Waza Media ዋዛ ሚዲያ

Waza Media ዋዛ ሚዲያ Waza Technology Institute is an organization established to build and play its role in building the future of digital Ethiopia.

🟪እንኳን ደና መጡ የዋዛ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን።


🟪Waza Technology Institute በስሩ የያዛቸው ተቋሞች እና ድርጅቶች
🟣Waza Media (ዋዛ ሚዲያ)
🟣Waza Technology Education (ዋዛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትምህርት)
🟣Waza Digital Technology Work (ዋዛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስራ) It includes comprehensive technology education, quality technology work, and contemporary media.

የቦሮ ህዝቦች ታሪክና ትውፊት ላይ መሰረት ያደረገ በደራሲ አመንቴ ገሺ የተሰናዳ “ቦር-ዘኢትዮጵያ” የተሰኘ መፅሐፍ በአሶሳ ከተማ ተመረቀ፡፡ በምርቃ ስነ-ስርዓቱ የቦሮ ሽናሻ ልማት ማህበር ቦ...
01/11/2025

የቦሮ ህዝቦች ታሪክና ትውፊት ላይ መሰረት ያደረገ በደራሲ አመንቴ ገሺ የተሰናዳ “ቦር-ዘኢትዮጵያ” የተሰኘ መፅሐፍ በአሶሳ ከተማ ተመረቀ፡፡

በምርቃ ስነ-ስርዓቱ የቦሮ ሽናሻ ልማት ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገብረሚካኤል ጉድሬ እንዳሉት “ቦር-ዘኢትዮጵያ” የተሰኘ መፅሐፍ የቦሮ ህዝቦች የረጅም ዘመን ታሪክና ትውፊትን የሚያወሳ የምርምር ሰነድ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ታሪክን በትክልል ሰንዶ ለትውልድ ማሳወቅ፣ ማስቀመጥና ማስተላለፍ ለአንድ ህዝብ ብሎም ለሀገር ያለው አበርክቶው የላቀ መሆኑን ገልፀው የመፅሐፉ ደራሲ አመንቴ በቀጣይ መሰል የምርምር ስራዎችን ለሚሰሩ አካላት ስንቅ ይሆናቸዋልም ብለዋል፡፡

የመፅሐፉ ደራሲ አመንቴ ገሺ እንደሚሉት የቦር-ዘኢትዮጵያ መፅሐፍ ዓመታትን የጠየቀ የምርምር ስራ ውጤት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በታሪክ ሰነዶች እና በተለያዩ መዛግብቶች ፍተሻና ከብሔረሰቡ ታላላቅ አባቶች ጋር በተደረገ ቃለ-መጠይቅን መነሻ አድርጎ የተሰናደ የምርምር ሰነድ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

ይህ በቦሮ ህዝቦች ላይ የሚያተኩረው የታሪክና የትውፊት መፅሐፍ የምርምር ሂደቱ ቀጣይነት ባላቸው ሁለት ቅፆች ምሉዕነቱ እንደሚረጋገጥም ፀሐፊው ጠቁመዋል፡፡

ለመፅሐፉ እውን መሆን አበርክቶ ለነበራቸው አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በመፅሐፉ ዙሪያ ዳሰሳዊ እይታቸውን ያቀረቡ አካላት በበኩላቸው ደራሲው ያካሄደው ዓመታትን የተሻገረ የምርምር ሂደት የሚደነቅ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ታሪካዊና ትውፊታዊ ሰነዱ በቀጣይ መሰል ስራዎችን ለሚሰሩ አካላት መነሻ እንደሚሆንም አስረድተዋል፡፡

በቦሮ ህዝቦች ዘንድ የነበረውን በታሪክ ተውልዱ በልኩ እንዲያውቅ የሚያስችል ሰነድ ነው ያሉት ደግሞ የመፅሐፉ ምርቃ ስነ-ስርዓቱ ታዳሚያን ናቸው፡፡

መፅሐፉ በ288 ገፆች የተከተበ ሲሆን በ4 መቶ 95 ብር ገበያ ላይ ውሏል፡፡

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የተሰጠ መግለጫ******** ከመስከረም 1/2018 /ዓ.ም ጀምሮ ለመንግስት ሰራተኞች የተፈቀደው የደመወዝ ማሻሻያ ተግባራዊ እንዲሆን በክልሉ መንግ...
31/10/2025

