Luwa Media

Luwa Media ብዝሃነት ለኢትዮጵያ አንድነት፤ ልዩነታችንን በእኩልነት የምታስተናግድ ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የራሳችንን ጡብ እናስቀምጣለን። ኢትዮጵያ!
(10)

 #መረጃ: ሉዋ ሚዲያ አብዝቶ ሽፋን ሰጥተዉ ስታገል የነበረው ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ከድሀው እናት በኃይል በመቀማት ያስገነቡት ቤት ትናንትናው ዕለት ለእውነተኛ ባለቤት ተመልሷል።ሀዋሳ ላይ...
02/11/2025

#መረጃ: ሉዋ ሚዲያ አብዝቶ ሽፋን ሰጥተዉ ስታገል የነበረው ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ከድሀው እናት በኃይል በመቀማት ያስገነቡት ቤት ትናንትናው ዕለት ለእውነተኛ ባለቤት ተመልሷል።

ሀዋሳ ላይ በክልሉ እና በከተማ አስተዳደሩ ሹማሚንት ከደሃው ላይ ስልጣናቸውን ተጠቅመው ወደ 88 የሚጠጉ የቀበሌ ቤቶችን በመንጠቅ፣ ቁጥራቸው ወደ 627 የሚጠጋ የቤተሰብ አባላቶችንም አፈናቅለው ሜዳ ላይ ጥለዋቸዋል ስንል በተደጋጋሚ ዘግበን እንደነበር አይዘነጋም።

ከፌደራሉ መንግስት በተላለፈዉ ትዕዛዝ መሠረት ከብዙ ጥቂቱ በዚህ ሳምንት ለተፈናቃዮች እንደተመለስ ሰምተናል። እን አገዛዙ ገለጻ ሁለተኛ ዙር ተብሎ የተሰየመዉ የትናንቱ ቤት ግን ከሁሉም ከሁሉም በላይ እኛም በተደጋጋሚ አጽንኦት ሰጥተን ያጋለጥነዉ ቤት ነበር።

የዚህ ቤት ቀማኛ አፈናቃይዋ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ይባላሉ። ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ቀድሞ የክልሉ ሰዉ ሀብት ቢሮ ሃላፊ የነበሩ እና የባለስልጣናት ቤተሰቡ የመንግስት መስሪያ ቤት ወሳኝ፣ ወሳኝ መደቦችን ያለዉድድር ያደሉ እና ለዘመዶቿዋ ኮሌጅ እንኳ ሳይጨርሱ ይህ መደብ ለአንተ፣ የአንች ነዉ እያሉ የተፈለገዉ ሰዉ ትምህርት ጨርሶ እስክመጣ ለአመታት ስያስቀመጡ እንደነበር ይነገራል።

እኚህ ሃላፊዋ በተሰጣት ተልእኮ መሠረት የሰክተሩን ሪሶርስ አሟጠዉ በባለስልጣናት ቤተሰብ ካደራጁ በኋላ ነዉ አሁን ወዳሉበት የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊነት የተመደቡት፣ ይህ ሰክተር በፈደራሉ መንግስት ትኩረት አቅጣጫ መሠረት ከፍተኛ የገንዘብ ፍሰት የሚገኝበት ሰክተር እንደሆነ ይታወቃል።

እኚሁ ባለስልጣን የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልም ናቸዉ፣ የክልሉ ምክር ቤት አባልነትን ጨምሮ አጠቃላይ ከ15 በላይ ተቋማትን በቦርድ አባልነት የሚመሩ የክልሉ ፕሬዚዳንት የአቶ ደስታ ሌዳሞ በጣም ታማኝ፣ የቅርብ ሰው እና ቀኝ እጅ ናቸው።

ክብርት ወይዘሮዋ ከ2013 ጀምሮ እሰካሁን ድረስ የሚኖሩት በሀዋሳ ከተማ በተለምዶው TTC (ሀዋሳ መምህራን ኮሌጅ) ፊት ለፊት በሚገኘው የመንግስት የቁጠባ ቤት ውስጥ ነው።

በቁጠባ ቤት እየኖሩም ሌላ ተጨማሪ ቤት ያምራቸውና በምስሉ ላይ በምታዩት ግቢ ውስጥ ይኖሩ የነበሩትን እናት ጨክነው በማባረር በኮንትራክተር ባለቤታቸው (ከጥቂት ግዜ በፊት 1,624 ብር ተቀጣሪ ሹፌር የነበረ) አማካኝነት፤ ከሐዋሳ ማዘጋጃ ቤት የኮሪደር ልማቱ በጀት ውስጥ ተካቶ እና እራሷ ከምትመራዉ ቢሮ በጀት ተጨምሮበት በምታዩት መልኩ ቤቱ እምር ብሎ ተሰርቶ አልቆ ከቤተሰቦቿ ጋር ጠቅልላ ልትገባ ሁለት ሳምንት ሲቀራት ከፌዴራሉ መንግስት በተሰጠው ቀጭን ትዕዛዝ ተግባራዊ እንዲደረግ የተባለው ግምገማ ተቀመጡ።

