Arbaminch General Hospital

Arbaminch General Hospital ይህ የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ትክክለኛው የፌስቡክ ገጽ ነው!

20/08/2026



በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የክረምት በጎ ተግባር ነፃ የሕክምናና የምርመራ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።           __________________________               ...
19/08/2026

በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የክረምት በጎ ተግባር ነፃ የሕክምናና የምርመራ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።
__________________________
ነሐሴ 13/2018
አርባምንጭ

በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የዘንድሮው የክረምት በጎ ተግባር አገልግሎትን በማስመልከት በሆስፒታሉ የተለያዩ የጤና ምርመራዎች እየተሰጡ እንዳለ የገለፁት የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተወካይና የሜዲካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አዲሱ ተስፋዬ ይህ ተግባር የሚቀጥልና የትኛውም ሰው መቶ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል በማሳሰብ በሆስፒታላችን እየተሰጠ ያሉ የምርመራ ዓይነቶች መካከል






እንዲሁም
ቀዶ ህክምና አገልግሎት ከቀን 15-17 ሊሰጥ እንዳለ እና በተመሳሳይም ደግሞ መርሀግብሮችን በመከወን እንደሚቀጥሉም አሳስበዋል።

የሆስፒታሉ የ Nursing and Midwifery Service Director የሆኑት አቶ በዛብህ በቀለ አክለውም እያንዳንዱ የሕብረተሰባችን ክፍሎች ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ጤና ምርመራ በማድረግ እንዲያረጋግጡ እና ከድንገተኛ ስጋት ራሳቸውን እንዲጠብቁ ሲሉም አሳስበዋል።

ሁሉም ሰው የጤናውን ሁኔታ ባለማረጋገጡ ምክንያት የተለያዩ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችና ድንገተኛ ሕመሞች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ስለጤናቸው ሁኔታ ምርመራን በማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ የጠቆሙት የሆስፒታሉ የሕክምና ጥራት አገልግሎተት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጠረፉ ተካ አሳስበዋል።

የምርመራ ሂደቱም በተለያዩ የግንዛቤ መስጫ መንገዶችን በመጠቀም በድምጽ ማጉያ እና በተለያዩ የጤና መረጃ የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በመጠቀም አገልግሎቱን በጥሩ ሁኔታ እየተሰጠ መሆኑን አንዳንድ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።

🏥

የ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠናዊ ስብሰባን ለአገር ገፅታ ግንባታ ከማዋል አንጻር የሚድያ ሚና ከፍተኛ ነዉ__________ከነሐሴ 16/2018 ጀምሮ አገራችን የምታስተናግደው የ7...
18/08/2026

የ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠናዊ ስብሰባን ለአገር ገፅታ ግንባታ ከማዋል አንጻር የሚድያ ሚና ከፍተኛ ነዉ
__________

ከነሐሴ 16/2018 ጀምሮ አገራችን የምታስተናግደው የ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠናዊ ስብሰባ (RC76) በማስመልከት ለሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ ተካህዷል።

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ስለጉባዔው ግንዛቤ ለመፍጠር እና ለቅድመ ዝግጅቶች የሚደረገው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ቋንቋዮች የሚሰሩ ሚዲያዎች አጋጣሚውን እንደ ኮንፈረንስ ቱሪዝም እና መልካም ስም መፍጠሪያ ያሉ ጥቅሞችን ግንዛቤ ውስጥ ባስገባ ሁኔታ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የጤና ሚኒስቴር ህዝብ ግንኙነት እና ጤና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተገኔ ረጋሳ በበኩላቸዉ ባስተላለፉት መልዕክት በተለያዩ ግዜያት እንደ ወረርሽኝ ያሉ የጤና ስጋቶችን በተቀናጀ ሁኔታ በመረባረብ ውጤቶችን እንዳስመዘገብነው ሁሉ ለአንድ ሳምንት አካባቢ በሚቆየው ይህ ትልቅ ጉባኤ በጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከሚደረሱባቸው መግባባቶች እና ውሳኔዎች በተጨማሪ የአገር ገፅታ የሚገነባበት አጋጣሚ በመሆኑ ሁሉም የሚዲያ አውታሮች እና የሚመለከታቸው አካላት በአገራዊ ስሜት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በአገራችን የአህጉር እና አለም አቀፍ ጉባኤዎችን በስኬት የማስተናገድ አቅም እና ልምድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ተጠቁሟ።