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የተሰጠ መግለጫ
********

ከመስከረም 1/2018 /ዓ.ም ጀምሮ ለመንግስት ሰራተኞች የተፈቀደው የደመወዝ ማሻሻያ ተግባራዊ እንዲሆን በክልሉ መንግስት ውሳኔ መተላለፉ ይታወቃል፡፡

ይህንን ተከትሎ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ከክልሉ ፋይናስ ቢሮ ጋር በመተባበር ከክልል እስከ ወረዳ ላሉ ተቋማት ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች በአዲሱ የደመወዝ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ግንዘቤ በመፍጠር የደመወዝ ኮንቨርሽኑ እንዲሰራ አድርጓል፡፡

ይሁን እንጂ በተሰራው የደመወዝ ኮንቨርሽን መሰረት አንዳንድ ተቋማት ለሰራተኞቹ ደብዳቤ ያደረሱ ቢሆንም ክፍያውን ተግባራዊ ለማድረግ የፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር የፈቀደው የ10 ወር በጀት ከክልሉ የመንግስት ሰራተኞች ቁጥር አንጻር ሲታይ በቂ ባለመሆኑ እና ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጉድለት(እጥረት) ያስከተለ መሆኑን ከክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በዚህ መሰረት በቅርቡ በነበረው የብልጽግና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የክልል ፕሬዘዳንቶች፣ ከገንዘብ ሚኒስትር እና ከፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነሩ ጋር በነበረው የጋራ መድረክ ጉድለቱ የክልላችን ብቻ ሳይሆን በሌሎች ክልሎችም ያጋጠመ በመሆኑ ጥያቄው በጋራ ተነስቶ የበጀት ጉድለት ያጋጠማቸው ክልሎች የበጀት ልዩነቱ የተፈጠረው በመረጃ ክፍተት መሆንና አለመሆኑን እንዲሁም በክልሉ ወይም በፌደራል ደረጃ ስለመሆኑ የልዩነቱን ምክንያት እንደገና አጣርተን ለውሳኔ እንዲቀርብ በቀጥታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

በመሆኑም የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ እያንዳንዱ ሴክተር መ/ቤት ሰርቶ ያቀረበውን ኮንቨርሽን በድጋሚ የማጣራት ስራ እየሰራ ስለሆነ ውጤቱ እስከሚታወቅ ድረስ በክልል የሚገኙ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች በማህበራዊ ሚዲያ ከሚናፈሱ አሉባልታዎች እራሳቸውን በመቆጠብ አፈጻጸሙን በትዕግስት እንዲጠባበቁ በማሳሰብ መረጃው ተጣርቶ ሲታወቅ እና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ በጀቱን ለእያንዳንዱ ባለ በጀት መ/ቤት ሲያሳውቅ ክፍያ የሚፈጸም ይሆናል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ
ጥቅት 21/01/2018 ዓ.ም
አሶሳ

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ‎*************‎‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
27/10/2025

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ
‎*************

‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሥራ ኃላፊዎችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

‎አቶ አሻድሊ ሀሰን ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በነበራቸው ቆይታም በተለይም በጥቃቅና አንስተኛ ዘርፍ ለተደራጁ ማህበራት ባንኩ ቅድሚያ በመስጠት የብድር አቅርቦቶችን ለማሻሻል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በሰፊው መክረዋል።

‎የክልሉ መንግሥት የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚያደርገው ጥረት ባንኩ የተሻለ የብድር አማራጭ እና አቅርቦትን እንዲያመቻች አቶ አሻድሊ ጠይቀዋል።

‎የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ ባንኩ በክልሉ ሁለንተናዊ ልማት እድገት ውስጥ አስፈላጊ የብድር አቅርቦቶችን እንደሚያመቻች ገልጸዋል።

‎የክልሉ መንግሥት ሰላምን በማጽናት ውጤታማ የልማት እና የመልካም አስተዳድር ሥራዎችን ማከናወኑን ርዕሰ መስተዳድር  አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ‎*****‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም) ...
27/10/2025

