Luwa Media

Luwa Media ብዝሃነት ለኢትዮጵያ አንድነት፤ ልዩነታችንን በእኩልነት የምታስተናግድ ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የራሳችንን ጡብ እናስቀምጣለን። ኢትዮጵያ!
(9)

አስደሳች ዜና: ሁለቱን የሲዳማ አጀንዳዎች በምክክሩ ዳግም እንዲመለሱ ተደርጓል ሲሉ ኤርሚያስ ብልሶ ገለጹ“ሁለቱንም የሲዳማ ጥያቄዎች ታግለን አስመልሰናል” ሲሉ በብሔራዊ ምክክሩ የሲዳማን ክል...
22/08/2026

አስደሳች ዜና: ሁለቱን የሲዳማ አጀንዳዎች በምክክሩ ዳግም እንዲመለሱ ተደርጓል ሲሉ ኤርሚያስ ብልሶ ገለጹ

“ሁለቱንም የሲዳማ ጥያቄዎች ታግለን አስመልሰናል” ሲሉ በብሔራዊ ምክክሩ የሲዳማን ክልል ተወካይ እና ይህንን ተግባር ለማፈጸም በቀዳሚነት እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት ወጣት ኤርሚያስ ቢሊሶ ገልጸዋል።

እንደ ኤርሚያስ ገለጻ፣ በምክክሩ ሂደት ቀደም ሲል ተይዞ የነበረው ከአጀንዳ ተቆረጠው የቀሩ ሁለት የሲዳማ ጥያቄዎች ዳግም ወደ ምክክር ሂደቱ እንዲመለሱ ተደርጎ ጸድቋል ብሏል። እነዚህም ሲዳምኛ ቋንቋ በፌደራል ደረጃ የሥራ ቋንቋ እንዲሆን የሚጠይቀው እና የፍቼ ጫምባላላ በዓል በኢትዮጵያ ብሔራዊ በዓላት ውስጥ እንዲካተትና በዓመታዊ የበዓላት አቆጣጠር ውስጥ እንዲሰፍር የሚጠይቀው አጀንዳ ናቸው።

ኤርሚያስ ቢሊሶ፣ እነዚህ አጀንዳዎች ከምክክሩ ሂደት ተቆርጠው መውጣታቸው በሲዳማ ተወካዮች ዘንድ ጥያቄ እንዳስነሳ በመጠቆም፣ አጀንዳዎቹ ዳግም እንዲመለሱ ለማድረግ ትግል መደረጉን በመግለፅ «‛ሁለቱንም የሲዳማ ጥያቄዎች ታግለን አስመልሰናል’ እንኳን ደስ አለህ» ስል፣ አንድ በክልሉ የሚንቀሳቀስ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ምክክር ህደት ውስጥ የነበሩ ተሳታፊዎች ያቀረቡት የቅሬታ ደብዳቤ በማያያዝ “35 ቀን የማንን ጎፈሬ ስታበጥሩ ቆይታችሁ አሁን ቅሬታ አቀረባችሁ? ይህ ባለቀ ግዜ ውስጥ መልክ ለመስራት የሚደረግ እሩጫ ተቀባይነት የለውም፣ ከተጠያቂነትም አታመልጡም፣ አስምሩበት” ብሎ ባስተላለፈው መልዕክት ስር በሃሳብ መስጫ ሳጥን ውስጥ ባሰፈረው ሃሳብ ገልጿል።

ይህ እውነት ሆኖ ከሆነ እጅግ በጣም ደስ የምል ዜና ነው። በተለይ ለሲዳማ ሕዝብ ቋንቋዊ፣ ባህላዊና ማንነታዊ ጥያቄዎች አዲስ ተስፋ የሚፈጥር ነው። ሆኖም አጀንዳዎቹ ዳግም ወደ ምክክሩ መመለሳቸው ብቻ ሳይሆን፣ በምክክሩ ሂደት በተጨባጭ ምን ውሳኔ እንደተላለፈ፣ በምን ደረጃ እንደተካተቱና የመጨረሻ ውጤታቸው ምን እንደሚሆን በጊዜ ሂደት መገምገም የሚገባ ይሆናል።

