Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department

Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department It is a means to share information with the globe,to give our customers what is new ,positive change and progress of our city.

Sharing true information for our followers .

‎በሀዋሳ ሐምሌ 24 የሚካሄደው የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብር በቂ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቋል።‎‎በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 24 የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አ...
29/07/2025

‎በሀዋሳ ሐምሌ 24 የሚካሄደው የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብር በቂ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቋል።

‎በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 24 የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን የከተማ ደጋፊ አመራርና የከተማ አስተባባሪዎች ምልከታ አድርገዋል።

‎7ተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ሐምሌ 24 እንደ ሀገር 700 ሚሊየን እንደ ክልል ስምንት ሚሊየን ችግኝ ተከላ ይካሄዳል።

‎በሀዋሳ ከተማ በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በአንድ ጀንበር ችግኝ ለመትከል መዘጋጀቱ ተገልጿል።

‎በመርሀግብሩ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የከተማችን ወጣቶች በችግኝ ተከላ የሚሳተፉበት እንደሆነና ተከላዉ ልክ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ ቀኑን ሙሉ የሚደረግ እንደሆነ ተገልጿል።

‎ለተከላዉ የሚሆን ጉድጓድና የችግኝ ማጓጓዝ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን ህብረተሰቡም በችግኝ ተከላ በነቂስ እንዲሳተፍ ጥሪም ቀርቧል።

ያዩዋት የሚያደንቋት፤ ያላዩዋት የሚናፍቋት ውብ ከተማ!!!                      ሀዋሳ-ሲዳማ-ኢትዮጵያ                       ዳዎኤ ቡሹ ትላለች!!!
29/07/2025

ያዩዋት የሚያደንቋት፤ ያላዩዋት የሚናፍቋት ውብ ከተማ!!!
ሀዋሳ-ሲዳማ-ኢትዮጵያ
ዳዎኤ ቡሹ ትላለች!!!

‎"በ2017 በጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበት ቢሆንም ለህዝባችን ተጠቃሚነት ልዩ ትኩረት ሰጥተን የሚንሰራቸው ስራዎችም መኖራቸውን መዘንጋት የለብንም" የክልሉ ርዕሰ መ...
28/07/2025

‎"በ2017 በጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበት ቢሆንም ለህዝባችን ተጠቃሚነት ልዩ ትኩረት ሰጥተን የሚንሰራቸው ስራዎችም መኖራቸውን መዘንጋት የለብንም" የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ

‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/ጉዳ/መምሪያ
‎ሀዋሳ
‎ሐምሌ 21/2017 ዓ.ም

‎በብልጽግና ፓርቲ ሲዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት''የሀሳብና የተግባር አንድነት ለላቀ ድልና ስኬት'' በሚል መሪ ቃል የክልል፣የዞንና የወረዳ አመራሮች የ2017 በጀት አመት ስራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት አመት ዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ ማካሄድ ተጀምሯል።

‎የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ የመድረኩ ዋና አላማ በየደረጃው ያሉ አመራር የ2017 በጀት ዓመት በፖለቲካ፣ በልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በሠላም ዕቅድ አፈጻጸም የታዩ ጠንካራ አፈጻጸም ለማስቀጠልና ደካማ አፈጻጸም ደግሞ በሚስተካከልበት ዙሪያ ጠንካራ አቋም ይዘን በቀጣይ 2018 በጀት አመት ለተሻለ ውጤት ለመስራት ወስነን የምንወጣበት ነው ብለዋል።

‎የአመራሩ ምዘና በመ/ቤቱ ዕቅድ አፈጻጸም ከ70% እንዲሁም በሌሎች ወሳኝ መመዘኛ ነጥቦች ከ30% እንደሆነ በመግለጽ በመስፈርቶቹ መሠረት ተመዝነው እንደሚያልፉ እና በመቀጠልም በ2018 በጀት አመት በሚፈጸሙ ዋና ዋና ግቦች ዙሪያ የጋራ አቋም ተይዞ ከወዲሁ ዝግጅት የሚደረግ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ደስታ ሌዳሞ አስገንዝበዋል።

