Luwa Media

Luwa Media ብዝሃነት ለኢትዮጵያ አንድነት፤ ልዩነታችንን በእኩልነት የምታስተናግድ ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የራሳችንን ጡብ እናስቀምጣለን። ኢትዮጵያ!
(11)

ጎጎጎጎል ሲዳማ ቡና 2 - 1 ነጌሌ አርሲ  #ሮሪ  #ሲዳማ!! 🔥🔥🔥🔥ሉዋ ሚዲያ
25/04/2026

ጎጎጎጎል ሲዳማ ቡና 2 - 1 ነጌሌ አርሲ #ሮሪ #ሲዳማ!! 🔥🔥🔥🔥

ሉዋ ሚዲያ

 #ኢትዮጵያ  #ዋንጫ: ሲዳማ ቡና የአምናውን የሴራ “ክብር ገፈፋ” ለመበቀል በቁጭ የጀመረው እንቅስቃሴ ዘርፌ-ብዙ አዎንታዊ ውጤቶች እያስመዘገበ ይገኛል።አርሲ 0 - 1 ሲዳማ ቡና !!ሉዋ ሚ...
25/04/2026

#ኢትዮጵያ #ዋንጫ: ሲዳማ ቡና የአምናውን የሴራ “ክብር ገፈፋ” ለመበቀል በቁጭ የጀመረው እንቅስቃሴ ዘርፌ-ብዙ አዎንታዊ ውጤቶች እያስመዘገበ ይገኛል።

አርሲ 0 - 1 ሲዳማ ቡና
!!

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: በሲዳማ ክልል የመንገድ መሠረተልማት እጦት ማህበረሰቡ አደጋ ላይ ወድቀዋል፤ የሲዳማ ክልል ሆሮሬሳ፣ ቡራ፣ ዳኤላ እና አርበጎና ወረዳዎች ሕዝብ በመንገድ እጦት ከፍተኛ ሁኔታ ችግር ...
25/04/2026

#መረጃ: በሲዳማ ክልል የመንገድ መሠረተልማት እጦት ማህበረሰቡ አደጋ ላይ ወድቀዋል፤

የሲዳማ ክልል ሆሮሬሳ፣ ቡራ፣ ዳኤላ እና አርበጎና ወረዳዎች ሕዝብ በመንገድ እጦት ከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ የአካባቢው ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው።

በተለይም በቡራ ወረዳ ሸታመ ቀበሌ አንዲት ታማሚ እናት ወደ ሕክምና ተቋም ለማድረስ የሚያስችል መንገድ ባለመኖሩ፣ የአካባቢው ወጣቶች በትከሻቸው ተሸክመው ለማጓጓዝ መገደዳቸውን የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በተከሰተ ማንኛውም ድንገተኛ ሕመም፣ ምጥ የያዛቸው እናቶች ሆነ ሌላ አደጋ ነዋሪዎች ያለምንም አማራጭ በቃሬዛ ተሸካሚነት ብቻ ሕይወት ለማትረፍ እየተገደዱ ነው።

ነዋሪዎቹ “በዚህ ዘመን አንድ አካባቢ መንገድ የለውም ማለት አሳፋሪ ነው” ሲሉ ቁጥታቸው በመግለፅ ላይ ናቸው። በመሆኑም የሚመለከታቸው የክልሉና የፌዴራል መንግሥት አካላት ይህን የተረጋገጠ የሕዝብ ችግር በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጥሪ ቀርቧል።

መንገድ ለዘመናዊ ሕክምና፣ ለንግድና ለትምህርት ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ መሠረታዊ ክብር መጠበቂያ መሆኑን እናሳስባለን!

👉 እርስዎም ይህን ልጥፍ በማጋራት ለአካባቢው ሕዝብ ድምፅ ይሁኑ!

#ሲዳማ #ቡራ #ሸታመ #ኢትዮጵያ

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: ሲዳማ ክልል ዝቅተኛ የመራጮች ምዝገባ ተደርጓል፣ ቦርዱ ሁለት ምርጫ ጣቢያ ማገዱን ገልጿል፣ የምርጫ ሂደት በርከት ያሉ ተግዳሮቶች ያስተናገደ መሆኑን ተነግሯልብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ...
24/04/2026

#መረጃ: ሲዳማ ክልል ዝቅተኛ የመራጮች ምዝገባ ተደርጓል፣ ቦርዱ ሁለት ምርጫ ጣቢያ ማገዱን ገልጿል፣ የምርጫ ሂደት በርከት ያሉ ተግዳሮቶች ያስተናገደ መሆኑን ተነግሯል

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በክልሉ ህግ ጥሰት የፈጸመው ናቸው ያላቸውን ሁለት ምርጫ ጣቢያዎች መሰረዙን አስታውቋል። ቦርዱ ይህንን ይበል እንጂ በርከት ያሉ ጥሰቶች እንደተፈጸመ የአይን እማኞች ይናገራሉ። የክልሉ ዘጎች ከምርጫ ራሳቸውን ማግለላቸው ተነግሯል። እስከ አሁን ባለው መረጃ መሠረት የመራጮች ምዝገባ አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆኑ ተገልጿል።