የኮሪያ–ኢትዮጵያ  የልብ ቀዶ ሕክምና የአጋርነት ፕሮግራሞች የልዩ ሕክምና አገልግሎትን ለማስፋፋትና የሰው ኃይል አቅምን ለማጠናከር ወሳኝ ናቸው________የኮሪያ-ኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ሕክምና...
17/08/2026

የኮሪያ–ኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ሕክምና የአጋርነት ፕሮግራሞች የልዩ ሕክምና አገልግሎትን ለማስፋፋትና የሰው ኃይል አቅምን ለማጠናከር ወሳኝ ናቸው
________

የኮሪያ-ኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ሕክምና ሥልጠና ፕሮግራም በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የልብ ቀዶ ሕክምና አቅምን በማሳደግና የኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በማብቃት ጉልህ ውጤት ማስመዝገቡም ተመላክቷል።

በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላለፉት 10 ዓመታት ለተከናወነው የልብ ቀዶ ህክምና የአቅም ግንባታ ሥልጠና የእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ፣ ትብብሩ ከአጭር ጊዜ ሕክምና ድጋፍ ባለፈ ዘላቂ የባለሙያ አቅም ግንባታ ስራን ማጠናከር መሆኑን ገልጸዋል።

የደቡብ ኮሪያ አምባሳደር ጂም ኮንግ በበኩላቸው፣ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ከአምስት ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ የሕክምና ባለሙያዎች በራሳቸው የልብ ቀዶ ሕክምና ማከናወን መጀመራቸው የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የልብ ህክምና ባለሙያዎች በዓመት ከ150 በላይ የልብ ቀዶ ሕክምናዎችን እያከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፣ ይህም የ10 ዓመቱ ትብብር የዕውቀት ሽግግርና የአቅም ግንባታ ውጤት እንደሆነ ገልጸዋል።

የኮሪያ እና የኢትዮጵያ ባለሙያዎችን ትብብር በማጠናከር ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ የልብ ሕክምና ባለሙያዎች የሥልጠና ማዕከል እንዲሆን የሚያስችል ሥራ ለማስፋፋት ዕቅድ መኖሩ ተገልጿል።

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ታሪካዊ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሄደ::ነሐሴ 07/12/2018 ዓ.ም አርባ ምንጭየአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት ሁለት...
13/08/2026

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ታሪካዊ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሄደ::

ነሐሴ 07/12/2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት ገደማ በሕክምና ትምህርት፣ በምርምርና በሕክምና አገልግሎት ዘርፍ አብሮት ለሰራውና የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከተው ለአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ታሪካዊ የምስጋና እና የእውቅና መርሃ ግብር አካሂደ።

በዕለቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ኢንጂነር አብደላ ከማል ባስተላለፉት ዋና መልዕክት፣ አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ዋነኛ የመማሪያ፣ የምርምር እና የተግባር ልምምድ (Attachment Site) ሆኖ በመቆየት ብቁ ሐኪሞችንና የጤና ባለሙያዎችን ለማፈራት ላደረገው በዋጋ የማይተመን አስተዋፅኦ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል። ፕሬዝዳንቱ አፅንዖት ሰጥተው እንደተናገሩት፣ በአሁኑ ወቅት የተደረገው የባለሙያዎች ሽግግር የሁለቱን ተቋማት ግንኙነት የሚያቆም ሳይሆን፣ በዩኒቨርሲቲው እና በአጠቃላይ ሆስፒታሉ እንዲሁም በአካባቢው በሚገኙ የጤና ተቋማት መካከል ያለው አጋርነትና ትብብር በቀጣይም በተሻለ ጥራትና አቅም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቦርድ ሰብሳቢና የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ለዩኒቨርሲቲው የጤናና ሕክምና ትምህርት የተግባር ልምምድ ማዕከል በመሆን ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል። የተደረገው የባለሙያዎች ሽግግር የሕብረተሰቡን አገልግሎት ሳይጎዳ መከናወኑ አርአያነት ያለው መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም በጋራ ሥራዎች ላይ ትብብሩ እንደሚቀጥልና ለዚህም የዩኒቨርሲቲው ቦርድ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ደስታ ጋልቻ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የሁለቱን ተቋማት ታሪካዊ የትብብር ጉዞና የደረሱበትን የዕድገት ምዕራፍ በሰፊው አብራርተዋል። ዶ/ር ደስታ እንዳመለከቱት፣ እስከ 2003 ዓ.ም ድረስ ተቋም ለተቋም ምንም ዓይነት የጽሁፍ ውል ሳይኖር የሆስፒታሉ ባለሙያዎችን እንደ እንግዳ መምህርነት ሲጠቀም የቆየ ቢሆንም፣ በኋላ ላይ የልምድ ልውውጥ በማድረግ በተዘጋጀ የጋራ መግባቢያ ስምምነት (MOU) መሠረት የተቀናጀና ስልታዊ ሥራ ሲከናወን ቆይቷል። ዩኒቨርሲቲውም ከአገልግሎት ማግኘት ባሻገር ለሆስፒታሉ እንደ አልትራሳውንድ፣ አልጋዎች፣ ኮምፒውተሮች፣ ፕሪንተሮች እና ልዩ ልዩ የቢሮ ቁሳቁሶችን በድጋፍ ሲያቀርብ መቆየቱን አወስተዋል።

ዶ/ር ደስታ አክለውም የማስተማሪያና ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሉ ከታህሳስ 16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ተኝቶ ሕክምናን ጨምሮ ሰፊ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተከትሎ፣ የሥራ መስተጓጎል እንዳይፈጠር በተዋቀረው የ"Exit Strategy" ኮሚቴ ምክረ-ሐሳብ መሠረት ውጤታማ የሥራ ሽግግር መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት በልዩ ሁኔታ ስምምነት ከተደረገባቸው አገልግሎቶች (እንደ ፊስቱላ እና ፕላስቲክ ሰርጀሪ ያሉ) በስተቀር ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ የዩኒቨርሲቲው ባለሙያዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል መጠቃለላቸውን አስረድተዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ ዶ/ር አዲሱ ተስፋዬ በበኩላቸው ለተደረገው ታሪካዊ የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዶ/ር አዲሱ ሁለቱ ተቋማት ባለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት ገደማ ውስጥ እጅግ ውጤታማና ፍሬያማ የጋራ ሥራዎችን ማከናወናቸውን ገልጸዋል። አክለውም የተደረገው የሥራና የባለሙያዎች ሽግግር የማህበረሰቡን የሕክምና አገልግሎት በማይጎዳና በማያስተጎጉል መልኩ መጠናቀቁን ገልጸው፣ ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ላደረገው በዋጋ የማይተመን ድጋፍ አመስግነው ይህ ስልታዊ አጋርነት በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና እንደማይቋረጥ አረጋግጠዋል።

በታሪካዊው የእውቅና መርሃ ግብር ላይ የቦርድ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ፣ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ቦጋለ ገብረማሪያም፣ አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ጳውሎስ ታደሰ እንዲሁም የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተ...
12/08/2026

