Arba Minch FM 90.9 / አርባ ምንጭ ኤፍ ኤም 90.9

Arba Minch FM 90.9 / አርባ ምንጭ  ኤፍ ኤም 90.9 የአርባ ምንጭ ኤፍ ኤም 90.9 ሬድዮ የህብራዊነት ድምፅ በመሆኑ ያዳምጡታል ይናገሩበታልም !

ምሁራንን በማስተባበር ሀገር የያዘችውን የለውጥ ጉዞ ማሳካት እንደሚቻል የኮንሶ ዞን አስተዳደር አስታወቀ አርባምንጭ ነሐሴ 30 ፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)የኮንሶ ምሁራን ማህበር "ላስተማ...
05/09/2025

ምሁራንን በማስተባበር ሀገር የያዘችውን የለውጥ ጉዞ ማሳካት እንደሚቻል የኮንሶ ዞን አስተዳደር አስታወቀ

አርባምንጭ ነሐሴ 30 ፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

የኮንሶ ምሁራን ማህበር "ላስተማረኝ ማህበረሰብ ምን ላድርግ?" በሚል መሪ ቃል 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል።

ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኮንሶ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጉራሾ ጎስኬ፣ ምሁራን የአገሪቱን የለውጥ ጉዞ በማገዝ ትልቅ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚንሸራሸሩ አሉታዊ መልዕክቶች እንዲወገዙ እና ምሁራን የእድገት እንቅፋት ከሆኑ ነገሮች እንዲርቁ አሳስበዋል።

የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ አቶ ኩማቾ ኩሴ፣ ምሁራን ለተማሩበት ማህበረሰብ የሚበጅ ነገር እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ ፤ ማህበሩ የተለያዩ ችግር ፈቺ ጥናቶችንና ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ እንዲሁም ከኮንሶ እስከ አሜሪካ ባሉ ቅርንጫፎች ውስጥ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከንግግር ባሻገር የሀገርቱንና የኮንሶን አንድነት ለማጎልበት፣ በእውቀት ላይ የተመሰረቱ ተግባራዊ መፍትሄዎችን ለመፍጠር፣ ለሰላም ግንባታ በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ሀሳቦች ቀርበዋል።

የኮንሶን እርከኖች ለመስራት ትጋትና ትዕግስት እንደሚያስፈልግ በመጥቀስ፣ ምሁራንም የሚመኙትን የተለወጠ እና የበለጸገ ማህበረሰብ ለመፍጠር በጽናትና በትብብር መስራት እንዳለባቸው ተገልጿል።

በመጨረሻም "ሰላም ይቀድም"፣ "ተባብረን እንጓዝ" የሚሉ መርሆች ተንጸባርቀዋል።

በጉባኤው የተገኙ አባላትም ለህብረተሰባቸው በትጋት ለመስራት እና ከአጎራባች ዞኖች ምሁራን ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

ዘጋቢ ፡የአማሮ አርሳባ

የድህረ - ወሊድ ደም መፍሰስን በመለየትና በመቆጣጠር የእናቶችን ህመምና ሞት ማስቀረት ከሁሉም የጤና ተቋም እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ‎‎አርባምንጭ ነሐሴ 30 ፣2...
05/09/2025

የድህረ - ወሊድ ደም መፍሰስን በመለየትና በመቆጣጠር የእናቶችን ህመምና ሞት ማስቀረት ከሁሉም የጤና ተቋም እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ

‎አርባምንጭ ነሐሴ 30 ፣2017 ዓ.ም (ኤፍኤ 90.9)

‎"ኢንጀንደር ሄልዝ" ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከ 2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የእናቶችን ደም መፍሰስ መቆጣጠርና መለየት የሚያስችል የደም መፍሰስ መጠን መለኪያ (Calibrated drapes) ና ሌሎች የህክምና መገልገያዎችን በክልሉ ለሚገኙ ሆስፒታሎች ድጋፍ አድርጓል።

‎የክልሉ ጤና ቢሮ የቢሮ ኃላፊ ተወካይና የጤናና ጤና ነክ ግብአት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አቶ ዮሴፍ ሶይቆ እንደ ክልል በሁሉም አከባቢዎች የጤናውን ስርአት በማሻሻል ፍትሀዊና ጥራቱን የጠበቀ የጤና ተደራሽነት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው።