‎በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በበኩላቸው የአመራሩ ሚዘና በዋናነት የሚያተኩረው ባለፈው በጀት አመት የመጡ ስኬቶችን እንደ ጥሩ ልምድ በመውሰድ በአፈጻጸም ሂደት የታዩ ድክመቶችን በማረም በቀጣይ በተሻለ አፈጻጸም የህብረተሰቡ ኑሮ እንዲሻሻል ለማድረግ እንደሆነ አስረድተዋል።

‎መርሃ ግብሩ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን
‎የክልሉ ከፍተኛ አመራር፣ የዞኖችና የወረዳ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ በማለት የዘገበው የሲዳማ ክልል መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።

ርዕሰ አንቀፅየሲዳማ ፈርጥ ‎ከተማችን ስኬታማ ዓመትን አሳልፋለች!!!‎‎ከጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ እስከ የውጭ ዲፕሎማቶች በከተማችን ባሳለፍነው አመት መጥተው የልማት ስራዎችን አስመርቀ...
28/07/2025

ርዕሰ አንቀፅ

የሲዳማ ፈርጥ ‎ከተማችን ስኬታማ ዓመትን አሳልፋለች!!!

‎ከጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ እስከ የውጭ ዲፕሎማቶች በከተማችን ባሳለፍነው አመት መጥተው የልማት ስራዎችን አስመርቀዋል፤ ጎብኝተዋልም።

‎የውጭ ተቋማት እና የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ጉባኤያቸውን አድርገዋል። በቆይታቸውም ደስተኛ ሆነው በአገልግሎታችን ምቾት ተሰምቷቸው ተመልሰዋል።

‎በርካታ ባለሀብቶች የልማት ትሩፋታችንን ተከትለው መዋዕለ ንዋያቸውን አፍሰው ሀዋሳን ሊያተርፉባት ዘርተው ስራ ጀምረዋል።

‎በሌላም ለበርካቶች የስራ እድል ፈጥረው እነሆ ከማለታቸው ባሻገር የውጭ ምንዛሬን የሚያመጣ ተልኳቸውን ፈፅመዋል።

‎በሌማት ትሩፋት ረገድ በከተማችን በተደረገው ጥረት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ከሀዋሳ ባለፈ ምርቱ ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማድረሱ ረገድ በተደረገው ስራ ውጤታማ ተግባር መፈፀም ተችሏል።

‎በቱሪዝም ረገድ ከተማችን በሳለፍነው ዓመት 623 ሺህ የሀገር ውስጥና የባህር ማዶ ጎብኚ በከተማችን በመገኘት የጉብኝት ጊዜያቸውን ያማረና የሰመረ ማድረግ ተችሏል።

‎በዚህም ከ 861 ሚሊዮን ብር ገቢ ወደ ከተማዋ እንዲመጣ አበረታች ስራ ማከናወን ተችሏል።

‎የህብረተሰቡን የቆየ የልማት ጥያቄ እውን ከማድረግ አንፃር ኤንዲፒ ባልተሰራባቸው አካባቢዎች 11 ስራዎችን በማውረድ እፎይታ የሰጠ ብሎም የከተማዋን ዘመናዊ ስሪት እውን ማድረግ ተችሏል።

‎ከንፁህ የመጠጥ ውሀ ግንባታ ስራ ጋር በተያያዘም ከተማዋ 260 ሚሊዮን ብር በመመደብ ለ100 ሺህ ሰው የሚያጠጣ ንፁህ የመጠጥ ውሀ ዝርጋታ ስራን በሂጠታ ፋራ አካባቢ በመገንባት ላይ ያለው ፕሮጄክት በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።

‎ከኮሪደር ልማት ስራ አንፃርም የሀዋሳን ውበትና ልማት የሚያሳይ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ ያለን በአንደኛው 1.3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራን በማከናወን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በተገኙበት ማስመረቅ ተችሏል።

‎በሌላም 5.6 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውና የከተማዋን ዘላቂ ልማት የሚያጎናፅፈው የኮሪደርና የአስፋልት ስራ ግንባታው 70 በመቶ ላይ ይገኛል።

‎ከገቢ ስራችን አንፃርም ከተማዋ በበጀት ዓመቱ መሰብሰብ የሚያስችላትን አቅም በመንደፍ በተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት የተገኘበት ሆኖ ማከናወን ተችሏል።

‎ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር የህብረተሰቡን እንግልት መቀነስ የሚስችል የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በከተማዋ በመጀመር የስማርት ከተማ ግንባታ ከሆኑ አብነቶች አንፃር ስኬታማ ውጤት መመዝገብ ተችሏል።