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከነሀሴ 13 እስከ 15/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን የፈተናው መርሃ-ግብርና ሌሎች መረጃዎች በቴሌግራም ቻናል(https://t.me/M0H_EThiopia) ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከዩኒሴፍ (UNICEF) በተገኘ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ድጋፍ ሆስፒታል ለአንድ ማዕከል (One-Stop Center) አገልግሎት ተቋማት የሚሆን የገንዘብና ...
12/08/2026

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከዩኒሴፍ (UNICEF) በተገኘ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ድጋፍ ሆስፒታል ለአንድ ማዕከል (One-Stop Center) አገልግሎት ተቋማት የሚሆን የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ርክብክብ አካሄደ።

አርባምንጭ ፤ነሐሴ 06/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት)

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከዩኒሴፍ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ፕሮግራሙ ለሚካሄድባቸው ለአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ፣ ለሴፍ ሀውስና ለአንድ ማዕከል አገልግሎት ተቋም አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

‎ይህ የተሰጠው የቁሳቁስ ድጋፍበአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አንድ ማዕከልን ለማጠናከርና የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሳለጥ እንደሆነ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ካሰች ኤልያስ ተናግረዋል።

‎ወ/ሮ ካሴች ኤልያስ በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚደርስ ጥቃትን ተከትሎ የሚመጣውን ጉዳት ለመቀነስ ብሎም ለመከላከል ያልተቋረጠ ድጋፍ መስጠት ወሳኝ እንደሆነ በመገንዘብ የተጠቂዎችን ስነልቦና ከማከም የሚጀምር በመሆኑ አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማሟላት በክልል ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

‎በሆስፒታሎቹ የሚሰጡትን አገልግሎቶች የሚያገኙ ተጠቂ የሆኑ ሴቶችና ህጻናት በተገቢው እንድታከሙ ለቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት የቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ካሴች ኤልያስ በተለይም የማህጸን ውልቃት ታካሚ እናቶች እንድጠቀሙና ተገቢውን ህክምና እንዲያገኙ ለማድረግ ልዩ የገንዘብ ድጋፍ ጭምር እንደሚደረግም ተናግረዋል።

‎የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አብነት ተስፋዬም የተደረገላቸውን ድጋፍ አድንቀው በቀጣይ ተጠቂ እናቶችን በመለየትና በህክምናው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ጥረት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜድካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አዲሱ በበኩላቸው ድጋፉ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ደረጃውን በተወሰነ መልኩ የሚያሻሽል መሆኑን ጠቅሰው ለተደረገው ድጋፍ ከልብ አመስግነዋል።

‎ይህ ድጋፍ በሆስፒታሎቹ ለአንድ ማዕከል ታካሚ ሴቶችና ህጻናት ብሎም በማህጸን ውልቃት ህመም ምክንያት ለሚታከሙ እናቶች የሚሰጠውን ህክምና የሚያግዝና አገልግሎቱን ለማጠናከር ሚናው ከፍ ያለ መሆኑን በየሆስፒታሎቹ የነበሩ እናቶች ተናግረዋል።

12/08/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Meron Nekere Emuye, Fikre Hailemaryam, Dawit Dana, Alazar Kanta, Yibae Adane, Temesgen Teshome, Ayoma Angeta, Nujba Bilcha, Wandesha Waje Wando, Sembetu Adalo, Dav Ked, Nizar Abdu Bungula, Sami Yegeta Lij, Zenebe Zenebe Zebid, Tesfahun Adisu, Becho Butu, Sami Aleme, Melese Lukas Melese Lukas, Banchi Almayehu, Alemayehu Abriham, Abeba Demissie, Chinke Tikimu, Enda'le Tesfa, Thomas Hole, Belachew Bekele, Dawit Darko, Afework Giorgis, ዜና ገብርእግዚአብሔር ሜንሤ, አባይነሽ ማሞ, Selamu Ethiopia, Elfiňěšh Yiŝåk, Abi Yue Eususe Lijji, Abinet Ako, Temesgen Daniel, Aster Gizachew, Tofluos Buzuneh, Mesele Sulamo, Abel Birhanu, Geberiel Maglash, Wozi Wozi, Tenkele Temba, Daniel Dayiso, Tamirat Habitamu

አስደሳች ዜና  ለጋሞና አካባቢዋ ዞኖች በሙሉ!በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከነሐሴ 15-17/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 03 ቀን የሚቆይ ዘመቻ ለማካሄድ ተዘጋጅቷል።የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ...
12/08/2026

አስደሳች ዜና ለጋሞና አካባቢዋ ዞኖች በሙሉ!

በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከነሐሴ 15-17/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 03 ቀን የሚቆይ ዘመቻ ለማካሄድ ተዘጋጅቷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ፣ ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እንዲሁም ከትረስት በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር የላንቃና ከንፌር መሰንጠቅ ነፃ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጄ ስለሆነ፣

ሁሉም ባለድርሻ አካላት የከንፌርና ላንቃ መሰንጠቅ ጤና ችግር ያለባቸው በማንኛውም ዕድሜ ክልል ያሉ ዜጎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማሳወቅና የመቀስቀስ ሥራ እንድትሰሩ የአክብሮት ጥሪ እያስተላለፍን ፣

ልብ ይበሉ❤❤!!

ማንኛውም የችግሩ ተጋላጭ ወገኖች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ጤና ተቋማት መረጃውን በማድረስ እና ወደ አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በመምጣት በነፃ መታከም የሚትችሉ መሆኑን የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በአክብሮት ጥሪውን ያስተላፋል፡፡

#እንዳያመልጥዎ!

ማሳሰቢያ ፤ ለታካሚዎች የሕክምና ፤የትራንስፖርት፤ የምግብ እና የአልጋ ወጪ በድርጅቱ ይሸፈናል፡፡
ሼር ሼር በማድረግ አዳርሱልን+++
ለበለጠ መረጃ
· 0926104204 ወይንም
· 0926427383 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል የተሻገረው የኢትዮጵያ የጤና ጉዞ ዘመናዊ ሕክምናን በሀገር ውስጥ በመስጠት እና በላብራቶሪ ምርመራ ዘርፍ የተጀመረው ለውጥ የጤና ሉዓላዊነትን በተግባር ያሳየ ነው።...
08/08/2026

ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል የተሻገረው የኢትዮጵያ የጤና ጉዞ

ዘመናዊ ሕክምናን በሀገር ውስጥ በመስጠት እና በላብራቶሪ ምርመራ ዘርፍ የተጀመረው ለውጥ የጤና ሉዓላዊነትን በተግባር ያሳየ ነው።

የዜጎች ጤና፣ በሕክምና ተደራሽነት እና ዜጎች በችግር ጊዜ በሀገራቸው ውስጥ የሚያገኙት የሕክምና አቅምም እየተሻሻለ መምጣቱ ተነገረ።

ነሐሴ 02/2018 ዓ.ም ጤና ቢሮ ኮሚኒኬሽን | ጂንካ
_______________

ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የተጀመሩ ለውጦች ከተለመደው የጤና አገልግሎት ማስፋፋት በላይ የሚሄዱ ናቸው።

ይህ ለውጥ አንድ ትልቅ ጥያቄን ይመልሳል፤ ኢትዮጵያ ለዜጎቿ የሚያስፈልገውን የጤና አገልግሎት በራሷ አቅም ምን ያህል ማቅረብ ትችላለች? የጤና ልማቱ አንዱ ግልጽ መገለጫ የጤና ተቋማትን አቅም ማሳደግ ነው።

አዳዲስ ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ ያሉትን ተቋማት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በላቀ ምርመራ መሳሪያዎችና በልዩ ሕክምና አቅም ማስፋፋት የለውጡ አካል ሆኗል።

