Visit Gamo Arbaminch

Visit Gamo Arbaminch #እውነት የሆኑ መረጃዎችን ለህዝብ እናደርሳለን ።

የሶዶ ከተማ አስተዳደር የጋሞ ብሔር ዘመን መለወጫ “ዮ...ማስቃላ” በዓል ጥሪ ተቀበለ​የሶዶ ከተማ አስተዳደር በጋሞ ዞን በሚከበረው  “ዮ...ማስቃላ” የጋሞ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ላይ ...
03/09/2026

የሶዶ ከተማ አስተዳደር የጋሞ ብሔር ዘመን መለወጫ “ዮ...ማስቃላ” በዓል ጥሪ ተቀበለ

​የሶዶ ከተማ አስተዳደር በጋሞ ዞን በሚከበረው “ዮ...ማስቃላ” የጋሞ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ላይ እንዲታደሙ የቀረበላቸውን ጥሪ ተቀብሏል።

ጥሪውን የሶዶ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ መንግሥቱ ትግሮ እና የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፊስሐ ፀጋዬ በጋራ በመሆን ተቀብለዋል።

​ጥሪውን ያቀረቡት ከጋሞ ዞን እና ከአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የልዑካን ቡድን አባላት የሆኑት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ተስፉጺሆን ዘነበ፣ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ቡዙነህ እና የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አብነት ተስፋዬ ናቸው።

​በወቅቱም የዞኑ አመራሮች ጥሪውን በመቀበል ለመላው የጋሞ ዞን ሕዝብ “እንኳን ለ“ዮ...ማስቃላ” በዓል በሰላም አደረሳችሁ” በማለት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኮንሶ ዞን አስተዳደር በጋሞ ዞን በሚከበረው “ዮ ማስቃላ” በዓል ላይ ለመታደም የቀረበለትን ጥሪ ተቀበለየኮንሶ ዞን አስተዳደር በጋሞ ዞን በሚከበረው “ዮ ማስቃላ” የጋሞ ዘመን መለወጫ በዓል...
03/09/2026

የኮንሶ ዞን አስተዳደር በጋሞ ዞን በሚከበረው “ዮ ማስቃላ” በዓል ላይ ለመታደም የቀረበለትን ጥሪ ተቀበለ

የኮንሶ ዞን አስተዳደር በጋሞ ዞን በሚከበረው “ዮ ማስቃላ” የጋሞ ዘመን መለወጫ በዓል ላይ እንዲታደም ከጋሞ ዞን አስተዳደር የቀረበለትን ጥሪ ተቀበለ።

ጥሪውን የተቀበሉት የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ ሲሆኑ፣ ለመላው የጋሞ ዞን ሕዝብ እንኳን ለ“ዮ ማስቃላ” በዓል በሰላም አደረሳችሁ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

“ዮ ማስቃላ” የጋሞ ሕዝብ የዘመን መለወጫ ባህላዊ በዓል ሲሆን፣ በዓሉ መስከረም 12/2019 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል።

01/09/2026

የአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ ሀብት የማሰባሰብ ሥራ 3ዙር አቶ ይሉሀል አካሉ 200 ሺ (200,000) ብር ገቢ አድርገዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ለመመለስ ሁሉ አቀፍ ሪፎርም መጀመሩ ተገለጸ፡፡ክለቡ የቅድመ ውድድር ዝግጅት የሚጀምርበት ጊዜም ታውቋል፡፡የአርባምንጭ ከተማ እግር ኳ...
01/09/2026

የአርባ ምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ለመመለስ ሁሉ አቀፍ ሪፎርም መጀመሩ ተገለጸ፡፡

ክለቡ የቅድመ ውድድር ዝግጅት የሚጀምርበት ጊዜም ታውቋል፡፡

የአርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ከ2003 ዓ.ም ወዲህ ከፕሪሚዬር ሊጉ ለ3ኛ ጊዜ መውረዱ ይታወሳል፡፡
ክለቡ በፕሪሚዬር ሊጉ ተፎካካሪ ሆኖ መዝለቅ ያልቻለበትን መነሻ በመለየት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ፕሪሜር ሊጉ በመመለስ ተፎካካሪ ሆኖ እንዲዘልቅ ሁሉ አቀፍ ሪፎርም እየተከናወነ መሆኑን የክለቡ ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር መስፍን መንዛ ገልጸዋል፡፡

ክለቡ የአካባቢውን እግር ኳስ እምቅ ዓቅም መጠቀም የሚያስችለውን አሰራር መዘርጋት የሪፎርሙ ቀዳሚ ተግባር ነው ያሉት የቦርዱ ሰበብሳቢ፣ የሪፎርም ቲም በማደራጀት የተጀመረው ተግባር አበረታች ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ክለቡን ወደ ፕሪምየር ሊጉ መመለስ የሚችሉ ክህሎት ያላቸው ተጫዋቾችን ምልመላ የዘርፉ ባለሙያዎች በተሳተፉበት መደረጉን ጠቁመው፣ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾችን ከፕሪሚየር ሊጉ እና ከፍተኛ ሊጉ እንዲካተቱ ተደርጓል ብለዋል፡፡

