Luwa Media

Luwa Media ብዝሃነት ለኢትዮጵያ አንድነት፤ ልዩነታችንን በእኩልነት የምታስተናግድ ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የራሳችንን ጡብ እናስቀምጣለን። ኢትዮጵያ!
(10)

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ውድቀትና የቁልቁለት ጉዞ ማን ነው ተጠያቂው?!አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስን የቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ የሾመው የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ ለዳሞ የመጀመሪያ ተጠያቂ ናቸው...
12/08/2025

የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ውድቀትና የቁልቁለት ጉዞ ማን ነው ተጠያቂው?!

አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስን የቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ የሾመው የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ ለዳሞ የመጀመሪያ ተጠያቂ ናቸው። ሰለ ስፖርት ግንዛቤ የለሌውንና በወንጀል የተጨመላለቀውን ሰው አምጥቶ የሲዳማ ቡና ቦርድ አመራር ሰብሳቢ አድርጎው በመሾሙ ለሲዳማ ህዝብ ሀፍረት ቀዳሚ ተጠያቂ ነው። ሁለተኛ ተጠያቂ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ነው። አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በወቅቱ ባደረጃው የፖለቲካ ጡንቻ እያስፈራራ፣ የደጋፊዎችን ጬሄት በገንዘብ እየገዛ ክለቡን ከስፖርት ህግ ውጭ በጡንቻ እየመራ መቀመቅ በመክተቱ ሁለተኛ ተጠያቂ ነው።

በሦስተኛ ደረጃ ያለው የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የቦርድ አመራሮች ናቸው። በተለይም በተጨዋቾች ግዥ ወቅት የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ከአንድ ተጨዋች ከ1-4 ሚሊዮን ብር ፈርቅ በመያዝ ግዥ የፈፀሙ (አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ፣ አቶ ፍሬው አሬራ፣ አቶ ወሰንየለህ፣ ዶ.ር ዳዊት ሀዬሶ እና ከደጋፊዎች ማህበር አቶ ደጀነ ማርቆስ) ዋነኛ ተጠያቂዎች ናቸው። ከእነሱ ባሻገር የተጨዋቾች ግዥ ውሳኔ ያፀደቁ የቦርድ አመራሮች በሙሉ ለሲዳማ ቡና ውድቀትና ለሲዳማ ህዝብ ውርደት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ።

በአራተኛ ደረጃ የክለቡ ሥራ አስክያጅና ኮችንግ ስታፍ ተጠያቂ ናቸው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እገዳ ኪሣራም ቢሆን ገንዘብ ከፍሎ የሲዳማን ህዝብ ክብር መጠበቅ እየቻሉ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት ይዞ በመሄድ፣ የታገዱ ተጨዋቾችን በማሰለፍ፣ ቢያንስ ለኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታ እንኳን አንድም የቅጣት ገንዘቡን ከፍለው የታገዱ ተጨዋ ማሰለፍ ወይም የታገዱ ተጨዋቾችን ባለማሰለፍ የክለቡን ጥቅምና የህዝቡን ክብር መጠበቅ እየቻሉ ሆን ብለው በማሰለፋቸው ክለቡን ጎድተዋሉ። የሲዳማን ህዝብ አዋርደዋሉና ተጠያቂ ናቸው።

በአምስተኛ ደረጃ ይህ ሁሉ የሕግ ጥሰት እያለ ብለው ህዝብንና መንግሥትን ያሳቱ የክለቡን የውስጥ ውስጡን ጉዳይ የሚያውቁ የክለቡ አመራሮች በሙሉ ለዋንጫ አቀባበል ለባከነው ሀብትና ጉልበት፣ ደጋፊውና ሰፊው ህዝብ በአቀባበል ሥርዓቱ ለገጠመው ሀፍረት ተጠያቂ ናቸው።

ስድስተኛ በሕግ አግባብ ውጭ የተገዙ ተጨዋቾችም ክለቡ ለገጠመው ኪሣራና ያለአግባብ ለጎደፈው ሰፊው የሲዳማ ህዝብ ክብርና ስም ተጠያቂ ናቸው። ከሕግ አግባብ ውጭ እንደፈረሙ እያወቁ የተቀበሉትን ገንዘብ የክለቡን ጥቅምና የህዝቡን ክብር በጠበቀ መልኩ መያዝ ሲገባቸው በእንዝላልነት በመያዝ ከለቡን ለውስብሰብ ችግር በመዳረግ ለሲዳማ ህዝብ ውርደት ምክንያት በመሆናቸው ከተጠያቂነት አያመልጡም።

