Saro Media Network

Saro Media Network ወቅታዊ ፣ ታማኝ እና ሚዛናዊ መረጃ የሚያገኙበት ገጽ ነው ‼️

12/06/2026

አስተዋይ ሴት ልጅ 🥰🥰

Saro Media Network
12/06/2026

Saro Media Network

በጋሞ ዞን ውስጥ የት ይመስላቹሀል ??
12/06/2026

በጋሞ ዞን ውስጥ የት ይመስላቹሀል ??

‎በአርባምንጭ ከተማ  ከ7 ሺህ በላይ ተማሪዎች  ክልላዊ ፈተና እንደሚወስዱ ተገለፀ ‎‎በአርባምንጭ ከተማ ከ7 ሺህ በላይ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ ፈተና እንደሚወስዱ የከተማው ...
12/06/2026

‎በአርባምንጭ ከተማ ከ7 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ ፈተና እንደሚወስዱ ተገለፀ

‎በአርባምንጭ ከተማ ከ7 ሺህ በላይ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ ፈተና እንደሚወስዱ የከተማው ትምህርት መምሪያ አስታወቀ፡፡

መምሪያው የ2018 ዓ.ም ክልላዊ የፈተና አሰጣጥ ሂደት በማስመልከት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

‎የዘንድሮው ክልላዊና ሀገር አቀፍ ፈተና ከኩረጃ በጸዳ መንገድ ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን የመምሪያው ኃላፊ አቶ አብርሐም አምሳሉ ገልጸዋል፡፡
‌‎
‎አክለውም ዘንድሮው ከ3ሺህ 700 በላይ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ከ3 ሺህ 500 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

‎የ6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 8 እና 9/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

‎ተማሪዎች በፈተና ወቅት የሚያስፈልጋቸውን ቁሳቁስ ብቻ ይዘው እንዲገኙ እና የፈተና ህጎችን እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርበዋል።

‎ፈታኝ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች በጥብቅ ዲሲፕሊን እና በከፍተኛ ኃላፊነት ሥራቸውን እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

‎የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ አክሊሉ ኢያሱ በበኩላቸው፣ ፈተናው ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል ።

‎የሻራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አባ ወለደ ገብርኤል በቀለ ፣ ተማሪዎች ከኩረጃ በፀዳ መልኩ አንዲፈተኑ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ አስገንዝበዋል፡፡

‎የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረቡ ሰነዶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተወያይተዋል፡፡

የፌስቡክ ድንገተኛ መቋረጥ እና ወቅታዊ ሁኔታ‼️​ዛሬ በመላው ዓለም፣ በተለይም በኢትዮጵያ ከቀኑ 9:30 ጀምሮ የፌስቡክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ ቆይቷል።በዚህ መቋረጥ ምክንያት ተጠቃሚዎ...
12/06/2026

የፌስቡክ ድንገተኛ መቋረጥ እና ወቅታዊ ሁኔታ‼️

​ዛሬ በመላው ዓለም፣ በተለይም በኢትዮጵያ ከቀኑ 9:30 ጀምሮ የፌስቡክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ ቆይቷል።

በዚህ መቋረጥ ምክንያት ተጠቃሚዎች ወደ አካውንታቸው መግባት (Log in) መከልከል፣ ገጾችን ማደስ (Refresh) አለማስቻል እና መልዕክቶችን መላክ አለመቻል አጋጥሟቸው ነበር።

​ችግሩ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተ የቴክኒክ ብልሽት ነበር። ከፌስቡክ በተጨማሪ የሜታ ኩባንያ የሆኑት ኢንስታግራም (Instagram) እና ዋትስአፕ (WhatsApp) ላይም ከፊል መቆራረጦች ታይተዋል።

አገልግሎቱ በድንገት ሲቋረጥ በርካታ ተጠቃሚዎች "የፌስቡክ አካውንቴ ተጠለፈ (Hack ተደረገ)?" የሚል ስጋት አድሮባቸው የነበረ ቢሆንም፣ ችግሩ ከራሱ ከሜታ ኩባንያ ሰርቨር የመነጨ እንደነበር ታውቋል።

​የኩባንያው የቴክኒክ ባለሙያዎች ባደረጉት አስቸኳይ ጥገና፣ አሁን ላይ ችግሩ ተፈትቶ አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ ወደ ቀድሞ ሁኔታው ተመልሷል።