በዚህ ወሽመጥ ቆራጩ ግምገማም ስልጣናችሁን ተገን አድርጋችሁ ደሀውን አፈናቅላችሁ የግላችሁን ቤት ገንብታችሁ የገባችው ሁሉ ውጡ የሚል ትዕዛዝ ተላለፈ። ትዕዛዙ የመጣውም በቀጥታ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት ነበር። እኚህ ምስኪን ተፈናቃዮች ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመልክተውም ነበር።

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: ሀዋሳ ከተማ የመሬት መቀራመት እና መረጃ የማጥፋት ሥራ ተጠናክሮ መጧጧፉን ተነገረ፤በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማዋ ከንቲባ ሆኖ እንዲያገለግል የተመደበ የከተማ የአመራር...
01/11/2025

#መረጃ: ሀዋሳ ከተማ የመሬት መቀራመት እና መረጃ የማጥፋት ሥራ ተጠናክሮ መጧጧፉን ተነገረ፤

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማዋ ከንቲባ ሆኖ እንዲያገለግል የተመደበ የከተማ የአመራር፤ ለአንድ ወር ያህል ግዜ ከተማዋን እያስተዳደረ ያለ ካንቲባ፤ ቦታውን ለትክክለኛ ከንቲባ እስክያስረክቡ ድረስ፤ አቶ ደስታ ሌዳሞና አብረሃም ማርሻሎ በልማት ተነሽዎች እና በኢንቨስትመንት ስም ወደግል ሃብትነት የተወሰዱትን መሬት መረጃን እንዲያጠፉ ወይንም ወደ ህጋዊነት እንድቀይር ተልዕኮ ተሰጥቷቸዉ እየሰሩ መሆኑን ተነግሯል፡፡

በከተማ ዉስጥ የተዘለሉ ክፍት ቦታዎች መረጃ ያላቸዉ ግለሰብ ከዝህ ቀደም የሀዋሳን ከተማ መሬት በመዝረፍ የሚታወቁና በ2008 ዓ.ም ዳግም ታሀድሶ በሌብነት ተገምግሞ የተባረሩ አቶ ቸርነት ፍላቴ፤ ላለፉት አመታት ልዩ ከለላ በክልሉ አስተባባሪዎች ተስጥቶት የሀዋሳን መሬት ስዘርፍና ስያዘርፍ የነበረ አቶ ገዛኸኝ አርስቻ፤

የታቦር የሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ማዛጋጃ ቤት ሥራስኪያጅ የነበሩ በሌብነት ሰንሰለት ዉስጥ የቆዩ አቶ ማቲዎስ ማናየ፤ ከከንቲባዉ ጋር በመመሳጠር ከዝህ ቀደም የተዘለሉ ክፍት ቦታዎች፤ በመናኸርያ ክፍለ ከተማ፣ ዲያስፓራ ሳይትና በሀይቅ ዳር ክፍለ ከተማ፣ የመንግሥት መሬት ለግለሰቦች ካርታ ፕላን እያሰሩ እንደሆነና በአቶ ቸርነት ፍላቴ ስም ሀስተኛ ማህተም ተዘጋጅቶ ወደኃላ ተደርጎ እየተፈረመ እንደሆነ መረጃ ምንጮች ገልጿል።

አቶ ገዛኸኝ አርስቻና አቶ ማቲዎስ ማናየ ስም የማዛወርና መረጃ የማጥፋት ሥራ እየሰሩ እንደሆነና የክልሉ አመራር ሀዋሳን የመዝረፍ ዉጥን እያሳኩ እንደሆነና ከንቲባዉ ድርሻዉን እንድወስድ ከፕረዝዳንቱ አቅጣጫ መቀመጡን ለማወቅ ተችሏል::

ይህንን በተመለከተ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመረጃና ደህንነት አካላት በጥልቁ ክትትል እንድታደርጉና ለሕዝብ እንድታሳወቁ ጥርያችንን እናቀርባለን::

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: አቶ ሚሊዮን ማትዮስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሆኖ ተሾሙ፤የቀድሞ የደቡብ ክልል ርዕሰመስተዳድር የነበሩ አቶ ሚሊዮን ማቴ...
31/10/2025

#መረጃ: አቶ ሚሊዮን ማትዮስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሆኖ ተሾሙ፤

የቀድሞ የደቡብ ክልል ርዕሰመስተዳድር የነበሩ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሆኖ መሾማቸውን ከተማ አስተዳደሩ በይፋዊ ማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጹ አስነብቧል።