በደቡባዊ ሲዳማ ዞን እና በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን የቀረቡ እጩዎች 80 በመቶ የሚሆኑት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት ቤተዘመድ ወንድሞች እና የአጎቱ ልጆች መሆናቸው ተጠቅሷል። በዚህም ምክንያት ቀደም ሲል በከፍተኛ የጎሳኝነት ችግር የሚወቀሰው የክልሉ መንግሥት፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት አባላት የአመራሩ ቤተሰቦች በመሆናቸው የክልሉ ሕዝብ ደስተኛ አለመሆኑን ተገልጿል። በዚህም የክልሉ ሕዝብ ከምርጫ ራሱን ለማራቅ መወሰኑ ተነግሯል።

በሕዝብ አቋም የተደናገጠው የክልሉ አመራር ምርጫ አስፈጻሚዎችን በገንዘብ በመደለል ላይ መሰንበቱን ተነግሯል ። በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ጎርቼ ምርጫ ክልል ሙራንቾ ጎርቼ ምርጫ ጣቢያ 463 መራጮች በአካል ሳይቀርቡ ቤት ለቤት በመዞር ተመዝግቦ የተዘጋጀ ሐሰተኛ ሰነድ በሕዝብ ጥቆማ መያዙ ታውቋል። ይህም የምርጫ ዴሞክራሲያዊነትን አጠያያቂነት ውስጥ የሚከት ሆነው አልፏል። በተደጋጋሚ ምርጫውን ህገወጥ የሚያደርግ ድርጊት መፈጸሙን ተገልጿል።

ዘገባው 7ኛ ሀገራዊ የምርጫ ለማድረግ የመራጮች ምዝገባ ማድረግ ከተጀመረ አንስቶ ያለውን ተግዳራቶች በከፊል የሚያሳይና የአካባቢው ታማኝ ምንጮች ላይ የተመሠረተ ነው። በክልሉ ምርጫ ሂደት ላይ ይፋዊ አቋም ለማግኘት ከክልሉ ምርጫ ቦርድ ወይም ከሌሎች ኃላፊ አካላት ምላሽ አልተገኘም።

📸 ፋይል

ሉዋ ሚዲያ

የቀድሞ የሲዳማ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ አራርሶ ገረመው “ራእይ ከሚቆም ደመወዝ ቢቆም ይሻላል” ማለታቸው ትኩረት ስቧል።አቶ አራርሶ ...
23/04/2026

የቀድሞ የሲዳማ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ አራርሶ ገረመው “ራእይ ከሚቆም ደመወዝ ቢቆም ይሻላል” ማለታቸው ትኩረት ስቧል።

አቶ አራርሶ ይህን አባባል ያሰፈሩት በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ ገፃቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ሲሆን፣ በአንድ ወቅት የክልሉ ከፍተኛ የፋይናንስ ባለሥልጣን የነበሩ ግለሰብ “ደመወዝ ቢቆም ይሻላል” ማለታቸው በርካቶችን አስገርሟል።

አቶ አራርሶ በጽሑፋቸው ትውልድን “ለራእይህ ስትል ከእውነት ጎን አትታጣ፤ ተስፋህን በኃያሉ ላይ አድርገህ በርታ፣ ጽና። ቀኑ ነገ ሌላ ነው” ሲሉ ጽፈዋል። በመቀጠልም በሰፊው ምድር በትጋት መሥራት፣ ታማኝነት፣ እውነትን አለመካድ እና በእግዚአብሔር መደገፍ ወሳኝ ጉዳዮች እንደሆኑ አስምረውበታል።

የአቶ አራርሶ ጽሑፍ ይፋዊ መልዕት መነሻ በማድረግ ግለሰቡ ከሥልጣን መባረራቸው ጋር ተያይዞ መንግሥት ደመወዛቸውን አቁሞ ሊሆን እንደሚችል የሚገመት ሲሆን፣ የቀድሞ የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣን ግን ለዚህ ጽሑፋቸው ዝርዝር ማብራሪያ አልሰጡም።

አቶ አራርሶ ገረመው “አደራ ለዲናሯ” በሚል መጽሐፋቸውና “የሕዝብ ገንዘብ እንጥፍጣፊ ሳንቲም አይባክንም” በሚል አባባላቸው የሚታወሱ ቢሆንም፣ በ2014 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮውን በመሩበት ወቅት 2.6 ቢሊዮን ብር እንደተመዘበረ የሚገልጽ ሪፖርት ማስተናገዳቸው አይዘነጋም። ወቅቱን የሚያስታውሱ ምንጮች፣ በበጀት አመቱ ከፍተኛ ሀብት መዘረፉን ያስታውሳሉ።