በሰባተኛ ደረጃ በዚህ ሁሉ ሂደት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና የሊግ ካምፓኒው በሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ላይ የፈፀሙትን የሕግ ጥሰትና የአሠራር ክፍተት በመጥቀስ ጉዳዩን በCAS በዘርፉ እውቀትና ጥበብ በተካኑ ባለሙያዎች በመምራት የክለቡን ክብርና የሲዳማን ህዝብ ክብር መጠበቅ እየተቻለ አቤቱታ እንኳን በአግባቡ ማቅረብ ባለመቻል ጉዳዩ ከጅምሩ ውድቅ እንዲሆን ያደረጉ አመራሮችና አካላት የህዝብንና የመንግሥትን ሞራል መጠበቅ የሚያስችል ሌላ እድል ያመከኑ በመሆናቸው ተጠያቂነት አለባቸው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብና የሊግ ካምፓኒው በአራቱ ክለቦች ላይ ብቻ ምርመራ አድርገው ያሳለፉት አድሎአዊ ውሳኔ እንዳለ ሆኖ የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ በታገዱ የቦርድ አመራሮች እየተመራ የታገዱ ተጨዋቾች እያጫዎተ ዓመቱን ሙሉ ዝምታ መርጠው ማስተካከያና የእርምት እርምጃ መውሰድ በማይቻልበትና ከምንም በላይ የኢትዮጵያ ዋንጫ አጨብጭበው ሰጥተው ህዝቡ ደስታውን ገልፆ ለዋንጫው ጮቤ ረግጦ አቀባበል ካደረገ ቦኋላ ያስተላለፉት ውሳኔ በእግር ኳስ ዓለም እጅጉን የሚያሳፍር ከመሆኑም በላይ ለሰፊው የሲዳማ ህዝብ ፌዴሬሽኑ ያለውን ንቀት የሚያሳይ በመሆኑ ፌዴሬሽኑ የታሪክ ተጠያቂ ነው።

Luwa Media

የሲዳማ ቡና እግርኳስ ክለብ ሁኔታ ከመቸውም ጊዜ በላይ አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፤ ~ዎላ! ክለቡ ምን ያህል የአመራር ድክመትና ክፍተቶች እንዳሉበት እያየን ነው። ክለቡ በገደል አፋፍ ላይ ቆ...
12/08/2025

የሲዳማ ቡና እግርኳስ ክለብ ሁኔታ ከመቸውም ጊዜ በላይ አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፤ ~ዎላ!

ክለቡ ምን ያህል የአመራር ድክመትና ክፍተቶች እንዳሉበት እያየን ነው። ክለቡ በገደል አፋፍ ላይ ቆሟል። ክለቡ አሁንም በፌዴሬሽኑ የተጠየቀውን መስፈርት አያሟላም። ፌዴሬሽኑ በአሁኑ ወቅት የክለቡ ተጫዋቾችን ማዘዋወር እንደማይችል እና ከዝውውር እንደታገደ አስታውቋል። ክለቡ የውስጥ ደንብ እና መመሪያ ባለማሟላቱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል።

ክለቡ የውስጥ ደንቦች እና መመሪያዎችን አክብሮ አለመሙላቱ ምን ማለት ነው?

የክለቡ የውስጥ ደንብ እና መመሪያ በመጀመሪያ ደረጃ የክለቡን ስም እና ዓላማ ይገልፃል። ፌዴሬሽኑ ሁሉም ክለቦች ስማቸውን እንዲቀይሩ መመሪያ ሰጥቷል። የሲዳማ ቡና አመራሮች ለፌዴሬሽኑ ትርጉም የለሽ ክርክር ከማድረግ ውጪ፤ ምንም አይነት አማራጭ ሃሳብ እንዳላቀረቡ እያየን ነው። ሲዳማ ቡና የእግር ኳስ ክለብ ነው፤ ከሲዳማ ብሔር ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፤ ስለዚህ የክለቡን ደጋፊዎች በማነጋገር ምን መሆን እንዳለበት በፍጥነት መወሰን አለባችሁ። ይህ ካልሆነ ግን ክለቡ ከሊጉ ከመባረር ውጪ ሌላ አማራጭ አይኖረውም።

ሌላው የክለቡ የውስጥ ደንብና መመሪያ ተደርጎ የሚወሰደው የክለቡ አመራሮች ህጋዊነት ጉዳይ ነው። በጣም የሚያሳዝኑ ነገሮች እያየን ነው፤ አሁን ያሉት ሁሉም የቦርድ አባላት ለሁለት ዓመታት መታገዳቸውን በይፋ ተነግሯል። ሲዳማ ቡና ክለብ የእነዚህን ወንጀለኞች ቡድን ስልጣን ለመጠበቅ ሲባል፤ ከአፍሪካ ውድድር ዉጪ ሆኗል። አሁን ክለቡን ከኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ለማባረር ህገወጥ ስራ እየተሰራ ነው።

ፌዴሬሽኑ የክለቡ አመራሮችን ህጋዊነት አስመልክቶ ለክለቡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። ፌዴሬሽኑ የክለቡን አመራሮች እንደማይቀበል በይፋ አስታውቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ግን እስከአሁን ዝምታ ለክልሉ ህዝብ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ጉዳይ ሆኗል። የክልሉን ህዝብ ያዋረዱ አመራሮች ተጠያቂ ይሆናሉ ብለን እንጠብቃለን። የክለቡ የውዝፍ ክፍያ አለመክፈል የክለቡን የውስጥ ደንብና መመሪያ ካለማክበር ጋር የተያያዘ ጉዳይ ነው። በመጨረሻም ክለቡን ለመምራት ሞራል እና ብቃት የሌላቸው ግለሰቦች ክለቡን ወደ ጥልቅ ሸለቆ እየወሰዱት መሆኑን ሁሉም ሰው ማየት ይችላል።

ከፌዴሬሽኑ ለክለቡ ከተሰጠው ማስጠንቀቂያ መረዳት የምንችለው፤ በክለቡ ውስጥ ያሉ አመራሮችን የስልጣን ተዋረድ የክለቦችን የውስጥ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ህገወጥ ቡድን መሆኑን ነው። ግራ የተጋባ አመራር ያለው ክለብ ነው። አሁንም የክለቡ ስራ አስኪያጅ ያልታወቀ፣ የክለቡ የቦርድ አባላት ስራ የማይታወቅ እና የክለቡ ፕሬዝዳንት ስራ አይታወቅም።