‎በአጠቃላይ በ2017 በጀት ዓመት የሀዋሳ ከተማ ውጤታማ የሆነ ተጨባጭ ለውጦችን እውን ማድረግ ችላለች።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቀቀ።የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ‎ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም‎ሐዋሳየሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 9ኛ ...
27/07/2025

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቀቀ።

የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ
‎ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም
‎ሐዋሳ

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ 7 አጀንዳዎችን በማጽደቅ ነው የተጠናቀቀው።

በመድረኩ የቀረበው የአስተዳደሩ የ2017 ዓ/አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ ጸድቋል።

ከተከበሩ የም/ቤት አባላት በመድረኩ ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል የቆዩ ኘሮጀክቶች እንዲጠናቀቁ፣ ከደረሰኝ ጋር ያለ ግብይት እንዲስተካከል፣ ከነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት፣ ቁማር (ቤቲንግ) ቤቶች፣ ከውሃ መውረጃ ቦይ እና የመሳሰሉት በመድረኩ ተነስቷል።

የ2018 በጀት ዓመት ከቀረበ እቅድ አኳያም የተከበሩ የም/ቤት አባላት ትኩረት እንዲሰጠው ካሉት መካከል የከተማዋን ውበትና ጽዳት ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን የማስጠበቅ፣ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተደራሽነት ማስፋት ፣ የማዘጋጃቤታዊ ገቢም በቀጣይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጨማሪ አድርገዋል ።

የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ከመድረኩ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም፣ የቤተሰብ ብልጽግና በማረጋገጥና በሌሎችም ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

ከንቲበ መኩሪያ ከም/ቤት አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ የተገለጹትን ጉዳዮች ለማስተካከል በርካታ ስራዎች እንደተሰራ ተናግረው ለህብረተሰቡ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በበለጠ በቁርጠኝነት እና በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል።

በመድረኩ የቀረበው የሐዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት የ2017 ዓ/ም ሪፖርትና የ2018 ዕቅድ በም/ቤት አባላት ጸድቋል።

ፍ/ቤቱ ባቀረበው ሪፖርት በዓመቱ በወንጀል እና በፍትሃብሄር የቀረቡ ፋይሎች 11 ሺህ 2 መቶ 6 ሲሆኑ ውሳኔ ያገኙት ደግሞ 10 ሺህ 8 መቶ 70 መሆናቸው ተጠቁሟል።

በቀረበው ሪፖርትና ዕቅድ ዙሪያ ውይይት ተደርጎበት ጉባኤው ተጠናቋል።

Hawaasi Quchumi gashshooti 2018M,D bajeettete dirinni 6 bixille 6 biliyeene birra kaajjishi.H/Q/G/M/H/BiddishshaMaaja 20...
27/07/2025

Hawaasi Quchumi gashshooti 2018M,D bajeettete dirinni 6 bixille 6 biliyeene birra kaajjishi.

H/Q/G/M/H/Biddishsha
Maaja 20/2017 M.D
Hawaasa

Hawaasi Quchumi Amaalete mini 2ki doycho 9ki diri loosu yanna 23ki uurrinshu Songo aana Quchumu gashshooti 2018 bajeette 6 biliyeene 6 xibbe 66 mileene 6 xibbe 83 kume 4 xibbe 89 birra ikke A/mini wo'ma huuronni kaajjishino.

Bajeette shiqishinohu Hawaasi Quchumi womaashshunna miinju latishshi biddishshi Sooreessi Kalaa Gedahun Gabbisoho.

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ/ም በጀት 6 ነጥብ 6 ቢሊየን አጸደቀ።

የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ
‎ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም
‎ሐዋሳ

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 ዓ/ም በጀት 6 ቢሊየን 6 መቶ 66 ሚሊየን 6 መቶ 83 ሺህ 4 መቶ 89 ብር ሆኖ በም/ቤቱ በሙሉ ድምጽ ጽድቋል።

በጀቱን ያቀረበት የሐዋሳ ከተማ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ገዳሁን ገቢሶ ናቸው።