‎የክልሉ መንግሥት ሰላምን በማጽናት ውጤታማ የልማት እና የመልካም አስተዳድር ሥራዎችን ማከናወኑን ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ
‎*****

(አሶሳ፣ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም) ‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ሰላምን በማጽናት ውጤታማ የልማት እና የመልካም አስተዳድር ሥራዎችን ማከናወኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

‎የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት ባለፉት ወራት በፀጥታው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን ገምግሟል።

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በዚሁ ወቅት፣ የክልሉ መንግሥት የተገኘውን ሰላም ከማጽናት ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት እና የመልካም አስተዳድር ሥራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል።

‎በክልሉ የፀጥታ አካላት በከፈሉት ከፍተኛ መስዋዕትነት በአሁኑ ወቅት አንፃራዊ ሰላም መኖሩን አቶ አሻድሊ ተናግረዋል።

‎የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ታላላቅ ሀገራዊና ክልላዊ ፕሮጀክቶች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ግንባታቸው መጠናቀቅ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

‎የተመዘገበውን ሰላም ተከትሎ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ ሌሎች የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አበረታች ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

‎የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የበለጠ ለማስቀጠል እየተከናወኑ የሚገኙ ህዝቡን ያሳተፉ የሰላም ግንባታ ስራዎችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

‎የክልሉን እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን ወደ ልማት ለመቀየር እየተሠራ ነው ያሉት አቶ አሻድሊ፣ ለዚህም የተገኘውን ሰላምን በጋራ ማጽናት እንደሚጠበቅ አንስተዋል።

‎በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጄር ጀኔራል አማረ ባህታ፣ ሰራዊቱ በቀጠናው የተሰጠውን ሀገራዊ ግዳጅ በብቃት እየመራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

‎የክልሉ መንግስት ሰላም እንዲሰፍን ውስጣዊ ችግሮችን በራስ አቅም ለመፍታት ያሳየው ቁርጠኝነት ለሰራዊቱ ጉልበት ከመሆኑም በተጨማሪ ለሌሎች አካባቢዎች ተምሳሌት የሚሆን ነው ብለዋል።

‎ህዝቡ በሰላም ገብቶ እንዲወጣ እና የልማት ስራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ የተቀናጀ የሰላም ማስከበር ተግባራትን ማከናወን እንደሚገባ ሜጄር ጄኔራሉ ጠቁመዋል።

ለአቅመ ደካሞች እየተደረገ ያለው ድጋፍ የኢትዮጵያዊያንን የመረዳዳት ባህል አጉልቶ ያሳያል - ወ/ሪት ምስኪያ አብደላ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሐላፊ****(አሶሳ፣ ጥቅምት...
25/10/2025

ለአቅመ ደካሞች እየተደረገ ያለው ድጋፍ የኢትዮጵያዊያንን የመረዳዳት ባህል አጉልቶ ያሳያል - ወ/ሪት ምስኪያ አብደላ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሐላፊ

****

(አሶሳ፣ ጥቅምት 15/2017 ዓ/ም) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በሸርቆሌ ወረዳ በክረምት በጎ ፈቃድ ስራ ለሁለት አቅመ ደካመ ቤተሰቦች ያስገነባውን መኖርያ ቤት አጠናቅቆ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የወረዳው ዋና አፈ ጉባዔ ጨምሮ የወረዳ ካቢኔ አባላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዛሬው ዕለት የቤቶችን ቁልፍ ርክክብ አካሂዷል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወ/ሪት ምስኪያ አብደላ ለአቅመ ደካሞች እየተደረገ ያለው ድጋፍ የኢትዮጵያዊያንን የመረዳዳት ባህልን አጉልቶ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረው የመረዳዳት ባህሉ ጊዜና ሁኔታ ሳይገድበው ተጠናክሮ መቀጠል አለበትም ብለዋል ።