አቶ ሚሊዮን የትምህርት ሚንስትር ዲኤታ ጨምሮ በበርካታ መንግስት መስሪያ ቤት በከፍተኛ ኃላፊነት የሰሩ ሲሆን ከአድስ አበባ ከተማ ሹመት በፊት የማዕድን ሚንስትር ዲኤታ ነበሩ።

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: በሀዋሳ ከተማ በራስ ወዳድና ግለኛ አመራሮች በግዳጅ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ መኖርያቸው መመለስ መጀመሩን ተነገሯል፡፡ የራሳቸው ቤት እያላቸው አቅሜ ደካማና ድጋፍ የሚሹ አ...
31/10/2025

#መረጃ: በሀዋሳ ከተማ በራስ ወዳድና ግለኛ አመራሮች በግዳጅ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ መኖርያቸው መመለስ መጀመሩን ተነገሯል፡፡

የራሳቸው ቤት እያላቸው አቅሜ ደካማና ድጋፍ የሚሹ አካላትን በግዳጅ ከቤታቸው ያፈናቀሉ የክልሉና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በዚሁ ሳምንት ብልጽግና ፓርቲ አመታዊ ሥልጠና ላይ አዳማ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

በፓርቲ ጽህፈት ቤት አማካይነት ያለአግባብ ከቤት የተፈናቀሉ ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ መኖርያቸው የሚመልስ፤ በድርጊቱ የተሳተፉ አካላት ላይ አስተዳራዊና ህጋዊ እርምጃ እንድወሰድ አጣሪ ግብረኃይል ተብሎ የተሰየመው ግብረሀይል ውስጥ ያሉ አባላት በአመዛኙ የራሳቸው ቤት እያላቸው በግዳጅ ዜጎችን አፈናቅለው በመንግሥት ቤት የሚኖሩ በመሆናቸው የእርምጃው ሀቀኝነት ጥያቄ ዉስጥ ከቷል ተብሏል፡፡

የክልሉ አመራር ዜጎችን በግዳጅ አፈናቅሎ፤ የራሳቸውን ቤት አካራይቶ፤ የመንግሥት ቤቶች አስተዳደር አዋጅ ህገወጥ መመርያ በማውጣት እየተቀራመተ እንደሆነና ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ህገወጥ ድርጊትን እንዲያስቆም በተደጋጋሚ መዘገባችንም ይታወሳል።

ጉዳዩ ከክልሉ መንግሥት ቁጥጥር ውጪ ሆኖ “ሀሰት ነው፣ በሬወለድ ወሬ ነው” ስል የሰነበተው የአብረሃም ማርሻሎ የሚመራው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት፤ ከአንድ ወር በፊት ባካሄደው ግምገማ በሀዋሳ ከተማ የመሬት ወረራና የመንግሥት ቤቶች መቀራመት የክልሉና የከተማ አመራር ዜጎችን በግዳጅ አፈናቅሎ ጎዳና አውጥቷል በሚል፤ የመርሃ ግብር ሟሟያ የግምገማ መድረክ ፈጥሮ ከሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ውጪ በጉዳዩ ቀጥተኛ ተሳትፎና በወንጀል ድርጊት ላይ በተሳተፉ አካላት ላይ እርምጃ ሳይወስድ ቀርቷል።

በጉዳዩ ላይ ከፓለቲካ እርምጃ ባሻገር ህጋዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው የሚገቡ ህገወጥ መመርያ በማዘጋጀ በመንግሥትና ህዝብ ላይ ጉዳት ያደረሱ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት በመፍጠር ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ግንባታ ያከናወነ።

የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚተ አባል የሆኑ ወወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ ከተማ ውስጥ ህገወጥ የመንሥት ቤቶች ዕድሳት ሲደረግ ከህግ አግባብ ውጪ በመቶ ሚሊየኖች ገንዘብ ያዘዙና ለራሷም በ9 ሚሊየን በመንግሥት ቤት ግንባታ ያካሄዱ።

የከተማ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፍ አቶ ገድዎን ጋቢሦና በሌሎችም በተመሳሳይ ጥፋት ላይ የተሳተፉ አካላት ላይ እርምጃ ሳይወሰድ “ተፈናቃዮችን ወደ ቤታቸው ተመለሱ” የሚል ዜና በእርምጃው ሀቀኝነት ላይ ጥርጣሬ ጭሯል።

ምንም እንኳ ጫናው ዉጫዊ መሆንና የክልሉ መንግሥት በግዳጅ የገባበት እርምጃ ስሆን፤ በትናትናው ዕለት ከ188 ቤተሰቦች ውስጥ ሦስት ቤተሰብ ወደ ቤታቸው መመለሳቸውና ከንቲባውም ይህን ማድረጋቸው በአዎንታ የሚታይ ጉዳይ ነው ተብሏል።

