Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department

Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department It is a means to share information with the globe,to give our customers what is new ,positive change and progress of our city.
(2)

Sharing true information for our followers .

ሐዋሳ በልማት ያስመዘገበቻቸው ድሎች በስፖርቱም ዘርፍ ሊደገሙ ይገባል” – ከንቲባ ጥራቱ በየነሐዋሳ፣ ግንቦት 30/2018 ዓ.ምበሐዋሳ ከተማ በልማት መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ለከተማዋ...
07/06/2026

ሐዋሳ በልማት ያስመዘገበቻቸው ድሎች በስፖርቱም ዘርፍ ሊደገሙ ይገባል” – ከንቲባ ጥራቱ በየነ

ሐዋሳ፣ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም

በሐዋሳ ከተማ በልማት መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ለከተማዋ ነዋሪዎች ተስፋና ኩራት እየሆኑ ባሉበት ወቅት፣ ይህ መነቃቃት ስኬት በስፖርቱም ዘርፍ እንዲታይ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ጥሪ አቅርበዋል።

የሐዋሳ ከተማ ከንቲባና የሐዋሳ ከነማ እግር ኳስ ክለብ የበላይ ጠባቂ አቶ ጥራቱ በየነ ከክለቡ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች፣ የክለቡ አመራሮች እና የደጋፊ ማህበር አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት፣ የቡድኑ ስኬት ከውድድር ውጤት ባለፈ የከተማዋን ሕዝብ ተስፋና ኩራት የሚወክል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ከንቲባው በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሐዋሳ ከነማ እያሳየ ላለው ጥሩ አፈጻጸም ምስጋና አቅርበው፣ በቀሪዎቹ ጨዋታዎች በተጨማሪ ቁርጠኝነትና ትጋት በመጫወት የውድድር ዘመኑን በላቀ ውጤት እንዲያጠናቅቁ ተጨዋቾችና የቡድኑ አባላት የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በውይይቱ ወቅት ተጫዋቾች ያነሱትን ሀሳብ በትኩረት ያዳመጡት ከንቲባው፣ የከተማ አስተዳደሩ ለቡድኑ የሚያስፈልገውን ድጋፍና ማበረታቻ በቀጣይም እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል።

በመድረኩ የሐዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መልኩ ማርቆስ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም የታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ሰፊ ርብርብ መደረጉን ገልጸው የአስተዳደር፣ የፋይናንስና የውጤት ችግሮች በዝርዝር ተገምግመው በተወሰዱ እርምጃዎች የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉንና ዘንድሮም የውድድር ዘመን በድል ለማጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞችና አመራር አካላት በበኩላቸው፣ ከንቲባው ያደረጉት ውይይትና ማበረታቻ በቀጣይ ጨዋታዎች ላይ ትልቅ መነቃቃት እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

በህዝባችን ዘንድ ያለዉ የልማት ፍላጎት፣ ቅንነት እና ተነሳሽነት የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ለማሳካት ትልቅ አቅም ሆኖ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ተገለፀየሀ/ከ...
07/06/2026

በህዝባችን ዘንድ ያለዉ የልማት ፍላጎት፣ ቅንነት እና ተነሳሽነት የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ለማሳካት ትልቅ አቅም ሆኖ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ተገለፀ

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 30/2018 ዓ.ም

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ዛሬ ለታላቁ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ላለፉት ቀናት የነበረውን አፈፃፀሙን በመገምገም በቀጣይ በሚኖሩ አሰራሮች ላይ አቅጣጫ ያስቀመጠ ምክክር አድርገዋል።

በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ የፊት አመራርን ጨምሮ ሌሎች የኮሚቴ አመራርና አባላት ተገኝተዋል።

መድረኩን የመሩት የሀዋሳ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የከተማዋ ባለሀብት ፕሮጀክቱን ለመደገፍ ቃል የገባውን ገንዘብ ኮሚቴው ጠንካራ ክትትል በማድረግ ለማሰባሰብ እያደረገ ያለውን ጥረትን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

