Sidama federation

Sidama federation !!
!

05/07/2025
የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ እና የክለቡ የደጋፊዎች ማህበር በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋልሰኔ 28/2017 የሲዳማ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ እና ...
05/07/2025

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ እና የክለቡ የደጋፊዎች ማህበር በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል

ሰኔ 28/2017 የሲዳማ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ እና የክለቡ የደጋፊዎች ማህበር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሰጠዉን ዉሳኔ አስመልክቶ በጣምራ መግለጫ ሰጥተዋል።

መግለጫ የሰጡት የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጃጎ አገኘሁ እንደገለፁት የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ሰኔ 1/2017ዓ.ም የመላዉ ኢትዮጵያ ጨዋታ በግልፅ ተጫዉቶ በማሸነፍ ዋንጫ ስቀበል በወቅቱ የቀረቡ ቅሬታዎች አለመኖሩን ተናግረዋል።

ቦርዱ የተሰጠዉን ዉሳኔ አምርሮ የሚቃወም መሆኑንና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሰጠውን ዉሳኔ ዳግም እንዲያጠን አሳስበዋል።የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ ፍትህ ፍለጋ አስፈላጊውን ሁሉ አድርጎ ሁሉንም ህጋዊ የፍትህ አማራጮችን ለመጠቀም ዝግጁ መሆኑንም አቶ ጃጎ አገኘሁ አስረድተዋል።

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ አባል አቶ ወሰንየለህ ስምዖን በበኩላቸውየኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሰጠዉ ዉሳኔ ትክክል እንዳልሆነ ገልፀዉ በጨዋታዉ ላይ ምንም አይነት ቅሬታ ባልቀረበበት የተሰጠዉ ዉሳኔ የክለቡን ስነልቦና ለመስበርና የስፖርት ቤተሰብን በመናቅ የተሰጠ ዉሳኔ ስለሚመስል ዉሳኔዉ እንደገና መጤን አለበት ብለዋል።
አክለዉም ህብረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ በሀሰተኛ ወሬዎች መደናገር እንደለለበትና ሚዲያዎችም ለህብረተሰቡ ትክክለኛውን መረጃ ማስተላለፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የሲዳማ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነርና የክለቡ የቦርድ አባል አቶ ፍረዉ አሬራ በበኩላቸዉ ውሳነዉ የስፖርት ቤተሰቦችን ቅር የሚያሰኝ በመሆኑ ዳግም ማጤን እንዳለበት አሳስበዋል።

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ደጄነ ማርቆስ ስናገሩ ከዓመታት ዝጅት በኋላ የተገኘ ዉጤት በመሆኑ ህጋዊ ህደቶችን ተከትለን እስከ መከመጨረሻዉ ታግለን መብታችን ለማሰከበር ዝግጁ ነን ብለዋል።
በአጠቃላይ ወጥነት የጎደለዉና ቀድሞ አሳውቆ ጉዳቶችና ስብራቶች እንዳይኖሩ ከመከላከል ጋር በተያያዘ ሰፊ ክፍተት ያለው በመሆኑ መታረም እንዳለበት ቦርዱና የደጋፊ ማህበሩ በጋራ አሳስበዋል።

ለበለጠ መረጃ
➚ድረ ገጽ፦ https://sidamanrsps.gov.et
➚ፌስቡክ፡- Sidama National Regional State Communication Affairs Bureau
➚ዩትዩብ፦https://youtube.com/.bureau?si=r5EAWg8x4kXmLqQN
➚WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VadMPA2DDmFbMwfTjG3l
➚ቴሌግራም፦ https://t.me/SidamaCommunicationbureau

⚠️ FIFA Rules on Competition Integrity and Title OwnershipFIFA strictly prohibits the transfer of competition titles, cu...
03/07/2025

⚠️ FIFA Rules on Competition Integrity and Title Ownership

FIFA strictly prohibits the transfer of competition titles, cups, or trophies between clubs outside of sporting results. Here's why such actions are not recognized and may lead to sanctions:

⚖️ 1. Integrity of Competitions

According to Article 18 of the FIFA Statutes:

“Leagues and clubs must ensure that all matches and competitions are played in accordance with the principles of fair play, integrity, and sporting merit.”

🔒 This means:

Titles can only be won through official match results.