በመሆኑም የኤርሚያስ ቢሊሶ መግለጫ በተለይ በሲዳምኛ ቋንቋ የፌደራል ሥራ ቋንቋነት እና በፍቼ ጫምባላላ በዓል ዕውቅና ጉዳይ ላይ በቀጣይ የሚኖረው ይፋ የሚሆኑ የምክክር ውጤት በትኩረት የሚጠበቅ ይሆናል። ተቆረጠው የነበሩት ሁለቱ አጀንዳዎች ዳግም ወደ ምክክሩ መመለሳቸው ከተረጋገጠ፣ ይህ ለሲዳማ ተወካዮችና ለሲዳማ ሕዝብ አዎንታዊ እርምጃ ይሆናል።

ሉዋ ሚዲያ

የሲዳማ ተወካዮች በብሔራዊ ምክክሩ ያነሱት የሥራ ቋንቋ ጥያቄ እና ያምሮት ሀይሌ የተናገሩት አስተያየትበብሔራዊ ምክክሩ ላይ ሲዳማን ወክለው ከተሳተፉ ተወካዮች መካከል ያምሮት ሀይሌ አንዷ መሆ...
22/08/2026

የሲዳማ ተወካዮች በብሔራዊ ምክክሩ ያነሱት የሥራ ቋንቋ ጥያቄ እና ያምሮት ሀይሌ የተናገሩት አስተያየት

በብሔራዊ ምክክሩ ላይ ሲዳማን ወክለው ከተሳተፉ ተወካዮች መካከል ያምሮት ሀይሌ አንዷ መሆናቸው ተገልጿል።

በምክክሩ ወቅት የሲዳማ ተወካዮች ሲዳሙ አፎ የሀገሪቱ የሥራ ቋንቋ እንዲሆን ያቀረቡትን ሃሳብ ተከትሎ፣ ያምሮት ሀይሌ በደቡብ አካባቢ የሥራ ቋንቋ ሊሆን የሚገባው ወላይትኛ ቋንቋ መሆኑን መከራከራቸው ተሰምቷል።

ከዚህ አስተያየት ጋር በተያያዘ ለምን እንዲህ እንዳሉ በተጠየቁ ጊዜም፣ “በቃ ብያለው” በማለት አስተያየቱን ሆን ብለው እንደሰነዘሩ መናገራቸው ተገልጿል።

ይህ አስተያየት በሲዳማ ተወካዮች መካከል እና በምክክሩ ተሳታፊዎች ዘንድ ጥያቄ እንዲነሳ ማድረጉ ተጠቁሟል።

በመሆኑም የያምሮት ሀይሌ በምክክሩ ያቀረቡት አስተያየት በራሱ በህዝባዊ ውይይት ሊመዘን የሚችል ጉዳይ ሲሆን፣ ከአስተያየቱ በመነሳት ግለሰቧን “የውስጥ ባንዳ” መሆኑ እን በእንደዚህ ያሉ ባንዳዎች ክልሉን እንደወከሉ ማረጋገጥ ይቻላል።

ዋናው ጉዳይ በምክክሩ ላይ የተነሳው የቋንቋ ጥያቄ እና ያምሮት ሀይሌ በዚያ ላይ የሰጡት አስተያየት ሲሆን፣ በዚህ መሠረት ለወደፊትም በምክክሩ የተሳተፉ ሰዎች እያንዳንዱ ያነሷቸው ሃሳቦችና አቋሞች በማስረጃ ላይ ተመስርተው መመዝገብና መተንተን የተሻለ አቀራረብ እና ማን ምን አደረገ ለሚለው ሰነድ ይሆናል።

ሉዋ ሚዲያ

በሀገራዊ ምክክር ስም የሚካሄደው ሂደት የሲዳማን ሕዝብ አይወክልም —ሲፌፓአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. — የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ምክክር...
22/08/2026