‎ልምድ ያላቸው ከፍተኛ ባለሙናዎችን ከማሟላትና የጤና ተቋማትን ከማስፋፋት አኳያ ለውጥ መኖሩን ጠቅሰው በዚህም የእናቶችን ሞት መታደግ ተችሏል ብለዋል።

‎ የድህረ - ወሊድ ደም መፍሰስን መለየትና መቆጣጠር የሚያስችል መሳርያ በ 'ኢንጀንደር ሄልዝ ኢትዮጵያ' በኩል ለህክምና ተቋማት መድረሱ ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችል በመሆኑ ሁሉም የጤና ተቋም በዚህ ረገድ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

‎በክልሉ ጤና ቢሮ የእናቶችና ህጻናት ዳይሮክተሬት ዳይሬክተር አቶ መሪሁን ገብሩ ፤ የእናቶች ሞት በአብዛኛው የሚከሰተው ከደም መፍሰስ ጋር ተያይዞ በመሆኑ ይህን ለማስቀረት እንደ ክልል ሰፊ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

‎በቀጣይ የደም መፍሰስ መጠንን ለመለየት የሚረዱ የህክምና ቁሳቁሶችን በመጠቀም የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት ለመቀልበስ ባለሙያዎች በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

‎የ'ኢንጀንደር ሄልዝ' ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልና የሲዳማ ክልል አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ ኦርዶሎ ፤ ድርጅቱ የተቀናጀ የእናቶችና ህጻናት ጤና ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎እንደዚሁም በድህረ ወሊድ ወቅት በእናቶች ላይ የሚከሰት ደም መፍሰስን በግምት ከመለየት ይልቅ በእውቀትና በልኬት ላይ የተመሠረተ ስራ እየሰሩ መሆናቸውንና በዚህም ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ እናቶችን ተደርሽ ያደርጋል ብለውል።

‎በመርሀ ግብሩ በድህረ - ወሊድ ወቅት የሚከሰትን የእናቶችን ደም መፍሰስ አስመልክቶ የመፍትሄ ሀሳቦችን የሚዳስስ ጥናታዊ ጽሁፍ የቀረበ ሲሆን ተሳታፊዎች የእናት ሞት የቤተሰብ ሞት መሆኑን በመረዳት ሁሉም የህክምና ተቋምና ባለሙያዎች ለእናቶች ዋጋ ከፍለው መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

‎በመርሀ ግብሩ' ኢንጀንደር ሄልዝ ኢትዮጵያ' ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በክልሉ ለሚገኙ ሆስፒታሎች የእናቶችን ደም መፍሰስ መቆጣጠርና መለየት የሚያስችል የደም መፍሰስ መጠን መለኪያ እና ሌሎች የህክምና መገልገያዎችን ድጋፍ ማድረጉም ተጠቅሷል።

‎ዘጋቢ ፡ ማርታ ሙሉጌታ

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች በክህሎት የበቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት  ጥራት ያለውን ስልጠና መስጠታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የጋሞ ዞን ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መምሪያ አሳሰበአርባምን...
05/09/2025

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች በክህሎት የበቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ጥራት ያለውን ስልጠና መስጠታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የጋሞ ዞን ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መምሪያ አሳሰበ

አርባምንጭ ነሐሴ 30፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

በደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ የአርባ ምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒክ ኮሌጅ 'ከአድራ ጀርሜን ፕሮጀክት' ጋር በመተባበር በሶላር ፓኔል ተከላ እና ጥገና ዙሪያ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለ 3ኛ ጊዜ አስመርቋል።

የደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ /ቤት ሀላፊ ዶ/ር ኦርካዶ ኦልቴ የደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ ከመንፈሣዊ አገልግሎት በተጓዳኝ በልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ዘርፎች ከ30 በላይ የልማት ዘርፎች የአከባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ ማድረጉን አስረድተዋል።

የጀመርን የልማት ድርጅት ከደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ ጋር በመተባበር በሶላር ኢነርጂ ተከላና ጥገና ዙሪያ ለሶስኛ ተከታታይ ጊዜያት ያሰለጠናቸውን ወጣቶች ማስመረቁ ሥራ አጥነትን ከመቀነስ ባለፈ ለታዳሽ ሀይል ኢኮኖሚ ያለው ፋይዳ የጎላ ነው።

ስልጠናው የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ እና ታዳሽ ሀይል ዕሳቤን ተግባራዊ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑም ተብራርቷል።

ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ተግባር ተኮር በመሆኑ ሰልጣኞች ክህሎታቸውን ተጠቅመው ሥራ ፈጥረው እንዲሠሩ ያግዛቸዋል ያሉት ደግሞ የአርባ ምንጭ መካነ ኢየሱስ ኮሌጅ ዲን አቶ አደን አብዱሩሐማን ናቸው።

ኮሌጁ በተለያዩ የስልጠና መስኮች ተማሪዎችን እያሰለጠነ ሲሆን በአጫጭር ኮርሶች ደግሞ በታዳሽ ሀይል ዘርፍ በ"ግሪን ኢነርጂ ቲቪቲ ከአድራ ጀርመን ፕሮጀክት" ጋር በመተባበር ለሶስተኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 43 ሰልጣኞችን ማስመረቁንም ዲኑ አብራርተዋል።

የጋሞ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ አቶ ወንድሙ ኡቶ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎችን በመለየት ቴክኖሎጂን በማስፋፋት እና ሥራ አጥነትን ለመቅረፍ ባለመ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በዘርፉ የተሰማሩ ኮሌጆች ልምድ የሚቀሰሙባቸው እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግባቸው ከመሆናቸውም ባሻገር ጥራት ያለውን ስልጠና መስጠታቸውን እንዲያጠናክሩ መክረዋል።

ከሰልጣኞች መካከል ወ/ሮ ታብሌት ታምራት እና ጴጥሮስ ሳሙኤል እንዳሉን በስልጠና ቆይታቸው የተግባር ተኮር እና ንድፈ ሐሳቦችን መቅሰማቸው በቀጣይ ብቁ ሥራ ፈጣሪ እንድሆኑ ያበቃቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ሰልጣኞች ከዕለቱ ከእንግዶች እጅ የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸውዋል።

ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው

በግልና በማህበር ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ ንብ አናቢዎች ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩአርባምንጭ ነሐሴ 30፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)በ2017 በጀት አመት ከ 60 ሺህ ኪሎ ግራም በላ...
05/09/2025

በግልና በማህበር ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ ንብ አናቢዎች ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ

አርባምንጭ ነሐሴ 30፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

በ2017 በጀት አመት ከ 60 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት መገኘቱን የቁጫ አልፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ።

በንብ ማነብ ዘርፍ ኢንቨስትመንት መስክ ለመሰማራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ምቹ የሆነ ስነ ምህዳር በወረዳው መኖሩንም ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

በቁጫ አልፋ ወረዳ 255 አርሶ አደሮች በማር መንደር ተደራጅተው የንብ ማነብ ስራ በስፋት እየሰሩ ይገኛል።

በአንድ ባህላዊ ቀፎ በተፈጥሮ እውቀት የንብ ማነብ ስራ መጀመራቸውን የነገሩን አርሶአደር ዎጋ ዎይዴ በወረዳው ኮዶ ዎኖ ቀበሌ ጫቶ ንኡስ በስራው ላይ 26 ዓመት አስቆጥረዋል።

የእርሻ ስራን ወደጎን በመተው ንብ ማነብ ላይ ትኩረት ያደረጉት አርሶ አደሩ ዛሬ ከ150 በላይ የንብ ቀፎዎች እና 30 ዘመናዊ ቀፎ ባለቤት ናቸው።

እንደ አርሶአደር ዎጋ ዎይዴ ገለጻ በወር ከሚቆርጡት ማር ሽያጭ ከ1መቶ ሺ ብር በላይ ገቢ እንደሚያገኙ ጠቁመዋል።

ከማር ሽያጭ ገቢ በወረዳው ጥሩ መኖሪያ ቤት የገነቡት አርሶአደሩ በቅርቡ መኪና ለመግዛትም አቅደዋል።

ሌላኛው በማህበር በመደራጀት ወደ ንብ ማነብ ስራ የገቡት አርሶአደር ሳባ ሳና በሚኖሩበት አከባቢ በስፋት የሚገኘውን የተፈጥሮ ደን እና ወንዝ በመጠቀም ከ70 ቀፎ የሚያገኙትን ማር በአመት 3 ዙር በመቁረጥ ከፍተኛ ገቢ እያገኙ መሆኑን ጠቁመዋል።