ይህ በእንድህ እንዳለ፤ ዜጎችን ያፈናቀሉ አመራሮች ላጠፉት ጥፋት ተመጣጣኝና አስተማሪ እርምጃ ሊወሰድባቸው ስገባ፤ ፓርቲው ባዘጋጀው ዓመታዊ አቅም ግንባታ ሥልጠና አዳማ መከተማቸው ባለፈው በፓርቲ ጽ/ቤት አማካይነት የተቋቋመው ግብረኃይል ሥራ አጠያያቂ ያደርገዋል ተብሏል።

በዚህ ዙሪያ ማብራሪያ የጠየቅነዉ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያለዉ እና የከተማ ነዋሪ የሆኑ ሀሳብ ሰጪያችን፤ መንግስት ህጋዊና አስተዳዳራዊ እርምጃ ከመዉሰድ አስቀድሞ ቀናነት ካለዉ የፖለቲካ እርምጃ መውሰዱ የተገባ ነበር ያለ ስሆን፤ ጥፋተኞቹ አሁንም በአመራር ፑል ላይ እስካሉ ድረስ የግብረኃይሉ ሥራም ከመርሃ ግብር ባለፈ ፋይዳ የለውም ብሏል።

ከዝሁ ጋር በተያያዘ አጣሪ ግብረሃይ በአባልነት ያሉ አብዛኞቹ በመንግሥት ቤት የሚኖሩ በመሆናቸው ውጠታማነቱን ጥያቀ ውስጥ ይጥላል ተብሏል።

ሉዋ ሚዲያ

አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለችን መርዳት የምትፈልጉ ወገኖች በዚህ አድራሻ መሠረት እንርዳት! ኦሮሚያ ሕብረት ባንክ 1074700019327    ስልክ    0912137778    ኢትዮጵያ በቀለች።
31/10/2025

አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለችን መርዳት የምትፈልጉ ወገኖች በዚህ አድራሻ መሠረት እንርዳት! ኦሮሚያ ሕብረት ባንክ 1074700019327 ስልክ 0912137778 ኢትዮጵያ በቀለች።

 #መረጃ: ብርቱ ሴት አርቲስት  #ኢትዮጵያ  #በቀለች አቃተኝ እርዱኝ እያለች ነዉ። ወጣት፣ ብርቱ ሴት፣ አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለች በፖለቲካ አሻጥር እንድትራብ ተደርጋ አሁን ለደረሰችበት “...
31/10/2025

#መረጃ: ብርቱ ሴት አርቲስት #ኢትዮጵያ #በቀለች አቃተኝ እርዱኝ እያለች ነዉ።

ወጣት፣ ብርቱ ሴት፣ አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለች በፖለቲካ አሻጥር እንድትራብ ተደርጋ አሁን ለደረሰችበት “የወገን ደራሽ ወገን ነዉ” ጥሪ እንዲትዳረግ ተደርጋለች። የሲዳማ ህዝብ ከክልሉ መንግስት የደረሰዉን በደል እና ግፍ በማህበራዊ ሚዲያ ወጥታ ድምፅ በመሆኗ ከምትተዳደርበት የግል ኑሯዋ ተፈናቅላ ለእስራት ተዳርጋለች።

አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለች በተሰበረ ልቦና በኢምባ ታጅባ በማህበራዊ ሚዲያ እንደገለጸችዉ ከ10 አመት በላይ ሙዚቃ ስራዋ ያለ ማንም እገዛ ለብቻዋ መጋፈጧን በማንሳት አሁን ግን አልቻልኩም ብላለች።

አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለች አሁን ላይ በጣም የስነልቦና ጫና ዉስጥ መሆኗን ገልጻ፣ የሚረዳኝ ሰው አጥቻለሁ፣ አሁን ላይ ሰው ቤት ተቀጥሬ ለመስራት ብሞክር እንኳ ስለምታወቅ ያንን ማድረግ አልቻልኩም ብላለች።

አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለች ይህንን ያለችው በእጇ ያለዉን ስራዋን የኢትዮጵያ ህዝብን እና ታዋቂ ቲክቶከሮችን እባካችሁ አንድ በኦሮምኛ የተሰራ ስራ እጄ ላይ አለ እና ፕሮዲውስ እንዳደርገው ቻሌንጅ አስጀምሩልኝ አግዙኝም ብላለች።

Let's help the artist Ethiopia.

