Muluken Seifu G

Muluken Seifu G ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ።
ወደ ቆላስይስ ሰዎች 4:2

01/06/2025

ለጻዲቁ ህንፃ ምርቃት የሆቢቻ ሰዎች ያደረጉት በጎ ተግባር እነሆ ቂቤ ሶስት ትላልቅ እስር እና 2 ፍየል 🙏

ይሄ ስጦታ ከወላይታ ሆቢቻ ከተማ ኦርቶዶክሳዊያን ነው ለእንግዳ መቀበያ የሚሆን ሶስት ትላልቅ እስር ቂቤ እና ፍየል።

እናመሰግናለን እንግዶቻችን እየገቡ ይገኛሉ!
እግሮች ሁሉ ወደ ገዳም ኑ እንግዶቻችን በክብር ተቀብለን በክብር እንሸኛቸው የተዋህዶ ልጆች ጉዞ ወደ ገዳማችን።

Andualem Degefu አንዱሻ ደገፉ

13/05/2025

''Ethio Business" is a weekly program airing on Thursday evenings from 8:30 to 9:00 p.m., dedicated to providing viewers with concise and current business up...

02/05/2025
02/05/2025
24/04/2025

#የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ #አቶ ጴጥሮስ ወ/ማሪያም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል አስመልክተዉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተከበራችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መታሰቢያ በዓል አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል ነስቶ የተነሳበት የአሸናፊነት ማሳያ ነዉ።

የትንሳኤ በዓል ፈተናዎችን በፅናትና በትጋት በማለፍ ዳግም ማንሰራራት እንደምንችል የሚያመላክት ታላቅ የተስፋ ምልክት እና ሰብአዊነትንና ልግስናን፣ ቸርነትንና በጎነትን፣ ከራስ አልፎ ለሌሎች መኖርንና ይቅርታን፣ ምህረትንና ደግነትን ያስተምራል።

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሳኤው ለሰው ልጆች ለመዳን የከፈለዉን ታላቅ የደም ዋጋ የሚያሳይ በመሆኑ አርአያነቱን ተከትለን በየፈርጃችን የሚስተዋሉብንን ድክመቶቻችንና ውስንነቶቻችንን በማረም ለላቀ ህዝብ ተጠቃሚነት ተግተን መስራት ይጠበቅብናል፡፡

እኛ ኢትዮጵያዊያን እያገጠሙን ያሉንን ጊዜያዊ ፈተናዎችን በአሸናፊነት ለማለፍ በላቀ የትብብር መንፈስ መንቀሳቀስ ይጠበቅብናል።

ብዙ ከተቀበለ ብዙ ይጠበቃል! ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን በመስቀል ሞት አሳልፎ ሰጥቶ የፍቅሩን ጥልቀት ካሳየን ዛሬ በሀገራችን የተዘራዉን የጥላቻና የከፋፋይ አጀንዳን በመድፈቅ ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትንና እህትማማችነት እሴትን ማጎልበት ይገባል፡፡

ኢትዮጵያ በህብር ያገጠች የብዝሃ ሀይማኖት፣ ባህልና ቋንቋ ባለቤት ናት።

በመሆኑም ይህንን ታላቅ ዕሴት በመጠበቅና በመንከባከብ ከመራራቅ ይልቅ መቀራረብን፣ ከመገፋፋት፣ መደጋገፍንና መተባበርን በማጎልበት ሀገራዊ አንድነታችንን ልናጠናክር ይገባል፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ህይወትን ስላካፈለን እኛም ፈለጉን በመከተል በዓሉን ስናከብር አቅመ ደካሞችን በመንከባከብ፣ የታረዙትን በማልበስና የተራቡትን በማብላት፣ የታመሙትን በመጠየቅና በህግ ጥላ ስር ያሉ ወገኖችን በመጎብኘት እንድታከብሩ አሳስባለሁ።

መልካም የትንሣኤ በዓል።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!

24/04/2025
21/04/2025

ለመላው ክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ/ አደረሰን!

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ሀጢአት ራሱን አሳልፎ በመሰጠት ኋላም ሞትን ድል አድርጎ በመነሳት ፍቅሩን የገለጸበት ፣ለዓለም ሁሉ ብርሃን የወጣበት ታላቅ በዓል ነው።

ትንሳኤንውንም ለማየት ፈጣሪ መራራውን አርብ በጽናት፣በተሰፋና በትዕግስት አልፏል። በኋላም ከሞት በላይ ሆኖ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል።

ሰለሆነም ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ድል እንዳለ ከትንሳኤው ስለተረዳን ከፈተናዎች በላይ ተጉዘን ስኬት በማስመዝብ የኢትዮጵያን ትንሳኤ ለማረጋገጥ ከመቼውም ጊዜ በላይ እጅ ለእጅ ተያይዘን እንነሳ!