በሀገራዊ ምክክር ስም የሚካሄደው ሂደት የሲዳማን ሕዝብ አይወክልም —ሲፌፓ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. — የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ይፋ ባደረገው አቋም መግለጫ፣ ሂደቱ ከመሠረቱ ጀምሮ አካታችና ገለልተኛ እንዳልሆነ ገልጾ፣ በምክክር ስም የሚካሄዱ አጀንዳዎችንና ውሳኔዎችን እንደማይቀበል አስታውቋል።

ፓርቲው ኢትዮጵያ ከውስጣዊ ግጭቶች፣ ጦርነቶችና የፖለቲካ ቀውሶች አንጻር ነጻ፣ ገለልተኛ፣ አካታችና በመርህ ላይ የተመሠረተ ሀገራዊ ምክክር እንደሚያስፈልጋት ገልጿል። ሆኖም አሁን የሚካሄደው ሂደት ከእነዚህ መርሆች ጋር የማይጣጣም ነው ብሏል።

ሲፌፓ እንደገለጸው፣ ፓርቲው በመጀመሪያ ሂደቱ አካታችና ገለልተኛ አይሆንም በሚል ስጋት ከምክክሩ ውጪ ሆኖ ቆይቷል። በኋላ ግን ከሂደቱ ውጪ ሆኖ ከመተቸት ይልቅ በውስጥ በመሳተፍ ሂደቱን ለማስተካከል በሚል ከብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጋር መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙን ገልጿል።

ፓርቲው ወደ ሂደቱ ከገባ በኋላ የኮሚሽኑን አሠራርና የምክክሩን ሂደት በቅርበት ሲከታተል መቆየቱን ገልጾ፣ በሂደቱ ውስጥ የገዢው ፓርቲ ተጽዕኖ እንዳለ መገንዘቡን ተናግሯል።

በተለይም የምክክሩ አጀንዳ ከመለየት ጀምሮ የግጭት ተዋናዮችና ባለድርሻ አካላት በበቂ ሁኔታ እንዳልተሳተፉ፣ ለምክክር አስቻይ ሁኔታ እንዳልተፈጠረ እና ሂደቱም ውስብስብ የሆኑ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በቂ እንዳልሆነ ገምግሟል።

ሲፌፓ በመግለጫው ኮሚሽኑ ከገዢው ፓርቲ ተጽዕኖ ነጻ መሆን እንዳልቻለ በመጥቀስ፣ መንግሥትና ገዢው ፓርቲ ለእውነተኛ ሀገራዊ ምክክርና ድርድር ቁርጠኛ ባልሆኑበት ሁኔታ በሂደቱ መሳተፍ ትርጉም የለውም በሚል ከምክክሩ በይፋ መውጣቱን ገልጿል።

ፓርቲው ከምክክሩ ሂደት የወጣው በ07/05/2017 ዓ.ም. መሆኑን ጠቅሶ፣ ያኔ የወሰደው ውሳኔ በቂ ግምገማና ተጨባጭ ማስረጃ ላይ የተመሠረተ እንደነበር አስታውቋል።

በተጨማሪም ሲፌፓ በሲዳማ ክልል የምክክሩ ሂደት አካታችና ገለልተኛ ሳይሆን የገዢው ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ብቻ በሚበዙበት መልኩ እየተካሄደ ነው ሲል ተችቷል።

ይህ አካሄድ የሲዳማ ሕዝብን ማንነት፣ ቋንቋ፣ ባህልና በሕገ-መንግሥቱ የተረጋገጡ መብቶችን የሚያሳንስ ነው ብሎ ፓርቲው ገልጿል።

በመግለጫው መሠረት፣ ሲፌፓ በሀገራዊ ምክክር ስም እየተካሄደ ያለውን ማንኛውንም አጀንዳም ሆነ ውሳኔ እንደማይቀበል አስታውቋል። ሕዝቡና ትክክለኛ የፖለቲካ ኃይሎች ሳይሳተፉበት የሚደረግ ምክክር የሲዳማን ሕዝብ አይወክልም ሲልም አፅንዖት ሰጥቷል።