በተመሳሳይም ቃል ያልገቡ ሌሎች ባሀብቶችን እና የከተማዋ የንግዱ ማህበረሰብና ነዋሪ ልማቱን ከህዝብ ለህዝብ የተሰጠ ስለመሆኑ በቂ ግንዛቤ ኖሮአቸው ተሳትፎአቸው ከምንጊዜውም ይልቅ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ድጋፍ ማድረግ እንዲችሉም ከንቲባው አቅጣጫ ያመላከተ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ህዝባችን ለልማቱ እያሳየ ያለው ድጋፍ እና ተሳትፎ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሀይቅ ዳርቻ ፕሮጀክቱን ወደ ግንባታ ሂደት በማስገባትና በማከናወን ለሌላ የከተማ ከፍታ ትጋታችንን ለማስቀጠል ልንሰራ ይገባል ሲሉም አስረድተዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ የኮሚቴ አባላት በበኩላቸው የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ለትውልድ የሚቀመጥ ተፈጥሮ ካደለን ሀብቶቻችን ትልቁ እንደመሆኑ ለመጠበቅና ለማስዋብ ሁላችንም አሻራችንን ማሳረፍ ይገባናል ሲሉም ገልጸዋል።

ዛሬ በከተማዋ የታየው መነቃቃት ለሌላ ልማት የሚያተጋን ነው ያሉት የኮሚቴ አባላቱና አመራሩ ይህም ህዝቡ ለልማቱ ቅርብና ይበልጥ ተሳትፎውን ለማረጋገጥ አቅም በመሆን የሚያግዝ እንደሆነም አስረድተዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀይቅ ዳርቻ ልማት ላይ ለያዘው ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ 1.5 ቢሊዮን ብር በእቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቃል የተገቡ እንዲሁም ገና የሚሰበሰበዉ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ወደ አካወንት ገቢ በማድረግ ስራዉን ማፍጠን እንደሚያስፈልግ በመድረኩ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ሲዳማ ባንክ አ.ማ ለሐዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ።የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያሀዋሳ፣ግንቦት 29/2018 ዓ.ምየሲዳማ ባንክ አ.ማ እና የባንኩ ከፍተኛ አ...
06/06/2026

ሲዳማ ባንክ አ.ማ ለሐዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ።

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 29/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ባንክ አ.ማ እና የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች ለሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሚውል ድጋፍ ማድረጋቸውን አሳውቀዋል።

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለፀ።የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያሀዋሳ፣ግንቦት 29/2018 ዓ.ም​የሀዋሳ ሀይቅ ዳ...
06/06/2026

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለፀ።

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 29/2018 ዓ.ም

​የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የመጀመሪያ ምዕራፍ ለማስጀመር እየተደረገ ያለው የቅድመ ዝግጅት ስራን የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አመራር እና ባለሙያዎች ተዟዙረው ተመልክተዋል::

የመጀመርያው ምዕራፍ የግንባታው ምዕራፍ በፍቅር ሀይቅ አካባቢ የሚጀመር ሲሆን ለዚህም ቦታውን ነፃ የማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን ከንቲባው ተመልክተዋል::

​የሀዋሳ ሀይቅ ልማት በህብረተሰቡ ተሳትፎ ለመገንባት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ይፋ መደረጉ ይታወሳል:: በዚህ ወቅት የክልሉ መንግስትና ከተማ አስተዳደሩ ለሀዋሳ ሀይቅ ልማት ሀብት ማሰባሰቢያ ጥሪ ካቀረበ ጊዜ ጀምሮ ባለሀብቱ፣ የመንግስት ሰራተኛውና ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ በማድረግ ለፕሮጀክቱ መሳካት የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ ይገኛል::

በዛሬዉ የመስክ ጉብኝት ወቅት የሀዋሳ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የሀዋሳ ሀይቅ ልማት ስራ በቅርቡ እንደሚጀመር ገልፀው ለግንባታ የሚያስፈልገውን ሀብት ለማሰባሰብ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል::

"ነገዋን ዛሬ እየሰራች ካለችው ሀዋሳ ገና ብዙ እናያለን!"
06/06/2026

"ነገዋን ዛሬ እየሰራች ካለችው ሀዋሳ ገና ብዙ እናያለን!"