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ፡ በደቡባዊ ሲዳማ ዞን በአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን የሚታገሉ የማህበረሰብ ክፍል ነጥሎ ጥቃት ለማድረስ እየተንቀሳቀሰ ነዉ ተባለ፤ሚዲያች የአለታ ጩኮ ከ...
31/10/2025

#መረጃ፡ በደቡባዊ ሲዳማ ዞን በአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን የሚታገሉ የማህበረሰብ ክፍል ነጥሎ ጥቃት ለማድረስ እየተንቀሳቀሰ ነዉ ተባለ፤

ሚዲያች የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ብልሹ አሰራር በመረጃ ማጋለጡን ተከትሎ ከተማዋ ዉዝግቡ ተባብሶ ቀጥሏል። የችግሩ መንስኤ ናቸዉ ተብሎ በማህበረሰቡ የተነገሩ አካላት፣ ማዘጋጃ ቤት የተፈጠረውን የህዝብ ሀብት ምዝበራና ሠራተኞችን ማዕከል ያላደረገ የአሰራር ችግር፤ የከተማ አስተዳደሩ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታርኩ ቦጋለ ችግር አይደለም በማለት አድበስብሶ ለማለፍ ያደረጉት ሙከራ ተጨማሪ ቅሬታ አስነሥቷል።

ሰሞኑን በከተማው ማዘጋጃ ቤት ምዝበራ መኖሩንና በተለይም የማዘጋጃ ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አማክሎ ከመምራት ይልቅ፤ ሠራተኞችን ከፋፍሎ ቡድንተኝነት፤ በጎሳ እና በጥቅማጥቅም የተጋመደ አካሄድ እንዲሰፍን ማድረጉንና የሀብት ምዝበራ መኖሩን በመጥቀስ የሚመለከተው አካል ፈትሾ እንዲያስተካክል የተቋሙ ሠራተኞችና የከተማው ማህበረሰብ ለአዲሱ ከንቲባ ማመልከታቸውን ሉዋ ሚዲያ አድርሶ ዘግበን እንደነበር የሚታወስ ነው።

የከተማይቱ ባለስልጣን በትናንት ወዲያ እለተ ረቡዕ አጣሪ ቡድን ወደ ማዘጋጃ ቤት የተላከ ሲሆን፤ ቡድኑ ሠራተኞችንና የማዘጋጃ ቤት ኃላፊዎች በመሰብሰብ ያወያዬ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ። አብዘኛዎቹ የቅሬታ ምንጭ የሆኑ ነጥቦች ትክክል ሆነው ተገኝተዋል ነዉ የተባለው። የተወሰኑት ደግሞ ቀጣይ ማጣራትን የሚጠይቁም መሆናቸውን ተገልጿል።

ሆኖም ቡድኑን መርቶ ወደ ሥፍራው የሄደው የከተማ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታርኩ ቦጋለ “ነገሩ ቀላል ነው፤ ወደ ውጪ መውጣት ያልነበረበት ነው” በማለት ነገሩን በማቅለል መናገራቸው በሰራተኛውና በከተማ ነዋሪው ዘንድ ዳግመኛ ቅሬታ ፈጥሯል። በመሆኑም “የከተማው ሀብት እየተመዘበረ ሽፋን ለመስጠት የሚደረገው ጥረት የፓርቲው ኃላፊ ላይ ጥርጣሬ አሳድሮብናል” በማለት ነዋሪዎቹ ቅሬታቸውን ለሉዋ ሚዲያ በድጋሚ ልከዋል ።

የከተማ አስተዳደሩ ማህበረሰብ ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን አበክር በመታገል ላይ ይገኛል፤ ይህንን ተከትሎ በትናንትና ዕለተ ሀሙስ ባለስልጣኑ ይህንን ጉዳይ በመገምገም መፍተሔ ከመስጠት ይልቅ ብልሹ አሰራርን በዋናነት የታገሉ ናቸዉ ያላቸዉን ግለሰቦች ነጥሎ ከስራ ለማገድ እና ለማሸማቀቅ ያደረገዉ ሙከራ በማህበረሰቡ ዘንድ ተጨማሪ ዉጥረትን አንግሶ የሰራተኞች ላይ የታሰበዉን ከስራ ማገድ ዉድቅ አድርጓታል።

እንደ ከተማዋ ማህበረሰቡ አቋም ባለስልጣናቱ የተፈጠረዉን ችግሩን በመፈተሽ ተመጣጣኝ ውሳኔ ካልተሰጠ በቀር ቅሬታቸው ወደ ከፍባለዉ እርከን በማሳደግ ለሚመለከተው የሥልጣን እርከን ለማቅረብ እንደሚገደዱም አሳስበዋል።

ሉዋ ሚዲያ

30/10/2025

#መረጃ: የመንገድ መሠረተ ልማት እጦት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን የጭሬ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ፤