Clubs cannot donate, transfer, or assign league trophies to other clubs by agreement or symbolism.

🏛 2. National Associations Must Uphold Integrity

Each national football federation (e.g., the Ethiopian Football Federation – EFF) is mandated by FIFA to:

Operate independently, without political or emotional interference.

Enforce that titles and trophies are awarded only based on match outcomes.

Reject symbolic gestures that undermine competition fairness or statistical accuracy.

📚 3. Historical Record and Recognition

FIFA, CAF, and national federations:

Only recognize the team that officially won on the field.

Will not register any symbolic "title transfer" in historical records.

Maintain a strict database of winners based on sporting results.

📌 Example:
If Club A wins the league but later announces that they are "giving the trophy" to Club B, only Club A will remain the official champion.

🟥 4. Potential Violations

Such actions may constitute:

Bringing the game into disrepute

Sporting fraud or manipulation

Violation of Article 27 (FIFA Code of Ethics)

Undermining the authority of the federation

FIFA or CAF may launch an integrity investigation and impose:

Warnings or fines

Suspensions

Disqualification of clubs or officials

🔍 Enforcement Example:

If the EFF were to recognize a symbolic "trophy transfer" between clubs, it could trigger:

Review by CAF and FIFA

Questions of impartiality and

 # 👇   ከውሳኔው በኋላ አሱ በሚመራበት ሀገር ላይ የተለያዩ ጨዋታዎችን ሲያደርጉና በተለይ በተለይ እራሱ በሜዳ ሄዶ የታደመበትና በመጨረሻም በራሱ እውቅና ሰጥቶ ዋንጫና ሜዳሊያ በሸለመበት ...
02/07/2025

# 👇

ከውሳኔው በኋላ አሱ በሚመራበት ሀገር ላይ የተለያዩ ጨዋታዎችን ሲያደርጉና በተለይ በተለይ እራሱ በሜዳ ሄዶ የታደመበትና በመጨረሻም በራሱ እውቅና ሰጥቶ ዋንጫና ሜዳሊያ በሸለመበት ጉዳይ ላይ ዋንጫ ከተወሰደ ከሳምንታት በኋላ ወደኋላ በመሄድ ጨዋታዎችንና በራሱ የሰጠውን ዋንጫ የሚነጥቅ ውሳኔ የሰጠው በፊፋ አሰራርና ህግ መሠረት ስነስረዓታዊ ፍትህ ወይም procedural justice የጣሰ መሆኑንና የስፖርት ግልግል ፍ/ቤት ወይም ውድቅ ያደረገባቸው የተለያዩ ኬዞች አሉ👇👇👇

1. በ2001 GC, ፋይል ቁጥር CAS 2001/A/317 AEK Athens SK Slavia Prague V. UEFA
የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) መጀመሪያ ጨዋታው ሲካሄድ ዝም ብሎ አጫውተው በኋላ ላይ የተቀጡ ተጨዋቾች በመሳተፋቸው ምክንያት ውጤቱን የሰረዘበት ጉዳይ ወደ ቀርቦ የግልግል ፍ/ቤቱ ቃል በቃል ሲተረጎም:
"UEFA ከጨዋታው በፊት በመጀመሪያ እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው መጫወት የሌለባቸውን ተጫዋቾችን ካጫወተ በኋላ ውጤቱን ውድቅ ማድረጉ የስነስረዓት ፍትሃዊነትን ወይም procedural fairness የጣሰ ነው የUEFA ውሳኔ ብሎ ውድቅ አድርጎበታል።

☝️ ነው።

2. በ2005, ፋይል ቁጥር CAS 2005/A/983&984 Maccabi Haifa V. UEFA ላይ EUFA ማካቢ የተባለ ተጨዋች መጫወት የለሌበትን የተለያዩ ጨዋታ ከተጫወተ በኋላ UEFA ዝም ብሎ ቆይቶ በኋላ ወደኋላ የወሰነውን ውሳኔ ውድቅ ያደገበት ነው። የእስፖርት የግልግል ፍ/ቤቱ ወይም CAS ውድቅ ያደረገበት ምክንያት አንደ ጨዋታው እንዲቀጥል የለቀቀው ወደኋላ ሄዶ ውድቅ ማድረግ ተገማችነትንና የስነስረዓታዊ ፍትህ የሚቃረን ነው በሚል ነው።

