣የመተሳሰብና ህብረብሔራዊ አንድነትን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።

ሁሉም አደረጃጀቶች በክረምቱ ወራት በበጎ ተግባር ተሰማርተው የፓርቲያችን የትኩረት አቅጣጫ የሆነውን ሰው ተኮር ልማት የመደጋገፍና የመረዳዳት ሥራዎችን ከግብ ለማድረስ በትኩረት መስረት እንደሚያስፈልግ አቶ ከይራቱ አብራርተዋል።
የዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን

የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረኮችን በማጠናከር የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተመላከተጥቅምት 5/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ...
15/10/2025

የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረኮችን በማጠናከር የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ

ጥቅምት 5/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከንግድና ገበያ ልማት እና ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ላይ የተዘጋጀ የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረክ በወልቂጤ ከተማ ከማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።

የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖ እንደተናገሩት የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረኮች በማጠናከር የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረኮች የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ወሳኝ ሚና አላቸው ያሉት ምክትል አፈጉባኤዋ በክትትልና ቁጥጥር ስራዎች ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል።

ምክር ቤቱ ለክልሉ ህዝብ ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዕድገት መፋጠን ፋይዳ ያላቸውን ህጎች በማውጣት ፣አፈፃፀማቸውን በመከታተልና በመቆጣጠር በርካታ ስራዎችን ሰርቷል ብለዋል።

በንግድ ስርዓቱ ህገወጥ ንግድና የዋጋ ንረት እንዲሁም በትራንስፖርት ዘርፍ አለአግባብ የታሪፍ ጭማሪ አሁንም ህዝቡ የሚማረርባቸው መሆኑን አንስተዋል።

የንግድ ስርዓቱን ከደላላ በማላቀቅ ቀጥታ የግብይት ስርዓት ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረው ህገ ወጥነትን ለመከላከል የህብረተሰብ ተሳትፎን ማጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል።

የትራንስፖርት አደጋ በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያስከተለ መሆኑን ጠቅሰው መድረኩ ጉድለቶች ለይቶ በመወያየት የመፍትሄ ሀሳቦች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል።

አሁን የደረስንበት የእድገት ደረጃ የሚመጥን አገልግሎት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የመልካም አስተዳደር ማነቆዎችን በወቅቱ በመለየት መፍታት እንደሚገባ ተናግረዋል።

በውይይት መድረኩ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ባዩሽ ተስፋዬን ጨምሮ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች፣ የክልልና የጉራጌ ዞን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና የወልቂጤ ከተማ የማህበረሰብ ተወካዮች እየተሳተፉ ነው።
ዘገባው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ነው

ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት የመከባበርና የመተሳሰብ እሴቶችን ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። *****ጥቅምት 5/2018)፣የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢ...
15/10/2025

ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት የመከባበርና የመተሳሰብ እሴቶችን ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ።
*****
ጥቅምት 5/2018)፣የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የአፈጻጸም ግምገማና የግብ ስምምነት መድረክ እየተካሄደ ነው።

በየአካባቢው ዘላቂ ሰላምን በማጽናት የእድገትና የልማት ስራዎችን ለማረጋገጥ በህዝቡ መካከል የመከባበርና የመተሳሰብ እሴቶችን ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታውቋል ።

የቢሮውና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት አመት የአፈጻጸም ግምገማና የያዝነው የ2018 በጀት አመት የግብ ስምምነት መድረክ በሆሳዕና ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ መድረኩን ሲከፍቱ እንዳሉት ሰላም የመተማመን፣ የመተሳሰብና የፍትሃዊነት ውጤት በመሆኑ በእነዚህ የጋራ እሴቶች ላይ በልዩ ትኩረት መስራት ያስፈልጋል። ዘርፉ በእነዚህ እሴቶች መረጋገጥ ላይ በትኩረት መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል ሃላፊው።

ለግጭት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን በጥናት መለየትና ፈጣን ምላሽ መስጠት ይገባል ያሉት አቶ ተመስገን ከዚህ ጎን ለጎንም በህዝቦች መካከል የወንድማማችነትና አብሮነት እሴቶች ላይ መስራት ይገባል ሲሉም አክለዋል።

በክልሉ እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶች አብዛኛዎቹ በግልና በጥቂት ቡድኖች ከተዛቡ ፍላቶች የሚመነጩ በመሆናቸው እነዚህን ግላዊ ጭፍን ፍላጎቶች ከህዝቡ መነጠል እንደሚገባ የቢሮ ሃላፊው ገልጸዋል ።

ቀላል የሚመስሉ ጉዳዮች ዋጋ እያስከፈሉ ነው ያሉት አቶ ተመስገን ቅጭቶችን አስቀድሞ መከላከል፣ ፈጣን ምላሽ መስጠት፣የኮሚኒቲ ፖሊሲንግን ማጠናከር ፣ተጠርጣሪዎችን ህግ ፊት ማቅረብ፣ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን መቆጣጠር ከሁሉም በላይ የማህበራዊ ሚዲያ ውዥንብሮችንና የጥላቻ መልዕክቶችን መልክ ማስያዝ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።
በገባው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ነው

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በዌራ ድጆ ወረዳ የስምቢጣ ቀበሌ እየለማ የሚገኝ የሙዝ ክላስተር አሁናዊ ከፊል ገጽታ በፎቶ፣በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በመሸጋገር ኢኮኖሚያዊ ብ...
15/10/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በዌራ ድጆ ወረዳ የስምቢጣ ቀበሌ እየለማ የሚገኝ የሙዝ ክላስተር አሁናዊ ከፊል ገጽታ በፎቶ፣

በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በመሸጋገር ኢኮኖሚያዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚሰሩ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በየአከባቢው አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው።

20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ጥቅምት  5/2018) በማ...
15/10/2025

20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ጥቅምት 5/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ደማቅ በሆነ መልኩ ለማክበር በቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እየተደረገ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዓሉን ለማክበር ከቅድመ ዝግጅት ኮሚቴዎች ጋር በጽ/ቤታቸው በነበራቸው የምክክር መድረክ እንደገለጹት 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

የበዓሉ መከበር የክልሉን ጸጋዎች ከማስተዋወቅ ባለፈ በህዝቦች መካከል ያለውን ትስስር ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችል ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በደማቅ ሁኔታ ማክበር እንዲቻል አብይ ኮሚቴ ተቋቁሞ ተከታታይነት ያለው የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ መሆኑ ይታወሳል።
ዘገባው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ነው

Address

Alaba K'ulito
212

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaba Tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Halaba Tv:

Share