በቀድሞው አሠራር በሀገር ውስጥ በቂ የምርመራ አቅም ባለመኖሩ ሕይወትን ሊያሰጉ የሚችሉ የበሽታ ናሙናዎች ወደ ውጭ አገራት ይላኩ ነበር። ይህ የገንዘብ ወጪን ብቻ ሳይሆን የምርመራ ውጤት እስኪመጣ የሚወስደው ጊዜ የታካሚውን ሕክምና ያዘገያል።

ዛሬ ግን በሀገር ውስጥ የላቀ የላብራቶሪ አቅም በመገንባት ይህንን አሰራር በመቀየር ላይ ነው።

በአለርት የተገነባው ዘመናዊ ላብራቶሪም በዚህ ረገድ ከሚጠቀሱ ምሳሌዎች አንዱ ነው።

የጤና ሉዓላዊነት በሆስፒታልና በላብራቶሪ ብቻ አይጠናቀቅም በዚህም መድኃኒት የጤና ሥርዓቱ ዋነኛ መሠረት ነው።

አንድ ሀገር ሆስፒታል ቢገነባ፣ ዘመናዊ ማሽኖችን ብታሟላ ነገር ግን መድኃኒትን በተረጋጋ ሁኔታ ማቅረብ ካልቻለች የጤና ራስን መቻል ሙሉ አይሆንም።

ስለዚህ የመድኃኒት ምርትን በሀገር ውስጥ ማሳደግ በመድኃኒት አቅርቦት ራስን ለመቻል የሚደረገው ጉዞ የጤና ልማቱ ዋነኛ አጀንዳ ነው።

በላብራቶሪዎችና በጤና ተቋማት መካከል የዲጂታል መረጃ ልውውጥ ማሳደግ የምርመራ ጊዜን ለማሳጠር፣ የታካሚ መረጃን በተሻለ ሁኔታ ለማስተዳደርና የጤና ውሳኔዎችን በመረጃ ላይ ለመመስረት ያግዛል።

ስለሆነም ከአንድ የጤና ተቋም የተነሳ ናሙና ወይም መረጃ በፍጥነት ወደ ልዩ ምርመራ ማዕከል ሊደርስ እና ውጤቱም በዲጂታል ሥርዓት ወደ ሕክምና ቦታው ሊመለስ ከቻለ ቴክኖሎጂው በቀጥታ የሰው ሕይወትን የሚያገለግል መሣሪያ ይሆናል።

አንድ ድሃ ዜጋ ውድ የሆነ የምርመራ ወጪ መሸፈን ሳይችል ሕክምናው እንዳይዘገይ፣ አንድ ታካሚ ውጤቱን ለሳምንታት ሳይጠብቅ፣ ቤተሰብ የሚወደውን ሰው ለሕክምና ወደ ሩቅ አገር ለመላክ እንዳይገደድ ይህ የጤናው ዘርፍ የታየው ልማት ትክክለኛ ትርጉም አለው።

ባለፉት የለውጡ ዓመታት የተጀመሩት የጤና ዘርፍ ለውጦች እንደ አንድ የተናጠል ፕሮጀክት ሳይሆን እንደ አንድ ትልቅ ራዕይ ሊታዩ ይገባል።

የናሙና ስደትን ማብቃት፣ የውጭ ሕክምና ጥገኝነትን መቀነስ፣ የመድኃኒት ምርትን ማሳደግ እና የዘመናዊ ምርመራ አቅምን በሀገር ውስጥ ማስፋፋት እነዚህ ሁሉ በአንድ ላይ ሲታዩ የሚገኘው ውጤት የጤና ሉዓላዊነት ነው።

ኢትዮጵያ የጤና ሥርዓቷን ከማስፋፋት ወደ ማዘመን ከዘመን ወደ ራስን መቻል እየተሻገረች ነው።

ይህ ጉዞ ገና የተጠናቀቀ ባይሆንም አቅጣጫው ግን ግልጽ ነው ጤና በገበያ የሚገዛ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን የሀገር ሉዓላዊነት መሠረት መሆኑን ያሳየ ነው።(ጤሚ)

Address

Gamo Zone
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arbaminch General Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share