Arbaminch post

Arbaminch post Arbaminch news channel. stay connected!!

ዜና ዕረፍት 💔አርባምንጭ ከተማ እጅግ ደግ ልጇን አጥታለች!በበጎ አድራጎት ሥራዎቹ ይታወቅ የነበረው ወጣት ተወዳጅ መኮንን በድንገተኛ ህልፈት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ የብዙዎችን ልብ በሀዘን...
10/07/2025

ዜና ዕረፍት 💔

አርባምንጭ ከተማ እጅግ ደግ ልጇን አጥታለች!

በበጎ አድራጎት ሥራዎቹ ይታወቅ የነበረው ወጣት ተወዳጅ መኮንን በድንገተኛ ህልፈት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ የብዙዎችን ልብ በሀዘን አድምቷል።

ተወዳጅ በከተማዋ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራት ግንባር ቀደም ተሳታፊ ሲሆን፣ በተለይም ለመኖሪያ ቤት እጦት የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ እና የበርካታ ድሆችን ሙሉ የህክምና ወጪ በመሸፈን ይታወቅ ነበር።

እነዚህ ደግ ሥራዎቹ የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትንና ፍቅርን አስገኝተውለት ነበር፤ ከተማዋም ሁሌም በአመስጋኝነት ታስበዋለች።

ይህ ድንገተኛ ሞት ለመላው ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ፣ እና የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ሁሉ ታላቅ ሀዘንን ጥሎ አልፏል።

* ለቤተሰቦቹ
* ለጏደኞቹ
* ለወዳጅ ለወዳጆቹ

መፅናናትን እንመኛለን።

ነፍስህን በአፀደ ገነት ያኑራት! 🙏

©️የአርባምንጭ በጎ ፈቃደኞች ማህበር

"የጤና አገልግሎትን ፍትሃዊ፣ ተደራሽ፣ ዘላቂና ጥራት ያለው ለማድረግ መስራት ይገባል" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የጤና ኤክስቴሽን ፕሮግራም ፍኖ...
27/06/2025

"የጤና አገልግሎትን ፍትሃዊ፣ ተደራሽ፣ ዘላቂና ጥራት ያለው ለማድረግ መስራት ይገባል" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የጤና ኤክስቴሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ አፈፃፀም መድረክ ተካሂዷል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ማጠቃለያ የኢትዮጵያ የምንጊዜም ጠላት ድህነት ነው ያሉ ሲሆን፥ ሰርተን በመለወጥ ድህነትን ታሪክ ማድረግ አለብን ብለዋል።

የሚሰራ አምራች ዜጋ ለማፍራት የጤናው ዘርፍ ትልቁን ድርሻ ይይዛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ የጤና ኤክስቴሸን ባለሙያዎች ላለፉት ሃያ ዓመታት በየቀበሌው መስዋትነትን ከፍለው በመስራት በጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ትልቅ ለውጥ ማስመዝገብ መቻላቸውን ገልፀዋል።

የተረጂነት ባህልን በመቀየርና የሕዝቡን ጤና በመጠበቅ ረገድ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የዘመኑ አርበኞች መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ብዙ ነገር ባልተመቻቸበት ሰርተው ማስመዝገብ ለቻሉት ስኬት የክልሉ መንግስት እውቅና የሚሰጠው መሆኑንም ተናግረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይም በክልሉ የጤና አገልግሎትን ፍትሃዊ፥ ጥራት ያለው፣ ተደራሽ እና ዘላቂ ለማድረግ ኃላፊነትን በከፍተኛ ደረጃ መውጣት እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ገልፀዋል።

ለዚህም 4 መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ መስራት እንደሚገባ በማሳሰብ በዝርዝር አስረድተዋል። እነዚህም፡-

*የሚያሰራ ጠንካራ ተቋማዊ ስርዓት በመዘርጋት የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፎኖተ ካርታን በአግባቡ በብቃት መተግበር የሚያስችል ስርዓት መፍጠር፣

*ተቋም በማዘመን፥ በማስፋትና በግብዓት በማሟላት ማጠናከር፤ በተለይም የሁለተኛ ትውልድ የጤና ኬላዎችን በማስፋፋትና እና ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል በማድረግ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ መስራት፣

*የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ወቅታዊ እና ቀጣይነት ያለው ፍላጎትን በመለየት ለሟሟላት መስራት፤ ይህም አቅም በፈቀደ መልኩ የዘርፉን የሰው ሃይል አቅም በማጎልበት እና በሰሩት ልክ ተገቢውን ጥቅማጥቅም እንዳገኙ ለማስቻል መስራትን ይጨምራል፤

*የመረጃ ስረዓቱን በማሻሻልና በማዘመን ወቅቱን የጠበቀ፥ ታአማኒነት ያለው እውነተኛ መረጃን ለማደራጀትና ተደራሽ ለማድረግ መስራት ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።

የጤና ኤክስቴንሽ ስራዎችን ለማሳካት ህዝቡን ባለቤት በማድረግ እና ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከር መስራት እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለው የክልሉ መንግስት ለውጤታማ የጤና ኤክስቴሽን ትግበራ በፍኖተ ካርታው መሰረት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።

ባለድርሻ አካላትም ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ርዕሰ መስተዳድሩ ከየዞኑ ለተመረጡ ሞዴል የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች እውቅና በመስጠት አበረታተዋል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

Address

Arba Minch'
4400

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arbaminch post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share