በሌላ በኩል፣ ፓርቲው ሲዳሙ-አፎ በእኩልነት መርህና ከሲዳማ ሕዝብ ቁጥር አንጻር ከፌደራል የሥራ ቋንቋዎች አንዱ እንዲሆን እንደሚታገል ገልጿል።

በተጨማሪም በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስ ተብሎ የተመዘገበው የሲዳማ ባህላዊ በዓል ፊቼ ጫምባላላ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ የበዓል ቀን እንዲሆን እንደሚታገል ፓርቲው በአቋም መግለጫው አስታውቋል።

ሲፌፓ በመግለጫው ያቀረባቸው አቋሞች የፓርቲው ኦፊሴላዊ አቋም መሆናቸውን ገልጾ፣ በሀገራዊ ምክክሩ ውስጥ የሲዳማ ሕዝብ እና ተወካይ የፖለቲካ ኃይሎች በትክክል ሳይሳተፉ የሚደረስ ውሳኔ ሕጋዊና የሕዝብን ፍላጎት የሚወክል ሊሆን እንደማይችል አስገንዝቧል።

ሉዋ ሚዲያ

 : አዲስ አበባ የፌዴራል መንግሥት መቀመጫ እና የኦሮሚያ ዋና ከተማ እንዲትሆን ተጠሪነቷ ለፌዴራል መንግሥት እንዲሆን ከመግባባት መደረሱ ተሰማ።የከተማዋ ነዋሪዎች በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመረ...
21/08/2026

: አዲስ አበባ የፌዴራል መንግሥት መቀመጫ እና የኦሮሚያ ዋና ከተማ እንዲትሆን ተጠሪነቷ ለፌዴራል መንግሥት እንዲሆን ከመግባባት መደረሱ ተሰማ።

የከተማዋ ነዋሪዎች በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመረጡት አካላት እንዲተዳደሩም ከመግባባት ላይ መድረሳቸው ተሰምቷል።

የኦሮሚያ ልዩ ጥቅም በሚል በህገመንግስቱ አንቀፅ 49 ንፁስ 5 የተደነገገው በጋራ ጥቅም እንዲተካም ተወስኗል።

በዚህ መሠረት አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁሉንም የፌዴራል መንግሥት የስራ ቋንቋዎች ይጠቀማል ተብሏል።

ቋንቋን በተመለከተ አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግሪኛ፣ ሶማሊኛ እና አፋሪኛ የፌዴራል መንግሥት የስራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ ስምምነት ላይ ተደርሷል ሲሉ ምንጮች ተናግረዋል። በተጨማሪም ኢሬቻ በብሔራዊ በዓልነት ከላንደር ውስጥ እንዲካተትም ስምምነት ላይ ተደርሷል።

ዘገባው ኦ ኤም ኤን
ሉዋ ሚዲያ

ሰበር ዜና: የአማራ ክልል ተመካካሪዎች የአዲስ አበባ ጉዳይ በሽምግልና እንዲወሰን የሚል ምክረ-ሃሳብ በመቅረቡ የምክክር መድረኩን ረግጦ ወጥተዋል!በመጨረሻም የክልሉ ባለስልጣናት ምልጃና ጉትጎ...
21/08/2026

ሰበር ዜና: የአማራ ክልል ተመካካሪዎች የአዲስ አበባ ጉዳይ በሽምግልና እንዲወሰን የሚል ምክረ-ሃሳብ በመቅረቡ የምክክር መድረኩን ረግጦ ወጥተዋል!

