ኢዜአ

ኢዜአ ይከተሉን ምርትና አገልግሎትዎን እናስተዋውቃለን።
09-42-81-81-42

26/06/2025
26/06/2025
26/06/2025
25/06/2025

ዛሬ በምሽት ዜና መፅሔት

👉 ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሄደዋል ። ይሄ ለዘርፉ ምን ማለት ነው ? በትንታኔ ተዘጋጅቷል ።

👉 የሚዲያ ባለሙያዎች የህግ ፣ የፋይናንስና የአሰራር ማሻሻያ እንዲደረግ ጠይቀዋል ? የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምን መፍትሄ አለው ? እንጠይቃል።

👉 ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽንና ጥራት ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው ። በጉባኤው ምን ተነሳ ? በዝርዝር ትሰማላችሁ ።

👉የአውሮፓ ህብረት ከሩሲያ ጋር የገባው የኢኮኖሚ ጦርነት ወደ ወታደራዊ ግጭት እየተሸጋገረ ይገኛል። ሂደቱ ምን አዲስ ነገር በአለም ጂኦፖለቲካ ላይ ያስከትል ይሆን? ይዳሰሳል ።

👉ስፖርት - ቶማስ ፓርቴ አርሰናልን እንደሚለቅ ተረጋግጧል ። አዲዲስ የዝውውር መረጃዎች ዝግጁ ናቸው ።

የእለቱ አብይ ርእሰ ጉዳዮች በዝርዝር እና በትንታኔ ።

የዜና ክፍል ጋዜጠኞች እነዚህን ጨምሮ ሌሎች ዘገባዎችን አካተው በፋና የምሽቱ ዜና መጽሔት ሊያስደምጧችሁ ዝግጁ ናቸው ።

ሳሙኤል እንዳለ ይጠብቃችኋል።

በኤፍ ኤም 98 .1 እና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ ኤፍ ኤሞቻችንን እንዲሁም www.fanamc.com በመላው ሃገሪቱና በዓለም ዙሪያ ስርጭታችንን መከታተል ትችላላችሁ።

ከምሽቱ 1: 00 ሰዓት ይጠብቁን።

24/06/2025

7:00

24/06/2025

Good News for Middle East & Good News for the World.
Israel-Iran agreed to the consistnent cease fire with the help of Qatar says US President Donald Trump. Hope it’s true..!

21/06/2025
20/06/2025

የዛሬ ሰኔ 13፣ 2017 የቀን 6፡00 የቀጥታ ስርጭት ዜና ዋና ዋና ጉዳዮች

 #ሳይማሩና ዕውቅና ሳያገኙ ቀዶ-ህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ወንድማማቾች ተያዙ።በቼክ ሪፐብሊክ በኢንተርኔት ባገኙት መመሪያ ለበርካቶች የጥርስ ህክምና ሲሰጥ የነበረ አንድ የ22 ዓመት ወጣት ...
19/06/2025

#ሳይማሩና ዕውቅና ሳያገኙ ቀዶ-ህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ወንድማማቾች ተያዙ።

በቼክ ሪፐብሊክ በኢንተርኔት ባገኙት መመሪያ ለበርካቶች የጥርስ ህክምና ሲሰጥ የነበረ አንድ የ22 ዓመት ወጣት እና ሁለት ረዳቶቹ ክስ ተመሰረተባቸው።

እነዚህ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተካሳሾች ህክምና ለመስጠት የሚያስችል ፍቃድ ሳይኖራቸው ሃቭሊኮቭ ብሮድ በሚገኝ ቤታቸው ውስጥ ቀዶ ህክምና ጭምር ለማድረግ የሚያስችላቸውን ክሊኒክ ከሁለት ዓመት በፊት ነበር የከፈቱት።

በዚህ ክሊኒክ "አስፈላጊው የባለሙያ እውቀት ሳይኖራቸው" በርካቶችን 'እያከሙ' እንደነበር ፖሊስ ገልጿል።

ኢዜአ

የ8 ዓመት ታዳጊን ብስኩት ልግዛልሽ በማለት አታሎ አስገድዶ የደፈረ ግለሰብ በ15 ዓመት ተቀጣ!በምስራቅ ቦረና ዞን ነገሌ ወረዳ አስተዳደር  በስምንት ዓመት ታዳጊ ላይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃ...
19/06/2025

የ8 ዓመት ታዳጊን ብስኩት ልግዛልሽ በማለት አታሎ አስገድዶ የደፈረ ግለሰብ በ15 ዓመት ተቀጣ!

በምስራቅ ቦረና ዞን ነገሌ ወረዳ አስተዳደር በስምንት ዓመት ታዳጊ ላይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት የፈጸመው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገልጿል ።

የምስራቅ ቦረና ዞን ፖሊስ ዋና መምሪያ የሴቶች እና ህጻናት ጉዳይ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዘውድነሽ አበበ ነገሩኝ ሲል ብስራት ሬዲዮ አንዳጋራው ተከሳሽ ዮሴፍ ፈጠነ የታዳጊዋ ወላጆች ወደ ስራ መሄዳቸውን ጠብቆ ብስኩት ልግዛልሽ በማለት አታሎ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት በመውሰድ ጥቃቱን እንደፈጸመባት ተጠቁሟል።