በአሁኑ ወቅት በአቶ አራርሶ ያልተለመደ አባባል ዙሪያ የሚነሳው ሙግት በቀጣይ ቀናትም አዲስ ተጨማሪ ኩነቶችን ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ይገመታል።

ሉዋ ሚዲያ

የህዝብን ድምጽ ለማፈን እየተሰራ ባለበት የሚደረገው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተዓማኒነቱን በማጣቱ ተቀባይነት የለውም ሲሉ ተቃዋሚዎች ከሰሱ፤መጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ በሲዳማ ክልል የሚካሄድበት ሂደ...
23/04/2026

የህዝብን ድምጽ ለማፈን እየተሰራ ባለበት የሚደረገው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተዓማኒነቱን በማጣቱ ተቀባይነት የለውም ሲሉ ተቃዋሚዎች ከሰሱ፤

መጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ በሲዳማ ክልል የሚካሄድበት ሂደት ከባድ የተዓማኒነት ቀውስ ውስጥ መውደቁንና በክልሉ የሚገኘው ህዝብ ድምጽ አልባ ለማድረግ ሰፊ የማፈን ስራ እየተከናወነ መሆኑን በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ኃይሎች አስታወቁ።

ከአንጋፋ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በተያያዘ የተሰራጨው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በሲዳማ ህዝብ ዘንድ ሰፊ ተቀባይነት ያላቸው አማራጭ ሀሳቦች ይዘው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እየተደናቀፉ ሲሆን በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ታሪካዊ ድርጅቶች ደግሞ በስፋት እየጠፉ እንደሚገኙ ተገልጿል።

በተለይ የሲዳማ ህዝብ የዲሞክራሲ ልምምዱን እንዳያደርግ ሆን ተብሎ የታቀደ እንቅፋት እየተጣለበት ነው የሚለው ውንጀላ እየሰፋ መጥቷል። በዚህም ሂደት ውስጥ ትልቁንና ዋነኛውን ድርሻ እየተወጣ ያለው ተቋም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሆኑን በርካታ ወገኖች አረጋግጠዋል። የቦርዱ አያያዝ በክልሉ ለሚገኘው ህዝብ ፍትሃዊ የፖለቲካ ተሳትፎ ዕድል እየገደበ መሆኑን የሚያሳዩ ማስረጃዎች እየተበራከቱ ነው።

“ሲዳማ ህዝብ የዲሞክራሲ ልምምድ እንዳያደርግ ታቅዶ እየተገበረ ይገኛል። ይህንን ሁሉ አፈና በማካሄድ ትልቁን ድርሻ የተወጣው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው” የሚል መግለጫ የተሰጠ ሲሆን፣ በዚህ ተቋም አማካይነት የሚካሄደው ሳባተኛ ሀገራዊ ምርጫ በሲዳማ ክልል ውስጥ ፈጽሞ ተቀባይነት እንደሌለውና ምንም ዓይነት ተዓማኒነት ሊኖረው እንደማይችል በግልጽ ተገልጿል።

ይህ ሁኔታ በሲዳማ ክልል ብቻ ሳይሆን በመላ ሀገሪቱ ያለው የምርጫ ሂደት እምነት የሚጣልበትና ሁሉን አቀፍ ነው ለማለት እንደማያስደፍር የፖለቲካ ተንታኞች እያስጠነቀቁ ነው። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ለቀረበው ክስ እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ አልሰጠም።

በሲዳማ ክልል የሚገኘው ህዝብ ድምጹ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ የሚሰማበት ስርዓት እንዲዘረጋ የሚጠይቅ ከፍተኛ ቅሬታ የተስተዋለ ሲሆን፣ አሁን ያለው ሂደት የህዝቡን የፖለቲካ ተሳትፎ ያለአግባብ እየገደበ መሆኑን የሚያረጋግጡ አመላካቾች እየጎሉ መጥተዋል።

ሉዋ ሚዲያ

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ ከሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ መገለሉን በመግለጽ የምርጫ ቦርድን ውሳኔ “ስልታዊ ማደናቀፍ” ስል ከሰሰየሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመሳተፍ ...
22/04/2026

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ ከሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ መገለሉን በመግለጽ የምርጫ ቦርድን ውሳኔ “ስልታዊ ማደናቀፍ” ስል ከሰሰ

የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመሳተፍ ያቀረበው ጥያቄ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውድቅ መደረጉን ተከትሎ ሰፋ ያለ የአቋም መግለጫ አውጥቷል። ፓርቲው በሰጠው መግለጫ የምርጫ ቦርድ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ፓርቲውን ለማደናቀፍ ሲሰራ መቆየቱን በመግለጽ በሲዳማ ክልል የሚደረገው ምርጫ ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል።