ከንቲባ ጥራቱ በየነ በዳቶና አካባቢው ግንባታቸው እየተፋጠነ ያሉ የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎችን ተዟዙረው ተመለከቱየሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያሀዋሳ፣ግንቦት 28/2018 ዓ...
05/06/2026

ከንቲባ ጥራቱ በየነ በዳቶና አካባቢው ግንባታቸው እየተፋጠነ ያሉ የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎችን ተዟዙረው ተመለከቱ

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 28/2018 ዓ.ም

ከንቲባው ከፊት አመራራቸው እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ነው ዛሬ ለህብረተሰቡ ዘላቂ የልማት ፍላጎት በአስተዳደሩ በትኩረት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ በዳቶ አካባቢ በመገኘት ምልከታቸውን ያደረጉት።

የልማት ስራዎቹ በፍጥነት እየተከናወኑ ያሉና ለአካባቢው ማህበረሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆን በሚችሉበት አግባብ ላይ ከንቲባ ጥራቱ በየነ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በአካባቢው በተለይም በ4ኛ ዙር እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ስራ የተመለከቱት ከንቲባው ግንባታው ሊፋጠን በሚችልበት ዙሪያም ከተቋራጭና አማካሪ ድርጅቶች ጋር መክረዋል።

በተያያዘም በዳቶ አካባቢ መጪው የክረምት ወቅትን ታሳቢ ያደረጉና የህብረተሰቡን የቆየ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ታስቦ እየተከናወነ የሚገኘውን የመንገድ ከፈታ ስራን የተመለከቱት ከንቲባ ጥራቱ በየነ ስራው በዘላቂነት ለነዋሪው እፎይታ የሚሰጥ ሆኖ እንዲተገበርና የተጀመሩ ስራዎች በላቀ ፍጥነት እንዲጠናቀቁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየት አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ከመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች ጋር በተያያዘ በተለይም የተቀናጀ የግንባታ ሂደት ዘላቂነት ላለው የህዝብ አገልግሎትና ተጠቃሚነት ከተለያዩ ተቋማት ጋር ሊኖር ስለሚገባው የድርሻ ቅብብሎሽ የከተማዋን ልማት ባስቀደመ መልኩ ከዳር ለማድረስ ሊሰራ እንደሚገባ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በምልከታቸው ጠቁመዋል።

ማስታወቂያለሀዋሳ ሀይቅ ልማት ፕሮጄክት ገቢ ማሰባሰቢያና የምስጋና ፕሮግራም በአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የነበረው በሌሎች በሀገራዊ ፕሮግራሞች ምክንያት...
05/06/2026

ማስታወቂያ

ለሀዋሳ ሀይቅ ልማት ፕሮጄክት ገቢ ማሰባሰቢያና የምስጋና ፕሮግራም በአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የነበረው በሌሎች በሀገራዊ ፕሮግራሞች ምክንያት ለሰኔ 23/2018 ዓ.ም መተላለፉን በአክብሮት እንገልፃለን!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተደረገውን ጥረት እንደተሞክሮ በመጠቀም በልማቱ ረገድ ይበልጥ ርብርብ ማድረግ እንዲቻል ጥሪ አቀረ...
04/06/2026

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተደረገውን ጥረት እንደተሞክሮ በመጠቀም በልማቱ ረገድ ይበልጥ ርብርብ ማድረግ እንዲቻል ጥሪ አቀረበ

የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ
ግንቦት/27/2018/ዓም/ሐዋሳ

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ ፍፁም ሰላማዊ፣ ተዓማኒነት ያለውና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ በመጠናቀቁ ለከተማዋ አመራር እና የፀጥታ አካላት የምስጋና መድረክ አካሄደ።

የከተማው አጠቃላይ አመራርና የፀጥታ መዋቅሩ ቁርጠኝነትና ቅንጅት ለምርጫው ስኬታማነት ፍትሃዊ፣ ገለልተኛ ፣ነፃና ታዓማኒነት ያለው ምርጫ ለማካሄድ እጀ ንፁህና ልበ ንፁህ ሆኖ ማገልገሉና የተሰጠውን አቅጣጫ ተቀብሎ የመራበት አግባብ ለምርጫው ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱም ከመድረኩ ተመላክቷል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ምርጫ መሆኑን መድረኩን የመሩት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገልፀው ለምርጫው ሰላማዊነትና ዴሞክራሲያዊነት ለሰሩና በምርጫው ሂደት ለተሳተፉ ለሁሉም አካላት የሚያኮራ ውጤት የተመዘገበበት ምርጫ መሆኑን አክለዋል።