በዚህም በአነስተኛ ወጪ ጥራት ያለው ቡድን ተገንብቷል የሚሉት ዶክተር መስፍን፣ ጽህፈት ቤቱን ጨምሮ በሁሉም እርከኖች ባሉ ቡድኖች ሪፎርሙ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

የክለቡ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ትግሉ ኃይሌ በበኩላቸው፣ የአርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በከፍተኛ ወጪ እና በተሻለ መሰረተ ልማት ለውድድር ቀርቦ በተደጋጋሚ ውጤት ማጣቱን ገልጸዋል፡፡

ይህን ችግር ለመቅረፍ ቡድኑን የማሊያ ፍቅር ባለቸው ተጫዋቾች የማዋቀር ተግባር በባለሞያዎች ተደግፎ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ለዋናው ቡድን መጋቢ የሆኑ የተስፋ ቡድኖችም መደራጀታቸውን አብራርተዋል፡፡

በቀጣዩ የውድድር አመት ክለቡን ወደ ሊጉ ለመመለስ ከፕሪሜዬር ሊጉና ከብሔራዊ ሊጉ ተጨዋች የማስፈረምና የነባር ተጨዋቾችን ውል የማደስ ተግባር መከናወኑን ጠቁመው፣ ባለተሰጥኦ ተጨዋቾችን አሳታፊ በሆነ እና ያሰልጣኞችን ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ ምልመላ መካሄዱን አስረድተዋል፡፡

የክለቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ፍላጎት ኢልዶ በ2018 የውድድር ዘመን የተመዘገበው ውጤትን ተከትሎ የተፈጸሙን ጥሰቶች ለሪፎርሙ መነሻ መሆናቸውን ገልጸው፣ ጥሰት የፈጸሙ አካላት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል፡፡

ቡድኑን በአነስተኛ ወጪ ለማዋቀር የተጫዋቾች ምልመላና የአሰልጣኝ ቡድን አደረጃጀት መከናወኑን ገልጸው፣በዚህም በአርባ ምንጭ ከተማ ከሚካሄደው የክረምት በጎ ፈቃድ ‹ልማት ካፕ› ውድድር 15 ተጫዋቾችን መመረጣቸውን አስረድተዋል፡፡

ታዳጊ እና አዲስ የፈረሙ ተጫዋቾችን ጨምሮ 26 የቡድን በዓላት መዋቀራቸውን አስረድተው፣ የ20019 ውድድር ዘመን ቅድመ ውድድር ዝግጅት መስከረም 4/2019ዓ.ም እንደሚጀመር ስራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ የሚያስችለውን የደረጃ ማሻሻያ ስራ እያለቀ ያለው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አባያ ካምፓስ የስፖርት ማዘውተሪያ ስታድየም ።
01/09/2026

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ የሚያስችለውን የደረጃ ማሻሻያ ስራ እያለቀ ያለው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አባያ ካምፓስ የስፖርት ማዘውተሪያ ስታድየም ።

31/08/2026

መላው የጋሞ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ!
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ሚንስቴር አድስ ውሳኔ አስተላልፏል።ጎንደር፣ አርባምንጭ ፣ነቀምት እና ጅግጅጋ ከተሞች ላይ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ይገነባሉ።

The New Face of Addis Ababa: Meketeya 🌿Meketeya is emerging as a vibrant new face of Addis Ababa; where green landscapes...
31/08/2026

The New Face of Addis Ababa: Meketeya 🌿

Meketeya is emerging as a vibrant new face of Addis Ababa; where green landscapes, modern pathways, public spaces, art, recreation, and breathtaking views come together.

A renewed city, greener, healthier, and ready for tomorrow. 🇪🇹✨

the place where you can enjoy Riding a bike, hiking, and running!

እየዳነ ሄደ እየዳነ..ከጥቂት ዓመታት በፊት የአዲስ አበባ መስተዳድር በዋና ዋና የትራፊክ መብራቶች አካባቢ የሚለምኑ አንድ ሃያ እናቶችን ሰብስቦ ሥልጠና ሰጠና ወደ ሥራ አሠማራቸው፡፡ እነዚህ...
31/08/2026

እየዳነ ሄደ እየዳነ..