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ የተቋቋመው የሲዳማ ህዝብ በክልልነት ከተደራጀ በኋላ ገዢው ፓርቲ ነባር የፖለቲካ፣ የባህልና የሚዲያ ተቋማትን በማፍረስ ለህዝቡ አማራጭ ኃይል እንዳይኖር በማድረግ በአንድ ገዢ ፓርቲ አማካይነት ለመጨቆን የተሸረበ ሴራ በመታየቱ እንደሆነ ፓርቲው በመግለጫው አመልክቷል።

በተለይም ለረዥም አመታት ህዝቡን ሲያታግልና ሲያነቃቃ የቆየው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ በክልሉ ማግስት በሴራ መፍረሱን ተከትሎ ገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ሜዳውን ብቻውን ተቆጣጥሮ ህዝቡን የመልካም አስተዳደር፣ ልማትና ፍትህ እጦት እያጋለጠ በመሆኑ ራሱን ችሎ የቆመ የፖለቲካ ተቋም መመስረት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት እንደሆነ ገልጿል።

ፓርቲው ከአመሠራረቱ ጀምሮ በሁለት መንገዶች ሴራ ሲደረግበት እንደቆየ አስታውቋል። የመጀመሪያው በመዋቅራዊ አፈና ሲሆን የክልሉ መንግስት አማካይነት የፓርቲው አመራሮችን ማሰር፣ መሰወር፣ ማሳደድ፣ ወከዋ፣ ድብደባ እና የፓርቲው ቢሮዎች መዝጋት ይገኙበታል። ሁለተኛው ደግሞ በፓርቲው ውስጥ ተልዕኮ የተቀበለ አንጃ ሀይል በመፍጠር ፓርቲውን ከውስጥ ለማፍረስ የተደረገ ሙከራ ነው።

ፓርቲው ወደ ህዝብ ለመውረድ ባደረገው እንቅስቃሴ በዞን ከተሞችና ወረዳዎች የተከፈቱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በጸጥታ ኃይሎች መዘጋታቸውን፣ አባላት መታሰራቸውንና ከሥራ መፈናቀላቸውን አመልክቷል። በተጨማሪም የፓርቲው ዋና ቢሮ በጸጥታ ኃይሎች በጉልበት መሰበሩንና የጽህፈት ቤት ሠራተኞች መታሰራቸውን ገልጿል።

ፓርቲው ከውስጥ ለማፍረስ የተሸረበውን ሴራ ቀድሞ በመንቃት አንጃዎችን በማጥራትና የነበረውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ በተደረገው ሂደት ውስጥ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህገወጥ ጣልቃ ገብነት እንዳደረገ ተናግሯል። ቦርዱ ከፓርቲው በዲሲፕሊን ጥሰት ከተሰናበቱ ህገወጥ ኃይሎች ጋር በመስራት ፓርቲው ስራውን እንዳያከናውን ሲያደናቅፍ ቆይቷል።

ፓርቲው ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በመውሰድ ለሁለት ዓመታት በቀጠለው ክርክር እስከ ሰበር ችሎት ድረስ በማሸነፍ የቦርዱን ውሳኔዎች ማሻሩን ገልጿል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም የሰጠውን ውሳኔ ቦርዱ ተግባራዊ ሳያደርግ በመቅረቱ ጉዳዩ እስከ ሰበር ችሎት ድረስ ሄዶ ጥር 20/2018 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ፓርቲው አሸናፊ መሆኑን አስታውቋል።

ምንም እንኳ የምርጫ ቦርድ አካሄድ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምህዳር እውነተኛ፣ ተዓማኒና ፍትሓዊ ምርጫ ይደረጋል ተብሎ የሚታመን ባይሆንም፣ ፓርቲው በመጀመሪያ ግዜ ምርጫን የሚወዳደር እንደመሆኑ መጠን እና ህዝቡን የዲሞክራሲ ባህል ልምምድ ማድረግ የጎላ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር የካቲት 19/2018 ዓ.ም ጥያቄ ማቅረቡን አመልክቷል።

ይሁንና ቦርዱ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ተግባራዊ ሳያደርግ በመቅረቱ እና የ2015 በጀት አመት የኦዲት ሪፖርት አለመቅረቡን በምክንያትነት በመጥቀስ ፓርቲው "እግድ ላይ" ስላለ የምርጫ ጥያቄው ውድቅ መደረጉን በየካቲት 16/2018 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

ፓርቲው ይህንን ውሳኔ በመቃወም በአምስት ዋና ዋና ነጥቦች የተደገፈ ማስረጃ ለቦርዱ ማቅረቡን ገልጿል። ከነዚህም መካከል፡-

1. የማስጠንቀቂያ ደብዳቤዎች ለፓርቲው አለመድረሳቸው፡ ቦርዱ የላካቸው ማስጠንቀቂያ ደብዳቤዎች ፓርቲውን ወክሎ የተቀበለው በዲሲፕሊን ጥሰት ከፓርቲው የተሰናበተው ግለሰብ መሆኑንና ይህንንም ለቦርዱ ማሳወቁን አመልክቷል።