ክለቡ ሙሉ ለሙሉ መስራት ያልቻለው ሌላ ምን አለ? ለክለቡ ከተሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መረዳት የምንችለው፤ ክለቡ በተመለከተ የሚደረግ ስብሰባ ስነስርአት እና አጠቃላይ የስብሰባ መስፈርቶች በክለቦች የውስጥ ደንብና መመሪያ መሰረት ያልተከተሉ ናቸው። ክለቡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጠበት ሌላው ጉዳይ፤ የፋይናንስ አስተዳደርን በተመለከተ ነው። ከመጨረሻው ማስጠንቀቂያ የምንረዳው ክለቡ ፋይናንሱን እንዴት እንደሚያስዳድር፣ የበጀት አወጣጥ ሂደቱ፣ የገንዘብ አሰባሰብ እና ሪፖርት አቀራረብ ላይ ከፍተኛ ችግሮች እንዳሉበት ነው። ክለቡ ኦዲት ይደረግ እያልን በየጊዜው እየጮኸን ቢሆንም፤ የክለቡ አመራሮች በህገ ወጥ ተግባር እየቀጠሉ ነው። ክለቡ አመራሮች clop በአግባቡ ባለመሙላት ሌላ ለክለቡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

የክለቡ አመራሮች ይግባኙን ለ CAS በአግባቡ ባለማቅረባቸው ባልተገባ መንገድ ክለቡ ተሸንፈዋል። አሁን የክለቡ አመራሮች ሌላውን መስፈርት በትክክል መሙላት እንዳልቻሉ አይተናል። የክልሉ ፕሬዝዳንት ይህንን ህገወጥ ድርጊት በክለቡ እየገጠመው ያለውን አደጋ ለማስወገድ ጊዜ ሰጥተው መፍትሄ ሊሰጡ ይገባል። ከሲዳማ ቡና ውጪ በፕሪሚየርሊጉ ሁለት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጠበት ክለብ የለም።

በመሆኑም ጊዜ ሳያባክኑ አዳዲስ እውቀት ያላቸውን የቦርድ አመራሮችን በመሾም ክለቡን ከቅጣት መታደግ አለባቸው።

የቡና ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ሊጎዳ የምችል እና በአከባቢው ማህበረስብ ላይ ከፍተኛ የጤና ችግር ሊያስከትል የምችል ውሳኔ በክልሉ መንግሥት መወሰኑን ተሰማ፡፡                     ከ...
11/08/2025

የቡና ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ሊጎዳ የምችል እና በአከባቢው ማህበረስብ ላይ ከፍተኛ የጤና ችግር ሊያስከትል የምችል ውሳኔ በክልሉ መንግሥት መወሰኑን ተሰማ፡፡

ከእሸት ቡና ኢንዱስትሪ ፍቃድ አሰጣጥ ጋር ተያይዞ በተደጋጋሚ በሙስና እና አድሏዊ ስራ ስምሪት አሰራር ስማቸው የሚነሳው የክልሉ መንግስት በ2018 በጀት አመት ተጨማሪ 250 የእሸት ቡና ኢንዱስትሪ ፍቃድ በተለመደዉ መንገድ በማደል ህዝባዊ ቅቡልነት እጦት ለመመለስ በምል የተሳሳተ ግምት እና ግምገማ አቋም መያዛቸው ተሰምቷል፡፡

ስማቸዉ እንድጠቀስ ያልፈለገዉ መረጃ ምንጫችን ገለጻ ቡናና የሲዳማ ህዝብ ተነጣጥለው የምታዩ አይደለም ብለው፤ እስከአሁን ባለው መረጃ ከ561 በላይ የቡና ኢንዱስትሪዎች ተቋቁመው ወደ ሥራ የገቡ መሆኑን ገልፆ፤ በተለያየ ምክንያት በእርጅና ሥራ ያቋረጡ 84 ኢንዱስትሪዎች ሥራ ያቋረጡ መሆኑን እና ቀርዎቹ በሥራ ላይ እንደሆኑ ገልጸው፤ ሥራ ላይ ካሉ ኢንዱስትሪዎች 98 ኢንዱስትሪ የደስታ ሌዳሞ አስተዳደር ከክልል ምስረታ ዋዘማ አንስቶ እስከ 2017 ድረስ ባለው ጊዜ ከ1 ሚሊየን እስከ ሁለት ሚሊየን እጅ መንሻ በመቀበል ያደለው ህገወጥ ፍቃድ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

የቡና ኢንዱስትሪዎች ወራጅ ወንዞችን ተከትሎ የምቋቋሙ እንደመሆናቸው መጠን በአግባቡ ካልተያዙ ለአከባቢ ብክለት ከፍተኛ ድርሻ አላቸው። የአከባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በአግባቡ ስለማይቆጣጠራቸው እነዚህ የተበከሉ ወንዝ ተጠቃሚ ማህበረሰብ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛል።

