Waza Media ዋዛ ሚዲያ

Waza Media ዋዛ ሚዲያ Waza Technology Institute is an organization established to build and play its role in building the future of digital Ethiopia.

🟪እንኳን ደና መጡ የዋዛ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን።


🟪Waza Technology Institute በስሩ የያዛቸው ተቋሞች እና ድርጅቶች
🟣Waza Media (ዋዛ ሚዲያ)
🟣Waza Technology Education (ዋዛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትምህርት)
🟣Waza Digital Technology Work (ዋዛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስራ) It includes comprehensive technology education, quality technology work, and contemporary media.

የለውጡ መንግሥት ውስብስብ ችግሮችን በመፍታት ታላላቅ ሀገራዊ ድሎችን ማስመዝገቡን በብልፅግና ፓርቲ  ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ*************(አሶሳ፣...
13/12/2025

የለውጡ መንግሥት ውስብስብ ችግሮችን በመፍታት ታላላቅ ሀገራዊ ድሎችን ማስመዝገቡን በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ
*************

(አሶሳ፣ታህሳስ 4/2018 ዓ.ም) የለውጡ መንግሥት ውስብስብ ችግሮችን በመፍታት ታላላቅ ሀገራዊ ድሎችን ማስመዝገብ መቻሉን በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መርህ ሀሳብ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ፣ በመደመር መንግስት የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በጠንካራ ህብረ ብሄራዊ አንድነት የተጋመደ ብልፅግናን እንዲያረጋግጥ በርካታ እርምጃዎች መወሰዱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ታላላቅ በረከቶችን ለማጨናገፍ የሚታትሩ ባንዳዎችን በታላላቅ ብስራቶችና ትሩፋቶች ማምከን ተችሏል ብለዋል።

የህዝቡ አብሮነት እና አንድነት እንዲቀጥል በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን የተናገሩት አቶ ፍቃዱ፣ ታሪካዊ ጠላቶችን በጋራ መታገል እንደሚገባም ገልጸዋል።

እንደ ሀገር ውስብስብ ችግሮችን በመቋቋም ታላላቅ ድሎችን ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅሰው፣ መንግስት የህዝቡን ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ በመፍታት ዘላቂ ሰላምና ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየተራ ነው ብለዋል።

የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በመፍጠን፣ መፍጠር እና መዝለል እሳቤ የተቃኘ በማድረግ በጥራትና በፍጥነት እንዲከናወኑ በቅርበት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚያስችሉ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የክረምትና የበጋ ወራት አገልግሎቶችን በማስቀጠል ምርትና ምርታማነት ማሳደግ ያስፈልጋል።

በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፣ ባለፉት ዓመታት በክልሉ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር በዕቅድ የተያዙ መሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ አዳጋች እንደነበር ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ ክልሉን ወደሰላም በመመለስ እና የተገኘውን ሰላም በመጠቀም በርካታ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ለዚህ ስኬት የህብረተሰቡ ድጋፍ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

ከለውጡ ወዲህ ክልሉ ያለውን እምቅ ሀብት በማልማት ህብረተሰቡ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ ኢሳቅ ጠቅሰዋል።

በክልሉ በተለያዩ ከተሞች የኑሮ ውድነት እንዲባባስ በማድረግ እና ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚታትሩ አካላት ከድሪጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባም አቶ ኢሳቅ አስገንዝበዋል።

የሶማሌ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀሊሞ ሀሰን በበኩላቸው፣ መንግስት የህብረተሰቡን አዳጊ ጥያቄዎችን በመለየት ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል ብለዋል።

መንግስት የዜጎችን የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል የጀመረውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ህዝባዊ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው‎*************‎‎አሶሳ፣ ታህሳስ 4/2018 ዓ/ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ት...
13/12/2025

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ህዝባዊ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
‎*************

‎አሶሳ፣ ታህሳስ 4/2018 ዓ/ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች!!" በሚል መርህ ሀሳብ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በአሶሳ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

