Discover South Ethiopia

Discover South Ethiopia The Land of Diversity and Peace❗

👉https://www.facebook.com/profile.php?id=61550826170135

👉South Ethiopia❗

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ።ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን በመጠቀም ህዝብን ከህዝብ ጋር፣ ህዝብን ከመንግስት ጋር ለማጋጨት እና ከሌሎች የአገ...
29/08/2025

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ።

ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን በመጠቀም ህዝብን ከህዝብ ጋር፣ ህዝብን ከመንግስት ጋር ለማጋጨት እና ከሌሎች የአገራችንና የክልላችን ሰላም ለማናጋት በውስጥና በውጭ ከምንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በትስስር በመሥራት የተጠረጠሩ 9 ግለሰቦችን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ ማጣራት ጀምሯል፡፡

እነዚህ ተጠርጣሪዎች ማንነታችን አይታወቅም በሚል የክልሉን ህዝብ ስላምና ለዘመናት የቆየ አብሮነት እንዲሸረሸርና ጥርጣሬ እንዲፈጠር ምንም መሠረት የሌላቸውን ሀሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት ለዚሁ ተግባራቸው ከጀርባቸው ሆነው ጥቅም የሚሰጧቸውን ጥቂት ግለሰቦች ፍላጎት ለማሳካት ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ ናቸው፡፡

ተጠርጣሪዎች የጥላቻ ንግግርን፣ ሀሰተኛ የመረጃ ስርጭት እና ስም የማጥፋት እኩይ ሥራ እንደ አንድ የገቢ ማግኛ ምንጭ አድርገው እየተጠቀሙ ቆይተዋል፡፡

የክልሉ ፖሊስ ህግ በማስከበር የክልሉን ህዝብ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በማንኛውም በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን እና ቡድኖችን በህግ ቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ የማጣራት ሥራውን አጠናክሮ የሚቀጥል ስለሆነ ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ፈጻሚዎችን በሀሳብና በገንዘብ በመደገፍ የራሳቸውን ድብቅ ዓላማ ለማሳካት ከጀርባ ሆነው የሚሠሩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

በዚህ አጋጣሚ የእነዚህን ግለሰቦች መሠረተ-ቢስ መረጃ በመቃወምና የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ የክልሉ ፖሊስ በሚያደርገው እንቅስቃሴ መረጃ በመስጠት ከፍተኛ ትብብር የሚያደርጉ የህብረተሰብ ክፍሎችን እያመሰገነ ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ ፖሊስ እየወሰደ ያለውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ያሳውቃል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን

ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ/ም
ላስካ

የጀግና እናት 🙏ዛሬ ጀግና የሆኑ እናት እናስተዋዉቃችሁ፦ ከወላይታ!የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢንጅነር ሀይለማርያም ደሳለኝ ወላጅ እናት ሲሆኑ ወልደው ለወግ ለማእረግ ካበቋቸው ልጆ...
08/08/2025

የጀግና እናት 🙏

ዛሬ ጀግና የሆኑ እናት እናስተዋዉቃችሁ፦ ከወላይታ!

የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢንጅነር ሀይለማርያም ደሳለኝ ወላጅ እናት ሲሆኑ ወልደው ለወግ ለማእረግ ካበቋቸው ልጆች መካከል

1/ የቀድሞ ጠ/ሚ/ር ክቡር ኢንጂነር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣

2/ የኢትዮጵያ ሲቭል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ ፕረዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ፣

3/ የአድስ አበባ መንገድ ትራንስፖርት የመንገድ ደህንነት ኃላፊ ኢንጅነር ገነቱ ደሳለኝ፣

4/ የሀዋሳ ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል መምህር ዶ/ር ብስራት ደሳለኝ፣

5/ የዱቦ ሆስፒታል ሰዉ ሀብት አመራር ዳይሬክተር አቶ መስፍን ደሳለኝ፣

6/ የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ም/ኃላፊ ዳዊት ደሳለኝ፣

7/ የፌደራል መንገድ ትራንስፖርት ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግሥት ደሳለኝ፣

8/ የግል ኢንቨስተር አቶ ማርቆስ ደሳለኝ እና ደረጄ ደሳለኝ እናትም፣ አባትም ሆነው ያሳደጉ ለኢትዮጵያ ያበረከቱ ጀግና ኢትዮጵያዊት እናት ናቸው!

በዛ ላይ እሳቸው ራሱ ዶክተር ናቸው!

እናት ሀገር ነች ሲባል በምክንያት ነው!