የቀበሌና የወረዳ ግብርና ባለሞያዎችን ሞያዊ ድጋፍ ያደነቁት አርሶ አደሮቹ የማር ማጣሪያ እና የዘመናዊ ቀፎ አቅርቦትን ጠይቀዋል።

የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን
በርገኔ በወረዳው 693 ንብ አንቢዎች 10 ሺህ 845 ቀፎን በመጠቀም በአመት 60ሺህ 6መቶ kg ማር መሰብሰብ ተችሏል።

255 አርሶ አደሮች በማር መንደር ተደራጅተው የንብ ማነብ ስራን እንዲሰሩ በመደረጉ ተጨባጭ ውጤት በመመዝገብ ላይ ይገኛል።

እንደ አቶ ተመስገን ገለጻ ወረዳው 1 ነጥብ9 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ 228 ዘመናዊ ቀፎዎችን በመግዛት በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እና ግለሰቦች ድጋፍ ለማደረግ አቅዷል።

ዘጋቢ ፡ አሰግድ ተረፈ

የድህረ ወሊድ ደም መፍሰስን በመለየትና በመቆጣጠር የእናቶችን ህመምና ሞት ማስቀረት ከሁሉም የጤና ተቋም እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀአርባምንጭ ነሐሴ 30፣2017ዓ....
05/09/2025

የድህረ ወሊድ ደም መፍሰስን በመለየትና በመቆጣጠር የእናቶችን ህመምና ሞት ማስቀረት ከሁሉም የጤና ተቋም እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ

አርባምንጭ ነሐሴ 30፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

"ኢንጀንደር ሄልዝ" ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት የእናቶችን ደም መፍሰስ መቆጣጠርና መለየት የሚያስችል ፕሮግራም ማስጀመርያ መርሀ ግብር በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወነ ይገኛል።

በመድረኩ የክልሉ ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ ግብአት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣንና የቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ዮሴፍ ሶይቆን ጨምሮ በክልሉ የሚገኙ አጠቃላይ ሆስፒታል ኃላፊዎች ፣ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያዎችና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በመርሀ ግብሩ በክልሉ ለሚገኙ ሆስፒታሎች የደም መፍሰስ መጠን መለኪያ (Calibrated drapes) ድጋፍ እንደሚደረግም ይጠበቃል።

ዘጋቢ:- ማርታ ሙሉጌታ

የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ  ከሚረዱ  ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ገለፀአርባምንጭ ነሐሴ 29፣2017ዓ.ም (ኤ...
04/09/2025

የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ገለፀ

አርባምንጭ ነሐሴ 29፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

በክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራው ልዑካን ቡድን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ አስተዳደር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ ድጋፍ አስጀምረዋል።

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መመራቱን ገልፀዋል።

ምክር ቤቱ በተለያዩ መዋቅሮች እንደ ክልል የተጀመረውን ክረምት በጎ ተግባር ባህል ለማድረግ በገረሴ ከተማ አስተዳደር የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርተው ለማስረከብ ማስጀመሩን ተናግረዋል።

ለእንደነዚህ ያሉ እናቶች መድረስ ከፈጣሪ በረከት ማግኛ፣ ፓርቲው የያዘውን ዓላማ ማሳኪያና የዜጎች ህይወት መቀየሪያ ተግባር ስለሆነ ሁሉም በእውቀት በጉልበት ያለውንና ሀሳቡን በመለገስ እንዲተባበር ጥሪ አስተላልፈዋል።

የገረሴ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ አቶ ኤርማያስ እሸቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ የክልል ምክር ቤቱ ለዜጎች ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ በዚህ ክረምት ከሃያ በላይ ቤቶችን ለአቅሜ ደካሞችና ጧሪ ላጡት ሰርቶ በማስረከብ የብልጽግና ጉዞ እውን ያደርጋል ብለዋል።

የቤት ግንባታ ድጋፍ የተጀመረላቸው ወ/ሮ አልብቶ ቦላ በተደረገላቸው ድጋፍ የተሰማቸው ደስታ ገልፀው ድጋፍ ያበረከቱ አካላትን አመስግነዋል።

6 ልጆችን በሞት አጥተው ጧሪ በሌላቸው ወቅት ለደረሰላቸው ወገኖች ፈጣሪ ዕድሜ እንዲያራዝምላቸው መርቀዋል።

ዘጋቢ ፡ ተነሳ ተረፈ

በሀገሪቱ በሚገኙ 5 ተፋሰሶች በ 45 ሚሊየን ዩሮ የተቀናጀ የውሀ ሀብት አስተዳደር ስራ እንደሚከናወን የኢፌዴሪ ውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም ...
03/09/2025