‎ለበለጠ መረጃ
‎👉Our page https://www.facebook.com/profile.php?id=100064180623390
‎👉Our Telegram Channal
https://t.me/hawassacitycommunication
‎👉Our tiktok Account
‎tiktok.com/
‎Our WhatsApp Group
https://chat.whatsapp.com/Hw8xlXGEIlu5OfFzKbltO9
‎👉Our Instagram Account
https://www.instagram.com/hawassacom?igsh=MTJtdmh6eW5hM3QydA==
‎👉Our X Account
https://x.com/CityHawass34782?t=Pqws9rQukeetk4gFoKPffw&s=09
‎👉Our website
‎www.hawassa.gov.et

ዳዎኤ ቡሹ ብለን እንደተቀበልን ‎ከንግስ መልስ ለእንግዶቻችን የቀረበ የጉብኝት ጥቆማን እነሆ ብለናል‎‎ለክብራን እንግዶቻችን በሙሉ ከንግስ መልስ ወዲህ ባሉት ቀናት ከወዳጅ ዘመድና ቤተሰብ ጋ...
27/07/2025

ዳዎኤ ቡሹ ብለን እንደተቀበልን ‎ከንግስ መልስ ለእንግዶቻችን የቀረበ የጉብኝት ጥቆማን እነሆ ብለናል

‎ለክብራን እንግዶቻችን በሙሉ ከንግስ መልስ ወዲህ ባሉት ቀናት ከወዳጅ ዘመድና ቤተሰብ ጋር በከተማችን ለመዝናናት ምራጫችሁ ቢሆኑ ብለን ለጥቆማ ያህል፦

‎👉 የክልላችንን ባህል፣ ታሪክና ትግል ብሎም አኗኗር የሚተርከውን ሀውልታችንና የከተማችን ልዩ መገለጫ የሆነው የሲዳማ ሱሙዳን በመጎብኘት፣

‎👉 የሀዋሳ ሀይቅና ትሩፋቱን በመጎበኘት፣

‎👉 የጉዱማሌ ፓርክን መናፈሻ ፓርክ በመጎብኘት፣

‎👉 የታቦርና የአላሙራ ተራራን፣

‎👉 የባህል መገለጫችን የሆኑትን ቡርሳሜን ጨምሮ ሌሎች አብሮነታችንን የሚጠቅሱ ምግቦችን በመቋደስ፣

‎👉 ለእንቅስቃሴ ምቹ የሆኑት የከተማዋ የኮሪደር ልማት ስራዎች፣

‎👉 አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማቶቻችን ጎራ በማለት፣

‎👉 በሲዳማ ባህል አዳራሽ ግቢ የተተከሉ የሲዳማን ታሪክ ያፀኑ አባቶችን እና የትግላቸውን ውጤትን በመጎብኘት፣

‎👉 በሀዋሳ ዙሪያ የሚገኘው የወንዶገነት ፍል ውሀን ከተፈጥሮ ጋር በማውጋት

‎👉 የይርጋለም ጊዳዎ ፍል ውሀን እና

‎👉 ሌሎች በክልላችን የሚገኙ መስህቦችንና ታሪካዊ ቦታዎችን በመጎበኘት አይረሴ ትውስታን ሰንቃችሁ ትመለሱ ዘንድ ተጋብዛችኋል።

‎በዚህ ሁሉ ውስጥ በቂና ተገቢ አገልግሎት የሚሰጡ የፋይናንስ ተቋማቶቻችንን ጨምሮ እንግዳን ምቾት የማይነሳው የህዝባችን አቀባበል ይገኝበታል።

‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

‎ለበለጠ መረጃ
‎👉Our page https://www.facebook.com/profile.php?id=100064180623390
‎👉Our Telegram Channal
https://t.me/hawassacitycommunication
‎👉Our tiktok Account
‎tiktok.com/
‎Our WhatsApp Group
https://chat.whatsapp.com/Hw8xlXGEIlu5OfFzKbltO9
‎👉Our Instagram Account
https://www.instagram.com/hawassacom?igsh=MTJtdmh6eW5hM3QydA==
‎👉Our X Account
https://x.com/CityHawass34782?t=Pqws9rQukeetk4gFoKPffw&s=09
‎👉Our website
‎www.hawassa.gov.et

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ጉባእኤ በሶስተኛው ቀን ውሎው እንደቀጠለ ይገኛል። ‎‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/ ጉዳ/መምሪያ‎ሀዋሳ‎ሐምሌ 20/2017 ዓ.ምምክ...
27/07/2025