የቡና ኢንዱስትሪ ፍቃድ አሰጣጥ የራሱ የሆነ ግልጽ መመሪያ እና መሥፈርት ያለው፣ የቡና ምርታማነትና ፖተንሻል ከግምት ያስገባ እና የቡና ጥራት ከግምት ያስገባ፤ ከአንዱ ኢንዱስትሪ ወደለላይኛው ኢንዱስትሪ 3 ኪሎ ሜትርና ከዝያ በላይ እርቀት እንዲኖረው የምል ግልጽ መሥፈርት ያለው መሆኑን ይታወቃልደ

ይሁን እንጂ ፍቃድ ለመሥጠት በአዋጅ መሠረት ሥልጣን የተሰጠው ግብርና ቢሮ ሆኖ እያለ፤ ቢሮው ከላይ የተጠቀሱ መሥፈርቶችን ስለምጠይቅና በቢሮ በኩል ጉቦ ለመሰብሰብ ሲላልተመቻቸው፤ በህገወጥ መንገድ በፕረዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፍና በዞን አስተዳዳርዎች አማካይነት፤ የመረጃ ምንጮቻችን ጥቆማ እንደሚያመለክተው፤ አዲስ ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ ጠያቂዎች ከእየአንዳንዳቸዉ ሁለት ሚሊየን ጉቦ እየተሰበሰበ እንደሆነና ተጨማር 250 ኢንዱስትሪ ፍቃድ ለማደል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤትና የዞን አስተዳደሮች በጦፌ የሙስና ግብይት ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል።

በሌላ በኩል አርሶ አደር ያልሆኑ እና ምንም የመሬት የይዞታ ደብተር የለላቸው የባለ ልዩ ጣዕም (ስፔሻል ቡና) ፍቃድ በምሥራቃዊ ዞን አንድ ሚሊየን ብር ጉቦ፤ በደቡባዊ፣ በማዕከላዊና ሰሜናዊ ዞኖች ከሦስት መቶ ሽህ በላይ ጉቦ እየከፈሉ መሆናቸዉ ተነግሯል። የዞን አስተዳዳርዎች በአደባባይ የምፈፀመዉ ሙስና ተዋናይ በመሆን ከመደበኛ ተግባራቸው ተነጥለው ጉቦ በማሰባሰብ ላይ ይገኛሉም ተብሏል።

ይህ ድርጊት እየተፈፀመ ያለዉ ብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ሙስናን እንታገላለን በማለት ባለ ሳባት ነጥብ ያለዉ የአቋም መግለጫ እያወጡ ባሉበት ሁነታ መሆን በምክር ቤቱ አቋም ላይ ጥርጣሬ አሳድሮአል።

ሉዋ ሚዲያ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የሲዳማ ቡና  ከለብ ወቅታዊ ሁኔታ አሰመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ለሚዲያዎች ጥሪ አድርጓል ፣ዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድቤት የሲዳማ ቡና ይግባኝ ሙሉ በሙ...
10/08/2025

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የሲዳማ ቡና ከለብ ወቅታዊ ሁኔታ አሰመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ለሚዲያዎች ጥሪ አድርጓል ፣

ዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድቤት የሲዳማ ቡና ይግባኝ ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ውሳኔ መስጠቱ ይታወቃል። ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ሰኞ ነሐሴ 5/2017 ከቀኑ 8:00 ላይ ካዛንቺስ በሚገኘው ጁፒተር ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ተዘጋጅቷል።

በመሆኑም የሚዲያ አካላት በስፍራው እና በሰዓቱ ተገኝታችሁ ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ እና የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡ በማክበር እንጠይቃለን ሲሉ ገልጿል።

ሉዋ ሚዲያ

ሲዳማ ክልል ከሁሉም ጥፋት ጀርባ አቶ ደስታ ለዳሞ እጆች በረዥሙ አሉ፤ ላለፉት ሳባት አመታት የሲዳማ ክልል ዉስጥ የተከናወነ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊ፣ ማህበራዊ ብሎም ስነልቦናዊ ዉርደት እያንዳን...
09/08/2025

ሲዳማ ክልል ከሁሉም ጥፋት ጀርባ አቶ ደስታ ለዳሞ እጆች በረዥሙ አሉ፤

ላለፉት ሳባት አመታት የሲዳማ ክልል ዉስጥ የተከናወነ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊ፣ ማህበራዊ ብሎም ስነልቦናዊ ዉርደት እያንዳንዱ ጥፋት እና ከአጥፊዎች በስተጀርባ የአቶ ደስታ ለዳሞ እጆች በረዥሙ አሉ። በመሆኑም ለሁሉም ቀዉስ ተጠያቂ ማንም አይደለም የመምራት አቅም ሆነ እዉቀት የለለዉ አቶ ደስታ ናቸዉ።

ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ በተመለከተ የአመታት ፍቅር በኃላ፤ ዘርፎ ባካበቱት ገንዘብ ተነፋፍቶ፣ እርስ በርሳቸዉ ትከሻ መለካካታ እና የስልጣን ሹክቻ ዉስጥ ገብቶ፤ በመጨረሻ በኃይል አሰላልፍ ብልጫ ተወስዶበት ቁጥጥር ሥር የሚገኘው አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ፊታዉራርነት እና የክልሉ ፕረዝዳንት “የበላይ ጠባቂነት” በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ውስጥ የተፈጸመው ዘረፋ እና እስፖርታዊ ፋይናንስ አሰራር ጥሰት ያልታሰበ ሳይሆን፤ ሆን ተብሎ እዛ አከባቢ ያለዉን ሀብት ለመቀራመት እና ተቋሙን አደጋ ላይ ለመጣል የተሰራበት ነዉ።