2. የኦዲት ሰነዶች ከፓርቲው ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው፡ በዲሲፕሊን ክስ ላይ የነበረው የፓርቲው ቀድሞ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር የፓርቲውን ቢሮ በሀይል ሰብሮ በመግባት የኦዲት ሰነዶችን መቆጣጠሩን ገልጿል።

3. ፓርቲው በእግድ ላይ አለመሆኑ፡ የተላኩት ደብዳቤዎች ማስጠንቀቂያ እንጂ የእግድ ደብዳቤዎች እንዳልነበሩ አመልክቷል።

4. ውሳኔው ሚዛናዊነት የጎደለው መሆኑ፡ ኦዲት ማድረግ ግዴታ ቢሆንም የቦርዱ ህገወጥ ውሳኔዎች ለችግሩ በቂ ምክንያት መሆናቸውን ጠቁሟል።

5. ኦዲት ለማድረግ ምቹ ሁኔታ አለመፈጠሩ፡ ፓርቲው የፍርድ ቤት ውሳኔ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ኦዲት ለማድረግ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠርለት ቢጠይቅም ምላሽ ሳያገኝ መቆየቱን አስረድቷል።

ፓርቲው ከቦርዱ ኃላፊዎች ጋር በቀጥታ በመነጋገር የኦንላይን ምዝገባ በልዩ ሁኔታ እንደሚከፈትለትና በምርጫው ለመወዳደር የሚያስችል ሁኔታ እንደሚፈጠርለት ቃል መግባቱን ቢገልጽም፣ ቦርዱ ቃሉን በማፍረስ የኦዲት ጉዳዩን ወደ ፌዴራል ጠቅላይ ኦዲተር ቢሮ በመላክ ጊዜን ማባከኑን አመልክቷል። በድጋሚ በተደረገው ኦዲትም ከቀድሞው ጋር ተመሳሳይ ውጤት ቢገኝም ቦርዱ የመራጮች ምዝገባ የሚዘጋበትን ጊዜ አሳልፎ በመስጠት ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉን ገልጿል።

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በመግለጫው የሚከተሉትን ዋና ዋና አቋሞች አስቀምጧል፦

1. በሲዳማ ክልል የሚደረገው ምርጫ ተቀባይነት የለውም፡ ፓርቲው የሲዳማ ህዝብን አማራጭ አልባ ለማድረግ የተጀመረው ሴራ መጠነ-ሰፊና ያልተቋረጠ መሆኑን ገልጾ፣ በተግባሩ ዴሞክራሲን እየገደለ ያለው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሆኑን አረጋግጧል። በዚህም ምክንያት ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሲዳማ ክልል ውስጥ ተቀባይነትና ተዓማኒነት የሌለው መሆኑን አስታውቋል።

2. ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህገመንግስትን እየተላለፈ ነው፡ ቦርዱ በህገመንግስቱ አንቀጽ 102 መሰረት የተቋቋመ ቢሆንም ህገመንግስቱን በማክበር እየሰራ አለመሆኑን ጠቁሟል። በተለይም በአንቀጽ 38 ላይ የተሰጠውን የመመረጥና የመምረጥ መብት እንዳይከበር ማድረጉን አመልክቷል። በተጨማሪም የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲኣን) በጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት የተሰጠውን ውሳኔ በመጣስ ቦርዱ የተለየ አያያዝ መፈጸሙን አጋልጧል።

3. ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ማቅረብ፡ ፓርቲው በክልሉ የሚደረገው ምርጫ እንዲታገድና ውድቅ እንዲሆን ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚያቀርብ አስታውቋል።

ፓርቲው ለህዝብ ባቀረበው ጥሪ: ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ "የምናደርገውን ትግል መላው የሲዳማ ክልል ህዝብ ከጎናችን እንዲቆም ጥሪ እናደርጋለን" ሲል አሳስቧል።

ምንጭ: ይህ ዘገባ የተዘጋጀው በሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በይፋ በተሰጠው የአቋም መግለጫ ላይ ተመስርቶ ነው። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኩል የተሰጠ ምላሽ እስካሁን አልተገኘም።

ሉዋ ሚዲያ

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝብ አማራጭ በማሳጣት የአንድ ፓርቲ ባሪያ ለማድረግ በብልጽግና ተቀርጾ የተሰጠውን ፕሮጀክት ሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን)ን በማክሰም የጀመረውን ሲዳማ...
22/04/2026

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝብ አማራጭ በማሳጣት የአንድ ፓርቲ ባሪያ ለማድረግ በብልጽግና ተቀርጾ የተሰጠውን ፕሮጀክት ሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን)ን በማክሰም የጀመረውን ሲዳማ ፌደራሊስት ፖርቲ (ሲፈፓ)ን በሰበብ አስባቡ ከምርጫ በማግለል ደግሞታል።