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ጉባእኤ በሶስተኛው ቀን ውሎው እንደቀጠለ ይገኛል።

‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/ ጉዳ/መምሪያ
‎ሀዋሳ
‎ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም

ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው የአስተዳደሩን የ2018 ዓ/ም ዕቅድን በማድመጥ እና በጀቱን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‎በመጨረሻም የሐዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት የ2017 ዓ.ም ሪፖርትን እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ን በማቅረብ ውይይት ተደርጎበት ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‎ለበለጠ መረጃ
‎👉Our page https://www.facebook.com/profile.php?id=100064180623390
‎👉Our Telegram Channal
https://t.me/hawassacitycommunication
‎👉Our tiktok Account
‎tiktok.com/
‎Our WhatsApp Group
https://chat.whatsapp.com/Hw8xlXGEIlu5OfFzKbltO9
‎👉Our Instagram Account
https://www.instagram.com/hawassacom?igsh=MTJtdmh6eW5hM3QydA==
‎👉Our X Account
https://x.com/CityHawass34782?t=Pqws9rQukeetk4gFoKPffw&s=09
‎👉Our website
‎www.hawassa.gov.et

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎ የከተማ አስተዳደሩ  የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል።  የከተማ አስተ...
26/07/2025

የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎ የከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል።

የከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እየተደረገበትም ይገኛል ።

የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ
‎ሐምሌ 19/2017 ዓ.ም
‎ሐዋሳ

‎ምክር ቤቱ በዚህ በሁለተኛ ቀን ውሎው የም/ቤቱ 2ኛ ዙር 9ኛ ዓመት የስራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ እና የም/ቤቱ የ2017 ዓ/ም ሪፖርትና የ2018 ዕቅድ ቀርቦ ጸድቋል።

የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ የአስተዳደሩን 2017 ዓ/ም ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት በከተማዋ በርካታ ስራዎች በስኬት መጠናቀቅ የቻለበት ዓመት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የሲዳማንና የሐዋሳን ከፍታ የሚያረጋግጥ የኮሪደር ልማት፣ የፋራ ሂጣታ ውሃ ኘሮጀክት፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ግንባታ፣ በህብረተሰብ ተሳትፎ ጭምር የተሰሩ የፖሊስ ጽ/ቤቶችና የመሳሰሉትን ጠቁመዋል።

ከ15-25 ዓመታት የቆየ ማስፋፍያ ቦታ ኘላን የማውረድ ስራ፣ ለ17 ዓመታት የቆየ የአደረጃጀት ስራ ምላሽ የተገኘበትም ነው ሲሉ ከንቲባ መኩሪያ አክለዋል።

በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለመመለስ እንዲሁም ከተማችንን ተወዳዳሪ ለማድረግ ጭምር ከህዝባችን ጋር በጋራ እንሰራለን ነው ያሉት።

የሐዋሳ ከተማ ም/ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ደምሴ ዳንጊሶ በአስፈጻሚ አካላት የሚሰሩ ስራዎችን በዓመት አራት ጊዜ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግ ገልጸዋል።

በከተማዋ በተሰሩ ልማት ስራ፣ ከተማን በማስተዋወቅ፣በሰላምና ጸጥታ ስራ ለሌሎች ተሞክሮ መሆን የተቻለበት መሆኑን አክለዋል።

ተጀምረው የቆዩ ኘሮጀክቶችም በተሻለ ሁኔታ የተሰሩ እንዳሉ ገልጸዋል።

ከተከበሩ የም/ቤት አባላት መካከል አቶ ዘላለም ላሌ እና ወ/ሮ ወርቅአንጥፉ በላይ እንደገጹት በሪፖርት የቀረቡ ሀሳቦች በተግባር የተመለከትናቸው ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

የኮርደር ልማት ስራ፣ የተመረቁ ኘሮጀክቶች፣ ቀደም ብለው የተጀመሩና በመጠናቀቅ ላይ ያሉ ኘሮጀክቶች እና በህብረተሰብ ተሳትፎ ጭምር የተሰሩትን በተጨባጭ ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ አክለዋል።

አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም አንዳንድ ከተጀመሩ የቆዩ ኘሮጀክቶችም እንዲሁ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል ።

