02/11/2025
#መረጃ: ሉዋ ሚዲያ አብዝቶ ሽፋን ሰጥተዉ ስታገል የነበረው ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ከድሀው እናት በኃይል በመቀማት ያስገነቡት ቤት ትናንትናው ዕለት ለእውነተኛ ባለቤት ተመልሷል።
ሀዋሳ ላይ በክልሉ እና በከተማ አስተዳደሩ ሹማሚንት ከደሃው ላይ ስልጣናቸውን ተጠቅመው ወደ 88 የሚጠጉ የቀበሌ ቤቶችን በመንጠቅ፣ ቁጥራቸው ወደ 627 የሚጠጋ የቤተሰብ አባላቶችንም አፈናቅለው ሜዳ ላይ ጥለዋቸዋል ስንል በተደጋጋሚ ዘግበን እንደነበር አይዘነጋም።
ከፌደራሉ መንግስት በተላለፈዉ ትዕዛዝ መሠረት ከብዙ ጥቂቱ በዚህ ሳምንት ለተፈናቃዮች እንደተመለስ ሰምተናል። እን አገዛዙ ገለጻ ሁለተኛ ዙር ተብሎ የተሰየመዉ የትናንቱ ቤት ግን ከሁሉም ከሁሉም በላይ እኛም በተደጋጋሚ አጽንኦት ሰጥተን ያጋለጥነዉ ቤት ነበር።
የዚህ ቤት ቀማኛ አፈናቃይዋ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ይባላሉ። ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ቀድሞ የክልሉ ሰዉ ሀብት ቢሮ ሃላፊ የነበሩ እና የባለስልጣናት ቤተሰቡ የመንግስት መስሪያ ቤት ወሳኝ፣ ወሳኝ መደቦችን ያለዉድድር ያደሉ እና ለዘመዶቿዋ ኮሌጅ እንኳ ሳይጨርሱ ይህ መደብ ለአንተ፣ የአንች ነዉ እያሉ የተፈለገዉ ሰዉ ትምህርት ጨርሶ እስክመጣ ለአመታት ስያስቀመጡ እንደነበር ይነገራል።
እኚህ ሃላፊዋ በተሰጣት ተልእኮ መሠረት የሰክተሩን ሪሶርስ አሟጠዉ በባለስልጣናት ቤተሰብ ካደራጁ በኋላ ነዉ አሁን ወዳሉበት የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊነት የተመደቡት፣ ይህ ሰክተር በፈደራሉ መንግስት ትኩረት አቅጣጫ መሠረት ከፍተኛ የገንዘብ ፍሰት የሚገኝበት ሰክተር እንደሆነ ይታወቃል።
እኚሁ ባለስልጣን የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልም ናቸዉ፣ የክልሉ ምክር ቤት አባልነትን ጨምሮ አጠቃላይ ከ15 በላይ ተቋማትን በቦርድ አባልነት የሚመሩ የክልሉ ፕሬዚዳንት የአቶ ደስታ ሌዳሞ በጣም ታማኝ፣ የቅርብ ሰው እና ቀኝ እጅ ናቸው።
ክብርት ወይዘሮዋ ከ2013 ጀምሮ እሰካሁን ድረስ የሚኖሩት በሀዋሳ ከተማ በተለምዶው TTC (ሀዋሳ መምህራን ኮሌጅ) ፊት ለፊት በሚገኘው የመንግስት የቁጠባ ቤት ውስጥ ነው።
በቁጠባ ቤት እየኖሩም ሌላ ተጨማሪ ቤት ያምራቸውና በምስሉ ላይ በምታዩት ግቢ ውስጥ ይኖሩ የነበሩትን እናት ጨክነው በማባረር በኮንትራክተር ባለቤታቸው (ከጥቂት ግዜ በፊት 1,624 ብር ተቀጣሪ ሹፌር የነበረ) አማካኝነት፤ ከሐዋሳ ማዘጋጃ ቤት የኮሪደር ልማቱ በጀት ውስጥ ተካቶ እና እራሷ ከምትመራዉ ቢሮ በጀት ተጨምሮበት በምታዩት መልኩ ቤቱ እምር ብሎ ተሰርቶ አልቆ ከቤተሰቦቿ ጋር ጠቅልላ ልትገባ ሁለት ሳምንት ሲቀራት ከፌዴራሉ መንግስት በተሰጠው ቀጭን ትዕዛዝ ተግባራዊ እንዲደረግ የተባለው ግምገማ ተቀመጡ።
በዚህ ወሽመጥ ቆራጩ ግምገማም ስልጣናችሁን ተገን አድርጋችሁ ደሀውን አፈናቅላችሁ የግላችሁን ቤት ገንብታችሁ የገባችው ሁሉ ውጡ የሚል ትዕዛዝ ተላለፈ። ትዕዛዙ የመጣውም በቀጥታ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት ነበር። እኚህ ምስኪን ተፈናቃዮች ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመልክተውም ነበር።
ሉዋ ሚዲያ