‎በመድረኩም በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፣ የሶማሌ ክልል ሴቶች ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀሊሞ ሀሰን፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢስሃቅ አብዱልቃድርን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

‎በውይይት መድረኩም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች
‎የተውጣጡ የህዝብ ተወካዮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የወጣቶች ተወካዮች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።



የሰነድ ማረጋገጫንና የምዝገባ አገልግሎትን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ተገልጋዩን ከእንግልት ለማስቀረት እየተሰራ ነው************* (አሶሳ ለታህሳስ:- 03/04/2018 ዓ.ም )‎ የሰነድ ...
12/12/2025

የሰነድ ማረጋገጫንና የምዝገባ አገልግሎትን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ተገልጋዩን ከእንግልት ለማስቀረት እየተሰራ ነው
*************

(አሶሳ ለታህሳስ:- 03/04/2018 ዓ.ም )‎ የሰነድ ማረጋገጫንና የምዝገባ አገልግሎትን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ተገልጋዩን ከእንግልት ለማስቀረት እየተሰራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አስካለች አልቦሮ አስታወቁ።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ DARS ቴክኖሎጂ የኦንላይን አገልግሎትን በይፋ አስጀምሯል።

‎በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አስካለች አልቦሮ እንዳሉት በክልሉ ሲሰጥ የቆየው የሰነድ ማረጋገጥ አገልግሎት ደህንነቱን ባልጠበቀ መልኩ ሲስራ መቆየቱን አስታውሰዋል።

‎ ሆኖም የሰነድ ማረጋገጥና የምዝገባ አገልግሎት ዘመኑን በዋጀ ዲጂታላይዝ በማድረግ ተገልጋዩን ከእንግልት ለማስቀረት እየተሰራ ስለመሆኑን ወይዘሮ አስካል ተናግረዋል።

‎ለስኬታማነቱም የባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲሁም ግብዓት በማሟላት የክትትልና ድጋፍ ስራዎች መስራታቸውንም አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ መሃመድ ሀሚድ በሰነድ ማረጋገጥና ምዝገባ አገልግሎት ላይ የሚስተዋለውን እንግልትና የአሰራር ችግር ለመቅረፍ DARS ቴክኖሎጂ የኦንላይን አገልግሎትን በይፋ መጀመሩን ተናግረዋል።

‎የኢፌዴሪ ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ ኪኒሶ ቀልጣፋ፣ ተዓማኒነቱና ድህነቱ የተረጋገጠ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት ቴክኖሎጂው አይነተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

‎የሀገሪቱ የመረጃ ስርዓት በአንድ ማዕከል መሆኑ ደግሞ ለተለያዩ አገልግሎቶች መሳለጥ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል አቶ ሀሚድ።

‎ተደራሽነቱ ላይም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።

የተቋሙ ሰራተኞች እና የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው ቴክኖሎጂው ሀሰተኛ መረጃን ከማስቀረት ባሻገር ቀልጣፋ፣ ምቹ ጊዜና ጉልበት ቆጣቢ በመሆኑ በሌሎች ተቋማትም መተግበር እንዳለበት ተናግረዋል።

20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በሆሳዕና- አብዮ ኤርሳሞ ስታዲየም
08/12/2025

20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በሆሳዕና- አብዮ ኤርሳሞ ስታዲየም

የ20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል  ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የባህል ቡድን በፎቶ።
08/12/2025

የ20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የባህል ቡድን በፎቶ።

08/12/2025

ቀጥታ ስርጭት 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን

የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን አዘጋጅ የሆነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል  ያበረከተው ልዩ ሽልማት ክቡር ፕረዚዳንት አቶ አሻዲል ሀሰን ...
07/12/2025

የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን አዘጋጅ የሆነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያበረከተው ልዩ ሽልማት ክቡር ፕረዚዳንት አቶ አሻዲል ሀሰን ተረክበዋል።