የምርጫው ስኬት እንደተጠበቀ ሆኖ በከተማዋ በበጀት ዓማቱ የተጀመሩ የልማት ስራዎች በተያዘላቸው የጊዜ እና የዲዛይን ጥራት መሰረት ተጠናቀው ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እና በድል ለማጠናቀቅ በላቀ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም ከንቲባው አያይዘው ገልፀዋል።

የሐዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ዋና ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ በበኩላቸው ነዋሪው የተለያዩ ጫናዎችን ተቋቁሞ በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብቱን መጠቀሙ የከተማው ነዋሪ ሰላም ወዳድነት አንዱ ማሳያ መሆኑን ገልፀው በቅንጅትና በጋራ ከተሰራ በምርጫው የተመዘገበው ውጤት ማንኛውንም ስራ በብቃት ማሳካት እንደሚቻል አመላካች ነውም ብለዋል።

በመድረኩ በክብር እንግድነት የተገኙት የሲዳማ ክልል ከተማና መሰረተልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ሰለሞን በነዋሪው ሰላም ወዳድነትና የጎለበተ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ እንዲሁም በምርጫ ስራው በአመራሩና የፀጥታ አካላት ገለልተኛ፣ ፍትሃዊና ነፃ ሆኖ ማገልገል ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

"ቀናችሁ ከማለዳው ጀምሮ ልክ እንደ ሀዋሳ ውበት ፍክት ያለና የተወደደ ይሁን"መልካም ቀን!
04/06/2026

"ቀናችሁ ከማለዳው ጀምሮ ልክ እንደ ሀዋሳ ውበት ፍክት ያለና የተወደደ ይሁን"

መልካም ቀን!

ከንቲባ ጥራቱ በየነ በከተማዋ በፍጥነት ግንባታው እየተገባደደ የሚገኘውን 4ኛ ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ያለበትን ደረጃ ተመለከቱበምልከታው በብልፅግና ፓርቲ የሀዋሳ ቅርንጫፍ ሀላፊ አቶ ማራዶና...
03/06/2026

ከንቲባ ጥራቱ በየነ በከተማዋ በፍጥነት ግንባታው እየተገባደደ የሚገኘውን 4ኛ ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ያለበትን ደረጃ ተመለከቱ

በምልከታው በብልፅግና ፓርቲ የሀዋሳ ቅርንጫፍ ሀላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ፣ የከተማዋ የፊት አመራርና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮ/መምሪያ
ሀዋሳ፣
ግንቦት 26/2018 ዓ.ም

የሀዋሳ ከተማን ውበት እና ሁለንተናዊ ፈጣን ዕድገትን እያሳለጠ የሚገኘውና ስራው በቅርቡ በይፋ የተጀመረው 4ኛ ዙር የሀዋሳ የኮሪደር ልማት ስራ በከፍተኛ ፍጥነት እና በተለወጠ የስራ ባህል 24/7 በከተማዋ በአራት የተለያዩ አቅጣጫዎች በመከናወን ላይ ይገኛል።

ግንባታው ያለበትን ደረጃና አጠቃላይ የፕሮጀክቶቹን አተገባበር አስመልክቶም ዛሬ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ይህን ከሳውዝ ስታር- መናሃሪያ- ሼል፣ ከሳውዝ ስታር - እርሻ ጣቢያ፣ ከሱሙዳ-ሎጊታን እና ከጥቁር ውሃ - ሳውዝስፕሪንግ ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በስፍራው ተዟዙረው ተመልክተዋል።

በምልከታቸውም ከንቲባው ስራው በከፍተኛ ፍጥነት እና ጥራት እየተከናወነ እንደሚገኝ በመመልከት በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆም ለሌላ የከተማዋ ውበትና ፈጣን እድገት ሊውል በሚችልበት ዙሪያም ከተቋራጭና አማካሪ ድርጅቶት ጋር ተወያይተዋል።

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share