‎ለበለጠ መረጃ
‎👉Our page https://www.facebook.com/profile.php?id=100064180623390
‎👉Our Telegram Channal
https://t.me/hawassacitycommunication
‎👉Our tiktok Account
‎tiktok.com/
‎Our WhatsApp Group
https://chat.whatsapp.com/Hw8xlXGEIlu5OfFzKbltO9
‎👉Our Instagram Account
https://www.instagram.com/hawassacom?igsh=MTJtdmh6eW5hM3QydA==
‎👉Our X Account
https://x.com/CityHawass34782?t=Pqws9rQukeetk4gFoKPffw&s=09
‎👉Our website
‎www.hawassa.gov.et

‎''የሲዳማን ክልል ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እንሠራለን'' ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ‎‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/ጉዳ/መምሪያ‎ሀዋሳ‎ሐምሌ 19/2017 ‎‎በዛሬው እለት የሲዳማ ክ...
26/07/2025

‎''የሲዳማን ክልል ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እንሠራለን'' ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ

‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/ጉዳ/መምሪያ
‎ሀዋሳ
‎ሐምሌ 19/2017

‎በዛሬው እለት የሲዳማ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ከተሰማሩ ባለሀብቶች ጋር በክልሉ ልማት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እያካሄዱ ይገኛሉ።

‎በምክክር መድረኩ ላይ ርዕሰ-መስተዳድሩ ባስተላለፉት መልዕክት የክልሉ መንግስት ባለፉት አምስት ዓመታት የክልሉን ሁለንተናዊ ልማት ለማረጋገጥ ከባለሀብቱ ጋር በጋራ ያከናወናቸውን ስኬታማ ተግባራት አስረድተዋል።

‎በብልፅግና ጎዳና ላይ በሚገኘው የክልሉ ልማት የባለሀብቱ ሚና ጉልህ ድርሻ እንዳለው የጠቀሱት ርዕሰ-መስተዳድሩ፤ በቀጣይሞ የህዝባችንን የመልማት ፍላጎት እውን ለማድረግ ባለሀብቱ ከመንግሥት ጋር ተቀናጅቶ መሥራት እንዳለበት ገልፀዋል።

‎በክልሉ ኢንቨስተሮችን መሳብ የሚያስችል የተፈጥሮ ሀብት፣ የሰው ሀይል፣ መሠረተ-ልማት እና ሌሎች በርካታ ቅድመ-ሁኔታዎች መኖራቸውን ያስረዱት ርዕሰ-መስተዳድሩ፤ መንግስት በዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑና አስረድተዋል።

‎በተለይም ክልሉ የሚታወቅበትን ጥራት ያለው የቡና አምራችነትን ይበልጥ ለማጎልበትና የተሻለ የውጪ ምንዛሪን ለማግኘት በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ጠንክረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ነው ርዕሰ-መስተዳድሩ ያሳሰቡት።

‎በመድረኩ ላይ ከተሳታፊዎቹ ጥያቄና አስተያየት እየቀረበ ሲሆን፤ ርዕሰ-መስተዳድሩ ምላሽና ማብራሪያ የሚሰጡ ይሆናል።

‎በምክክር መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፤ በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንቨስተሮችና ባለሀብቶች፤ ቡና አምራች አርሶ አደሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ በማለት የዘገበው የሲዳማ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ነው።

‎‎ለበለጠ መረጃ
‎👉Our page https://www.facebook.com/profile.php?id=100064180623390
‎👉Our Telegram Channal
https://t.me/hawassacitycommunication
‎👉Our tiktok Account
‎tiktok.com/
‎Our WhatsApp Group
https://chat.whatsapp.com/Hw8xlXGEIlu5OfFzKbltO9
‎👉Our Instagram Account
https://www.instagram.com/hawassacom?igsh=MTJtdmh6eW5hM3QydA==
‎👉Our X Account
https://x.com/CityHawass34782?t=Pqws9rQukeetk4gFoKPffw&s=09
‎👉Our website
‎www.hawassa.gov.et

‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በከተማዋ ተከብሮ መጠናቀቁን አስመልክቶ ምስጋና አቀረበ‎‎የከተማዋ ከንቲባ አቶ መኩሪያ ማርሻዬ የዘንድሮው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል...
26/07/2025

‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በከተማዋ ተከብሮ መጠናቀቁን አስመልክቶ ምስጋና አቀረበ