በ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል ዋዜማ የተዘጋጀ የእራት ግብዣ እና የእውቅና መርሃ-ግብር በመካሄድ ላይ ነው። *************በ20ኛው የኢትዮጵያ ...
07/12/2025

በ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል ዋዜማ የተዘጋጀ የእራት ግብዣ እና የእውቅና መርሃ-ግብር በመካሄድ ላይ ነው።
*************

በ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል ዋዜማ የተዘጋጀ የእራት ግብዣ እና የእውቅና መርሃ-ግብር በመካሄድ ላይ ነው። በመረሀ ግብሩም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ር/መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሀሰን፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ ወ/ሮ አስካለ አልቦሮ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በዝግጅቱ ላይ ታድመዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት መቀመጫ የሆነችው ሆሳዕና "ዴሞክራሲያዊ መግባባት፣ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ለማክበር ዝግጅቷን አጠናቅቃ ዋዜማው ላይ ተገኝታለች።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የባህላዊ ቡድን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል የዋዜማ ድባብ ላይ በሆሳዕና
07/12/2025

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የባህላዊ ቡድን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል የዋዜማ ድባብ ላይ በሆሳዕና

የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል የዋዜማ ድባብ በሆሳዕና (በምሥል)፦
07/12/2025

የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል የዋዜማ ድባብ በሆሳዕና (በምሥል)፦

‎በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ መገንባት የሁሉም ድርሻ ሊሆን ይገባል፦ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ‎************‎‎(አሶሳ፣ ኅዳር 26/2018 ዓ/ም) ሙስናን ...
05/12/2025

‎በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ መገንባት የሁሉም ድርሻ ሊሆን ይገባል፦ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ
‎************

‎(አሶሳ፣ ኅዳር 26/2018 ዓ/ም) ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ በመገንባት የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የሁሉም ድርሻ ሊሆን እንደሚገባ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ገለጹ።

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል "ትውልድን በስነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በዓለማቀፍ ደረጃ 22ኛው፣ በኢትዮጵያ ደግሞ 21ኛው የጸረ-ሙስና ቀን በክልል ደረጃ ዛሬ በፓናል ውይይት ተከብሯል።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ‎ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፣ የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ መገንባት ወሳኝ ተግባር ነው ብለዋል።

‎ለዚህም ትውልዱን ከታች ጀምሮ በስነ-ምግባር ማነጽ የሁሉም ድርሻ መሆኑን ተናግረዋል።

‎የመንግሥት ተቋማት ተጋልጋዮችን ከማጉላላት እና ከእጅ መንሻ የጸዳ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አሰራር ዘርግተው ሊሰሩ እንደሚገባ አስረድተዋል።

‎በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ ሙስናን ሙስናና ብልሹ አሰራርን ከመጸየፍ ባለፈ ተግባሩን ማጋለጥ እና ተገቢ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባም ወ/ሮ አስካለች ገልጸዋል።

‎የክልሉ ስነ-ምግባር እና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ከማል ሀሰን፣ ሙስና በዓለማቀፍ ደረጃ ልማት እና ብልጽግና እንዳይረጋገጥ ቀደሚ ስጋት መሆኑን አንስተዋል።

‎ሙስናና ብልሹ አሰራር የሚፈጸምበት መንገድ ውስብስብ እና ድብቅ በመሆኑ በአንድ ተቋም ብቻ ለውጥ ማምጣት አስቸጋሪ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፣ በጸረ-ሙስና ትግል ውስጥ ሁሉም በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

‎የጸረ-ሙስና ቀንን ከማክበር ባለፈ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ እና የተቋማትን አገልግሎት በማሻሻል ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት ባለድርሻ አካላት የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Asosa

Website

https://www.edu.wazatechinstitute.com/, https://www.media.wazatechinstitute.com/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Waza Media ዋዛ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Waza Media ዋዛ ሚዲያ:

Share

Category