ረጅም ዕድሜ ከጤና ለእናታችን!

(ማራኪ ወግ)

አቶ አዲሱ አረጋ የግብርና ሚኒስትር ሆነው ተሾሙጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ አቶ አዲሱ አረጋን የግብርና ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል፡፡አቶ አዲሱ አረጋ በምክትል ርዕሰ...
01/08/2025

አቶ አዲሱ አረጋ የግብርና ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ አቶ አዲሱ አረጋን የግብርና ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል፡፡

አቶ አዲሱ አረጋ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ ሆነው ሲያገልግሉ ነበር፡፡

ከዛሬ ጀምሮ የግብርና ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው ሐምሌ 11/2017 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ  ክልል ምክር ቤት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ  በተገኙበት 6ኛ ዙር ...
18/07/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው

ሐምሌ 11/2017 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአርባምንጭ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡

በጉባኤው የምክር ቤቱ ረቂቅ ቃለ ጉባኤ ማፅደቅ ፣ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ማድመጥና የ2018 የበጀት አመት ጠቋሚ ዕቅድ እንዲሁም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ምክር ቤቱ የተለያዩ አዋጆችና ደንቦችን ጨምሮ ሹማቶችን የሚያጸድቅ ይሆናል ።

በጉባኤው የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አለማየሁ ባዉዲ ፣የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የምክር ቤቱ አባላትና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

በጉባኤው መክፈቻ በክልሉ ምክር ቤት የተዘጋጀ የፎ ኤግዚቪሽን ተጎብኝቷል።

በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል።አሁን...
16/07/2025

በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል።

አሁንም ህጋዊ የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ የሰው ሃይል በተለያዩ የሞያ ዘርፎች በቁጥር ከፍተኛ የሆነ የሰው ሃይል እንደሚያስፈልግ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መረጃ ገልፀዋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የሞያ ዘርፎች መሰማራት የምትፈልጉ በሙሉ ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ፎርሙን ሞልታችሁ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል እናሳውቃለን።

Driving & Transportation
1. Light Vehicle Driver
2. Heavy Vehicle Driver (e.g., Grader Operator)
3. House Driver
4. Trolley Operator

Security & Safety
5. Security Guard
6. CCTV Surveillance Operator
7. Office Security Personnel
8. Plumber
9. Electrician
10. HVAC Technician
11. AC Technician
12. Pumper

Domestic & Facility Services
13. Housekeeper
14. House Maid
15. House Cleaner
16. Housekeeping Supervisor
17. Houseman
18. Caretaker
19. Steward
20. Laundry Attendant
21. Bellman

Hospitality & Food Services
22. Receptionist
23. Waiter/Waitress
24. Barista
25. Sous Chef
26. Pastry Chef / Dessert Chef
27. Garde Manger Chef
28. Arabica Cuisine Chef
29. Kitchen Assistant
30. Private Cook
31. Room Attendant
32. Hotel Assistant Manager

Healthcare & Caregiving
33. Nurse
34. Junior Nurse
35. Home Care Nurse
36. Private Nurse
37. Junior Midwife / Clinical Nurse
38. Elderly Care Assistant
39. Live-in Support Assistant
40. Neonatal Intensive Care Unit (NICU) Nurse
41. Junior Physiotherapist

Childcare Services
42. Babysitter
43. Childcare Worker

Beauty & Salon Services
44. Hairdresser
45. Hairstylist
46. Beauty Therapist
47. Salon Manager
48. Nail Technician
49. Nail Art Instructor
50. Massage Therapist
51. Makeup Artist

Agriculture & Farming
52. Indoor Farmer
53. General Farm Worker

Administrative & Marketing
54. Junior Administrative Assistant
55. Junior Marketing Assistant
56. Junior Account Manager
57. Sales Representative
58. Purchaser

Skilled Labor
59. Construction Worker
60. Laborer
61. Tailor
62. Storekeeper
63. Supervisor

Retail & Customer Services
64. Cashier
65. Promoter

https://for

አርባምንጭ : ደግ ልጇን አጥታለች   | በአርባምንጭ ከተማ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች የሚታወቀው  ወጣት ተወዳጅ መኮንን ለድሆች የመኖሪያ ቤት እንዲሁም ሙሉ የህክምና ወጪ በመሸፈን አ...
10/07/2025

አርባምንጭ : ደግ ልጇን አጥታለች

| በአርባምንጭ ከተማ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች የሚታወቀው ወጣት ተወዳጅ መኮንን ለድሆች የመኖሪያ ቤት እንዲሁም ሙሉ የህክምና ወጪ በመሸፈን አርባምንጭ ሁሌም የምታመሰግነው ወጣት በድንገት ማረፉ ተሰምቷል።