በወረዳው በመንገድ መሠረተ ልማች ችግር ቅሬታቸውን ለሉዋ ሚዲያ የተናገሩ የቦኮላና ላሌሳ አከባቢ ነዋሪዎች የመንገድ መሠረተልማት ላለፉት አስራ አንድ አመታት ጀምሮ የነዋሪዎች ቅሬታ ሰምቶ መልስ የሚሰጥ አካል መጥፋቱን ተናግሯል።

ነዋሪዎቹ በመንገድ እጦት ምርቶቻቸዉን ወደገበያ ለማቅረብ ማሰብ ለእነሱ ቅንጦት መሆኑን የተናገሩት ነዋሪዎቹ ፤ ነፍሰጡር እንኳ ወደ ሆስፒታል ማድረስ አለመቻሉን፣ ታማሚና ወላድ በቃሬዛ ከቦኮላ እስከ ጭሬ ከተማ በቃሬዛ ለመሸከም እንደሚገደዱ ተናግረዋል።

በመንገድ መሠረተ ልማት ችግር ጋር የቴሌ ኮሙኒኬሽን ኔትወርክ ማስፋፊያ አለመኖር ታክሎበት ማህበረሰቡን ለተደራራቢ እንግልትና ስቃይ መዳረጉን ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት።

ነዋሪዎቹ የገጠማቸውን አንገብጋቢ የመንገድ ችግር በእራሳቸው ለመፍታት የአከባቢውን ነዋሪዎች እያስተባበሩ
የሚገኙ ሲሆን፤ መንግሥት የጭሬ ህዝብ ችግር ለመፍታት የማይንቀሳቀስ ከሆነ ተቃውሟቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አሳስበዋል።

ሉዋ ሚዲያ

 #መረጃ: የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት ዉሳኔ የደስታ ለዳሞ አስተዳደር ተግባራዊ ከማድረግ ይልቅ አፈራሽ ተልዕኮ ላይ በመሰማራት በፌደራል መንግሥት ላይ ንቀት አሳይቷል አሉ አባላቱ፡፡ ሰሞኑ...
29/10/2025

#መረጃ: የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት ዉሳኔ የደስታ ለዳሞ አስተዳደር ተግባራዊ ከማድረግ ይልቅ አፈራሽ ተልዕኮ ላይ በመሰማራት በፌደራል መንግሥት ላይ ንቀት አሳይቷል አሉ አባላቱ፡፡

ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች ላይ “ፕረዝዳንታችን ሥራ ላይ ናቸው” የሚልና የስድስት ዓመት የደስታ ሌዳሞ አመራር ትሩፋቶች በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ቅስቀሳ እንድካሄዱ ትዕዛዝ በመሥጠት ቅስቀሳ ላይ የሰነበተው የክልሉ መንግሥት፤ ከአንድ ወር በፊት ከወትሮ በተለየ ሁነታ የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት ያላፀደቀውን ከንቲባ በመሰየም ለሁለት ሳምንት የፈደራል መንግሥት አስተያየት ስጠባበቅ ቆይቶ ከ15ቀን በኃላ ምክር ቤት አቅርቦ ያፀደቀው፤ ከንቲባ ከመሰየሙ በፊት የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ያስቀመጠውን አቅጣጫ ላለመቀበል እንዳደረገ ተነግሯል።

እንደመረጃ ምንጫችን ገለጻ ከሥራ አስፈጻሚ ኮሚተ ስብሰባ ቀደም ተብሎ ተነግሮት ተልዕኮውን ይቀበል እንጅ ግለሰቡ ቅመኛና እልኸኛ ስለሆነ የአቶ አደም ፋራሀ ተልዕኮ ላለመፈጸም እያቅማማ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ የሚያሳየው በፓርቲው ዉስጥ በስነ-ምግባር ግድፈት ሊታረሙ የሚገቡና ራሳቸዉን በሌብነት ገንብተው ወደ ንጉሣዊነት የቀየሩ በደሞክራስያዊ ማዕከላዊነት የማይገዙ በፓርቲው ውስጥ አናርክዝም ለመፍጠር ምቹ ጊዜ እየጠበቁ ያሉ ሌቦች መበራከታቸው ማሳያ ነው ተብሏል፡፡

አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ በርካታ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸው ተጠቅሶ ለጠቅላይ ሚኒስተር ጽ/ቤት፣ ለብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት፣ ለፍትህ ሚኒስተርና ለፈደራል ስነ-ምግባርና ፀሬ ሙስና ኮሚሽን በማስረጃ የተደገፈ ጥቆማ ቀርቦ እርምጃ አለመወሰዱ የልብ ልብ እንደተሰማቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ይህ በእንድህ እንዳለ ዛሬ በሚጀምረው የፓርቲ ሥልጠና መልስ በክልሉ የአመራር ለውጥ ይደረጋል በሚል የክልሉ አስተባባር ኮሚተ፤ የመጨረሻ ምደባ ሊሆን ይችላል በሚል ከክልል ቢሮ እስከ ወረዳ የራሳቸውን ቤተሰብ እያደራጁ እንደሆነ ታውቋል፡፡