በህዝብ ቀጥኛ ድጎማ በሚደረግለት ይህ በርካታ ደጋፊዎች ያለበት ግዙፍ እግር ኳስ ክለብ ውስጥ፤ በዋነኛነት ለህዝብ አደራ ግድ የማይሰጣቸዉ፣ የግልጥቅም ላይ ተመርኩዞ ክልሉን መቀመቅ ዉስጥ የከተቱ፣ የክልሉ መንግሥት እና ባስቀመጣቸው ማፊያ ተዋናይነት በተፈጸመ ቅሌት ምክንያት የስፖርቱ ደጋፊ እና መላው ህዝቡ አሳዝኗል።

አሁን የተፈጠረው ክስተት በክልሉ ውስጥ ሌብነትን በመላመዳቸው በተነሳ ሙስናነቱን በዘነጉ ግለሰቦች የተፈጸመ መሆኑ አያጠራጥርም። ሁነቱን ልዩ ያደረገው ሌብነቱን “ሌብነት ነው” ቢሎ የሚጠራ ተቋም ከክልሉ ውጭ መምጣቱ ብቻ ካልሆነ በስተቀር መሰል ዘግናኝ ቅሌቶች በክልሉ በየቀኑ የሚፈጸሙ ለነገም መቆማቸው አጠራጣሪ ናቸው።

ከመንግሥት መስሪያ ቤቶች ወጥቶ መልኩን በመቀየር በኢትዮጵያ እግር ኳስ ሜዳዎች ላይ ራሱን የገለጠውን የሲዳማ ክልል ህዝብ ሰቆቃ የፌደራል መንግሥት፣ የዴሞክራሲ፣ የፍትህ ተቋማት እና የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ በማድረግ በክልሉ ውስጥ የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት እንደ መነሻ እንዲወስዱት ጥሪ እናቀርባለን።

ሉዋ ሚዲያ

ቀድሞ ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ለማስጠየት በቂ መረጃ ባለመቅረቡ በዋስትና መብት ልለቅ እንደምችል ፍርድ ቤቱ አስታወቀ፤አቶ አለማየዉ ጢሞቴዎስ ባሳለፍነው ሰኞ ሀምሌ 29 ወደ ችሎት የቀረበ ስሆን ፍር...
08/08/2025

ቀድሞ ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ለማስጠየት በቂ መረጃ ባለመቅረቡ በዋስትና መብት ልለቅ እንደምችል ፍርድ ቤቱ አስታወቀ፤

አቶ አለማየዉ ጢሞቴዎስ ባሳለፍነው ሰኞ ሀምሌ 29 ወደ ችሎት የቀረበ ስሆን ፍርድ ህደቱ ዳኞችና መርማሪ ፖልስ ለረጅም ሰአት ያከራከረ ሆነዉ አልፏል ተብሉዋል። በሰዳማ ክልል መንግስት ተከሰዉ ታስሮ የምገኘዉ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ከታሰረ በኃላ ለመርማሪ ፖልስ የመጀመሪያ ቃሉን ከሰጠ ወድህ ፍርድ ቤት ስቀርብ ይህ ለሁለተኛ ግዜ መሆኑን ታዉቆዋል።

አቶ አለማየዉ ጥሞቲዎስ በመንግስት ተከሰዉ ከታሰረ በኃላ የተከሰሰበት ጉዳይ አስመልክተዉ መጀመርያ ቃሉን ለፍርድ ቤት በሰጠበት ግዜ ከሳሽ አቃበ ህግና መርማሪ ፖልስ አስፈላግ ምርመራ አድርጐ ባለመጨረሱ ተጨማሪ ግዜ ይሰጠኝ ብሎ ጠይቀዉ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ ግዜ ቀጠሮ ሰጥቶ እንደነበረ ምንጮች ለሉዋ ሚዲያ ገልጸዋል።

ግዜ ቀጠሮዉ ደርሶ ሁለተኛ ግዜ ወደ ፍርድ ቤት የቀረበዉ ተከሳሽ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ፤ የተከሰሰበትን ጉዳይ አስመልክተዉ መርማሪ ፖልስ እስከ አሁን ያገኘዉ መረጃ ለችሎቱ እንድያቀርብ ዳኞችን መጠየቁን ተነግሩዋል።

ይሁን እንጂ መርማሪ ፖልስ እስከ አሁን የምፈልገዉን መረጃ አላገኘዉም፣ የኦድት ርፓርት አልደረሰኝም፣ ተከሳሹ ምጠቀመዉን የግል ስልክ ፈትሻችዉ ላኩልን ብለን ለኢንሳ የላክነዉ ብሆንም እስከ አሁን ኢንሳ ምንም መልስ አልሰጠንም ወዘተ ምክንያት ደርድሮ፤ ሰለዝህ አሁንም ተጨማሪ ግዜ ቀጠሮ 14 ቀን ይሰጠኝ ብሎ መጠየቁን መረጃ ምንጮቻችን ነግሮናል።