ለቤተሰብ፣ ወዳጅ፣ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።

የአርባምንጭ በጎ ፍቃደኞች ማህበር

የወላይታ ዞን ምክር ቤት ባደረገው 4ኛ ዙር 13ኛ የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ፦ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በም/ማዕረግ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፤ዶ/ር አማሬ አቦታ የወላይታ ዞን ...
08/07/2025

የወላይታ ዞን ምክር ቤት ባደረገው 4ኛ ዙር 13ኛ የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ፦

ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በም/ማዕረግ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፤

ዶ/ር አማሬ አቦታ የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ ፤

አቶ ተስፋሁን ታዲዮስን የፓለቲካ ስበት ማዕከልና የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አድርጎ ሾሟል።

የክልል ክለቦች ሻምፕዮና ምድብ ድልድል
04/07/2025

የክልል ክለቦች ሻምፕዮና ምድብ ድልድል

በክልሉ እየተደረገ ያለው የአንድነት መድረክ ልምድ የሚወሰድበት ነዉ ፦ አቶ አደም ፋራህ ሰኔ 24/2017 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው  የሠላም፣ የአን...
01/07/2025

በክልሉ እየተደረገ ያለው የአንድነት መድረክ ልምድ የሚወሰድበት ነዉ ፦ አቶ አደም ፋራህ

ሰኔ 24/2017 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ጉባኤ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።

በወቅቱ የተገኙት የኢፌድሪ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ፣ክልሉ በታሪክ በባህልና በተፈጥሮ ፀጋ የታደለ መሆኑን ገልጸዋል ።

ኢትዮጵያ ብዝሃ ማንነት የሚኖሩባት መሆኑን የገለፁት አቶ አደም ፋራህ ፣በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙት ብሔር ፣ብሔረሰቦች ይህንኑ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

በክልሉ 32 ብሔሮች ፣ብሔረሰቦች እንደሚገኙ የገለፁት አቶ አደም ፋራህ ክልሉ ፣በተመሰረተ አጭር ጊዜ ውስጥ፣ ከነባር ክልሎች ጋር መሰለፍ መቻሉን ገልጸዋል ።

በክልሉ ያሉት የታሪክ፣ የባህልና የተፈጥሮ እምቅ ፀጋዎች ክልሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የብልጽግና ተምሳሌት መሆኑን ገልጸው፤ ለም መሬቱ፣ የተፈጥሮ ሀብቱ እና ታታሪ ሕዝቦቹ የልማት ምሰሶ እንደሆኑ ተናግረዋል።

በፖለቲካ መስክ የክልሉን ተቋማት አደራጅቶ ወደ ሥራ በማስገባት፣ የሕዝብ ንቅናቄ እና የአመራር አንድነት የሚያመጡ ተግባራት መከናወናቸውን ለክልሉ ትልቅ አቅም ነው ብለዋል።

በዚህም ፣በክልሉ እየተከናወኑ ያሉት የልማት ስራዎች አንዱ ማሳያ መሆናቸውን አቶ አደም ፋራህ ጠቁመዋል ።

በኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሰረት ነዉ ያሉት አቶ አደም ፋራህ ፣በቀጣይም በክልሉ ህዝብ ዘንድ ያለዉን አብሮነት በዘላቂነት ለማስቀጠል መስራት እንደሚገባም አስረድተዋል ።

በክልሉ ያሉት የጋራ ማንነትቶች እንዲጎለብቱ የተጀመሩት ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸውም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል ።

በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የተጀመረው የመደመር ፍልፍስና ዉጤት በሀገሪቱ ሁለንታዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ስለማስቻሉ የገለፁት አቶ አደም፣ በክልሉም ይህንኑ ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል ።

በክልሉ የተጀመሩ የገዢ ትርክት ዕሳቤዎች እንዲጠናከሩ የኢፌድሪ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል ።

በቀጣይ በክልሉ ያለዉን ታሪክ ባህልና ቋንቋ እንዲሁም የተፈጥሮ ፀጋ ለጋራ ብልጽግና መጠቀም እንደሚገባም አስረድተዋል ።

ጉባዔው ''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል ።

በጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በተጨማሪ ፣የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደን ጨምሮ ሌሎች የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ፣የሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ተሳታፊ ሆነዋል ።