3.2010 ላይ ስሙ ያልተጠቀሰ ክለብ እና የሆነ ሀገር ፌደሬሽን ጋር በተደረገው ክርክር ፋይል ቁጥር CAS 2010/A/2187 ላይ ፌደሬሽኑ የሆነ ክለብ የተቀጡ ተጫዋቾችን ሲያጫውት እያየ ከቆየ በኋላ በሆነ ጊዜ የክለቡን ውጤት ውድቅ ያደረገበት ሲሆን, CAS "ፌደሬሽኑ ግራ ማጋባት ሂደት ውስጥ የራሱ አስተዋፆ ስላለው ውድቅ ማድረጉ ተገቢ አይደለም ብሎ ወስኗል። ቃል በቃል "Federation contributed to the confusion" በሚል ውድቅ አድርጎበታል።

4. በ2008, ፋይል ቁጥር CAS 2008/A/1583፣ Danilov v. Football Association of Serbia ጉዳይ ላይም የግልግል ፍ/ቤቱ ማህበሩ ከራሱ ድርጊት ጋር የሚጋጭ ተመሳሳይ ውሳኔ ውድቅ አድርጎበታል።

5. በ2013፣ ፋይል ቁጥር CAS 2013/A/3091 – Al-Masry SC v. Egyptian FA በሆነ ውሳኔ የግብፅ እግር ኳስ ማህበር አል ማስሪ በተሰኘ ክለብ ላይ ዘግይቶ እርምጃ በመውሰዱ ምክንያት ብቻ የግልግል ፍርድ ቤቱ (CAS) ውሳኔውን ሽሯል። ውሳኔውን የሻረበት ምክንያት "finality of competion result, lack of prompt decision, unpredictability and lack of procedural fairness" የሚል ነው። ሀሳቡ በመሰረቱ፣ አንድ ውድድር እንዲካሄት እስከተፈቀደ ድረስ ውጤት ቀድሞ እየታወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው በመጀመሪያ ሳይከለከል በኋላ ወደኋላ ሄዶ መሠረዝ አይቻልም።via professor tesema

01/07/2025

ከሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

| የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በዛሬው ቀን የሰጠው ተገቢነት የሌለው ውሳኔ እጅግ አሳዝኖናል።

ብርቅዬ የክለባችን ተጫዋቾች በጨዋታ ሜዳ የገጠሙትን ሁሉንም ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉ የአደባባይ ምስጥር ነዉ። ይሁን እንጂ የሊግ ካምፓኒ ያወጣውን የፋይናንስ ደንብ አላከበራችሁም በሚል በክለቡና በተጫዋቾች ላይ ቅጣት ተጥሎባቸዋል ቢባልም ክለቡ ያነሳዉ ዋንጫ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ በ48 ክለቦች መካከል የተደረገው መሆኑ ዕሙን ነው።

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የታገዱ ተጫዋቾችን አሰልፎ ከሆነ በጥሎ ማለፉ ያሸነፋቸው ክለቦች በሙሉ ፎርፈ አግኝተው ጉዳያቸው እንደገና መታየት አለበት እንደ ማለትም ይሆናል። ስለዚህ እርስ በርስ የሚጣረሱ ሀሳቦችን በማገናኘት ውጤቱን ለመቀማት መሞከር ተገቢና ህግን የተከተለ ውሳኔ ነው ብለን አናምንም።

ፌዴሬሽኑም ዉሳኔውን ከህግጋቱ ጋር በማገናዘብ እንደገና እንዲያጠነዉ ቅሬታችንን እናሰማለን። ጀግኖች ተጫዋቾቻችን የህዝባችን የሁልጊዜ ባለውለታዎቻችን ስለሆናችሁ አሁንም ህዝቡ የስፖርቱ ቤተሰብ ከጎናችሁ መሆኑን እንገልፃለን ።