በሌላ በኩል በዞኖችና ወረዳ ጉቦ እየተሰበሰበ የሰነበተው የቡና ኢንዱስትርና ፍቃድና የሀዋሳ ከተማ መሬት ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ለመሥጠት በትላንትና ዕለት በዝግ ስብሰባ ላይ የቆዩት የጊዜ እጥረት ስላጋጠማቸው ካቢነውን መሰብሰብ ሳይችሉ ቀርቶ ዛሬ ማታ አዳማ ከኦሬንተሽን መልስ በካቢነው ሊያስወስን እንደሆነ ታውቋል፡፡

ከእሸት ቡና ኢንዱስትሪ ጋር በተደጋጋሚ ስማቸው የሚነሳ ስሆን፤ በዝህ ዙር ከፍቃድ ጠያቂ ባለሀብቶች ከሚሰበሰብ ጉቦ በተጨማሪ አስተባባሪ ኮሚተ፤

1. አቶ ደስታ ሌዳሞ በወንሾ ወረዳ፤
2. አቶ አብረሃም ማርሻሎ በሸበድኖ ወረዳ ተላሞ ቀበለ፤
3. ወ/ሮ ሀገረጽዮን አበበ ዳሌ ወረዳ ቱላ ቀበለ፤
4. አስፋው ጎነሦ በንሳ ወረዳ፤
5. በየነ ባራሣ ቦና ዙርያ ወረዳ፤
6. አሸናፊ ኤልያስ ዳራ ኦትልቾ ወረዳ የቡና ኢንዱስትሪ ፍቃድ መዉሰዳቸው ታውቋል።

በሌላ በኩል የሀዋሳ ከተማ መሬትን በሚመለከት የቀድሞ ሀዋሳ ማዛጋጃ ጊቢ፣ የቀድሞ ደቡብ ክልል ግብርና ቢሮ ጨምሮ 54 ፕሮጀክቶች በጉቦ ለማደል ዝግጅት መጠናቀቁ ታውቋል፡፡

ስጠቃለል ይህ በጥድፍያ ሊታደል ያለ ፍቃድና መሬት ህገወጥ ከመሆኑም ባሻገር፤ አመራሩ አጥፍቶ የመጥፋት መንገድ ስለሆነ በውሳነው ላይ የምትሳተፉ የካቢነ አባላት ጥንቃቀ እንድታደርጉ እያሳሰብን፤ የፈደራል መንግሥት ጉዳዩን በራሱ መንገድ እንድያጣራ እንጠይቃለን።

ሉዋ ሚዲያ

28/10/2025

የSidama News ዘገባ ሉዋ ሚዲያ

 #አስቅኝ: የክልሉ ገዥው መደብ ነን የምሉና የክልሉን መንግስት አንደኛው ክንፍ (ምክር ቤት) አፌ ጉባኤ ህዝቡን በጅምላ በመዛት ላይ ናቸዉ።የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፋጉባዔዋ እሳቸዉ በአፌጉ...
28/10/2025

#አስቅኝ: የክልሉ ገዥው መደብ ነን የምሉና የክልሉን መንግስት አንደኛው ክንፍ (ምክር ቤት) አፌ ጉባኤ ህዝቡን በጅምላ በመዛት ላይ ናቸዉ።

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፋጉባዔዋ እሳቸዉ በአፌጉባዔነት የሚመሩት መንግስት እና የክልሉ ፕረዝዳንቱ በአቶ ደስታ ለዳሞ መርነት የምፈፀም ብልሹ አሰራርን የምታገሉ አካላት ላይ የጅምላ ዘለፋን በማስከተል እርምጃ እንወስዳለን ማለታቸው አግራሞት ፈጥረዋል።

ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው የቃልአጋኖ ምልክት ተጠቅመው “ወዮላችው ዋዋ!” ብለው መዛታቸው መነጋገርያ ሆኗል፡፡ የክልሉን ህዝብ አንድ አድርጎ መምራት ያልቻለው ቅመኛና ጎጠኛ፣ በእትዮጵያ ታሪክ ተሰምቶ በማይታወቅ ሁነታ በሌብነት ሞደል የሆነ ክልል የሚመራ የደስታ ለዳሞ አስተዳደር ጠላቶቸ ናቸው በሚል ህዝብን በመፈረጅ የምታወቅ ከዝህ ቀደም ተረጋግቸ እንዳልሰራ እያደረጉኝ ነዉ በማለት ከፈደራል እስከ ወረዳ ድረስ ያለው ሲዳማን ማሻገር ይችላሉ ተብሎ እምነት የምጣልላቸዉን ግለሰቦች ላይ ጥቃት እያደረሰ መቆየቱ ይታወሳል።