ይህ የሚያሳየው ብልጽግና ሆነ የብልጽግና ጉዳይ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫ ቦርድ ተለጣፊና ደጋፊ ፓርቲዎችን እንጂ ተወዳዳሪ እና እውነተኛ ፓርቲዎችን ፈጽሞ ለማጥፋት እንደሚሰሩ እና አንባገነናዊ ስርዓት ውስጥ የስልጣን ማጽኛ ስምንት አመታት ጉዞ በኋላም ከፍርሃት ቀፎን መላቀቅ አለመቻሉን ነው።

እንደ ኮንደሚኒየም እጣ 80/20 ተብሎ ተሰርቶ ገና ከጅምሩ አሸናፊውን የታወቀው የዘንድሮ ምርጫም፣ ከሌሎት የሀገሪቱ ምርጫ ታሪክ ለየት የምልበት ባህሪ አንዱ ነው። ይህ አካሄድ የሀገሪቱ የፖለቲካ ባህል ግንባታ ወርዶ፣ ወርዶ የደረሰበት አዝቅት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ የዘንድሮው ምርጫ ገና ከጅምሩ ፍትሓዊነትን ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የሚከት ሆኗል።

ሉዋ ሚዲያ

ሲዳማ ክልል አንዳንድ አከባቢዎች ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ተነገረ።ከትናንት ጀምሮ በዳዬ ከተማ የትራንስፖርት መቋረጥ ለነዋሪዎች ከፍተኛ እንግልት በማስከተሉ መንገደኞች ሰዓ...
21/04/2026

ሲዳማ ክልል አንዳንድ አከባቢዎች ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ተነገረ።

ከትናንት ጀምሮ በዳዬ ከተማ የትራንስፖርት መቋረጥ ለነዋሪዎች ከፍተኛ እንግልት በማስከተሉ መንገደኞች ሰዓታት ተሰልፎ በመጠበቅ መስተናገድ አለመቻላቸውን ተናግረዋል። በሌላ በኩል ዛሬ ማልጋ ወረዳ በተመሳሳይ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንደተቋረጠ ከስፍራው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

በሲዳማ ክልል ምስራቅ ሲዳማ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ዳዬ ከተማ እና አካባቢዋ የትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጎል በመንገደኞች ላይ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና እየፈጠረ መሆኑ ተገልጿል።

ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች መሠረት፣ መንገደኞች ከሌሊቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በመናኸሪያው መነሻ ጣቢያ ተሰልፈው ወደ ተለያዩ አቅጣጫዎች ለመጓዝ ቢጠብቁም፣ ቀን ሙሉ አንድም ተሽከርካሪ ማግኘት እንዳልቻሉ ተገልጿል። ይህ ሁኔታ ተጓዦችን በከፍተኛ መከራ እና ድካም ውስጥ እንዲገቡ አድርጓል።

በተመሳሳይም ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን በማልጋ ወረዳ እና አከባቢው ተሽከርካሪዎች ከመናኻሪያ መጥፋታቸውን ተገልጿል። የችግሩ ዋነኛ ምክንያት መካከል፣ የነዳጅ እጥረት እና የማደያዎች አገልግሎት መቋረጥ በግልጽ ተጠቅሷል።

በሁኔታው የተማረሩ መንገደኞች መፍትሄ ፍለጋ ወደ ዳዬ ከተማ የመንገድና ትራንስፖርት ልማት ጽሕፈት ቤት ቢጓዙም፣ በግቢው ውስጥ ተደርድረው ያሉ ተሽከርካሪዎች ለሥራ ዝግጁ አለመሆኑ ችግሩን ይበልጥ እንዲጨምር አድርጓል።

መንገደኞች ለሰዓታት በመጠበቅ ከተጨማሪ ወጪ እና ከስራ መዘግየት ጋር የተያያዘ ጉዳት እያጋጠማቸው መሆኑን በምሬት ገልጸዋል። አንዳንድ ተጓዦች በተለይ የህመም ታካሚዎች፣ ተማሪዎች እና ዕለታዊ ሥራ ለመፈጸም የሚጉዙ ሰዎች በችግሩ በከፍተኛ ደረጃ እንደተጎዱ ገልጸዋል።

በሁኔታው ላይ እስካሁን ድረስ የክልሉ ወይም የዞኑ መንግስት አካላት የተወሰነ መፍትሄ እንዳልሰጡ ሲገለፅ፣ ተጎጂዎች ይህ የሕዝብ እንግልት ወደ ከፍተኛ ችግር ከመሸጋገሩ በፊት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።

የክልሉ መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ከፖሊስ ጠቅላይ መመሪያ ጋር በመተባበር በጉዳዩ ዙሪያ ግብረሃይል በማቋቋም ወደስራ መሠማራቱን በገለጸበት በዚህ ሳምንት ችግሩ እየተባባሰ መቀጠሉን እየተነገረ ይገኛል።