ህጻኗ ደም እየፈሰሳት መንገድ ላይ ወድቃ ያገኟት ነዋሪዋች ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ ወደ ህክምና ቦታ ተወስዳ እርዳታ እንድታገኝ መደረጉ ተገልጿል ። ተጎጂዋ ህክምና ከተሰጣት በኋላ ለፖሊስ በሰጠችው መረጃ መሰረት ጥቃቱን የፈጸመባት የ31 ዓመቱ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋል ችሏል።

ፖሊስ አስፈላጊውን በምርመራ በሀኪም እና ከሰዎች በተገኛ መረጃ መሰረት በማጠናከር መዝገቡን ለዓቃቢ ህግ ልኳል ። ዓቃቢ ህግ በወንጀል ህግ ቁጥር 6 /27 በህጻናት ላይ በሚፈጸም የህጻናት የግብረስጋ ድፍረት በደል በመጥቀስ ክስ መስርቷል።

ክሱን ሲከታተል የቆየው የምስራቅ ቦረና ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የሱፍ ፈጠነ ዕድሜዋ ባልደረሰች ልጅ ላይ አታሎ የመድፈር ጥቃት በመፈጸም ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በአስራ አምስት ዓመት እስራት እንዲቀጣ መወሰኑንም ነው ዘገባው ያመላከተው፡፡

ኢዜአ
EBC news
Sheger Times Media
Sheger Times
Sheger Time
Sheger Tube
Sheger Times

19/06/2025

የዜና እርማት ስለመስጠት

ድሬ ቲዩብ ሰኔ 11 ቀን 2017 "የራሳቸው ቆጣሪ ሳይኖራቸው ከጎረቤት በገመድ ኃይል ስበው በሚገለገሉ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ቅጣት እንደሚጣል ተገለጸ" በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ዘገባ አሠራጭቷል።

ይሁንና አዲስ በፀደቀው መመርያ አንቀፅ 2.3.2 ቅጣቱ የሚጣልበት የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት መፈጸሙ ለተረጋገጠበት ደንበኛ መሆኑን ተገንዝበናል። ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ እየጠየቅን ቅጣቱ የሚጣለው ስርቆቱን ከአቅርቦት መነሻ ለፈፀመ መሆኑ ተስተካክሎ እንዲነበብ ለመጠየቅ እንወዳለን።

ስርቆቱን የሚፈፅም ደንበኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ በጊዜያዊነት ከምሰሶ ወይም ከአቅርቦት መነሻ ላይ የሚቋረጥ ሆኖ የድርጅቱ የሕግ አገልግሎት ፖሊስ ወይም የህግ አካል የምርመራ ሒደቱን ማጠናቀቁን በጽሑፍ እስኪያሳውቅ እንዲሁም ደንበኛው የሚጠበቅበትን ክፍያ እስኪፈፅም እና መተማመኛ የውል ሠነድ ላይ እስኪፈርም ድረስ ተቋርጦ የሚቆይ ይሆናል፡፡ ሲስተም ላይ በጊዜያዊነት ተቋርጦ የሚቆይ ሆኖ ውሳኔ ካገኘ በኋለ ቀጣይ ርምጃ ይወሰዳል፡፡

በተጨማሪም ማቋረጡ እና ጥፋቱ ለሕግ አገልግሎት ክፍል ማስተላለፉ እንዲሁም የጥፋቱ መረጃ ፋይል መደረጉ እንደተጠበቀ ሆኖ ከሌሎች ክፍያ በተጨማሪ ውል በመተላለፉ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመካከለኛ ኢንዱስትሪ ታሪፍ መደብ ተጠቃሚ ብር 1,000,000.00 (አንድ ሚሊዮን ብር)፣ ለዝቅተኛ ኢንዱስትሪ ታሪፍ መደብ ተጠቃሚ ብር 750,000.00 (ሰባት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር)፣ ለጠቅላላ ታሪፍ መደብ ተጠቃሚ ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) እና ለመኖሪያ ቤት ታሪፍ መደብ ተጠቃሚ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ቅጣት ይጣላል።

ከዚህ በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ኃይል ሥርቆት በድጋሚ መፈጸሙ ለተረጋገጠ ደንበኛ ቀድሞ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ አስተዳደራዊ ቅጣቱ ሁለት እጥፍ እንዲከፍል ይደረጋል ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ ከመኖሪያ ቤት ታሪፍ መደብ ተጠቃሚ በቀር ለጠቅላላ ታሪፍ ደንበኛ 1 ሚሊዮን ብር፣ ለዝቅተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ ታሪፍ ደንበኞች ደግሞ 2 ሚሊዮን ብር ተቀማጭ (Security Deposit) ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያስይዝ ይደረጋል፡፡

ከሁለት ጊዜ በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት ለሚፈጽም ደንበኛ ከላይ የተቀመጠው እንደተጠበቀ ሆኖ አስተዳደራዊ ቅጣቱና ተቀማጩ (Security Deposit) ቀደም ሲል ከከፈለው በእጥፍ እንዲያሳድግ ይደረጋል፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት ፈጽሞና በአሠራር ሥርዐቱ መሠረት ተገቢውን መስፈርት አሟልቶ ኃይል የተገናኘለት ደንበኛ ለሁለት ዓመት በሕጋዊ አግባብ መጠቀሙ ሲረጋገጥ ያስያዘው ተቀማጭ (Security Deposit) ገንዘብ እንዲመለስለት የሚደረግ ይሆናል።
#ድሬቲዩብ

Address

Kamba Gamo
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢዜአ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share