በሀገሪቱ በሚገኙ 5 ተፋሰሶች በ 45 ሚሊየን ዩሮ የተቀናጀ የውሀ ሀብት አስተዳደር ስራ እንደሚከናወን የኢፌዴሪ ውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ

አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

‎ሚኒስቴሩ በስምጥ ሸለቆ ተፋስ በሚገኘው የ'ሀሬ' ወንዝ በተቀናጀ የውሀ ሀብት አስተዳደር ዙሪያ በርካታ የአፈርና ውሀ ስራዎች እንደሚሰሩ ጠቁሟል ።

‎ፕሮጀክቱ በአፈርና ውሀ ለይ የሚደርሰውን ብክለትና ብክነት ከመከላከሉም ባሻገር የአባያ ሀይቅን ከደለል የሚጠብቅ መሆኑም ተመልክቷል ።

‎አቶ አባተ ኡርኬ እና ይገዙ ኃ/ማሪያም ከጨንቻ ዘሪያ ወረዳ በመርሀ ግብሩ የተገኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም በአፈርና ውሀ ለይ ይደርስ የነበረውን ብክለትና ብክነት የሚታደግ መሆኑን ተናግረዋል ።

‎የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ደን አከባቢ ጥበቃና ልማት ጽ/ቤት የደን ልማት ባለሙያ አቶ ዘካሪያስ ጎዴቦ ፕሮጀክቱ ለአከባቢው ነዋሪ አበርክቶው ከፍተኛ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል ።

‎በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ውሀ ሀብትና መስኖ ምህንድስና ፋከልቲ ዲን ዶክተር አስቻለው ቸሬ ዩኒቨርስቲው በአከባቢው የሚገኙ ተፋሰሶችን በመጠበቅ የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከደለል ለመጠበቅ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቁመው በሀሬ ወንዝ ላይ የሚተገበረው ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንደሚኖረው ገልጸዋል ።

‎ዶ/ር ጠና አላምረው የውሀና መሬት ሀብት ማዕከል ምክትል ዳይሬክተር ሲሆኑ የፕሮጀከቱ መተግበር በአባያ ሀይቅ ላይ ይደርስ የነበረውን ደለል ከመከላከሉም ባሻገር የሙዝ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል ።

‎በሀገሪቱ በሚገኙ 5 ተፋሰሶች በ 45 ሚሊየን ዩሮ የተቀናጀ የውሀ ሀብት አስተዳደር ስራ እንደሚከናወን የገለፁት በየኢፌዴሪ ውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር የቤዚን ፕላን ዴስክ ኃላፊ አቶ አሰግድ አጀመ ናቸው ።

‎አባይ ፣ አዋሽ ፣ኦሞ ግቤ ፣ ተከዜና ስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ላይ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ እንደሚደረግ ያወሱት አቶ አሰግድ ፤ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚረዳ ከመሆኑም ባሻገር የተቀናጀ የተፋሰስ ሀብት አስተዳደር ስራዎችእንደሚሰሩ አብራርተዋል ።

‎ወሀ ሊጠፋ የሚችል ሀብት መሆኑን ያወሱት ኃላፊው በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ለመቀነስ ፕሮጀክቱ ለሚያደርገው ጥረት ማህበረሰቡ ያላሰለሰ ድጋፉን እንዲያደርግም ጠይቀዋል ።

‎ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ

የወባ በሽታ ስጋት ሆኖ መቀጠሉን  ዳራማሎ ወረዳ ዋጫ ጤና ጣቢያ  አንዳንድ የወባ በሽታ ታካሚዎች ተናገሩ።‎‎የዳራማሎ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት በዚህ ዓመት  በ30 ሺህ 837 ሰው ላይ የወባ...
03/09/2025

የወባ በሽታ ስጋት ሆኖ መቀጠሉን ዳራማሎ ወረዳ ዋጫ ጤና ጣቢያ አንዳንድ የወባ በሽታ ታካሚዎች ተናገሩ።

‎የዳራማሎ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት በዚህ ዓመት በ30 ሺህ 837 ሰው ላይ የወባ በሽታ ምልክት መታየቱን አስታውቋል።