ሉዋ ሚዲያ

በሲዳማ ክልል የተጠናከረ የትራፊክ ቁጥጥር፤ ከ157 ሺህ ብር በላይ ለተሳፋሪዎች መመለሱን ተነገረ።የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ከክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በመቀናጀ...
18/04/2026

በሲዳማ ክልል የተጠናከረ የትራፊክ ቁጥጥር፤ ከ157 ሺህ ብር በላይ ለተሳፋሪዎች መመለሱን ተነገረ።

የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ከክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በመቀናጀት በሐዋሳ ከተማ እና በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ውስጥ ያካሄደው የተቀናጀ የትራፊክ ቁጥጥር እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።

በዚህ ቁጥጥር ሂደት 245 ተሽከርካሪዎች የተመርመሩ ሲሆን 27 አሽከርካሪዎች የትራፊክ ደንብ በመጣሳቸው 31,500 ብር ቅጣት ተጣልባቸዋል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪ 32 አሽከርካሪዎች ከተፈቀደው ታሪፍ በላይ ክፍያ እንደተቀበሉ ተደርሶ 157,475 ብር ለተሳፋሪዎች እንዲመለስ ተደርጓል ተብሏል።

እንደ ቢሮው መግለጫ፣ ቁጥጥሩ በዋናነት ከታሪፍ በላይ ክፍያ መጠየቅ፣ ትርፍ ተሳፋሪ መጫን እና ያልተፈቀዱ የሥምሪት መርሀ ግብሮች ላይ ተከታትሎ የነበር ስሆን፤ የቁጥጥሩ ውጤት እንደሚያሳየውም ከታሪፍ በላይ ክፍያ በተለይ በከተማውና በዙሪያው የሚገኙ ዋና የመንገድ መስመሮች ላይ ተስፋፍቶ እንዳለ ተገልጿል።

ከችግር በብዛት የተጠቁ መስመሮች መካከል በንሳ ዳዬ፣ ቦና፣ ሀገረ ሰላም፣ አለታ ወንዶ፣ አለታ ጩኮ፣ ይርጋለም እና ወላይታ ሶዶ የሚያያዙ መንገዶች እንደሚገኙ ተገልጿል።
በቁጥጥሩ ወቅት የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች፣ የፖሊስ ትራፊክ ክፍል ኃላፊዎች እና የመንገድ ደህንነት ባለሙያዎች በጋራ ተሳትፈው ሥራውን አከናውነዋል።
ቢሮው በቀጣይ ይህን ዓይነት የተቀናጀ ቁጥጥር እርምጃ በሐዋሳ ከተማ እና በክልሉ ሁሉም ዞኖች ላይ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: በአገር ደረጃ የተሻሻለው አዲሱ ታሪፍ ከፍተኛው አንድ ኪሎሜትር 2.8 ሳንቲም ስሆን፤ ከዚህ ውጪ ያለው ክፍያ ህገወጥ ነው።የኢፌዴሪ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የወቅቱን የ...
18/04/2026

#መረጃ: በአገር ደረጃ የተሻሻለው አዲሱ ታሪፍ ከፍተኛው አንድ ኪሎሜትር 2.8 ሳንቲም ስሆን፤ ከዚህ ውጪ ያለው ክፍያ ህገወጥ ነው።

የኢፌዴሪ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የወቅቱን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ባሳለፍነው ሳምንት በአገር አቋራጭ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍ ላይ የ46.8 በመቶ ጭማሪ ማድረግ ይፋ አድርጓል። አዲሱ የታሪፍ ተመን በዛን ቀን ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ተገልጿል።

አዲሱ ታሪፍ ቀደም ሲል ከነበረው ተመን በአማካይ የ46.8 በመቶ ጭማሪ የታየበት ሲሆን፣ ስሌቱም እንደ ተሽከርካሪዎቹ ደረጃ (ደረጃ 1፣ ደረጃ 2 እና ደረጃ 3) እና እንደ መንገዱ ዓይነት (አስፋልት ወይም ጠጠር መንገድ) የሚለያይ ሆኖ ተበይኗል።

በዚህም መሠረት፦ ደረጃ አንድ ህዝብ ማመላለሻ በአስፋልት መንገድ ላይ ለአንድ ሰው በኪሎ ሜትር 2.6721 ብር ስሆን። በጠጠር መንገድ ደግሞ 2.8008 ብር ሆኗል። ይህ ማለት 100 ኪ.ሜ 208 ብር መሆኑ ነው።

በተሳሳይ ደረጃ ሁለት ህዝብ ማመላለሻ በአስፋልት መንገድ በኪሎ ሜትር 2.6301 ብር ስሆን፤ በጠጠር መንገድ ደግሞ 2.7103 ብር ሆኖ ተስተካክሏል።

እንዲሁም ደረጃ ሶስት ህዝብ ማመላለሻ በአስፋልት መንገድ 2.5902 ብር ስሆን በጠጠር መንገድ 2.6614 ብር እንዲከፈል ተወስኗል።