‎የከተማዋ ከንቲባ አቶ መኩሪያ ማርሻዬ የዘንድሮው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እና ሀይማኖታዊ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ ለመከበሩ የየዘርፉ ተዋናኝ እና የፀጥታ ሀይሉ ከህዝብ ጋር በቅርበት በማክበር ላደረጉት አስተዋፆኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎ከወትሮው በተለየ መልኩ የዘንድሮው የሀምሌ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓልን የሀዋሳ ከተማ ህዝብ ከተለያዩ ክፍላተ ግዛቶች ከመጡ እንግዶች ጋር በአብሮነት መንፈስ ስለማክበራቸውም ከንቲባው ተናግረዋል።

‎ሀዋሳ የምንጊዜም የሁላችንም ምርጫ ከተማ ናት ያሉት ከንቲባ መኩሪያ ማርሻዬ ይህን በመገንዘብ ህዝባችን ከበዓሉ ቀደም ብሎ ምዕመኑን ዳዎኤ ቡሹ ብሎ በመቀበል ፍፁም የሆነ አክብሮትን በመስጠት በአብሮነት መንፈስ ስለማክበሩም ተናግረዋል።

‎የሀዋሳ ተመራጭነት ዘርፈ ብዙ ነው ያሉት ከንቲባው ለዚህም የዛሬው በዓል ማሳያ ስለመሆኑም በመግለፅ በዓሉ በሰላም ተከብሮ ለመጠናቀቅ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት ክልላችንን የሚመጥን ስራ ስለመሰራቱ ተናግረዋል።

‎መላው በዓሉን ለማክበር የመጡ እንግዶች በቆይታቸው ያማረ ጊዜ በሀዋሳ እንደሚኖራቸው በመተማመን የተናገሩት ከንቲባ መኩሪያ ማርሻዬ ለዚህም ምቹ የመዝናኛና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማቶች በበቂ ሁኔታ በከተማዋ እንደሚጠብቋቸው በመጠቆም ነው።

‎ለበለጠ መረጃ
‎👉Our page https://www.facebook.com/profile.php?id=100064180623390
‎👉Our Telegram Channal
https://t.me/hawassacitycommunication
‎👉Our tiktok Account
‎tiktok.com/
‎Our WhatsApp Group
https://chat.whatsapp.com/Hw8xlXGEIlu5OfFzKbltO9
‎👉Our Instagram Account
https://www.instagram.com/hawassacom?igsh=MTJtdmh6eW5hM3QydA==
‎👉Our X Account
https://x.com/CityHawass34782?t=Pqws9rQukeetk4gFoKPffw&s=09
‎👉Our website
‎www.hawassa.gov.et

Hawaasi Quchuma Jawaata Dagatenna Mootimmate Qinaabbinno Beeqqonni Latisate Looso Kaajjinshe Sunfannita Quchumu Gashshoo...
26/07/2025

Hawaasi Quchuma Jawaata Dagatenna Mootimmate Qinaabbinno Beeqqonni Latisate Looso Kaajjinshe Sunfannita Quchumu Gashshooti Egensiisi.

H/Q/G/M/K/H/Biddisha
Hawaasa, Maaja 19, 2017

‎‎Hawaasi Quchumi Amaale Mini 2ki Doycho 10ki Diri loosu yanna 23ki iurrinshu songo ha'risanni afamanno.

‎Quchumu Kantiiwi Kalaa Mekuriy Maarshayehu,mootimma quchumu daga latishshunna danchu gashshooti xa'monna hasatto kaima assitino batinye loossa loossino yiino.

‎Quchumu daga mootimmate ledo halamatenni quchumu lophote deerra gotti assitanno kooriderete latishsha, cufantino doogga fanate looso dancha gumulonni loonsoonni yee,konne kaajjinshe sunfannita xawisino.

‎Owaante aate amanyoote woyyeessate lao tunge loonsanni gedenna seedu diri dagate danchu gashshootinna owaantete qarra ikkitino quchumu tantano woyyeessate looso loonsoonnita qummi assino.

‎Loosu kaayyo kalaqate, doogotenna hodhishshu,rosu ,fayyimmate,way tuqqishshinna shiqqo,giwirinnunna saadate latishshi widoonni diru giddo jawaata looso loonsoonni yiino.

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa City Administration Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share