ከጥቂት ዓመታት በፊት የአዲስ አበባ መስተዳድር በዋና ዋና የትራፊክ መብራቶች አካባቢ የሚለምኑ አንድ ሃያ እናቶችን ሰብስቦ ሥልጠና ሰጠና ወደ ሥራ አሠማራቸው፡፡ እነዚህ እናቶች ልጅ አዝለው ከጀንበር እስከ ጀንበር ሲለምኑ የሚሉ አሳዛኝ እናቶች ናቸው፡፡
ሃያዎቹ እናቶች ለሥልጠና ሲገቡ ፌስቡክ ላይ ጫጫታ ተፈጠረ፡፡ ተመሳሳይ ጽሑፍ በተለያየ ስምና ገጽ መውጣት ጀመረ፡፡ “ታፈሱ፤ ተለቀሙ፤ ታሠሩ፤ ሰብአዊ መብታቸወ ተነካ” የሚል ዘመቻ ተጧጧፈ፡፡ የእናቶቹ ሁኔታ ሲታይ ግን ደስታ ሊገድላቸው ደርሷል፡፡ በኋላ እናቶቹ ሲጠየቁ አንድ ምሥጢር አወጡ፡፡ ፖሊስ ያንን ተከትሎ ማደን ጀመረና አንድ ሦስት ሰዎችን ያዘ፡፡ በተለያየ ስም በፌስ ቡክ የሚያጋግሉት እነዚሁ ናቸው፡፡
ለካስ እነዚህን እናቶች ከገጠር አምጥተው በልመና ሥራ የሚያሠማሩት እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡ እነሱ ደኅና ኑሮ ይኖራሉ፤ መኪና ያሽከረክራሉ፤ ቤት ንብረት አላቸው፡፡ እነዚህ እናቶች ደም ተፍተው ከለመኑት ገንዘብ ማታ ማታ አንድ ሦስተኛውን አስቀርተው ሁለት ሦስተኛውን ገንዘብ ይወስዱባቸዋል፡፡ የት መለመን እንዳለባቸው የሚያሠማሯቸው እነዚህ ሦስት ሰዎች ናቸው፡፡ በዓል ሲሆን የቀን ገቢውን እንደ “ዕቅድ” ለክተው ይሰጧቸዋል፡፡ ካሳነሱ ግልምጫና ዱላው መከራ ነው፡፡

እናቶቹ ቢንገላቱ፤ ያዘሏቸው ልጆች በረሃብ ቢሞቱ ለሥምሪት ሰጪዎቹ ጉዳያቸው አይደለም፡፡ ለማኞቹ ለአስለማኞቹ የተቀጠሩ ባሮች ነበሩ፡፡ መስተዳድሩ ይሄንን “ሰይጣናዊ ኢንቨስትመንት” ነው የዘጋባቸው፡፡

በጫካ ያሉ ሰዎች ወደ ሰላማዊ መንገድ ሲመለሱ ኡጋንዳ፣ አውሮፓና አሜሪካ ያሉ ሰዎች ናቸው እሪታውን የሚያቀልጡት፡፡ የጫካ ታጣቂዎች ለእነዚህ ዳያስፖራዎች “ሰይጣናዊ ኢንቨስትመንት” ናቸው፡፡ ይለምኑባቸዋል፤ ዩቲዩብ ይሠሩባቸዋል፤ መዋጮ ይሰበስቡባቸዋል፤ ጀግና ጀግና ይጫወቱባቸዋል፡፡ የእነዚህ ዳያስፖራዎች እንጀራ በታጣቂው መከራና ስቃይ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ቢሞት፣ ቢቆስል ግድ የላቸውም፡፡ ለዚህ ነው “ለምን ከሞት አመለጥክ” ብለው ወደ ሰላም በመጣው ታጣቂ የሚናደዱት፡፡ “ለምን ሱቄን ዘጋህ” ማለታቸው ነው፡፡

በሌላ በኩል ልክ በልመና ላይ ተሠማርተው እንደነበሩት እናቶች ሁሉ ወደ ሰላም መንገድ ሲመጡ ታጣቂዎቹ ደስታቸው ወሰን አልባ ነው፡፡ “ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን” ይላሉ፡፡ በጫካ የቀሩትም “እኛንም በመንግሥታችሁ አስቡን” ይሏቸዋል፡፡ መውጫው ጠቦባቸው እንጂ ሁሉም እንደ ገና ዳቦ ከላይና ከታች መለብለብ መርሯቸዋል፡፡ ገና ለገና አክቲቪት እገሌና አክቲቪስት እገሊት ኑሮ መደጎሚያ፣ ልጅ ማሳደጊያ ያጣሉ ተብሎ ከሞት ጋር መጋፈጥ ታጣቂውን አንገፍግፎታል፡፡ አራት ኪሎ እንገባለን ያሉት ሰዎች ሽሬና መንደፈራ ገብተው “በስልክ አነጋግሪኝ በቀጭኑ ሽቦ” የሚለው ዘፈን እንደከፈቱለት ታጣቂው አይቷል፡፡

ከሰሞኑ አያሌ ታጣቂዎች ጫካውን ርግፍ አድርገው ትተው በጫካ ፕሮጀክት መደነቅ ጀምረዋል፡፡ ይሄንን ጉዳይ በጫካ ያሉት ታጣቂዎች ሲሰሙ፡-
“እየዳነ ሄደ እየዳነ” የሚለውን ይዘምራሉ አሉ፡፡
የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡

ቅድስት ድንግል ማርያም ወቶ ከመቅረት ትጠብቃችሁ የጎደላችሁን ያሰባችሁትን ትሙላላችሁ አሜን 🤲🙏❤️
31/08/2026

ቅድስት ድንግል ማርያም ወቶ ከመቅረት ትጠብቃችሁ የጎደላችሁን ያሰባችሁትን ትሙላላችሁ አሜን 🤲🙏❤️

ትላንት                እና               ዛሬ
30/08/2026

ትላንት እና ዛሬ

Address

Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Visit Gamo Arbaminch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share