ይህ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ እንዲሆን ለሁሉም የትራንስፖርት ማህበራትና የሚመለከታቸው አካላት መመሪያ የተላለፈ ሲሆን፣ ከተቀመጠው ታሪፍ በላይ በሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎችና ባለቤቶች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና እርምጃ እንደሚወሰድ ሚኒስቴሩ አስጠንቅቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም በተመሳሳይ መልኩ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በመዲናዋ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጡ ሚኒባሶች፣ ሀይገር ባሶችና የከተማ አውቶቡሶች ላይ የታሪፍ ማሻሻያ ማድረጉ ይታወሳል።

በመሆኑም የሲዳማ ክልል መንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አዲስ ተመንም አውጥቶ በይፋ ባይገልጽም በሀገር ደረጃ ከተተመነው ተመን የተለየ ልሆን እንደማይችል ግምት ውስጥ በማስገባት አንድ ተሳታፊ ለአንድ ኪሎሜትር 2 ብር ከ80 ሳንቲም መክፈል ይጠበቅበታል። ያማለት 100 ኪሎሜትር 208 ብር እና ከዚህ የዘለለ መሆን የሌለው መሆኑን አውቆ ተጓዦች በስግብግብ አሽከርካሪዎች እና የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች እንዳይበዘብዝ ጥንቃቄ ማድረግ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ክትትል ማድረግ ይገባል።

#ማሳሰቢያ: ተሳታፊዎች በየአካባቢያቸው የሚያጋጥማቸውን እክል በሉዋ ሚዲያ መረጃ መቀበያ ቦት በኩል መልእክት ስትልኩ ድምጻቸውን ለማሰማት ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልፃለን።

#በተጨማሪም: ማንኛውም ጥቆማና ቅሬታ ለማቅረብ መንገድና ትራንስፖርት ዘርፍ ነጻ ጥሪ መስመር 9968 ላይ ይደውሉ!

ሉዋ ሚዲያ

ከሀዋሳ ወደ ዞኖች፣ ከዞን ወደ ወረዳዎች የሚደረግ የዛሬው የትራንስፖርት እና የታሪፍ ሁኔታ እንዲሁም የቁጥጥር አይነት በየአካባቢያቸው ያለውን አንድምታ አካፍሉን።ትናንትና የክልሉ መንገድና ት...
18/04/2026

ከሀዋሳ ወደ ዞኖች፣ ከዞን ወደ ወረዳዎች የሚደረግ የዛሬው የትራንስፖርት እና የታሪፍ ሁኔታ እንዲሁም የቁጥጥር አይነት በየአካባቢያቸው ያለውን አንድምታ አካፍሉን።

ትናንትና የክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ እንደገለጸው የትራንስፖርቴሽን ችግርን ለማስቀረት ግብረሃይ ተቋቁሞ ስራ መጀመሩን ይታወቃል። ስለዝህ ይህንን ተግባር ለማሳለጥ እና የተገልጋዮች የተሻለ አገልግሎት ለማቅብ የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ይታመናል።

በመሆኑም የሚከተሉትን ተግባር በመፈጸም የተጀመረው ስራ ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል የሁላችንም ድርሻ እንወጣ፦

1. መረጃ መስጠት፦ ከተቀመጠው ታሪፍ በላይ የሚጠይቁ አሽከርካሪዎችን ለሚመለከተው አካል ወይም በየመናሃሪያው ላሉ ተቆጣጣሪዎች ጥቆማ በመስጠት ተባባሪ መሆን።

2. መብትን ማወቅ፦ የወጣውን የታሪፍ ተመን በማወቅ ተገቢውን ክፍያ ብቻ የመክፈል ልምድን ማዳበር። ከተተመነው ታሪፍ ውጪ የሚጠይቅ አሽከርካሪዎችን ማጋለጥ፣ ተሳታፊዎች በሙሉ በመተባበር ተጨማሪ ገንዘብ አለመክፈል።

3. አሽከርካሪዎችን ማበረታታት፦ ህግን አክብረው በቅንነት የሚያገለግሉ አሽከርካሪዎችን እውቅና መስጠትና ማመስገን። (ይህ መንግስትን የሚመለክት ጉዳይ ስለሆነ መንግስት በቀናነት ህዝብን የሚያገለግሉ ባለንብረቶች ማበረታታት ይገባዋል)

"የህግ የበላይነት የሚረጋገጠው በጋራ ስንቆም ነው! የክልሉ ትራንስፖርት ቢሮና የጸጥታ አካላት የጀመራችሁትን የማስተካከያ እርምጃ አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ህዝቡ ከጎናችሁ ነው!"

#ማሳሰቢያ: በያላቹበት የሚያጋጥማቸውን ችግር የሉዋ ሚዲያ መረጃ መስጫ የቴሌግራም ቦት በመጠቀም መረጃዎችን በመላክ ድምጻቸውን ማሰማት እንችላለን።

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Luwa Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category