‎የወረዳው አስተዳደርም ለህብረተሰቡ ዘላቂ መፍትሔ እንዲገኝ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን እንደሚሰራ ገልጿል።

‎ ዋጫ ጤና ጣቢያ ለህክምና የመጡት የዶምኣ ቀበሌ ነዋሪ ከሆኑት መካከል ወ/ሮ ብርሃነሽ ኮይራ እና የዋጫ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ማሞ ገ/ማሪያም የህክምና ባለሙያዎች ከሚያደርጉት ክትትል በተጨማሪ ህክምና እያገኙ ቢሆንም ዘላቂ መፍትሔ አላማኘታቸውን ገልፀዋል።

‎በተለይም አካባቢያቸውን አቋርጦ በሚሄደው የመስኖ ካናል የወባ ትንኝ የሚራባ መሆኑ ለወባ በሽታና ለሌሎች ውሃ ወለድ በሽታዎች መጋለጣቸውን አስረድተዋል።

‎አስተያየት ሰጪዎቹ የአልጋ አጎበርን ዘውትር የሚጠቀሙ መሆናቸውን አውስተው የሚሰጠው የግንዛቤ ትምህርትም ተጠክናሮ ቢቀጥል የተሻለ ነው ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

‎በዳራማሎ ወረዳ የዋጫ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዳግም ሉቃስ ወደ ጤና ጣቢያው ለህክምና አገልግሎት ከሚመጡ ተገልጋዮች፣ አብዛኛው የወባ በሽታ ተጠቂ መሆኑን ገልፀው በዚህ ዓመት የወባ በሽታን ለመርመር ናሙና ከሰጡ 33 ሺህ 101 ሰዎች ውስጥ 20 ሺህ 293 ሰው ላይ የወባ በሽታ ምልክት መገኘቱን አመላክተዋል።

‎ የበሽታውን ለመከላከልና ጫናውንም ለመቀነስ አስቻይ እርምጃዎችን እየወሰዱ መሆናቸውን ገልፀዋል።

‎የዳራማሎ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የኃላፊ ተወካይ አቶ ቱኮ ካሎ እንደ ወረዳ ዘጠኝ ቀበሌያት ለበሽታው በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አንስተው በዚህ ዓመት እንደ ወረዳ 51 ሺህ 694 ሰዎች ላይ የወባ በሽታ ምርመራ ተደርጎ፣ 30 ሺህ 837 ሰዎች ላይ የወባ በሽታ ምልክት መታየቱን አስታውቀዋል።

‎ ከዚህ ቀደም ለ19 ሺህ 434 ቤተሰቦች ወደ 47 ሺህ 750 የአልጋ አጎበር መሰራጨቱን ጠቁመው በተጨማሪም እስካሁን ባለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራን ጨምሮ የአልጋ አጎበር አጠቃቀም አሰሳ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

‎እንደ አቶ ቱኮ ገለፃ፣ ቀደም ሲል በተደረገው የአልጋ አጎበር አጠቃቀም አሰሳ 67 በመቶ የሚሆኑት ብቻ የአልጋ አጎበርን በተገቢው መንገድ ሲጠቀሙ፤ ቀሪ 33 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ለሌላ ዓላማ ሲጠቀሙ ተገኝተዋል።

‎ የመስኖ ካናሎች የሚያስከትሉትን የጤና ችግሮችን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው ጋር በመነጋገር ላይ እንገኛለን ያሉት አቶ ቱኮ በወንዝ ዳርቻዎችም ውሃ ያቆሩ ቦታዎች ላይ የኬሚካል ርጭት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

‎የዳራማሎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጢሞቴዎስ ጥላሁን በበኩላቸው በመስኖ ካናሎች ሳቢያ የሚመጣውን የወባ በሽታ ተጋላጭነት ለመቀነስና ለህብረተሰቡም ዘላቂ መፍትሔ እንዲገኝ ከአልሚው ጋር በመናበብ የወረዳው አስተዳደር የሚሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ዘጋቢ: አስናቀ ካንኮ

የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ ዋንጫን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በክብር ተረከበ አርባምንጭ ፣ ነሐሴ 28፣2017 ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ የኢትዮጵያ ዋን...
03/09/2025

የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ ዋንጫን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በክብር ተረከበ