ጥያቄ የቀረበለት ፍርድ ቤት ጉዳዩ የያዙ ዳኞች፤ ፖልስ ያቀረበዉ ምክንያት ዉድቅ አድርጎ እስከ አሁን የሰጠናችዉ ግዜ ያላቹትን መረጃ ለማሰባሰብ ከበቅ በላይ ነበር፤ ነገር ግን በተሰጣችዉ ግዜ ዉስጥ ምንም የምጨበጥ ነገር ማቅረብ አልቻላችዉም ብሎ መርማሪ ፖልሶችን ሀይለ ቃላት ተጠቅመዉ እንደወረፈ አቃበ ህግ ምንጮቻችን ነግሮናል።

አቶ አለማየዉ ጥሞቲዎስ በበኩሉ፤ ክልሉ መንግስት በምክር ቤት ያለ መከሰስ መብቴን አንስቶ ስያስረኝ መረጃ አለኝ ብሎ እንደሆነ ይታወቃል፤ ፖልስ ደግሞ አሁን መረጃ እየፈለኩ ነዉ ማለቱ ተቀባይነት ያለዉ ምክንያት አይደለም፤ ህግ ባለበት አገር ማንኛዉም ዜጋ ያለበቂ ማሰረጃ አይታሰርም እኔ ስዳማ ህዝብን በከፍተኛ ሀላፍነት ቦታዎች ሳገለግል የነበረኩ ሰዉ ነኝ ሰለዝህ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብቴን ያስከብርልኝ ማለቱን በማለት እንደተከራከረ ተነግሯል። የተከሳሽ ጠበቆችም ክሱ ዋስትና የምከለክል አይደለም ብሎ የህግ አንቀጾችን ጠቅሶ ብዙ መከራከርያ አቅርቦዋ።

እንደ ምንጮቻችን መረጃ፤ ዳኞቹም መርማሪ ፖልስ ለክስ እያቀረበ ያለዉ ምክንያት ዋስትና መብት የምከለክል አይደለም በማለት ለፖልስ ምላሽ ከሰጡ በኃላ ጉዳዩን ግራ ቀኝ አይቶ ከመጨረሻ ማስጠንቀቅያ ጋር ተጨማር ግዜ ቀጠሮ መስጠቱን ከምንጮች ሰምተናል።

በሌላ በኩል ማለዳ ሚዲያ ከምንጮች አገኘሁት ብሎ እንዳስነበበዉ መረጃ ከሆነ፤ ግለሰቡ የተከሰሰበት ተደራራቢ ክሶች ላይ ከሳሽ አቃቤ ህግ በቂ መረጃ እያቀረበ እንዳልሆነ የፍርድ ቤቱ ምንጮች አሳውቋል ብሏል። ሚዲያዉ አክሎም፤ በተለይ ግለሰቡ ስልጣኑን በመጠቀም የሰራቸው ወንጀሎች በአብዛኛው ግልጽ እንደሆነ የነገሩን የማለዳ ምንጮች የክልሉ መንግስት የአቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ የወንጀሉን ልክ እና ስፋት በጥልቀት እንዲታወቅ አልፈለገም ይባላል ብሏል።

ማለዳ ሚዲያ “መሰረጃ ያጋሩኝ አንድ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ባልደረባ” ብሎ እንደዘገበዉ፤ የክልሉ ፕረዝዳንት የአለማየሁ ጢሞቴዎስ የወንጀል መዝገብ በሚፈለገው ልክ እንዳይሄድ ቀድሞዎኑ የራሱን በድን አደራጅቶ ሲያደናቅፍ መቆየቱን ተናግሮ፤ በአሁኑ ጊዜ በፍርድ ቤት እየቀረቡ ያሉ የምርመራ ሰነዶች በተጨባጭ የግለሰቡን ወንጀል ዝርዝሮች አስረጂ አለመሆናቸውን አሳውቋል። ከዚህ ጋር የሚገናኘው ሉዋ ሚዲያ ዘግበን እንደነበር ይታወቃል።

በሌላ በኩል ፕሬዝዳንቱ ከግለሰቡ ጋር ቀጥተኛ የሆነ የተለያዩ የወንጀል ተሳትፎ ልኖራቸው ይችላል የሚል ምክንያታዊ ጥርጣሬ በመኖሩ አሁንም ቢሆን የግለሰቡን የፍትህ ሂደቱ በገለልተኛ ፍትህ አካላት ካልተመራ ውጤቱ የሚፈለገው እንደማይሆን ጠቁሟል።

ሉዋ ሚዲያ

ኢፌዲሪ ጉምሩክ ኮሚሽን ያወጣዉን ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ተከትላችሁ ተወዳድራችሁ ያለፋቸው የመጨረሻ እጩ ሰራተኞች ስም ዝርዝር ወጥቷል ኢፌዴሪ ጉሙሩክ ኮሚሸን ባወጣ ክፍት ስራ ቦታ ማስታ...
07/08/2025

ኢፌዲሪ ጉምሩክ ኮሚሽን ያወጣዉን ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ተከትላችሁ ተወዳድራችሁ ያለፋቸው የመጨረሻ እጩ ሰራተኞች ስም ዝርዝር ወጥቷል

ኢፌዴሪ ጉሙሩክ ኮሚሸን ባወጣ ክፍት ስራ ቦታ ማስታወቂያ ሲዳማ ክልል አመልካቾች ባለፈው ተወዳድረው ለጉምሩክ ያለፉ ተወዳዳሪዎች የመጨረሻ 147ቱ እጩ ሰራተኞች ስም ዝርዝር አወጥቷል።