አቅመ ደካሞችን መደገፍና ዜጎች የተቀራረበ ኑሮ እንዲኖራቸው የማስቻል ሥራ ከክረምት በጎ ፍቃድ ስራ አንዱ መሆኑን የተናገሩት የቢሮ ሐላፊዋ አቅመ ደካሞችን መርዳት ቀጣይነት ያለው እንዲሆንና በአስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ ከተረጂዎች ጎን መቆም እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።

ለቤት ግንባታው አስተዋጽኦ ላበረከቱ የተቋሙ ሰራተኞች፣ ለሸርቆሌ ወረዳ መንግስትና ህዝብ፣ በገንዘብም ሆነ በአይነት ድጋፍ ላደርጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይም በሚደረገው የበጎ ፍቃድ ስራ በመሳተፍ የድርሻቸውን እንዲወጡ የቢሮ ሐላፊዋ ጠይቀዋል።

የሸርቆሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰማኒ ሀሰን በሀገር ደረጃ የሚካሄዱ የክረምት በጎ-ፈቃድ አገልግሎት ሁሉም ኢትዮጵያዊ እርስበርስ በመደጋገፍና በመተባበር ለሌሎችም በጎ ገጽታችንን ለማሳየት ትልቅ እድል የፈጠረ ነዉም ብለዋል።

በሸርቆሌ ወረዳ ቤት ተገንብቶላቸው ቁልፍ የተረከቡ አቅመ ደካሞቹ ከዚህ በፊት በአስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ እንደነበርና አሁን በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የቤት ግንባታ የተደረገላቸው አቅመ ደካማ ቤተሰቦችም አክለው ለመፍረስ የተቃረቡ ቤቶች ወጥተው ወደ አዲስ ቤት መግባት በመቻላቸው የላቀ ደስታ እንደተሰማቸው ገልፀው ለተደረገላቸው ድጋፍ ቢሮውን አመስግነዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኤክስፖርት የሚደረጉ ምርቶች በስፋት እየተመረቱ ነው።በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017/18 ምርት ዘመን የመኸር ወቅት ከ289 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በቅባት እህል...
23/10/2025

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኤክስፖርት የሚደረጉ ምርቶች በስፋት እየተመረቱ ነው።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017/18 ምርት ዘመን የመኸር ወቅት ከ289 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በቅባት እህል ተሸፍኗል።

በምርት ዘመኑ የመኸር ወቅት በ1 ነጥብ 56 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ዕየለሙ ሲሆን ወቅታዊ የሰብል ቁመናቸውም በጥሩ ደረጃ ላይ ይገኛል።

በዘር ከተሸፈነው ሰብል ውስጥም 177 ሺህ 149 ሄክታር መሬት በሰሊጥ፣ 124 ሺህ 538 ሄክታር በአኩሪአተር እንዲሁም 81 ሺህ 470 ሄክታር መሬት ላይ ኦቾሎኒ/ለውዝ እየለማ ይገኛል፡፡

በክልሉ የቅባት እህል ምርታማነትን ለማሳደግ በኩታ-ገጠም (ክላስተር) ማልማት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ሲሆን ይህም እንደሀገር የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በማምጣት ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መካሄድ ጀመረ‎********************‎‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም) በቤኒሻ...
22/10/2025

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መካሄድ ጀመረ
‎********************

‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአስፈፃሚ አካላት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መካሄድ ጀምሯል።

‎የክልሉ የአስፈጻሚ አካላት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።

‎የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በመድረኩ ማስጀመሪያ እንደገለጹት፣ በ2018 በጀት ዓመት ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማትና የመልካም አስተዳድር ዕቅዶች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው።

‎በመጀመሪያ ሩብ ዓመት በመኸር እርሻ፣ በማዕድን፣ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በንቅናቄ ሥራዎች የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡን ተናግረዋል።

‎የአፈጻጸም ግምገማው በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የታዩ ጥሩ አፈጻጸሞችን በላቀ ሁኔታ በማስቀጠል ውስንነቶችን ደግሞ ለማረም ያግዛል ብለዋል።

‎የሩብ ዓመቱን አፈጻጸም በመገምገም በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት አቅጣጫ የሚቀመጥበት መሆኑንም አቶ አሻድሊ ገልጸዋል።

