01/06/2026
አረዳቴ የአካል ጉዳቴን ተጠቅሞ ሻወር ቤት ውስጥ ራቁቴን ጥሎኝ የዓመታት ድካሜን ሰርቆ ተሰወረ
እኔ ማዕበል እንዳሻው እባላለሁ።በመኪና አደጋ ምክንያት ሙሉ በሙሉ አካሌ ፓራላይዝድ በመሆኑ (የማይንቀሳቀስ) በመሆኑ...
በጎን ተኝቼ በአውራ ጣቴ ስልኬ ላይ በመጻፍ የምኖርና የተለያዩ መጻሕፍትንና የቴሌቪዥን ድርሰቶችን (ስክሪፕቶችን) የምደርስ ደራሲ ነኝ።
በፎቶው ላይ የምታዩት ተከሳሽ በጸጋው ሳሙኤል ሻንቆ የተባለው ግለሰብ ላለፉት 3 ዓመታት እኔን ከተኛሁበት የማስነሳት፣ የማስገባት፣ ገላዬን የማጠብ እና ሌሎች የቤት ውስጥ ድጋፎችን የሚያደርግልኝ ረዳቴ ነበር።
ሆኖም ግን (በ21/08/2018 ዓ.ም) ከቀኑ 7፡15 እስከ 7፡20 ባለው ጊዜ ውስጥ፣ እኔ በራሴ መንቀሳቀስ የማልችልበትን አጋጣሚ በመጠቀም የሚከተለውን ዘገናኝ ወንጀል ፈጽሞብኛል፦
1 እኔን ሻወር ቤት ውስጥ ሙሉ ራቁቴን ካስገባኝና ውሃ ካሞቀልኝ በኋላ፣ የእኔን የጩኸት ድምጽ ማንም እንዳይሰማ የውጭውን የቴሌቪዥን ድምፅ እና ዘፈን በከፍተኛ ሁኔታ በመክፈት የስርቆት ተግባር ፈጽም ተሰውሯል።
2 እኔ ራቁቴን ሻወር ቤት ውስጥ ረዳት አጥቼ በተቀመጥኩበት አቅመ-ቢስ የሆንኩበትን ሰዓት ጠብቆ ፣ ለሥራዬና ለዕለት ተዕለት ሕይወቴ የምጠቀምባቸውን፣ ገና ለቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለማቅረብ የተዘጋጁ እጅግ ውድ የሆኑ የስክሪፕት ድርሰቶቼ ያሉባቸውን ንብረቶች በሙሉ ሰርቆ ተሰውሯል።
የተሰረቁ ንብረቶች፦
ሬድሚ 13 ፕሮ ፕላስ 5ጂ (Redmi 13 Pro+ 5G) ስልክiPhone ስሌክ ፦ሳምሰንግ ታብሌት (Samsung Tablet)ፓወር ባንክ (Power Bank)....
ሌላ ተጨማሪ ስማርት ሳምሰንግ 24 ስልክ
ኤርፎን (Earphones) ስማርት ሰዓት
ጫማዎች፣ ልብሶች እና በጥሬው 13,400 ብር።
ይህ ግለሰብ እኔ በአካል ጉዳቴ ምክንያት ምንም ማድረግ እንደማልችል እያወቀ፣ ሕይወቴን ለአደጋ በሚያጋልጥ መልኩ ሻወር ቤት ውስጥ ጥሎኝ፣ የዓመታት ድካሜና የሥራዬ መሠረት የሆኑትን ስክሪፕቶች ያሉባቸውን ስልኮችና ንብረቶች ይዞ በመጥፋቱ በስነ-ልቦናም ሆነ በኢኮኖሚ ከፍተኛ ጉዳት ላይ እገኛለሁ።
ግለሰቡን ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ ቢኖር በአቅራቢያው ለሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ወይም በሚከተለው ስልክ ቁጥር በመደወል እንዲያሳውቀኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ።
📞 መረጃ ለመስጠት ስልክ ቁጥር፦0962017493
የድርጊቱ ቦታ፦ ኮዬ ፈጬ፣ ሸገር ሲቲ
አካሌ በሙሉ ፓራላይዝድ በመሆኑ ደከማነቴን ተጠቅም ነው የወሰደብኝ እባካችሁ ይህንን መልዕክት #ሼር በማድረግ ለሕግ አካላት እንዲደርስ እና የዚህን ግለሰብ ፎቶ በማሰራጨት በፈጣሪ እንድትተባበሩኝ እማፀናለሁ 🙏