የመጀመሪያ ዙር አወዳድሮ ያለፉ ተብሎ የወጣ ስም ዝርዝር የተቀሩት እጩ ተወዳዳሪዎች የአግባብነት ቅሬታቸው ለኮሚሽኑ አቅርበው የነበሩ ሲሆን፤ ቅሬታዉን ተከትሎ ኮምሽኑ ያደረገዉ ማጣራት መጀመሪያ ዙር ለእጩነት ካለፉት ውስጥ 58ቱ አግባቢነት የለውም ተብሎ በቅሬታ አቅራቢዎች እንዲተኩ ተደርጎ የመጨረሻ አሸናፊዎች ስም ዝርዝር ዛሬ ወጥቷል።

እንደ ተቋሙ ማስታወቂያ ዛሬ 8:30 ድረስ ርፖርት አድርጉ ነዉ የተባለው። እስከአሁን ርፖርት ያላደረጉ ጥቂት ልጆች ስላሉ #ሼር በማድረግ አድርሱላቸው!

ያለፋችሁ እንኳን ደስ አላችው!

ሉዋ ሚዲያ

በሲዳማ ሕዝብ ላይ አደገኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቷል ፤ዓለም አቀፍ ሚዲያ የሆነ BBC Afaan Oromo, DW Amharic, Ethio Forem እና ሌሎቹም ተቀባብለው ዘግበዋል፤ ...
07/08/2025

በሲዳማ ሕዝብ ላይ አደገኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቷል ፤

ዓለም አቀፍ ሚዲያ የሆነ BBC Afaan Oromo, DW Amharic, Ethio Forem እና ሌሎቹም ተቀባብለው ዘግበዋል፤ BBC Afaan Oromo በሲዳማ ወገን በኩል ያለዉን መረጃ ለማግኘት አልቻልኩም ብሎ የጀመረውን ሚዛናዊነት የጎደለዉ የአንድ ወገን ፍላጎት በAfan Oromo ያሰራጨውን ዘገባ፤ ትናንትናዉ ሌት በአመሻሽ ላይ DW Amharic ሳያጣራ ከአንድ ወገን ትሪክትና ውንጀላ ብቻ ይዞት የወጣው ዘገባ ሲዳማ ሕዝብን ተቀባይነት የለውም ።

በዘገባቸው ላይ ሲዳማ ክልል ከሆነ ወዲህ መሬት ጠቦኛል በማለት፤ ቤት እያቃጠሉ፤ ሰው እየገደሉ ወረራ ማካሄድ ጀምሯል የሚል ነው። ይህ ዘገባቸው ግን መላው የሲዳማ ሕዝብን ያስቆጣ ጉዳይ ሆነዋል፤ ዘገባቸውም ተቃራኒ ዘገባ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

ይህንን ግጭት ለሚዲያችን መረጃ መላኪያ Bot በኩል ወዲያውኑ የተላከልን ቢሆንም፤ ሲዳማ እና ኦሮሚያ ድንበር አከባቢ ህዝቡ ከዚህም፣ ከዛም ተቆራኝተዉ አንድ ላይ የሚኖር ህዝቦች በመሆኑ ብዙ ነገር እንዳለ ግምት ዉስጥ በማስገባት ፤ እንደዚህ አይነት ግጭቶች ጎልቶ ካልተወጣ በስተቀር ወደ ሚዲያ ማውጣት ተገቢ አይደለም፤ ከወጣ ግጭቱ ይባባሳል የሚል እምነት ስላለን ሳናወጣ ይዘን አቆይተንዉ ነበር።

አሁን ግን በራሳቸው የጀመሩት ሕገወጥ ተግባር BBC Afaan Oromo, DW Amharic እና ሌሎች በኩል የስም ማጥፋት ዘገባ እና በሲዳማ ሕዝብ ላይ ለመውረር የተፈለገው ዓላማ አሰራጭቷል። ሲዳማ ግን በየትኛውም ቦታና አከባቢ ግጭት ቀስቃሽና ነገር ፈላጊ ሕዝብ እንዳልሆነ ይታወቃል።

ይህንን ዘገባ በማስመልከት አቶ ጃዋር በበኩላቸው ወንድማማቾች ሲዳማ እና ኦሮሞ ህዝብ መካከል ግጭት ሆን ተብሎ ለመቀስቀስ የተሸረበ ሴራ መሆኑን አስታዉሶ ህዝቡ ይህንን አዉቆ የፖለቲካ መጠቀሚያ እንዳይሆን አፅንኦት ሰጥቷል።

በሲዳማ ክልል በኩል እስከአሁን ድረስ ምንም የተባለው ነገር ባይኖርም፤ ነገር ግን መልስ ይሰጣሉ ብለን እንጠብቃለን። ይሁን እንጂ ይህንን ዘገባ የሰሩ ጋዜጠኞችም በሚዲያ ሕግ መጠየቅ እንዳለባቸው ሚዲያችን በጽኑ ያምናል!

