Visit Arba Minch

Visit Arba Minch Media/News Company

05/06/2026

የ ቢንጎ ጨዋታ ስራ ለመጀመር ያሰባቹ አሁኑኑ ይደውሉልን በጣም በአነስተኛ % ዳጎስ ያለ ትርፍ
# ለ አዳድስ ኤጀንቶች የ3,000 ብር ነፃ ማበረታቻ ጋር !!
ፈጣን ምርጥ የ ቢንጎ ሲስተም ይደውሉልን

🔹 ለ ፑል ቤቶች
🔹 DSTV
🔹 GAME ZONE
🔹ለተለያዩ መዝናኛ ቤቶች
🔹ኬኖ ቤቶች
🔹ለክልል ከተሞች
ያለ እንተረነት የሚሰራ የ ስልክ እና የ ኮምፒውተር ያለው

CALL
+251901155759
www.katbingo.net

ወቅታዊ ታሪፍ!
05/06/2026

ወቅታዊ ታሪፍ!

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ሲቀላ ቅርጫፍ ዕቃ ጭኖ ለመሄድ የመጣው ተሽከርካሪ ጉዳይ ቅሬታን ፈጥሯል ~  ግንቦት 28/2018 ዓ.ም በትላንትናው ዕለት በሰራነው ዘገባ ከ40 ሺህ በላይ...
05/06/2026

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ሲቀላ ቅርጫፍ ዕቃ ጭኖ ለመሄድ የመጣው ተሽከርካሪ ጉዳይ ቅሬታን ፈጥሯል

~ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም

በትላንትናው ዕለት በሰራነው ዘገባ ከ40 ሺህ በላይ ደንበኞች ማፍራት የቻለው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ሲቀላ ቅርጫፍ ሊዘጋ መሆኑን የተመለከተ መረጃ ማድረሳችን ይታወሳል።

ጉዳዩን በተመለከተ አሁን የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው
በትላንትናው ዕለት ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ በሲቀላ ቅርንጫፍ የሚገኙ አጠቃላይ የባንኩን ዕቃዎች ለመጫን የመጣ ተሽከርካሪ በፀጥታ አካላትና በወጣቶች እርብርብ ዕቃውን እንዳይጭን መከልከሉን ለማወቅ ችለናል።

በባንኩ የሚገኙ ቁሳቁሶችን ለመጫን የመጣው ተሽከርካሪ በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ቆሞ ጥበቃ እየተደረገለት መሆኑንም ሰምተናል።

አርባምንጭ ሲቀላ ቅርጫፍን ለመዝጋት የሚደረገው እንቅስቃሴ አደገኛ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱም የመረጃ ምንጮቻችን ገልጸዋል።

ከ40 ሺህ በላይ ደንበኞችን በማፍራት ከ20 ዓመታት በላይ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ሲቀላ ቅርጫፍ ከሰኔ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ከነጭ ሳር ቅርንጫፍ ጋር ይዋሃዳል መባሉ በደንበኞቹ ዘንድ ቅሬታ መፍጠሩ ይታወቃል።

05/06/2026

ከ 2.5 ሚሊዮን የመንግስት ሠራተኛ ቢያንስ 300 መቶ ሺው ፖስት ሸር ቢያደርግ የእኛ ጉዳይ በጣም ሙዝ የመላጥ ያክል ቀላል ነው።

ዳኛዋ ውሳኔ ሲያነቡ በሽ*ጉጥ ተገ*ደሉ! 😭ተከሳሹ በምስሉ ላይ የሚታዩትን በሆለታ የወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቤተሰብ ችሎት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳን ዉሳኔ እያነበበች እያለች በ...
04/06/2026

ዳኛዋ ውሳኔ ሲያነቡ በሽ*ጉጥ ተገ*ደሉ! 😭

ተከሳሹ በምስሉ ላይ የሚታዩትን በሆለታ የወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቤተሰብ ችሎት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳን ዉሳኔ እያነበበች እያለች በሽ*ጉጥ ገድ*ሏቸዋል።

ግድ*ያው የተፈጸመውም ዛሬ ዳኛዋ ውሳኔ በማንበብ ላይ በነበሩበት ወቅት ነው።

 አስቸኳይ መረጃ፡ በአለልኝ ጉዳይ ላይ የይግባኝ ውሳኔው ውዝግብ አስነሳበማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች እየተሰራጨ ባለው መረጃ መሠረት፣ የአለልኝ ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አይዳ እና የባለቤታቸው እህ...
04/06/2026