ህዝባችን በፌደሬሽኑ ውሳኔ የተከፋ ቢሆንም የአፊኒ ባህል ያለው ታላቅ ህዝብ ስለሆነ ክስተቶችን በመረጋጋት መርምሮ በተገቢው እንዲያጠነውና ሂደቱን በትዕግሥት እንዲጠባበቅ በአክብሮት እየጠየቅን የተነፈግነው ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ጉዳዩን እስከ ፊፋ ገላጋይ ፍርድ ቤት ድረስ በይግባኝ ወስደን ለጉዳዩ ተገቢው እልባት እስኪሰጥ ድረስ የክለቡ ቦርድ ቁርጠኛ መሆኑን እያረጋገጥን መላው ህዝባችን፣ የስፖርቱ ቤተሰቦችና አፍቃሪያን በትዕግሥት እንድጠባበቅ እና ከክለቡ ጎን እንዲቆም የአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ሰኔ 24/2017 ዓ. ም ሀዋሳ ፣ ሲዳማ ፣ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ላይ ያስተለፈው የዛሬው ውሳኔ የሞራል የአሰራር እንዲሁም የህግ ጥሰት አለበት🎯 አቶ Ermias Tesfaye  ማን ነው?  👉በሴራ...
01/07/2025

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ላይ ያስተለፈው የዛሬው ውሳኔ የሞራል የአሰራር እንዲሁም የህግ ጥሰት አለበት🎯

አቶ Ermias Tesfaye ማን ነው? 👉በሴራ ከሲዳማ ቡና ሥራአስኪያጅነት የተነሳው የቀድሞ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ሥራአስኪያጅ ነበር። በአሁኑ ወቅት በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህር ነው።

እንደምከተለው አንድ በአንድ በማስረጃ አስደግፈን እናያለን 👇

የኢትዮጵያ ፕሪምየርሊግ አክሰዮን ማህበር የፋይናንስ ህጉን ጥሰዋል ባላቸው ክለቦች ላይ " የማህበሩን የፋይናንስ አስተዳደር መመሪያ ጥሳችኋል ፡፡" በማለት የቅጣት ውሳኔ በክለቦቹ ላይ ሲያስተላልፍ ክለቦቹ ይግባኛቸውን ወደ ፌደሬሽኑ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ይዘው ቀርበው ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው የሊግ ካምፖኒውን ውሳኔ በማፀናት ብይን መስጠቱ ይታወሳል፡፡

እንግዲህ በዚህ ጊዜ ከላይ በተጠቀሱት ውሳኔዎች ቅር የተሰኙት ክለቦች ጉዳዪን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት ወስደው ይግባኝ ጠይቀዋል፡፡

ይግባኛቸውን የተቀበለው መደበኛው ፍርድ ቤት የፌዴሬሽኑን ውሳኔ በእግድ እንዲቆይ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወቃል ፡፡

ይህንን አካሄድ እግር ኳሳዊ አይደለም በማለት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአለማቀፉ እግር ኳስ ማህበር FIFA ስለጉዳዪ ሚያዝያ 20/8/2017 እንዲሁም ግንቦት 7/2017 ዓ/ም በደብዳቤ ማሳወቁን እራሱን ፌፈዘዴሬሽኑ ለክለቦቹ በፀፈው ደብዳቤ አሳውቋል (ከታች ደብዳቤውን አያይዟለው)

የፌዴሬሽኑን ቅሬታ መነሻ በማድረግ FIFA ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ግንቦት 29/2017 ዓ/ም በፃፈው ደብዳቤ የክለቦቹ አካሄድ ትክክል አለመሆኑን ጠቅሷል በዚህም የመደበኛ ፍርድ ቤት ክርክሩን ክለቦቹ እንዲቆሙ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ሴራው እዚህ ጋር ነው

FIFA ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ይህንን ዳብዳቤ የፃፈው በ29/9/2017 ዓ/ም ነው ። ማለትም አርብ ዕለት ይህ ማለት የኢትዮጵያ ዋንጫ ከመደረጉ ሁለት ቀን ቀደም ብሎ ነው ማለት ነው።

እሁድ ማለትም ሰኔ 1/10/2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታ ተካህዷል ፡፡ ልብ እንደል ከሁለት ቀን በፊት ለፌዴሬሽኑ ከFIFA የተላከው ደብዳቤ ለክለቦቹ በዕለቱ መድረስ ሲገባው አልደረሳቸውም

በቀን 1/10/2017 ዓ/ም ዋንጫውን ሲዳማ ቡና አነሳ ፡፡ በሚያሳፍር መልኩ በሳምንቱ ማለት በ6/10/2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሸን ለክለቦቹ ከFIFA የተላከውን ደብዳቤ ይልካል፡፡