​ማስታወሻ፦ አሁንም ድረስ መተግበሪያው በትክክል እየሰራላችሁ ካልሆነ፣ ስልካችሁን 'Restart' በማድረግ ወይም ከፌስቡክ መተግበሪያው 'Log out' ብላችሁ እንደገና በመግባት መጠቀም ትችላላችሁ።

"በእውነት ተፀፅቻለሁ‼️" አርቲስት አስጌ ዴንዳሾአርቲስት አስገኘዉ ከሰሞኑ ከአርሲ ኦርቶዶክሳዉያን ጋር ተያይዞ በተገኘበት የስታዲየሙ ኮንሰርት በብዙዎች የገጠመዉን ተቃዉሞ ተከትሎ በፌስቡክ ...
12/06/2026

"በእውነት ተፀፅቻለሁ‼️" አርቲስት አስጌ ዴንዳሾ

አርቲስት አስገኘዉ ከሰሞኑ ከአርሲ ኦርቶዶክሳዉያን ጋር ተያይዞ በተገኘበት የስታዲየሙ ኮንሰርት በብዙዎች የገጠመዉን ተቃዉሞ ተከትሎ በፌስቡክ ገፁ የሚከተለዉን የይቅርታ መልዕክት አጋርቷል
👇👇👇

"ወዳጅ ወገኖቼ…

🫵🏽ባለቀሳችሁበት ቦታ ሳቃችሁ ይሰማ!!
🫵🏽ፈጣሪ የተሰበረውን ልባችሁን ጠግኖ ህመማችሁን ያስረሳ!! 🙌💔
🫵🏽በቃችሁ ይበላችሁ!!
🫵🏽ደስታ መቅደሳችሁን ፡ ቤታችሁን ይሙላው!!💕

ግና ግን…

ከ’ናንት ጫማ ወጥታችሁ ፡ በ’ኔ ጫማ አስቡኝ ፤
አትጥሉኝ አትግፉኝ ፡ ወደ እቅፋችሁ ሳቡኝ ፤
አቅጄ ያረኩኝ አንዳች የለም’ና ፡ እስኪ አፉ በሉኝ።🙏🏽❤️

አመሰግናለሁ ፤ እወዳችኋለውም።"

''የፌዴራል መንግሥቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ መውሰድ አለበት! ኢዜማ'' አካሄዱ ''መኢሶንን ይመስላል'' በሚል የሚተቸው ኢዜማ በትግራይ ያንዣበበውን ወታደራዊ ውጥረት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷ...
12/06/2026

''የፌዴራል መንግሥቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ መውሰድ አለበት! ኢዜማ''

አካሄዱ ''መኢሶንን ይመስላል'' በሚል የሚተቸው ኢዜማ በትግራይ ያንዣበበውን ወታደራዊ ውጥረት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡ የፌዴራል መንግስቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድም ጠይቋል፡፡

ሕውሓት ደርግን ጥሎ ስልጣን ከተቆጣጠረ አንስቶ የሰራቸውን ጥፋቶች የሚዘረዝረው መግለጫው፤ አሁን ላለው አገራወ ችግር መንስኤው ሕውሓት ያሠፈነው የብሔር ፖለቲካ እንደሆነ አንስቷል፡፡

ለፕሪቶሪያ ስምምነት አለመተግበር እና ለተፈናቃዮች አለመመለስ ሕውሓትን ብቻ ተጠያቂ ያደገው የፓርቲው መግለጫ፤ ይህንን ኃይል በቃህ ማለት እና በትግራይ ያሉ ወገኖቻችንን ከማያባራ መከራ መታደግ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል፤ ጦርነትን ሳይጀመር በፊት ማስቆም ይገባናል ሲል ጠይቋል፡፡

''እንደ ሕወሓት ዓይነት ደም የማይጠረቃ አካል እና እሱን የሚዘውሩ ጥቂት ግለሰቦች በቃችሁ ብሎ ለማስቆም እና የትግራይ ህዝብን ካላስፈላጊ መከራ ለመታደግ በህዝብ ላይ ምንም አይነት መስዋዕትነት በማያስከትል መልኩ በሕገወጥ ቡድኑ ላይ ብቻ ያነጣጠረ አስፈላጊ ሕጋዊ እርምጃ በመንግሥት እና ከመንግሥት ጋር በጋራ በሚቆሙ ማንኛውም ለትግራይ ማኅበረሰብ በሚቆረቆር አካል ሊወሰድ እንደሚገባ ያምናል'' በማለት ሕውሃት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡

  ኑሯቸውንና ትዳራቸውን በጽኑ እጃቸው አጥብቀው ይይዛሉ።ልጆቻቸው ማዕድ አጥተው የሰው ፊት እንዳያዩ፣ አንገታቸውን ደፍተው ከሰው በታች እንዳይሆኑ   ይተጋሉ።ገና ጎህ ሳይቀድ ወደ እርሻ ይተ...
12/06/2026

ኑሯቸውንና ትዳራቸውን በጽኑ እጃቸው አጥብቀው ይይዛሉ።

ልጆቻቸው ማዕድ አጥተው የሰው ፊት እንዳያዩ፣ አንገታቸውን ደፍተው ከሰው በታች እንዳይሆኑ ይተጋሉ።

ገና ጎህ ሳይቀድ ወደ እርሻ ይተምማሉ፤ ማይሎችን አቆራርጠው ፤ ልጆቻቸውንና ከብቶቻቸውንም ያጠጣሉ።

ይህንን ሁሉ ተራራ የሚያህል ኃላፊነት የሚሸከሙት በመጫጫንና በመጨናነቅ ሳይሆን፣ ከውስጥ በመነጨ ጥልቅ #ደስታ ነው።

ለእነሱ እረፍት ማለት ሥራ መፍታት ሳይሆን ሥራ ላይ መዋል ነው፤ የሚከፋቸውና የሚጠወልጉት ያለ ሥራ ሲውሉ ብቻ ነው።

በእርግጥም የታታሪነት ሕያው መሠረት፣ የማኅበረሰቡ የጀርባ አጥንትና የማኅበራዊ ትስስሩ ዋነኛ የብርታት ምንጭ ናት።

"ሀይላሾ” የተሰኘው ባለ ሁለት ወለል ዘመናዊ የሞተር ጀልባ በአርባ ምንጭ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል እየተደረገለት ይገኛልጋሞ ልማት ማህበር 60 ሰዎችን ማጓጓዝ የሚችል “ሀይላሾ” የተሰኘ ...
11/06/2026

"ሀይላሾ” የተሰኘው ባለ ሁለት ወለል ዘመናዊ የሞተር ጀልባ በአርባ ምንጭ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል እየተደረገለት ይገኛል

ጋሞ ልማት ማህበር 60 ሰዎችን ማጓጓዝ የሚችል “ሀይላሾ” የተሰኘ ባለ ሁለት ወለል ዘመናዊ የሞተር ጀልባ በዛሬው ዕለት ወደ አርባ ምንጭ ከተማ አስገብቷል።

ጀልባው ወደ ከተማዋ ሲገባም ከህብረተሰቡና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ደማቅ አቀባበል በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

“ቅድሚያ ለጋራ ልማት” በሚል መርህ የሚንቀሳቀሰው ጋሞ ልማት ማህበር፣ በአባያ ሐይቅ ላይ የቱሪዝምና የውሃ ትራንስፖርት አገልግሎቶችን ለማስፋፋት 60 ሰዎችን የመጫን አቅም ያለው “ሀይላሾ” የተሰኘ ባለ ሁለት ወለል ዘመናዊ የሞተር ጀልባ ማስገባቱን ገልጿል።

ይህ ዘመናዊ ጀልባ በአባያ ሐይቅ ላይ የቱሪዝም መስህቦችን ለማስተዋወቅ፣ የጎብኚዎችን ተደራሽነት ለማሳደግ እንዲሁም የውሃ ትራንስፖርት አገልግሎትን የበለጠ ለማዘመን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተጠቁሟል።

“ሀይላሾ” የተሰኘው ጀልባ ወደ ስራ ሲገባ በአካባቢው የቱሪዝም እንቅስቃሴን ከማነቃቃት ባለፈ ለኢኮኖሚያዊ እድገትና ለስራ እድል ፈጠራም አዎንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል።

11/06/2026

Part 7

Address

Arba Minch'

Telephone

+251911238014

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Saro Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Saro Media Network:

Share