አስቸኳይ መረጃ፡ በአለልኝ ጉዳይ ላይ የይግባኝ ውሳኔው ውዝግብ አስነሳ

በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች እየተሰራጨ ባለው መረጃ መሠረት፣ የአለልኝ ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አይዳ እና የባለቤታቸው እህት ባል የሆኑት ሉንጎ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ መለቀቃቸው እየተነገረ ይገኛል።

እነዚህ ግለሰቦች ከዚህ ቀደም ጥፋታቸውን አምነው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል።

የይግባኝ ችሎቱ ውሳኔ መነገሩን ተከትሎ፣ የብዙዎችን ትኩረት የሳበና ጥያቄዎችን ያስነሳ ጉዳይ ሆኗል።

ይህ መረጃ በአሁኑ ሰዓት የእኛ የዜና ክፍል ጉዳዩን አስመልክቶ ከአለልኝ ወንድም ተጨማሪ ማብራሪያ ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል።

ማህበረሰቡ ይህንን መረጃ እንደ "የተረጋገጠ" ከመውሰዱ በፊት፣ እስክናረጋግጥለት ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቅ እንጠይቃለን።

የሚወሩት ወሬዎች እውነት የሚሆኑ ከሆነ፣ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ አስመልክቶ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመተማመን ቀውስ ሊፈጥር እንደሚችል እየተነገረ ነው።

በሕግ ባለሙያዎችና በፍትሕ ሥርዓቱ ታዛቢዎች ዘንድም በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ የሚችል ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።

እኛም ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተልን፣ ትክክለኛውን መረጃ ከቤተሰብና ከታማኝ ምንጮች እንደደረሰን ለውድ ቤተሰቦቻችን የምናደርስ ይሆናል።

ይህ ጉዳይ እያደገ ያለ ዜና ነው፤
ተጨማሪ ዝርዝሮች ሲኖሩ እንመለሳለን።

©️ጉርሻ Page

🌴🌴🌴

በባሏ የተገደለች ነፍስ.....ግንቦት 25/2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ጋርሳ ሐኒቃ ዙሎ ቀበሌ በባልና በምስት መካከል በተፈጠረው ቀላል ግጭት የምስት ሕይወት በባሏ ተቀጥፏል።...
04/06/2026

በባሏ የተገደለች ነፍስ.....

ግንቦት 25/2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ጋርሳ ሐኒቃ ዙሎ ቀበሌ በባልና በምስት መካከል በተፈጠረው ቀላል ግጭት የምስት ሕይወት በባሏ ተቀጥፏል።

ነገሩ እንዲህ ነዉ። ወጣት ደነቀ ደባልቄ እና ወ/ሮ ማርታ ሞንጆሬ በዙሎ 01 ትዳር መስርተውና 2 ወንድ ልጆችን ወልደዉ በጋራ እየኖሩ ባሏ ኪስ አዉላቂ ሆኖ የተቸገረችዉ ምስት በየቀኑ የሚትሰማዉ ወሬ ለጆሮዋ ያልጣማት ምስት ይህ ስርቆት ወንጀል በአካባቢው የተወገዘ መሆኑን ስለምታውቅ ተበሳጭታ ልጆቿን ጥላ ከቤት ለማምለጥ በተደጋጋሚ ሙከራ አድርጋ (በቀበሌዉ በሽምግልና ብዛት ቤተሰቦቿ ተይዘዉ ለማምለጥ) አልተሳካላትም። ከዛሬ ነገ ባሏ ከዚህ ወንጀል ድርጊትና ከማጭበርበር ድርጊቶች እንድርቅ ያሰበችዉ ባሏን ከወንጀል ለማራቅ የወሰደችው እርምጃ ሕይወቷ እንድያልፍ አድርጓል።😭

በመሃል የአካባቢው ታዋቂ የአገር ሽማግሌዎች፤
1ኛ. አቶ አበራ ዘዉዴ፤
2ኛ. አቶ ገበየሁ ጋሼ እና
3ኛ. አቶ ወንዱ ካሳዬ ሆነዉ ወደ ሟች (ምስት) ቤተሰቦቿ (እናትና አባት ቤት) መጥተው ስለሚኗቸዉ ቤተሰቦቿ እንቢ ለማለት ከበዳቸውና አደራ እያሉ ለአገር ሽማግሌዎች አስረከቡ።

ሆኖም ነገሩ ቤተሰቦቿ እንደጠበቁት አልሆነም። በሽማግሌዎች ፊት ባሏ አቶ ደነቀ ደባልቄ የገዛ ምስቱን የ2 ወንድ የልጆቹን እናት ወይዘሮ ማርታ ሞንጆሬን በጩቤ ወጋት። ገ......ደላት።😭