በመጨረሻም የክልሉ ባለስልጣናት ምልጃና ጉትጎታ የተወሰኑት ተመልሶ አደራሽ የገቡ ብሆንም፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ መሆኑን በህገመንግስ እንዲሰፍር እና የፈደራል ዋና ከተማ ተጠረነቷም የፌደራል መንግስት እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚኖራት ግንኙነት በህግ እንዲወሰን ምክረሃሳብ ቀርቦ ጉባኤ ተበትኗል።

ሉዋ ሚዲያ

በጭፍን ጥላቻ በመነሳት ህዝብ ላይ በጅምላ የሚደረግ ስድብና ማንቋሸሽ መቆም አለበት። ሲዳማ ህዝብ እንደማንኛውም ኢትዮጵያ ህዝቦች የሚገባው ለማግኘት የመጠየቅና የጠየቀውን በክብር የማግኘት ሙ...
21/08/2026

በጭፍን ጥላቻ በመነሳት ህዝብ ላይ በጅምላ የሚደረግ ስድብና ማንቋሸሽ መቆም አለበት። ሲዳማ ህዝብ እንደማንኛውም ኢትዮጵያ ህዝቦች የሚገባው ለማግኘት የመጠየቅና የጠየቀውን በክብር የማግኘት ሙሉ መብት አለው።

አሃዳዊ ስርዓት በህልም እና በእውን የሚናፈቁ ሁሉ ያቺ ኢትዮጵያ ዳግም ላትመለስ በብሐር በብሔረሰቦች ትግል ተሸኝታለች። አሁን ኢትዮጵያ የሚትባል ሀገር የ86 ብሔርና 140 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ናት።

የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) ሊቀመንበር ረዳት ፕሮፌሰር ተሰማ ኤልያስ፣ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትችት አቀረቡ።ረ/ፕ ተሰማ ኤልያስ በምክክሩ የሚወሰነው ማንኛውም ውሳኔ የሲ...
21/08/2026

የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) ሊቀመንበር ረዳት ፕሮፌሰር ተሰማ ኤልያስ፣ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትችት አቀረቡ።

ረ/ፕ ተሰማ ኤልያስ በምክክሩ የሚወሰነው ማንኛውም ውሳኔ የሲዳማን ሕዝብ እንደማይወክል ተናግረዋል።

“መጀመሪያም አይተን እንደማይሆን ተረድተን ተመልሰን ወጥተናል” ሲሉ ረ/ፕ ተሰማ ኤልያስ የምክክሩን ሂደት መተቸታቸውን የፓርቲው አቋም አሳይተዋል።

የሲፌፓ ሊቀመንበር እንደገለጹት፣ ፓርቲያቸው ከአንድ ዓመት በፊት ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሂደት ለቆ የወጣው ኮሚሽኑ የሀገሪቱን ውስብስብ ችግሮች መፍታት የማይችል መሆኑን በመገንዘብ ነው።

ፓርቲው በወቅቱ ኮሚሽኑ ከሀገራዊ ችግሮች ይልቅ የገዢው ፓርቲን አጀንዳ የሚያስፈጽም መዋቅር ነው በሚል ትችት ከምክክሩ መውጣቱን ገልጿል።

ረ/ፕ ተሰማ ኤልያስ አሁንም በምክክሩ ሂደት ላይ ያላቸው ትችት ያልተቀየረ ሲሆን፣ በሂደቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች የሲዳማን ሕዝብ የሚወክሉ እንደማይሆኑ አስገንዝበዋል።

ይህ አቋም የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ ከምክክሩ ሂደት የወጣበትን ምክንያት እንደገና ያነሳ ሲሆን፣ የሀገራዊ ምክክሩ ውጤት ሁሉንም ብሔረሰቦችና ፖለቲካዊ አቋሞች በእኩል ማካተቱ ላይ ጥያቄ አስነስቷል።

በተለይም ከምክክሩ ውጭ የሆኑ የፖለቲካ ኃይሎች የሚያነሷቸው ጥያቄዎችና ቅሬታዎች በምክክሩ ውጤት ውስጥ እንዴት እንደሚካተቱ የሚለው ጉዳይ አሁንም የሚያጠያይቅ ሆኖ ቀጥሏል።