DW Amharic ያሰራጨው ዘገባ ከታች ባለው Link ላይ አግኙ
👇
https://www.facebook.com/share/p/16LPtUXrXp/

Luwa Media

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማህበር የቡና መለያ (ብራንድ) እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ ሲዳሞ የሀረር እና የይርጋጨፌ የቡና ስያሜዎችና የንግድ ምልክት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ ቢሆንም፤ እንደ ...
06/08/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማህበር የቡና መለያ (ብራንድ) እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ

ሲዳሞ የሀረር እና የይርጋጨፌ የቡና ስያሜዎችና የንግድ ምልክት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ ቢሆንም፤ እንደ ሌሎች ሀገራት የኢትዮጵያን ቡና የሚያስተዋውቅ ሀገራዊ የቡና የምርት መለያ አለመኖሩ ችግር እንደፈጠረ ይነሳል።

ለመፍትሄውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማህበር ከኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ዩኒቨርሲቲዎች እና የምርምር ማዕከላት ጋር በመሆን የቡና ብራንድ እያዘጋጀ መሆኑን ገልጿል።

የማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሁሴን አምቦ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የቡና ብራንድ ወይንም የቡና ምርት መለያን ለመፍጠር እየተሰራ ይገኛል።

ለዚህም የሲዳማ ቡና ብራንድ ዝግጅት ተጠናቆ የዝርዝር ይዘት መግለጫ ወይም (book of specification) ማዘጋጀት መጀመሩን አንስተዋል።

"ቡና የራሱ የሆነ ብራንድ ሲኖረው በዓለም አቀፍ ገበያ ያለው ተደራሽነት እንዲሁም ፍላጎት ይጨምራል" ሲሉ ዶክተር ሁሴን ተናግረዋል።

አክለውም የኢትዮጵያ ቡና ባለልዩ ጣዕም መሆኑን አንስተው፤ የአረቢካ ቡና በዓለም ገበያ ላይ ያለውን ከፍተኛ ተፈላጊነት አንስተዋል።

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ባለልዩ ጣዕም የግብርና ምርቶችንና ተያያዥ አገልግሎቶችን፣ የገበያ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግና አምራቾች ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ምርቶቹንና ተያያዥ አገልግሎቶችን በምቹ የአእምሯዊ ንብረት ዘዴ (ብራንድ) ማስጠበቅ እንደሚያስችል መግለጹ ይታወሳል።

ሉዋ ሚዲያ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች ስልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የሙስና ወንጀል በፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነ፤ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና...
06/08/2025

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች ስልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የሙስና ወንጀል በፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነ፤

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ችሎት የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሁለት የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች በፈፀሙት ስልጣንን ያለ አግባብ መገልገል ወንጀል ጥፋተኛ ሆነዉ በመገኘታቸዉ በጽኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላለፈ።

አንደኛ ተከሳሽ የሆኑት በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የምዝገባ እና ቁጥጥር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታምሩ ግንበቶ እና 2ኛ ተከሳሽ በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የውጪ ዜጎች ቁጥጥርና ቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጅላሉ በድሩ የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 9(1) (ሀ) መተላለፋቸው ተመላክቷል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ሙስና ጉዳዮች ችሎትም ተከሳሾቹ ጥፋተኝነታቸዉ በሰዉ እና በሰነድ ማስረጃ በመረጋገጡ 1ኛ ተከሳሽ ታምሩ ግንበቶ በ8 አመት ፅኑ እስራት እና 1 ሺህ ብር፤ 2ኛ ተከሳሽ ጅላሉ በድሩ ደግሞ በ4 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ ማሳለፋን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።

ሉዋ ሚዲያ

የሲዳማ ቡና እግርኳስ ክለብ ጥያቄውን (CAS) ዉድቅ አድርጓል ተብሎ በፌደሬሽኑ የተሰራጨው መረጃ አሳሳች ነዉ።ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዉሳኔ ቅር ተሰኝቶ ...
05/08/2025

የሲዳማ ቡና እግርኳስ ክለብ ጥያቄውን (CAS) ዉድቅ አድርጓል ተብሎ በፌደሬሽኑ የተሰራጨው መረጃ አሳሳች ነዉ።

ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዉሳኔ ቅር ተሰኝቶ ወደ ዓለም-አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (CAS) የወሰደው ይግባን ዋና ጉዳዩ ህደት ላይ መሆኑን ተገልጿል።

አለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት የሲዳማ ቡና ጥያቄን ውድቅ አድርጓል ሲል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የገለፀው አሻሻች መረዳ መሆኑን፤ በሲዳማ ቡና እግርኳስ ክለብ በኩል ተወክለው ጉዳዩን በመከታተል ላይ የሚገኙት ረ/ፕሮፌሰር ተሰማ ኤሊያስ በይፋዊ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ገልጸዋል።

እንደ ረ/ፕሮፌሰር ተሰማ ኤሊያስ ገለጻ ገላገይ ፍርድ ቤቱ ዉድቅ ያደረገዉ ዋና ይግባኙን ሳይሆን በሲዳማ ቡና በኩል የቀረበውን የአፍሪካ ዋንጫ ድልድል እንዳይካሄድ እገዳ እንዲደረግ ያቀረበዉ አቤቱታ ባልታወቀ ምክንያት ወድቅ አድርጓል ብሎ እሱንም እንደገና እንድታይ ጠይቀናል በማለት ገልጿል።

የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ በበኩላቸዉ በፌደሬሽኑ የተወሰነበትን ውሳኔ በመቃወም ወደ ዓለምአቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድቤት (CAS) በመውሰድ፤ የይግባኝ ሂደቱም በቁጥር "CAS 2025/A/11595 Sidama Bunna Football Club Vs Ethiopian Football Federation" ተመዝግቦ እየታየ ህደት ላይ ነዉ ብሏል።

ሉዋ ሚዲያ

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Luwa Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category