‎የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ቃሲም ኢብራሂም፣ በክልሉ በበጀት ዓመቱ በተለዩ 12 ዋና ዋና የትኩረት መስኮችን ለመፈጸም እየሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በተለያዩ ዘርፎች አበረታች አፈጻጸም መመዝገቡን ተናግረዋል።




በክልሉ 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው፡- የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ********************...
21/10/2025

በክልሉ 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው፡- የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ
**************************

(አሶሳ፣ ጥቅምት 11/2018 ዓ/ም) ‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ተናገሩ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ጽ/ቤት የበዓሉን አከባበር አስመልክቶ ከበዓሉ ዐቢይ ኮሚቴ፣ ከብሔረሰብ ምክር ቤቶች እና በየደረጃው ከሚገኙ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች እንዲሁም የኮሙኒኬሽን አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ በዚሁ ወቅት፣ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ሲከበር መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡

የዘንድሮውን 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን በልዩ ድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረው፣ ክልላዊ ዐቢይ እና ንኡሳን ኮሚቴዎች ተቋቁመው ወደሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

‎በዓሉን ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ማክበር ይገባል ያሉት ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፣ ለዚህም ሁሉም የባለቤትነት ድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

‎የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓልን ትልልቅ ስኬቶችን ካገኘንብት ማግስት መከበሩ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸው፣ በክልሉ በየደረጃው ያለውን የበዓል አከባበር ሂደት በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ማጀብ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መለሰ ኪዊ፣ በክልሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል በሁሉም አካባቢዎች እንደሚከበር ጠቁመው፣ በክልል ደረጃ በካማሺ ከተማ እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡

‎የበዓሉን ሂደት በሚዲያ ማጀብ መረጃዎችን በወቅቱ ለሕዝቡ ማድረስ እንደሚገባም አቶ መለሰ ተናግረዋል፡፡
‌‎
የዘንድሮው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን “ዴሞክራሴያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ከተማ በድምቀት እንደሚከበር ዐቢይ ኮሚቴው አስታውቋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ገለጹ*****...
20/10/2025

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ገለጹ
**************************

(አሶሳ፣ ጥቅምት 10/2018 ዓ/ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ ገለጹ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወካዮች በተመረጡባቸው የምርጫ አካባቢዎች ባካሄዷቸው የውይይት መድረኮች በተነሱ የሕዝብ ጥያቄዎች ዙሪያ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሂዷል።

‎የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙባረክ ኤልያስ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ወደ ተመረጡባቸው አከባቢዎች በመውረድ ባደረጉት የመራጭ ተመራጭ ውይይት ከህዝቡ የተነሱ ጥያቄዎችን የተመለከተ ሪፖርት አቅርበዋል።

‎በክልሉ በተለያዩ ወረዳዎች በ102 ቀበሌዎች 51 ሺህ 537 ሕዝብ ተሳተፈባቸው ውይይቶች መካሄዳቸውን ጠቁመው፣ የተለያዩ የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄዎች መነሳታቸውን ተናግረዋል።

‎ክልሉ ከነበረበት የጸጥታ ችግር ወጥቶ ወደሰላም በመመለስ በተለያዩ አካባቢዎች የሕዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ አበረታች የልማት ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

‎የመንገድ፣ የመብራት፣ የኔትወርክ፣ የመድኃኒት አቅርቦት ጥያቄዎች ከሕዝቡ መነሳታቸውን የተናገሩት አቶ ሙባረክ፣ የክልሉ መንግስት በህብረተሰቡ ዘንድ የሚጠየቁ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ እየሰራ ያለውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

በፌዴራል መንግሥት የሚከናወኑ የመንገድ ፕሮጀክቶች መጓተት ትልቁ የሕዝቡ ጥያቄ መሆኑን ጠቅሰው፣ በፌዴራል መንግሥት የሚመለሱ ጥያቄዎች እንዲመለሱ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ጠቅሰዋል።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ፣ በክልሉ የሚገኙ ዕድሎችን በመጠቀም እየተከናወኑ በሚገኙ ሥራዎች ትልልቅ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል።

