22/08/2026
አስደሳች ዜና: ሁለቱን የሲዳማ አጀንዳዎች በምክክሩ ዳግም እንዲመለሱ ተደርጓል ሲሉ ኤርሚያስ ብልሶ ገለጹ
“ሁለቱንም የሲዳማ ጥያቄዎች ታግለን አስመልሰናል” ሲሉ በብሔራዊ ምክክሩ የሲዳማን ክልል ተወካይ እና ይህንን ተግባር ለማፈጸም በቀዳሚነት እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት ወጣት ኤርሚያስ ቢሊሶ ገልጸዋል።
እንደ ኤርሚያስ ገለጻ፣ በምክክሩ ሂደት ቀደም ሲል ተይዞ የነበረው ከአጀንዳ ተቆረጠው የቀሩ ሁለት የሲዳማ ጥያቄዎች ዳግም ወደ ምክክር ሂደቱ እንዲመለሱ ተደርጎ ጸድቋል ብሏል። እነዚህም ሲዳምኛ ቋንቋ በፌደራል ደረጃ የሥራ ቋንቋ እንዲሆን የሚጠይቀው እና የፍቼ ጫምባላላ በዓል በኢትዮጵያ ብሔራዊ በዓላት ውስጥ እንዲካተትና በዓመታዊ የበዓላት አቆጣጠር ውስጥ እንዲሰፍር የሚጠይቀው አጀንዳ ናቸው።
ኤርሚያስ ቢሊሶ፣ እነዚህ አጀንዳዎች ከምክክሩ ሂደት ተቆርጠው መውጣታቸው በሲዳማ ተወካዮች ዘንድ ጥያቄ እንዳስነሳ በመጠቆም፣ አጀንዳዎቹ ዳግም እንዲመለሱ ለማድረግ ትግል መደረጉን በመግለፅ «‛ሁለቱንም የሲዳማ ጥያቄዎች ታግለን አስመልሰናል’ እንኳን ደስ አለህ» ስል፣ አንድ በክልሉ የሚንቀሳቀስ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ምክክር ህደት ውስጥ የነበሩ ተሳታፊዎች ያቀረቡት የቅሬታ ደብዳቤ በማያያዝ “35 ቀን የማንን ጎፈሬ ስታበጥሩ ቆይታችሁ አሁን ቅሬታ አቀረባችሁ? ይህ ባለቀ ግዜ ውስጥ መልክ ለመስራት የሚደረግ እሩጫ ተቀባይነት የለውም፣ ከተጠያቂነትም አታመልጡም፣ አስምሩበት” ብሎ ባስተላለፈው መልዕክት ስር በሃሳብ መስጫ ሳጥን ውስጥ ባሰፈረው ሃሳብ ገልጿል።
ይህ እውነት ሆኖ ከሆነ እጅግ በጣም ደስ የምል ዜና ነው። በተለይ ለሲዳማ ሕዝብ ቋንቋዊ፣ ባህላዊና ማንነታዊ ጥያቄዎች አዲስ ተስፋ የሚፈጥር ነው። ሆኖም አጀንዳዎቹ ዳግም ወደ ምክክሩ መመለሳቸው ብቻ ሳይሆን፣ በምክክሩ ሂደት በተጨባጭ ምን ውሳኔ እንደተላለፈ፣ በምን ደረጃ እንደተካተቱና የመጨረሻ ውጤታቸው ምን እንደሚሆን በጊዜ ሂደት መገምገም የሚገባ ይሆናል።
በመሆኑም የኤርሚያስ ቢሊሶ መግለጫ በተለይ በሲዳምኛ ቋንቋ የፌደራል ሥራ ቋንቋነት እና በፍቼ ጫምባላላ በዓል ዕውቅና ጉዳይ ላይ በቀጣይ የሚኖረው ይፋ የሚሆኑ የምክክር ውጤት በትኩረት የሚጠበቅ ይሆናል። ተቆረጠው የነበሩት ሁለቱ አጀንዳዎች ዳግም ወደ ምክክሩ መመለሳቸው ከተረጋገጠ፣ ይህ ለሲዳማ ተወካዮችና ለሲዳማ ሕዝብ አዎንታዊ እርምጃ ይሆናል።
ሉዋ ሚዲያ