የሚያስተዳድረውን ህዝብ የሚጠራጠረው እና የሚፈርጀው አስተዳደር፤ ሰሞኑን በወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ የሚመራ አቶ አየለ አላካ፣ አቶ የኔነ ሌላሞ፡ አቶ አበበ ይታደጉ እና አቶ መንግሥቱ ቡሎ ፀሀፊ የሆኑበትን አፍራሽ ጎጠኛ ቡድን በማደራጀት በክልሉ ሁከትና ብጥብጥ የጎሳ ግጭት እንድቀሰቀስ እየሰሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ቡድኑ የፕረዝዳንታቸው ፀሀይ መጥለቁና በክልሉ ለውጥ አይቀረ መሆኑን ተረድተው፤ ሲዳማ ክልል ሆኖ እንድደራጅ ከክብራቸውና ከጥቅማቸው በላይ የህዝብ ጥያቄ ያስበለጡ ለድል ያበቁ የቁርጥ ቀን ልጆች በነበሩና በፈደራል መንግሥት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃትና በውጠታማነት እየተወጡ ለሚገኙ የቁርጥ ቀን ልጆች ላይ አፍራሽ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን ደርሰንበታል።

ሲዳማ አንድ አድርጎ መምራት ተስኖት ክልሉን የሌብነት ተምሳለት ያደረገና ህዝባችንን ለከፍተኛ ማህበራዊ ቀውስ የዳረገውን አስተዳደር መታገል የዜግነት ግደታ እንጅ ወንጀል አይደለም ብለዉ ለሚዲያችን ሀሳባቸዉን ያጋሩት አንድ ምንጫችን ናቸዉ።

በመሆኑም በአፍራሽ ተልዕኮ የተሰማራችሁ የሲዳማ ህዝብ ትግል ወደማይቀለበስበት ደረጃ ስለደረሰ ከትዝብት ውጭ የህዝባችንን አንድነት የሚሸረሽር አፍራሽ እንቅስቃሰ እንድትታቀቡ ጥርያችንን እያቀረብን፤ ባለሁለት መታወቂያ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፤ በምርጫ የወከላቸው አቃፍ ህዝብ ላይ የተቀመጡበትን ቦታ የማይመጥን ንግግር ከማድረግ የማይቆጠቡ ከሆነ አንደኛውን መታወቂያ መልሰው ለይቶሎት እንድታገሉ እንመክራለን።

ሉዋ ሚዲያ

 : የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር የፓርቲው ልቀመምበር ረ/ፕሮፌሰር ተሰማ ኤልያስ (PhD) ፍንጭ ሰጡ፤ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ መጭው ሰባተኛውን ሀ...
28/10/2025

: የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር የፓርቲው ልቀመምበር ረ/ፕሮፌሰር ተሰማ ኤልያስ (PhD) ፍንጭ ሰጡ፤

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ መጭው ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር የፓርቲው ፕረዚዳንት ረዳት ፕሮፌሰር ተሰማ ኤልያስ (PhD) በይፋዊ ማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጻቸው እንደገለፁት “ሲፌፓ ለምርጫ ይወዳደራል፤ ዝርዝር ጉዳዩ በፓርቲው ይቀርባል።” ብሏል።

ሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ በ2014 ዓ.ም በፓርቲነት ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ ሰዉነት በማግኘት፤ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀስ ክልላዊ ፓርቲ መሆኑን ይታወቃል።

ፓርቲው ከምስረታው ጀምሮ በአጭር ግዜ ዉስጥ፣ በሁሉም ወረዳዎች ቢሮ በመክፈት ሚልዮኖች አባላት ያፈራና፤ በክልሉ ከፍተኛ ተጽእኖ መፍጠር የቻለ ግዙፍ ፓርቲ ስሆን፤ መንግስት ይህንን የፓርቲውን እንቅስቃሴ ለመገደብ እና ለማደናቀፍ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን በማስተባበር ያደረገዉ ሙከራ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቤቱታ በማቅረብ ድል ያነሳ ጠንካራ ፓርቲ ነዉ።

ከእዚህ ተግዳራቶች በኋላ ፓርቲዉ መጪውን ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደር ፍንጭ በመስጠቱ የፓርቲው ደጋፊዎች እና አባላት ደስታቸውን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ። እስከአሁን ፓርቲው ዝርዝር መረጃ ያልገለጸ ሲሆን፤ ዝርዝር መረጃን ስያሳወቅ ይዘን የምናቀርበው ይሆናል።

ሉዋ ሚዲያ

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Luwa Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category