ሉዋ ሚዲያ

የሲዳማ ተወካዮች ሲዳሙ አፎ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ እንዲሆን ጠየቁአዲስ አበባ — በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት ሲዳሙ አፎ/ሲዳሚኛ ቋንቋ በቀጥታ ከተመረጡት የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች ውጭ መ...
21/08/2026

የሲዳማ ተወካዮች ሲዳሙ አፎ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ እንዲሆን ጠየቁ

አዲስ አበባ — በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት ሲዳሙ አፎ/ሲዳሚኛ ቋንቋ በቀጥታ ከተመረጡት የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች ውጭ መደረጉን በመቃወም የሲዳማ ክልል የምክክር ተወካዮች ቅሬታ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ማቅረባቸውን ገለጹ።

ተወካዮቹ በቅሬታቸው ሲዳሚኛ ቋንቋ በተለያዩ የምክክር ቡድኖች ላይ ለፌዴራል የሥራ ቋንቋነት እንዲካተት ምክረ ሀሳብ መቅረቡን ጠቅሰው፣ በመጨረሻ ግን አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ፣ አፍ ሶማሌ እና አፋርኛ ቀጥታ እንዲመረጡ ተደርጎ ሲዳሚኛ በቀጣይ እንዲታይ መቅረቡ ቅሬታ እንዳስነሳባቸው አስረድተዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ ግልጽ የሆነ የምርጫ መስፈርት ሳይቀመጥ ሲዳሚኛን ከቀዳሚዎቹ ቋንቋዎች ውጭ ማድረግ አግባብ እንዳልሆነ ጠቁመዋል። በተጨማሪም በምክክር ቡድኖች የቀረቡ ምክረ ሀሳቦች በኋላ በሌላ ደረጃ ተለውጠው መቅረባቸው የአሰራር ጥያቄ እንደሚያስነሳ ገልጸዋል።

ተወካዮቹ ከቋንቋ ምርጫው ጋር በተያያዘ የእኩልነትና የፍትሐዊነት ጥያቄም አንስተዋል። በክልሎች ደረጃ እንደ መንግሥት የሥራ ቋንቋ የሚጠቀሙ ቋንቋዎች መካከል ሲዳሚኛ እያለ፣ ሌሎች ቋንቋዎች ለፌዴራል የሥራ ቋንቋነት በቀጥታ መመረጣቸው ሲዳሚኛን ብቻ ለየት አድርጎ ከዝርዝሩ ውጭ ማድረግ እንደሆነ ተችተዋል።

በቅሬታው ላይ ሲዳሚኛ በሲዳማ ክልል የሥራ ቋንቋ ከመሆኑም በላይ የመማሪያና የምርምር ቋንቋ ሆኖ እንደሚያገለግል፣ በቋንቋው ላይ ሰፊ ጥናትና ምርምር መካሄዱን ተጠቅሷል። ቋንቋው ከሲዳማ ክልል ውጭም በተለያዩ አካባቢዎች ተናጋሪዎች እንዳሉትና ከአጎራባች ሕዝቦች ጋር የመግባቢያ ሚና እንዳለው ተወካዮቹ አብራርተዋል።

በተጨማሪም ተወካዮቹ የሲዳማ ሕዝብ ቁጥርና ቋንቋው ያለውን ማህበራዊና ትምህርታዊ ተጠቃሚነት በመጥቀስ፣ ሲዳሚኛ ከሌሎች ቋንቋዎች ተለይቶ እንዲታይ የተደረገው ውሳኔ እንደገና እንዲጤን ጠይቀዋል።

በዚህ መሠረት የሲዳማ ተወካዮች ሲዳሙ አፎ በፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች ዝርዝር እንዲካተት ያቀረቡት ጥያቄ በሀገራዊ ምክክሩ የቋንቋ ጉዳይ ላይ ከተነሱ ዋና ጉዳዮች አንዱ ሆኗል።