አርባምንጭ ፣ ነሐሴ 28፣2017 ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ የኢትዮጵያ ዋንጫን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በክብር ተረክቧል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ የበላይ ጠባቂ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ፣ የዞኑ ም/አስተዳዳሪና የክለቡ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ፣ የሶዶ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ እታገኝ ኃለማያርምን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች፣ ተጨዋቾች እና ደጋፊዎች በተገኙበት የርክክብ ሥነሥርዓት ተደርጓል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጅራ ዋንጫውን ለክለቡ በክብር አስረክበዋል።

በወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ እና በሲዳማ ቡና እግር ኳስ መካከል በተደረገ የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ የሲዳማ አቻው 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ያሸነፈ ቢሆንም ተገቢ ያልሆነ ተጫዋች በማሰለፉ ምክንያት የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ቡድን 3 ንፁህ ጎል እና 3 ነጥብ በማግኘት አሸናፊ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መወሰኑን ይታወሳል።

ዋንጫው መጪዉ አርብ ነሓሴ 30/2017 ዓ.ም ወደ ወላይታ ዞን የሚገባውን የጀግና አቀባበል ለማድረግ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የስፖርት ጨዋነትን በተላበሰ መልኩ በንቃስ መውጣት እንዳለባቸውም ጥሪ ቀርቧል።

Via ፦ደቡብ ክልል መ/ኮ

ፑቲን እና ኪም በቤጂንግ ውይይት አደረጉ አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም  (ኤፍኤም 90.9)የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በቻይና ወታደራዊ ...
03/09/2025

ፑቲን እና ኪም በቤጂንግ ውይይት አደረጉ

አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በቻይና ወታደራዊ ትርዒት ላይ ከታደሙ በኋላ በቤጂንግ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ወቅት፤ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ከሩሲያ ጦር ጎን ሆነው ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።

የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት በድፍረት እና በጀግንነት ተዋግተዋል ሲሉም ተናግረዋል።

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በበኩላቸው፤ ፑቲን ለሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ስለሰጡት እውቅና አመስግነው፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እየጠነከረ መምጣቱን ገልፀዋል።

እንዲሁም "ለሩሲያ ማድረግ የምችለው ወይም ማድረግ ያለብኝ ነገር ካለ እንደ ወንድማማችነት ግዴታ አድርጌ እቆጥረዋለሁ” ሲሉ ኪም ለፑቲን ተናግረዋል።

ከጦርነቱ ባሻገር ኪም በጦርነት የተጎዳውን የኩርስክ ግዛት መልሶ ለመገንባት የሚረዱ ሰራተኞችን እንደሚልኩ ቃል ገብተዋል።

ኪም ለወደቁ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ቤተሰቦች ድጋፍ እንደሚያደርጉ እና መታሰቢያ ሃውልት እንደሚያቆሙላቸው መግለፃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም የውጭ ጥቃት በሚደርስበት ጊዜ የጋራ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል የመከላከያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።

via ፦ # EBC #

በክልሉ እየተስፋፋ የሚገኘውን የኤች. አይ.ቪ ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አሳሰበአርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)...
03/09/2025

በክልሉ እየተስፋፋ የሚገኘውን የኤች. አይ.ቪ ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አሳሰበ

አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስ የትኩረት አካባቢዎችን በመለየት እየተሰራ ስለመሆኑም ተመላክቷል፡፡

ዘር ፣ ቀለምና ጾታ ሳይለይ ምርታማ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመጉዳት ላይ ያለውን የኤች .አይ.ቪ/ ኤድስ ስርጭት ለመከላከል ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በንቃት ራሱን መጠበቅ እንዳለበት ይነገራል፡፡

ወ/ሮ አቢዮት አንጁሎ በአ/ምንጭ ከተማ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ የምክር አገልግሎት ከሚሰጡ በጎ የጤና ባለሙያዎች አንዷ ናቸው፡፡

የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል አቻ ለአቻ ትምህርት በመስጠትና ቫይረሱ የተገኘባቸው ግለሰቦችን ከጤና ተቋማት ጋር የማቆራኘት ስራ በመስራት ላይ መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡

መዘናጋትና የትምህርት መቀዛቀዝ ለቫይረሱ መስፋፋት አንዱ ምክንያት መሆኑን ወ/ሮ አቢዮት ጠቁመው በመንግስትና ረጂ ድርጅቶች የሚደረገው ድጋፍ ሊቀጥል ይገባልም ብለዋል፡፡

ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች በመለየት የምክርና ምርመራ አገልግሎት በመስጠት የበኩላቸውን እየተወጡ የሚገኙት ወ/ሮ ጽዮን ዳዊትና የጤና ባለሙያው አቶ ወንድፍራው ተፈራ ፤ የተተቂዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሆኑ ጥንቃቄ ይሻልም ብለዋል።

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዎናቃ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል የተጀመረው የምርመራና የምክር አገልግሎት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የኤች. አይ.ቪ /ኤድስ መከታተልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ ማቲዮስ ጋርሾ የምርመራ አገልግሎትን በማጠናከርና የግንዛቤ ትምህርቶችን በመስጠት የስርጭት መጠኑን መግታት እንደሚገባ ገልፀው በእርዳታ ላይ የተንጠለጠለውን ድጋፍ ገቢ ለመሸፈን መታቀዱን አስታቀዋል፡፡

ዘጋቢ ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው

የድል ፋና በመጀሪያ ደረጃ ሆስፒል አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን አንዳንድ በሆስፒታሉ ያገኘናቸዉ የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ ‎‎አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017...
03/09/2025

የድል ፋና በመጀሪያ ደረጃ ሆስፒል አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን አንዳንድ በሆስፒታሉ ያገኘናቸዉ የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

‎አርባምንጭ ነሐሴ 28፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)

‎አንዳንድ በሆስፒታሉ የሚታዪ የህክምና ቁሳቁስ ጉድለት እንዲሟሉም ተገልጋዮቹ ጠይቀዋል።

‎ሆስፒታሉ የበለጠ ተገልጋዮቹን ለማርካት እየሰራ መሆኑን ገልፃል።

‎ አቶ ኃይሉ ዳንኤል ከኦሮሚያ ክልል ገላና ወረዳ ለህክምና የመጡ ሲሆን የሆስፒታሉ ባለሙያዎች በሚሰጡት አገልግሎት መደሰታቸዉን ገልፀዉ አገልግሎት አሰጣጡ ከጊዜ ወደ እየተሻሻለ መምጣቱንም ተናግረዋል።

‎ በሆስፒታሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ አሰበች ዳኮማ እና አቶ አየለ ስፒታሉ ከድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎች ጀምሮ በሚሰጠዉ አገልግሎት መርካታቸዉን ተናግረዋል።

‎የህክምና አገልግሎት ከሰጠዉ ሐክም ፈውስ ከማግኘት በላይ የሚያረካ ነገር የለም ያሉት አቶ አየለ በሆስፒታሉ የነበረዉ የመድኃኒት እጥረት እዲቀረፍና ተጨማሪ የህክምና መስጫ መሣሪያዎች እንዲሟሉሞ ጠይቀዋል።

‎በሆስፒታሉ የአጠቃላይ ሀክም ዶ/ር ይድንቃቸዉ ሳሙኤል ተገልጋዮች በሆስፒታሉ ተገቢዉን አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ሁሉም ባለሙያዎች በቅንነት እዲያገለግሉ እየተደረገ ነው ብለዋል።

‎በሆስፒታሉ የሚስተዋሉ አንዳንድ የህክምና ቁሳቁሶችና የመድኃት እጥረት የበለጠ ተገልጋዮችን ለማርካት እንቅፋት መሆናቸዉንም ተናግረዋል።

‎የሆስፒታሉ ሜድካል ዳይሬክተር ዶ/ር መታሠቢያ መለሰ ተቋሙ ከጤና ጣቢያ ወደ ሆስፒታል ካደገ ጊዜ ጀምሮ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋይ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልፀዋል።

‎ተገልጋዮችን የበለጠ ለማርካት የቀዶ ጥገና ክፍል እና ተጨማሪ አልጋ ያስልጋል ያሉት ዶ/ሩ ሆስፒታሉ የሚሰጠዉን አገልግሎት በማስፋት በቅርቡ የራጅ ማሽን ወደ ሥራ እንደሚገባ ገልፀዋል።

‎ የሚስተዋለዉ የመድኃኒት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ ከጋሞ ልማት ማህበር ጋር በመሆን እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

‎ዘጋቢ ፡ ካታንሾ ካርሶ

Address

ARBAMINCH
Arba Mintch
0979711926

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arba Minch FM 90.9 / አርባ ምንጭ ኤፍ ኤም 90.9 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share