ያልተጠበቀ ወንጀል። ባሁኑ ሰአት ሽማግሌዎችም ሁሉ በካምባ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ በጥርጣሬ በእስር ላይ ይገኛሉ። አያድርስ ነዉ።

በቅርቡ በጋርሳ ሐኒቃ ዙሎ ወንጀል እየተበራከተ የመጣ ሲሆን በቅርቡ አንዲት ወጣት በቀበሌው ወደ ጋላልኦ ንዑስ ወደ ቤቷ እየሄደች ተዘርፋ የተገደለች ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የሟች ወንድም ባለፈው ሳምንት አቶ አቡጫ ሜንኮ የተባለው ከ70 ዓመት በላይ ሽማግሌ አቶ ኡሌ ኡቱሎ የተባሉትን ሽማግሌ (revenge) እቤታቸው በተኙበት በጠዋት ገብቶ በጩቤ ብዙ ቦታ ወግቷቸዉ ገድሎ በካምባ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራው እየተጣራ መሆኑ ተገልጿል።😭

በካምባ ዙሪያ ወረዳ በጋርሳ ሐኒቃ ዙሎ ቀበሌዎች እየተፈጸሙ ያሉ የሕገወጥ መሬት ወረራና የነፍስ ግዲያ ወንጀሎችን የጋሞ ዞን አስተዳደርና የሚመለከታቸው ባለድርሻዎች እያጠኑ አጥፊዎችን ለሕግ እንዲያቀርቡ ጥሪ እናቀርባለን።

ለሟች ማርታ ሞንጆሬ ቤተሰቦች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

03/06/2026

የቤት አበል የትራንስፖርት የህክምና ይታሰብ የደሞዝ ግብር ይቀነስ የደሞዝ ዝቅተኛ ወለል ይወሰን!!
ቻሌንጁን ተቀላቀሉ!!

ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የአንስቴዥያ እጩ ተመራቂ ተማሪዎችለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴርለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትጉዳዩ፦ ለCOC ፈተና ቅድመ ምዝገባ እንዲፈቀድልን የቀረበ አቤቱታእኛ የጅማ ዩኒቨርሲቲ...
03/06/2026

ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የአንስቴዥያ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች

ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር
ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት

ጉዳዩ፦ ለCOC ፈተና ቅድመ ምዝገባ እንዲፈቀድልን የቀረበ አቤቱታ

እኛ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የአንስቴዥያ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች ላለፉት 6 ዓመታት በትጋትና በጽናት ትምህርታችንን ስንከታተል ቆይተን ያካበትነውን የትምህርት ጉዞ በመጨረሻ ወደ ማጠናቀቅ ደረጃ ላይ እንገኛለን።

በተለያዩ ምክንያቶች የትምህርት ቆይታችን በካሪኩለሙ ከተወሰነው ጊዜ አልፎ በመራዘሙ ከ1 ዓመት በላይ ተጨማሪ ጊዜ ለማሳለፍ መገደዳችን ይታወቃል።

ይህ ሆኖ ሳለ: በቅርቡ የCOC ፈተና እንደሚሰጥ የሚታወቅ ሲሆን: ለፈተናው ለመመዝገብ የExit Exam ውጤት እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡ ብዙዎቻችን በዚህ ዙር ፈተናውን እንዳንወስድ ያደርገናል። እንደ አንስቴዥያ ባለሞያ ተጨማሪ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ፈተና (licence exam) ከፊታችን የሚጠብቀን በመሆኑ ወደ ስራው ዓለም ከመቀላቀላችን በፊት ሌላ ተጨማሪ ጊዜ እንድንጠብቅ የሚያደርግ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና የሞራል ጫና የሚያሳድርብን ሆኖ አግኝተነዋል።

በመሆኑም: የExit Exam ውጤት እስኪገለጽ ድረስ ለCOC ፈተና ቅድመ ምዝገባ እንዲፈቀድልን በአክብሮት እንጠይቃለን። ይህ አሰራር ተማሪዎች ካላስፈላጊ ወጪ: ያለስራ ከሚባክን ጊዜና ጉልበት ይታደጋል።

ስለዚህ ጥያቄያችንን በበጎ አመለካከት ተመልክታችሁ ተገቢውን ድጋፍ እንድታደርጉልን በትህትና እንጠይቃለን።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ
የአንስቴዥያ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች

Address

Gamo Zone
Arba Minch'
76115698

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Visit Arba Minch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share