ማስታወሻ፦ ይህ ዘገባ በተወካዮቹ የቀረበውን ቅሬታ መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ በቅሬታው የተነሱ የሕግ፣ የቁጥር እና የምክክር አሰራር ጉዳዮች ከተጠቀሱት ምንጮች የተገኙ ናቸው።

ሉዋ ሚዲያ

የምክክር ጉባዔው በኦሮሚያ አዲስ ጥያቄ ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ ገባአዲስ አበባ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም. በብሔራዊ ምክክር ጉባዔው የማጠቃለያ ሂደት ወቅት የኦሮሚያ ክልልን ወክለው የተሳተፉ...
21/08/2026

የምክክር ጉባዔው በኦሮሚያ አዲስ ጥያቄ ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ ገባ

አዲስ አበባ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም. በብሔራዊ ምክክር ጉባዔው የማጠቃለያ ሂደት ወቅት የኦሮሚያ ክልልን ወክለው የተሳተፉ ተመካካሪዎች ያቀረቡት አዲስ ምክረ ሀሳብ የጉባዔውን ሂደት ማራዘሙ ተገለጸ።

የኦሮሚያ ተወካዮች በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች በቂ አለመሆናቸውን በመግለጽ፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ መሆኗን በሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ የሚያረጋግጥ ምክረ ሀሳብ እንዲካተት መጠየቃቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

ወደ 300 የሚጠጉ ተመካካሪዎች ቅሬታቸውን ለምክክር ኮሚሽኑ አባላት እንዳቀረቡና ሦስት ኮሚሽነሮችም ቅሬታቸውን እንደተቀበሏቸው ተጠቅሷል። ተመካካሪዎቹ የጠየቁት ምክረ ሀሳብ ካልተካተተ ከምክክር ሂደቱ ሊወጡ እንደሚችሉም ለኮሚሽነሮቹ እንደገለጹ ምንጮቹ አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ የአማራ ክልል ተወካዮች ደግሞ አዲስ ጥያቄ በተዘጋ ጉዳይ ላይ እንዲቀርብ መደረጉን በመቃወም፣ የምክክር ሂደቱ የተደነገገውን አሠራር መከተል እንዳለበት ተናግረዋል። ከዚህ በፊትም አሠራሩ ከተጣሰ ከምክክሩ ሊገለሉ እንደሚችሉ ማሳሰባቸው ተገልጿል።

የክልል ተወካዮች ጉባዔ እንዲሰበሰብ መወሰኑም በአማራ ተወካዮች ትችት አስነስቷል። ተወካዮቹ የጋራ ማረጋገጫ ቡድን ሥራውን አጠናቆ ምክረ ሀሳቦችን ለሥራ ቡድኖች ካቀረበ በኋላ ጉባዔው መጠራት እንደነበረበት በመግለጽ፣ የተወሰደው እርምጃ ከተቀመጠው አሠራር ውጭ ነው ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል።

በዚህ ውዝግብ መካከል የምክክር ኮሚሽኑ ቀደም ሲል በዕቅድ ያልተያዘ የክልል ተወካዮች ጉባዔ እንዲካሄድ ጥሪ ማስተላለፉ ተገልጿል።

በመሆኑም የኦሮሚያ ተወካዮች ያቀረቡት አዲስ ጥያቄ፣ የአማራ ተወካዮች ያሰሙት ተቃውሞ እና የኮሚሽኑ የሂደት ውሳኔ በምክክር ጉባዔው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ አዲስ ውጥረት መፍጠሩ ታውቋል። የዛሬው የጉባዔው ውሎም የምክክሩን ቀጣይ ሂደት በእጅጉ ሊወስን ይችላል።

ሉዋ ሚዲያ

አዲስ አበባ የፌዴራል ከተማ እንድትሆን ተመካከሪዎች መስማማታቸው ተገለጸአዲስ አበባ፦ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ማዕቀፍና የፌዴራል ሥርዓቱ ውስጥ አዲስ አበባ ስላላት ሁኔታ ሲካሄድ በቆየው ም...
20/08/2026

