31/05/2026
ጅቡቲ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ለመገንባት የኢትዮጵያን የፋይናንስ ድጋፍ እየጠበቀች መሆኑን አስታወቀች
🇩🇯🤝🇪🇹
የጅቡቲ ወደቦችና ነፃ ቀጣናዎች ባለሥልጣን በመጪው የበጀት ዓመት በዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ለመገንባት የኢትዮጵያን ተሳትፎና ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን ይፋ አድርጓል።
የጅቡቲ ወደቦችና ነፃ ቀጣናዎች ባለሥልጣን ሰብሳቢ አቡበከር ሀዲ ኡመር ተቋማቸው ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) ጋር ድርድር እያደረገ እንደሚገኝ ለሀገር ውስጥ የግል ሚዲያ ገልፀዋል።
የነዳጅ ማከማቻው ከኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር በ 13 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደሚገነባ ተመላክቷል።
© Capital § Sputnik Ethiopia