ቀጣዩ ምዕራፍ እስካሁን በተፈጠረው መግባባት ላይ የሚገነባና በወንድማማችነት እሴት ላይ የሚፀና መሆኑን አምኖ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ተብሏል ።

እንዴት ማመን እችላለሁ። ዉድ ወንድሜ አሊ ከድር ዛሬ ጠዋት አብረን ስብሰባ ዉለን ለምሳ ተለይተን ከሰዓታት በኃላ ሲያጣህ አሊዬ። በጣም ልብ ሰባሪ። የቀድሞ የሲልጤ ዞን ዋና አስተዳዳርና የማ...
28/04/2025

እንዴት ማመን እችላለሁ።
ዉድ ወንድሜ አሊ ከድር
ዛሬ ጠዋት አብረን ስብሰባ ዉለን ለምሳ ተለይተን ከሰዓታት በኃላ ሲያጣህ አሊዬ። በጣም ልብ ሰባሪ።

የቀድሞ የሲልጤ ዞን ዋና አስተዳዳርና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ አሊ ከድር ባጋጠማቸው እጅግ ልብ ሰባሪ ድንገተኛ የመኪና አደጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን ለመግለፅ እወዳለሁ።

ነፍስህ በገነት ከደጋጎች አጠገብ ያሳርፍ ፈጣሪ።
ለመላዉ ቤተሰቦችህ፣ ሥራ ባልደረቦችህ እና ጓደኞችህ መጽናናትን ተመኘሁ።

አቶ ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር

ከዛሬ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በሀገራዊ ቁልፍ ጉዳዮች እንዲሁም በፓርቲ ተኮር ጭብጦች ላይ ለመጪዎቹ ሁለት ቀናት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል።
25/04/2025

ከዛሬ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በሀገራዊ ቁልፍ ጉዳዮች እንዲሁም በፓርቲ ተኮር ጭብጦች ላይ ለመጪዎቹ ሁለት ቀናት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ከፋይናንስ ቢሮ ጋር በመሆን ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች ማዕድ አጋራየክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ከክልሉ ፋይናንስ ቢ...
19/04/2025

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ከፋይናንስ ቢሮ ጋር በመሆን ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች ማዕድ አጋራ

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ከክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ጋር በመሆን በወላይታ ሶዶ ከተማ የሚገኙ ከ400 በላይ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች ማዕድ አጋርቷል።

በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ መረዳዳት ለአብሮነትና ለአንድነት እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ባህል ሊናደርገው ይገባል ብለዋል።

የለውጥ መንግስት ከመጣ በኃላ በመረዳዳትና በመደጋገፍ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው ያሉት አቶ ተፈሪ ይህን በጎ ተግባር ባህል አድርገን በማስቀጠል አቅማችን የቻለነውን ማድረግ ይጠብቅብናልም ብለዋል።

ፓርቲያችን ብልፅግና ሰው ተኮር ፓርቲ ነው ያሉት አቶ ተፈሪ ፓርቲው የሚመራው መንግስት የዜጎችን ህይወት ለመለወጥ አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

መልካም ነገሮችን በክልላችን በማጠናከር እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ መስራት እንዲሁም የእኛ እገዛ ለሚፈልጉ ወገኖችን መልካምነትንና በጎነትን ማሳየት ይገባል ብለዋል።

የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዱፄ ታምሩ በበኩላቸው ትንሳኤ በዓልን ስናከብር በጎነትንና መልካምነትን ለሌሎች በማሳየት ሊሆን ይገባል።

ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል ካለው ሌላው በማካፈል በዓሉን በጋራ ማክበር ያስፈልጋል ያሉት አቶ ዱፄ አቅም የሌላቸውን የመደገፍ ስራ ባህልን ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ከክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ጋር በመተባበር ከ400 በላይ አቅመ ደካሞች ማዕድ ማጋራት ፕሮግራም መካሄዱንም አስታውቀዋል።

በየአካባቢው ያሉ አቅም ደካምችንና አረጋዊያን መጠየቅና መደገፍ በምድራዊ ህይወት ብቻ ሳይሆን ከፈጣሪ ዘንድም ዋጋ ያለው መልካም ተግባር በመሆኑን ማጠናከር ይገባናል ሲሉም አሳስበዋል።

ሁሉም በየአካባቢው መልካም ተግባር በመፈጸም አብሮነትንና ፍቅርን እንዲያሳዩ ጥረ በማቅረብ በዓሉ የሠላምና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ተመኝተዋል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

Address

Sikela
Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Discover South Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share