አዲስ አበባ የፌዴራል ከተማ እንድትሆን ተመካከሪዎች መስማማታቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፦ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ማዕቀፍና የፌዴራል ሥርዓቱ ውስጥ አዲስ አበባ ስላላት ሁኔታ ሲካሄድ በቆየው ምክክር፣ ከተማዋ የፌዴራል ከተማ ተጠሪ እንድትሆን ተመካከሪዎች መስማማታቸው ተገለጸ።

የምክክሩ አዘጋጅ ቡድን ያቀረበው ቃለ ጉባኤ ዛሬ በተነበበበት ወቅት፣ አዲስ አበባ የፌዴራል ከተማ ሆና እንድትቀጥል ተመካከሪዎች የተስማሙበት ሀሳብ በቃለ ጉባኤው መካተቱ ታውቋል። በምክክሩ ወቅት ከከተማዋ ጋር በተያያዘ በአከራካሪነት ሲነሳ የቆየው “ልዩ ጥቅም” የሚለው አገላለጽም “የጋራ ጥቅም” በሚል እንዲተካ ሀሳብ መቅረቡ ተገልጿል።

በተጨማሪም አዲስ አበባ የፌዴራል ከተማ መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ተመሳሳይ የፌዴራል ከተማ ደረጃ የሚሰጣቸው ሌሎች ከተሞች እንዲኖሩ የሚል ምክረ ሀሳብም ቀርቧል። የኦሮሚያ መቀመጫነት ጉዳይ ሁለት አማራጮች ቀርበውለታል፤ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ስለመሆኗ የቀረበው ሀሳብ ግን የተለያዩ አቋሞች ያሉበት ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል።

የኦሮሚያ ክልልን የወከሉ ተሳታፊዎች አዲስ አበባ የክልሉ መቀመጫ መሆኗ በሕገ መንግሥቱ እውቅና እንዲሰጠው ሲጠይቁ፣ ሌሎች ተመካከሪዎች በበኩላቸው ከተማዋ የሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች መዲና በመሆኗ ለአንድ ክልል ብቻ መቀመጫ ልትሆን አይገባም በሚል ተቃራኒ አቋም ማቅረባቸው ተጠቅሷል። በዚህ ጉዳይ ላይ ሁለት አማራጭ ምክረ ሀሳቦች መቅረባቸውም ተገልጿል።

የመጀመሪያው አማራጭ፣ ሁሉም ክልሎች የራሳቸውን መቀመጫ እንዲመርጡ በሕግ እንዲደነገግ የሚል ነው። ሁለተኛው ምክረ ሀሳብ ደግሞ፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 49(5) መሠረት አዲስ አበባ ከኦሮሚያ ክልል ጋር በሚኖራት ግንኙነት ላይ ዝርዝር የሕግ ማዕቀፍ እንዲዘጋጅ የሚል ነው። ይህም ከተማዋ የፌዴራል ከተማ ሆና እንድትቀጥል ከሚቀርበው ሀሳብ ጋር ተያይዞ፣ በከተማዋና በኦሮሚያ ክልል መካከል ያለው ግንኙነት በግልጽ ሕጋዊ ማዕቀፍ እንዲመራ ያስቀምጣል።

በሌላ በኩል፣ የድሬዳዋ ከተማን ሁኔታ በተመለከተ ከተማዋ ለፌዴራል መንግሥት ተጠሪ እንድትሆንና ሕገ መንግሥቱ በሰጣት የቻርተር ከተማ ደረጃ እንድትተዳደር የሚል ምክረ ሀሳብ በቃለ ጉባኤው መቅረቡን ተመካካሪዎች ገልጸዋል።

በአጠቃላይ፣ በአዲስ አበባ የፌዴራል ከተማነት፣ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ባላት ግንኙነት እና በድሬዳዋ የአስተዳደር ደረጃ ዙሪያ የቀረቡት ሀሳቦች ቀጣይ የሕገ መንግሥታዊና ፖሊሲ ውሳኔዎች መነሻ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።

ሉዋ ሚዲያ

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Luwa Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category