ምን ማለት ነው
1. ጨዋታ ከመደረጉ ከሁለት ቀን በፊት የደረሰውን በውጤቱም ብዙ ትፅዕኖና ትርጉም ያለውን ደብዳቤ ታቅፎ አሊያም ደብቆ ቆይቆ በሳምንቱ መላክ?
2. ይኸ ደብዳቤ አርብ ዕለት ለፌደሬሽኑ እንደደረሰ ለክለቦቹ ቢደርስ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ እነዚህን ልጆች እንደማያሰልፍ የአደባባይ ሀቅ ነው
3. ይህ ሳይሆን ከቀረ በፌዴሬሽኑ እንዝላልነትም ይሁን ሴራ የዘገየው ደብዳቤ የህግ ውጤቱ በተለይ በሲዳማ ቡና ላይ የሚኖረው ውጤት ግልፅ ነው ። የተፈለገውም ይኸው ነውና፡፡
4. በዚህ ደብዳቤ ምክንያት በተሰራብን ሴራ የምናጣው ዋንጫ አይኖርም፡፡

በመሆኑም

የክለቡ ወዳጆችና ደጋፊወች
አመራሮች
የበላይ ጠባቂ ስለዚህ ሴራ እስከ CAS እንድንሟገት ይሁን፡፡

FIFA (CAS) ይዳኘናል ::

እግር ኳሳዊ ሴራ እናውቃለን ስንል በስሜት አይደለም ፡፡

ክፍል አንድ ከ Ermias Tesfaye ፌስ ቡክ ገፅ ይነበብ‼️

ማሳሰቢያ: ለዚህ ሁሉ ኪሣራና አጣብቅኝ የከተተን የኮቺን ስታፉና የቦርድ አመራሩ ጉድ አልረሳነውም። በፍፁም‼️

Shumulo Daga Gamba yittinowa Olu massara tokossa Dancha di'ikkino kayinilla Affa Hongeete loosottoHa ikkino daafo-- Maar...
27/06/2025

Shumulo Daga Gamba yittinowa Olu massara tokossa Dancha di'ikkino kayinilla Affa Hongeete loosottoHa ikkino daafo-- Maaro xa'mirri! Kayinilla አናጋንን! ግን ሹሙሎ አንተም አትቀባጠር! ዝም ብለህ ባለማወቅ እና በደስታ ምክንያት ያረኩት ድርጊት ስለሆነ ይቅርታ አድርጉኝ በል! የትኛውም ሀገር ላይ በጦር መሳሪያ ደስታ የሚገለፀው?

እንኳን ለቤትሽ አበቃሽህ የፍጥረታት ጌታ እግዚአብሔር!! እንኳን ደስ አለን!! በፍፁም መንግስት ዳግም ዘጎችን አሳባቸውን ለምን በነፃንነት ገለፃቸው በማለት ማሰር ልበቃ ይገባል!!
24/06/2025

እንኳን ለቤትሽ አበቃሽህ የፍጥረታት ጌታ እግዚአብሔር!! እንኳን ደስ አለን!! በፍፁም መንግስት ዳግም ዘጎችን አሳባቸውን ለምን በነፃንነት ገለፃቸው በማለት ማሰር ልበቃ ይገባል!!

22/06/2025
12/06/2025
~ስለ ሲዳማ ህዝብ እግዚአብሔር ይዋጋል!~የሲዳማን ጠላቶች ሁሉንም ያጠፋል!~ሲዳማ ትለማለች!!~ከጠላቶቿ ፊት ከፍ ከፍም ትላለች!~ልጆዎቿም ዳግም አንድ ይሆናሉ!~ የሚያሳንሷትም ያንሳሉ! ~ ...
12/06/2025

~ስለ ሲዳማ ህዝብ እግዚአብሔር ይዋጋል!
~የሲዳማን ጠላቶች ሁሉንም ያጠፋል!
~ሲዳማ ትለማለች!!
~ከጠላቶቿ ፊት ከፍ ከፍም ትላለች!
~ልጆዎቿም ዳግም አንድ ይሆናሉ!
~ የሚያሳንሷትም ያንሳሉ!
~ ልጆዎቿም ከብተና ይተርፋሉ!
~ በነገራችን ላይ ሲዳማ ማለት የዱሮሃ እስራኤል፣የአሁኗ #ሲዳማ ናት።

Address

Awassa

Opening Hours

Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama federation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share