‎የክልሉ መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄዎች መሠረት ያደረጉ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በየደረጃው በተካሄዱ ውይይቶች የተነሱ ቀሪ የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ ደግሞ በቀጣይ የእቅድ አካል በማድረግ የተቀናጀ ጥረት ሊደረግ እንደሚገባም ወ/ሮ አስካለች ተናግረዋል፡፡

የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው፣ የክልሉ መንግስት በክልሉ አቅም የሚመለሱ የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄዎችን ለመመለስ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰው፣ በቀጣይም ጥረቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

በክልሉ አሁን የተፈጠረውን ሠላም በመጠቀም በፌዴራል መንግስት የተያዙ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንዲከናወኑ ከትትሉ ሊጠናከር እንደሚገባም አንስተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት...
19/10/2025

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡

ዋዛ ሚዲያ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል፡፡

‎በክልሉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጸጋዎችን በማልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው፦አቶ አሻድሊ ሀሰን‎**********‎‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
18/10/2025

‎በክልሉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጸጋዎችን በማልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው፦አቶ አሻድሊ ሀሰን
‎**********

‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጸጋዎችን በማልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

‎በክልሉ የሚገኙ ጸጋዎችን በማልማት በኢኮኖሚ የጎለበተ ጠንካራ ክልል ለመገንባት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፥ በክልሉ ከለውጡ ወዲህ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋግጡ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መከናወኑን ተናግረዋል።

‎የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ክልሉን በፈይናንስ አቅም ማጎልበት ይገባል ያሉት አቶ አሻድሊ፣ ለዚህም ፀጋዎችን በአግባቡ ማልማትና ማስተዳደር ይገባል ብለዋል።

‎የቁጠባ ባህልን በማሳደግ በኢኮኖሚ አቅሙ የዳበረ ህብረተሰብን ለመፍጠር አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባም አቶ አሻድሊ ገልጸዋል።

‎በክልሉ የተገኙትን እምርታዎች ማስቀጠል ይገባል ያሉት አቶ አሻድሊ፣ በክልሉ ሁለንተናዊ ማንሰራራትና ብልፅግና እየታየ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል።

‎የመንግስት የልማት ድርጅቶችን በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ የክልሉን ህዝብ ህይወት በዘላቂነት ሊቀይሩ እንዲችሉም በትኩረት መስራት ያስፈልጋል።

‎ፈጠራና ፈጥነት የታከለበት አገልግሎት በመስጠት ህብረተሰቡ የሚያነሳቸው የልማት ጥያቄዎች ለመፍታት እንደሚሰራም አቶ አሻድሊ ሀሰን ጠቁመዋል።

‎በቆሎን በኩታ-ገጠም በቤንሻንጉል ጉሙዝ‎ ‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለግብርና ተስማሚ የአየር ንብረት፣ የከርሰ ምድር ውሃ እና ዝናብን ጨምሮ ለም የሆነ አፈር ያለውና ማንኛውንም አይነት ሰብ...
16/10/2025

‎በቆሎን በኩታ-ገጠም በቤንሻንጉል ጉሙዝ


‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለግብርና ተስማሚ የአየር ንብረት፣ የከርሰ ምድር ውሃ እና ዝናብን ጨምሮ ለም የሆነ አፈር ያለውና ማንኛውንም አይነት ሰብል ማምረት የሚችል ክልል ነው።

‎በክልሉ ለግብርና በተሰጠው ትኩረት የማምረት አቅሙን በማጠናከር የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተለያዩ የሰብል አይነቶችን በኩታ-ገጠም (ክላስተር) በማምረት ላይ ይገኛል።

‎በ2017/2018 የምርት ዘመን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ211 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በቆሎ በኩታ-ገጠም (ክላስተር) ለምቷል።

‎(ምስል፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን አብራሞ ወረዳ በኩታ-ገጠም (ክላስተር) እየለማ የሚገኝ የበቆሎ ሰብል አሁናዊ ገጽታ)

Address

Asosa

Website

https://www.edu.wazatechinstitute.com/, https://www.media.wazatechinstitute.com/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Waza Media ዋዛ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Waza Media ዋዛ ሚዲያ:

Share

Category