በመጨረሻም ይህንን በዓል ስናከብር አብሮነትን የሚያጎለብቱ፣ህብረትን የሚያጠናክሩ የጋራ እሴቶች ላይ በማትኮር፤በመረዳዳትና በመተሳሰብ እንድሆን እየጠየኩ በዓሉ የሰላም የፍቅርና የአብሮነት እንድሆን ከልብ እመኛለሁ።

21/04/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

ሚያዝያ 8/2017 ዓ.ም

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ፤ የክልሉ መንግስት የይቅርታ አዋጁን መስፈርት ላሟሉ 9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ይቅርታ የተደረገላቸው የሕግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩና በሕግ በተደነገገው አግባብ የይቅርታ መስፈርትን ማሟላታቸው በክልሉ መንግስት የይቅርታ ቦርድ ተጣርቶ የቀረቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የሕግ ታራሚዎቹ በመደበኛ የይቅርታ ሕግ እና ሌሎች ተጨማሪ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተብለዉ በልዩ ሁኔታ የቀረቡ፤ በማረሚያ ቆይታቸው ስለመታረማቸውና ስለመታነፃቸው ማረጋገጫ የቀረበላቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በዚሁ መሰረት የይቅርታው ተጠቃሚዎች በይቅርታ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት አዋጅ እና አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ይቅርታ በማያስከለክሉ ወንጀሎች ተሳትፈው፡-

በማረሚያ ቤት የቆዩ፤ በጤና ችግር፤ በዕድሜ መግፋትና ከሕጻናት ጋር አብረዉ የታሰሩ እንዲሁም ከተፈረደባቸው ሲሶ (1/3) እና ከግማሽ (1/2) በላይ የፍርድ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

አክለው ይቅርታው ከተደረገላቸው 9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች መካከል፡- 9 መቶ 85ቱ በሙሉ ይቅርታ ከእስር የሚፈቱ ሲሆን፤ ቀሪ 5 ታራሚዎች የእስራት ጊዜያቸው የተቀነሰላቸው መሆኑን ገልፀዋል።

የይቅርታ ተጠቃሚ ከሆኑት የሕግ ታራሚዎች መካከል 73ቱ ሴቶች ሲሆኑ፤ 9 መቶ 17ቱ ደግሞ ወንዶች መሆናቸውን አመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል በልማት ሊክሱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ህብረተሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በፈፀሙት ጥፋት የተፀፀቱና በአግባቡ ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት መልካምና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

21/04/2025
21/04/2025
21/04/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ፤ የክልሉ መንግስት የይቅርታ አዋጁን መስፈርት ላሟሉ 9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ይቅርታ የተደረገላቸው የሕግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩና በሕግ በተደነገገው አግባብ የይቅርታ መስፈርትን ማሟላታቸው በክልሉ መንግስት የይቅርታ ቦርድ ተጣርቶ የቀረቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የሕግ ታራሚዎቹ በመደበኛ የይቅርታ ሕግ እና ሌሎች ተጨማሪ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተብለዉ በልዩ ሁኔታ የቀረቡ፤ በማረሚያ ቆይታቸው ስለመታረማቸውና ስለመታነፃቸው ማረጋገጫ የቀረበላቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በዚሁ መሰረት የይቅርታው ተጠቃሚዎች በይቅርታ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት አዋጅ እና አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ይቅርታ በማያስከለክሉ ወንጀሎች ተሳትፈው፡-

በማረሚያ ቤት የቆዩ፤ በጤና ችግር፤ በዕድሜ መግፋትና ከሕጻናት ጋር አብረዉ የታሰሩ እንዲሁም ከተፈረደባቸው ሲሶ (1/3) እና ከግማሽ (1/2) በላይ የፍርድ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

አክለው ይቅርታው ከተደረገላቸው 9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች መካከል፡- 9 መቶ 85ቱ በሙሉ ይቅርታ ከእስር የሚፈቱ ሲሆን፤ ቀሪ 5 ታራሚዎች የእስራት ጊዜያቸው የተቀነሰላቸው መሆኑን ገልፀዋል።

የይቅርታ ተጠቃሚ ከሆኑት የሕግ ታራሚዎች መካከል 73ቱ ሴቶች ሲሆኑ፤ 9 መቶ 17ቱ ደግሞ ወንዶች መሆናቸውን አመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል በልማት ሊክሱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ህብረተሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በፈፀሙት ጥፋት የተፀፀቱና በአግባቡ ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት መልካምና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

21/04/2025

Address

Areka

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Muluken Seifu G posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Muluken Seifu G:

Share